መንግስትና ፓርቲ ያቀዷቸው ትላልቅ የልማት ህልሞች እንዲሳኩ በጽናትና በመርህ ሙስናን መከላከል ይገባል - ርዕሰ መስተዳደር እንዳሻው ጣሰው
******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 26/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ክቡር አቶ እንዳሻው ጣሰው መንግስትና ፓርቲ ያቀዷቸው ትላልቅ ህልሞች እንዲሳኩ የተጠናከረ የፀረ-ሙስና ትግል መደረግ እንዳለበት አሳሰቡ።
ክቡር ፕሬዚዳንቱ ቡታጅራ ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም የፀረ-ሙስና ቀን በዓል ላይ እንዳስታወቁት፣ ሙስና የብዙ አገሮችን ህልምና ትልም ያመከነና ለብዙ ቀውሶች መንስኤ ሆኗል።
ለሙስና ምክንያት ከሚሆኑ ጉዳዮች መካከልም የመልካም አስተዳደር መጓደል፣ አላግባብ የመጠቀም ፍላጎት፣ ስልጣንን ለማቆየትና ወደስልጣን ለመውጣት ያሉ ፍላጎቶች እንደሆኑም አንስተዋል።
የሙስና መገለጫ ከሆኑት መካከልም ስልጣንን አላግባብ መጠቀም፣ አሰራሮችን መጣስ፣ በቀጥታ ጥቅም ማግኘት፣ የፍትሀዊነት መጓደል፣ ፍትህን ማጣመም፣ የመንግስትን ጥቅም አሳልፎ መስጠት እና የመሳሰሉ ጉዳዮች እንዳሉም ርዕሰ መስተዳደሩ አብራርተዋል።
አገራችን ላይ አሁን ከሚታዩ ችግሮች ከ50 እስከ 60 ከመቶ የሚሆኑት ዋነኛ ምንጫቸው ሙስና እና ብልሹ አሰራሮች እንደሆኑም አመልክተዋል።
ሙስናን በወሳኝ መልኩ ለመከላከል በመርህ ላይ የተመሰረተ ትግል ማድረግ፣ ጽናት፣ የጋራ መግባባት፣ ህብረተሰብን በየደረጃው ማሳተፍ ቁልፍ ተግባራት መሆናቸውንም ርዕሰ መስተዳደር እንዳሻው አሳስበዋል።
የህዝቡ እርካታ እስኪረጋገጥ የፀረ-ሙስና ትግሉን ማጠናከር፣ ቤተሰብ፣ ትምህርት ቤትና የሀይማኖት ተቋማት አካባቢ በሥነምግባር የታነፀ ትውልድ ለመቅረጽ ተቀናጅቶ መንቀሳቀስ እንደሚገባም አመላክተዋል።
በጉዳዩ ላይ መግባባትና ሀሳቡን ተግባራዊ ማድረግ፣ በቂ ትግል ማድረግ፣ ተቀናጅቶ መስራት፣በየሴክተሩ የፀረ-ሙስና ትግል ማጠናከር፣ ህግን ተግባራዊ ማድረግ፣ ከህዝቡ የሚነሱ ቅሬታዎችን ለቅሞ መመለስ ዋነኛ የፀረ-ሙስና ትግሉ አጀንዳዎች መሆናቸውንም ርዕሰ መስተዳደር እንዳሻው ጣሰው አሳውቀዋል።
ኮሚሽኑ በእጁ የሚገኙ ጥቆማዎችን መሰረት በማድረግ ቶሎ ወደስራ እንዲገባም አሳስበው ስራዎች በሚዲያ እየታጀቡ መሄድ እንዳለባቸውም አመላክተዋል።
የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ማሞ ቴጋ በበኩላቸው የፀረ-ሙስና ቀን የመከበሩ ዋነኛ አላማ ሙስና እያስከተለ ያለውን ዘርፈ ብዙ ችግር ለመከላከል እና በዘርፉ የሚደረገውን ትግል ለማጠናከር ነው ብለዋል።
ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን በመለየት ግንዛቤ በመፍጠር ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በትብብር መስራት የሙስናን ችግር መቅረፍ እንደሚያስችልም ኮሚሽነሩ ጠቁመዋል።
በሙስናና ብልሹ አሰራር ምክንያት ወጣቱ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የችግሩ ተጎጂ ነው ያሉት ኮሚሽነር ማሞ የዘንድሮው የጸረ ሙስና ቀን ሲከበር የወጣቶችን ሥነምግባር እና ታማኝነትን ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ስለመሆኑም አስረድተዋል።
በክልሉ ሙስናና ብልሹ አሰራርን መከላከል የሚያስችል የትውልድ ሥነምግባር ግንባታ ላይ በመስራት የአሰራር ጥናቶችን ማካሄድ፣ ለሚቀርቡ የሙስና ወንጀል ጥቆማዎች ፈጣን ምላሽ መስጠት ከመከላከል ያለፉ የሙስና ወንጀል ጉዳዮችን ለሚመለከታቸው የፍትህ አካላት ማስተላለፍ ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 26/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ክቡር አቶ እንዳሻው ጣሰው መንግስትና ፓርቲ ያቀዷቸው ትላልቅ ህልሞች እንዲሳኩ የተጠናከረ የፀረ-ሙስና ትግል መደረግ እንዳለበት አሳሰቡ።
ክቡር ፕሬዚዳንቱ ቡታጅራ ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም የፀረ-ሙስና ቀን በዓል ላይ እንዳስታወቁት፣ ሙስና የብዙ አገሮችን ህልምና ትልም ያመከነና ለብዙ ቀውሶች መንስኤ ሆኗል።
ለሙስና ምክንያት ከሚሆኑ ጉዳዮች መካከልም የመልካም አስተዳደር መጓደል፣ አላግባብ የመጠቀም ፍላጎት፣ ስልጣንን ለማቆየትና ወደስልጣን ለመውጣት ያሉ ፍላጎቶች እንደሆኑም አንስተዋል።
የሙስና መገለጫ ከሆኑት መካከልም ስልጣንን አላግባብ መጠቀም፣ አሰራሮችን መጣስ፣ በቀጥታ ጥቅም ማግኘት፣ የፍትሀዊነት መጓደል፣ ፍትህን ማጣመም፣ የመንግስትን ጥቅም አሳልፎ መስጠት እና የመሳሰሉ ጉዳዮች እንዳሉም ርዕሰ መስተዳደሩ አብራርተዋል።
አገራችን ላይ አሁን ከሚታዩ ችግሮች ከ50 እስከ 60 ከመቶ የሚሆኑት ዋነኛ ምንጫቸው ሙስና እና ብልሹ አሰራሮች እንደሆኑም አመልክተዋል።
ሙስናን በወሳኝ መልኩ ለመከላከል በመርህ ላይ የተመሰረተ ትግል ማድረግ፣ ጽናት፣ የጋራ መግባባት፣ ህብረተሰብን በየደረጃው ማሳተፍ ቁልፍ ተግባራት መሆናቸውንም ርዕሰ መስተዳደር እንዳሻው አሳስበዋል።
የህዝቡ እርካታ እስኪረጋገጥ የፀረ-ሙስና ትግሉን ማጠናከር፣ ቤተሰብ፣ ትምህርት ቤትና የሀይማኖት ተቋማት አካባቢ በሥነምግባር የታነፀ ትውልድ ለመቅረጽ ተቀናጅቶ መንቀሳቀስ እንደሚገባም አመላክተዋል።
በጉዳዩ ላይ መግባባትና ሀሳቡን ተግባራዊ ማድረግ፣ በቂ ትግል ማድረግ፣ ተቀናጅቶ መስራት፣በየሴክተሩ የፀረ-ሙስና ትግል ማጠናከር፣ ህግን ተግባራዊ ማድረግ፣ ከህዝቡ የሚነሱ ቅሬታዎችን ለቅሞ መመለስ ዋነኛ የፀረ-ሙስና ትግሉ አጀንዳዎች መሆናቸውንም ርዕሰ መስተዳደር እንዳሻው ጣሰው አሳውቀዋል።
ኮሚሽኑ በእጁ የሚገኙ ጥቆማዎችን መሰረት በማድረግ ቶሎ ወደስራ እንዲገባም አሳስበው ስራዎች በሚዲያ እየታጀቡ መሄድ እንዳለባቸውም አመላክተዋል።
የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ማሞ ቴጋ በበኩላቸው የፀረ-ሙስና ቀን የመከበሩ ዋነኛ አላማ ሙስና እያስከተለ ያለውን ዘርፈ ብዙ ችግር ለመከላከል እና በዘርፉ የሚደረገውን ትግል ለማጠናከር ነው ብለዋል።
ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን በመለየት ግንዛቤ በመፍጠር ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በትብብር መስራት የሙስናን ችግር መቅረፍ እንደሚያስችልም ኮሚሽነሩ ጠቁመዋል።
በሙስናና ብልሹ አሰራር ምክንያት ወጣቱ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የችግሩ ተጎጂ ነው ያሉት ኮሚሽነር ማሞ የዘንድሮው የጸረ ሙስና ቀን ሲከበር የወጣቶችን ሥነምግባር እና ታማኝነትን ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ስለመሆኑም አስረድተዋል።
በክልሉ ሙስናና ብልሹ አሰራርን መከላከል የሚያስችል የትውልድ ሥነምግባር ግንባታ ላይ በመስራት የአሰራር ጥናቶችን ማካሄድ፣ ለሚቀርቡ የሙስና ወንጀል ጥቆማዎች ፈጣን ምላሽ መስጠት ከመከላከል ያለፉ የሙስና ወንጀል ጉዳዮችን ለሚመለከታቸው የፍትህ አካላት ማስተላለፍ ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ወጣቶች ሙስና እና ብልሹ አሠራሮችን በመታገል ለሀገረ ግንባታ በትጋት እንዲሰሩ የሀረሪ ክልል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ጥሪ አቀረበ
******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 26/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በአለም አቀፍ ጀረጃ ለ21ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን በማስመልከት የውይይት መድረክ መካሄዱ ተገልጿል።
በሀረሪ ክልል 21ኛውን አለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን ለማክበር ዝግጆቶች መደረጋቸውን የሀረሪ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን አስታውቋል።
ኮሚሽኑም በዓሉ አከባበር በተያዙ ኹነቶች ዙሪያ የውይይት መድረክ አካሒዷል።
በመድረኩ የሀረሪ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ አዳል ሙላቱ እንደገለፁት ወጣቶች የነገ ሀገር ተረካቢ እንደመሆናቸው ሙስና እና ብልሹ አሠራሮችን በመታገል ለሀገር ግንባታ በትጋት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ሙስና ዓለም አቀፍ ወንጀል መኾኑን የገለጹት ኮሚሽነሩ፥ በፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ እያደረሰ ያለውን ጉዳት ማኅበረሠቡ ተገንዝቦ ለፀረ-ሙስና ትግሉ አጋዥ እንዲሆንም ትኩረት መደረጉን ተናግረዋል።
በክልሉ የፀረ-ሙስና ቀንን በተለያዩ ሁነቶች ለማክበር መታቀዱን ገልፀው፥ ለአብነትም የተማሪዎች ጥያቄና መልስ፣ ከወጣት ሊጎች ጋር የውይይት መድረክ፣ የሀብት ምዝገባ ስራና የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ለህብረተሰቡ ለመስጠት መታቀዱን ገልፀዋል ።
በሥነምግባር ግንባታ እና በፀረ-ሙስና ትግሉ የሃይማኖት፣ የዴሞክራሲ፣ የፍትሕ ተቋማትና የሲቪክ ማኅበራት ህብረተሰቡ የድርሻቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።
የዘንድሮው አለምዓቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን "ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፣ የነገን ስብዕና ይገነባል!" በሚል መሪ ሀሳብ ለ21ኛ ግዜ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ እንደሚገኝ የሀረሪ መገናኛ ብዙሃን ድርጅት ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 26/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በአለም አቀፍ ጀረጃ ለ21ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን በማስመልከት የውይይት መድረክ መካሄዱ ተገልጿል።
በሀረሪ ክልል 21ኛውን አለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን ለማክበር ዝግጆቶች መደረጋቸውን የሀረሪ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን አስታውቋል።
ኮሚሽኑም በዓሉ አከባበር በተያዙ ኹነቶች ዙሪያ የውይይት መድረክ አካሒዷል።
በመድረኩ የሀረሪ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ አዳል ሙላቱ እንደገለፁት ወጣቶች የነገ ሀገር ተረካቢ እንደመሆናቸው ሙስና እና ብልሹ አሠራሮችን በመታገል ለሀገር ግንባታ በትጋት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ሙስና ዓለም አቀፍ ወንጀል መኾኑን የገለጹት ኮሚሽነሩ፥ በፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ እያደረሰ ያለውን ጉዳት ማኅበረሠቡ ተገንዝቦ ለፀረ-ሙስና ትግሉ አጋዥ እንዲሆንም ትኩረት መደረጉን ተናግረዋል።
በክልሉ የፀረ-ሙስና ቀንን በተለያዩ ሁነቶች ለማክበር መታቀዱን ገልፀው፥ ለአብነትም የተማሪዎች ጥያቄና መልስ፣ ከወጣት ሊጎች ጋር የውይይት መድረክ፣ የሀብት ምዝገባ ስራና የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ለህብረተሰቡ ለመስጠት መታቀዱን ገልፀዋል ።
በሥነምግባር ግንባታ እና በፀረ-ሙስና ትግሉ የሃይማኖት፣ የዴሞክራሲ፣ የፍትሕ ተቋማትና የሲቪክ ማኅበራት ህብረተሰቡ የድርሻቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።
የዘንድሮው አለምዓቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን "ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፣ የነገን ስብዕና ይገነባል!" በሚል መሪ ሀሳብ ለ21ኛ ግዜ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ እንደሚገኝ የሀረሪ መገናኛ ብዙሃን ድርጅት ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ብልሹ አሰራሮችን እና ሙስናን ለመከላከል ወጣቶች ላይ መስራት የተሻለ ውጤት ያመጣል ተባለ
******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 26/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የቤንሻጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ ሠራተኞች 21ኛውን ዓለምአቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን "ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፣ የነገ ስብዕናን ይገነባል!" በሚል መሪ ቃል በፓናል ውይይት አክብረዋል፡፡
በውይይቱ የተገኙት የቢሮው ኃላፊ ተወካይ አቶ ታረቀኝ ወዲ ቀደም ባሉ በርካታ ዓመታት ሙስናን ለመታገል ብዙ ስራዎች የተሰሩ ቢሆንም የሚፈለገውን ያህል ለውጥ ባለመምጣቱ በተለየ ሁኔታ ወጣቶች ላይ መስራት የተለየ ውጤት ሊያመጣ እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡
የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የዘድሮውን የፀረ-ሙስና ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች እያከበረ መሆኑን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 26/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የቤንሻጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ ሠራተኞች 21ኛውን ዓለምአቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን "ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፣ የነገ ስብዕናን ይገነባል!" በሚል መሪ ቃል በፓናል ውይይት አክብረዋል፡፡
በውይይቱ የተገኙት የቢሮው ኃላፊ ተወካይ አቶ ታረቀኝ ወዲ ቀደም ባሉ በርካታ ዓመታት ሙስናን ለመታገል ብዙ ስራዎች የተሰሩ ቢሆንም የሚፈለገውን ያህል ለውጥ ባለመምጣቱ በተለየ ሁኔታ ወጣቶች ላይ መስራት የተለየ ውጤት ሊያመጣ እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡
የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የዘድሮውን የፀረ-ሙስና ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች እያከበረ መሆኑን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319