ለፍትህ ዘርፍ መካከለኛ አመራሮች የሙስና መከላከል እና ሥነምግባር ግንባታ ላይ ስልጠና እየተሰጠ ነው
******************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 26/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ለፍትህ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት መካከለኛ አመራሮች "ሥነምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልእኮ ስኬት" በሚል መሪ ቃል በፍትህ ዘርፍ የሚስተዋሉ የሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ ስልቶች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ስልጠና እየተሰጠ ነዉ፡፡
በስልጠናዉ የተገኙት የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ፈቃዱ ሰቦቃ ማስልጠኛ ሞጅሉ በ2016 በጀት አመት የተደረገን የሙስና ስጋት ዳሰሳዊ ጥናት ግኝትን መነሻ አድርጎ የብልሹ አሰራር መገለጫዎችና ምልክቶቹን በማየት መከላከያ ስልቶቹ ላይ መግባባት ላይ ለመድረስ ታስቦ መዘጋጀቱን ገልፀዋል፡፡
በተለይም ተቋማት ተኮር ችግሮችን ለመፍታት በየዘርፎቹ ሞጁሎች መዘጋጀታቸዉንም ተቁመዋል፡፡
ምክትል ኮሚሽነሩ አያይዘዉም ህዳር ወር አለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን የሚከበርበት ወር በመሆኑ ከዚሁ ጋር ተያይዞ መዘጋጀቱን ጠቁመው፣ አመራሩ በፍትህ ዘርፍ የሚስተዋሉ የሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ ስልቶችን በመለየት ሰራተኞቹን የማነፅ፣ የመገንባትና ብልሹ አሰራር ክፍተቶችን እየለየና እየደፈነ መሄድ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
በፍትህ ሚኒስቴር የተቋም ግንባታና ሪፎርም ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ክቡርኤርሚያስ የማነብርሃን (ዶ/ር) በበኩላቸው በስልጠናዉ ተካፋይ የሆኑ አመራሮች ብልሹ አሰራርና ሙስና የሚያስከትለዉን አደጋ በመገንዘብ ወደተቋማቸዉ ሲመለሱ ሰራተኞቻቸዉን በማሰልጠን ዉጤታማ፣ ግልፅና አሳታፊ ስርዓትን እዉን ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
በተጨማሪም ዉጤታማና የተሳካ ስልጠና እንዲሆን በመመኘት ስልጠናዉን በጋራ ላዘጋጁት የፍትህ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት፣ የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን እንዲሁም ለፀረ-ሙስና ፎረም ምስጋናቸዉን አቅርበዋል፡፡
የስልጠናዉ ዋና አላማ የፍትህ ዘርፍ እንደማንኛዉም ተቋም ለሙስና ተጋላጭ መሆኑን ተረድቶ በዘርፉ የሚፈፀመዉ ሙስና በዜጎችና በሀገር ላይ የሚያደርሰዉን ከፍተኛ ጉዳት በመገንዘብ በተቋሙ የሚከናወነዉን የስራ ሂደት ከሙስና እና ብልሹ አሰራር የፀዳ እንዲሆን ለማድረግ የራሳቸዉን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ማስቻል መሆኑም ተጠቁሟል፡፡
ስልጠናዉ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሲሆን፣ የሙስና ወንጀል ምንነትና አይነቶች፣ በፍትህ ዘርፍ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራር መከላከያ ስልቶች ላይ መግባባት ላይ መድረስ የሚሉ ይዘቶች ላይ ተመስርቶ የሚሰጥ ይሆናል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
******************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 26/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ለፍትህ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት መካከለኛ አመራሮች "ሥነምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልእኮ ስኬት" በሚል መሪ ቃል በፍትህ ዘርፍ የሚስተዋሉ የሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ ስልቶች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ስልጠና እየተሰጠ ነዉ፡፡
በስልጠናዉ የተገኙት የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ፈቃዱ ሰቦቃ ማስልጠኛ ሞጅሉ በ2016 በጀት አመት የተደረገን የሙስና ስጋት ዳሰሳዊ ጥናት ግኝትን መነሻ አድርጎ የብልሹ አሰራር መገለጫዎችና ምልክቶቹን በማየት መከላከያ ስልቶቹ ላይ መግባባት ላይ ለመድረስ ታስቦ መዘጋጀቱን ገልፀዋል፡፡
በተለይም ተቋማት ተኮር ችግሮችን ለመፍታት በየዘርፎቹ ሞጁሎች መዘጋጀታቸዉንም ተቁመዋል፡፡
ምክትል ኮሚሽነሩ አያይዘዉም ህዳር ወር አለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን የሚከበርበት ወር በመሆኑ ከዚሁ ጋር ተያይዞ መዘጋጀቱን ጠቁመው፣ አመራሩ በፍትህ ዘርፍ የሚስተዋሉ የሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ ስልቶችን በመለየት ሰራተኞቹን የማነፅ፣ የመገንባትና ብልሹ አሰራር ክፍተቶችን እየለየና እየደፈነ መሄድ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
በፍትህ ሚኒስቴር የተቋም ግንባታና ሪፎርም ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ክቡርኤርሚያስ የማነብርሃን (ዶ/ር) በበኩላቸው በስልጠናዉ ተካፋይ የሆኑ አመራሮች ብልሹ አሰራርና ሙስና የሚያስከትለዉን አደጋ በመገንዘብ ወደተቋማቸዉ ሲመለሱ ሰራተኞቻቸዉን በማሰልጠን ዉጤታማ፣ ግልፅና አሳታፊ ስርዓትን እዉን ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
በተጨማሪም ዉጤታማና የተሳካ ስልጠና እንዲሆን በመመኘት ስልጠናዉን በጋራ ላዘጋጁት የፍትህ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት፣ የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን እንዲሁም ለፀረ-ሙስና ፎረም ምስጋናቸዉን አቅርበዋል፡፡
የስልጠናዉ ዋና አላማ የፍትህ ዘርፍ እንደማንኛዉም ተቋም ለሙስና ተጋላጭ መሆኑን ተረድቶ በዘርፉ የሚፈፀመዉ ሙስና በዜጎችና በሀገር ላይ የሚያደርሰዉን ከፍተኛ ጉዳት በመገንዘብ በተቋሙ የሚከናወነዉን የስራ ሂደት ከሙስና እና ብልሹ አሰራር የፀዳ እንዲሆን ለማድረግ የራሳቸዉን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ማስቻል መሆኑም ተጠቁሟል፡፡
ስልጠናዉ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሲሆን፣ የሙስና ወንጀል ምንነትና አይነቶች፣ በፍትህ ዘርፍ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራር መከላከያ ስልቶች ላይ መግባባት ላይ መድረስ የሚሉ ይዘቶች ላይ ተመስርቶ የሚሰጥ ይሆናል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ኮሚሽኑ ሙስናን በመከላከል እና ህግን በማስከበር ዙሪያ የትስስር እና የቅንጅት አሰራርን ሊያጠናክር የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጋር ተፈራረመ
**************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 26/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ሙስናን በመከላከል እና ህግን በማስከበር ዙሪያ የትስስር እና የቅንጅት አሰራርን ሊያጠናክር የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጋር ተፈራርሟል፡፡
በፊርማ ሥነስርዓቱ የተገኙት የፌደራል የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሳሙኤል ኡርቃቶ (ፒኤችዲ) ኮሚሽኑ ትውልዱን በሥነምግባር በማነፅና ሙስናን በመከላከል ረገድ በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡
በቀጣይም ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ጋር በመቀናጀት መረጃና መስረጃን መሰረት በማድረግ ሙሰኞችን ተጠያቂ የማድረግ ስራ በቅንጅት እንሰራለን ብለዋል፡፡
የዛሬው ስምምነት በሁለቱ ተቋማት ነባር የሥራ ትስስሮች ቢኖሩም በቀጣይ በሥነምግባር ግንባታ እና ሙስና መከላከል ሥራ ላይ አጠናክሮ ለመቀጠል ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ኮሚሽነሩ አክለውም የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በአጭር ጊዜ ወስጥ እንደሀገር የሚያኮራ የዘመነ ተቋም እየገነባ መሆኑን ተናግረው፣ የመግባቢያ ስምምነቱ የሙስና ወንጀል መከላከልና የምርመራ ሥራን ዕውቀትና ብቃትን መሠረት ባደረገ መልኩ ለመስራት ትልቅ ዕድል ይፈጥራል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በበኩላቸው በመግባቢያ ሰነዱ ፊርማ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር ከሀገራዊ ሪፎርሙ በኃላ የመንግስት ተቋማት በጋራ ተቀራርበው እና ተቀናጅተው የመስራት ባህል በከፍተኛ ደረጃ እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡
የሙስና ወንጀልን ለመከላከል በሁለቱ ተቋማት የበለፀገውን ቴክኖሎጂ በጋራ አስተሳስሮ በመጠቀም የሚቀርቡ የሙስና መዝገቦች ላይ ጠንካራ ምርመራ በማድረግ ጠርተው ለአቃቢ ሕግ እንዲቀርቡ ስምምነቱ ትልቅ እድል ይፈጥራልም ብለዋል፡፡
ክቡር ኮሚሽነር ጀነራል አያይዘውም የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የሙስና ወንጀልን በመከላከልና ሙስናን የሚፀየፍ ማህበረስብ እንዲፈጠር በሀገራችን እየተደረገ ያለውን ርብርብ በማገዝ ከፍተኛ ሥራ እያከናወነ መሆኑን አንስተዋል፡፡
በቀጣይም የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ባለሙያዎችን በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በማሰልጠንና የተለያዩ ምርምርና ጥናቶችን በማካሄድ ድጋፍ እንደሚደረግ ገልፀዋል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
**************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 26/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ሙስናን በመከላከል እና ህግን በማስከበር ዙሪያ የትስስር እና የቅንጅት አሰራርን ሊያጠናክር የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጋር ተፈራርሟል፡፡
በፊርማ ሥነስርዓቱ የተገኙት የፌደራል የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሳሙኤል ኡርቃቶ (ፒኤችዲ) ኮሚሽኑ ትውልዱን በሥነምግባር በማነፅና ሙስናን በመከላከል ረገድ በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡
በቀጣይም ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ጋር በመቀናጀት መረጃና መስረጃን መሰረት በማድረግ ሙሰኞችን ተጠያቂ የማድረግ ስራ በቅንጅት እንሰራለን ብለዋል፡፡
የዛሬው ስምምነት በሁለቱ ተቋማት ነባር የሥራ ትስስሮች ቢኖሩም በቀጣይ በሥነምግባር ግንባታ እና ሙስና መከላከል ሥራ ላይ አጠናክሮ ለመቀጠል ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ኮሚሽነሩ አክለውም የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በአጭር ጊዜ ወስጥ እንደሀገር የሚያኮራ የዘመነ ተቋም እየገነባ መሆኑን ተናግረው፣ የመግባቢያ ስምምነቱ የሙስና ወንጀል መከላከልና የምርመራ ሥራን ዕውቀትና ብቃትን መሠረት ባደረገ መልኩ ለመስራት ትልቅ ዕድል ይፈጥራል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በበኩላቸው በመግባቢያ ሰነዱ ፊርማ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር ከሀገራዊ ሪፎርሙ በኃላ የመንግስት ተቋማት በጋራ ተቀራርበው እና ተቀናጅተው የመስራት ባህል በከፍተኛ ደረጃ እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡
የሙስና ወንጀልን ለመከላከል በሁለቱ ተቋማት የበለፀገውን ቴክኖሎጂ በጋራ አስተሳስሮ በመጠቀም የሚቀርቡ የሙስና መዝገቦች ላይ ጠንካራ ምርመራ በማድረግ ጠርተው ለአቃቢ ሕግ እንዲቀርቡ ስምምነቱ ትልቅ እድል ይፈጥራልም ብለዋል፡፡
ክቡር ኮሚሽነር ጀነራል አያይዘውም የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የሙስና ወንጀልን በመከላከልና ሙስናን የሚፀየፍ ማህበረስብ እንዲፈጠር በሀገራችን እየተደረገ ያለውን ርብርብ በማገዝ ከፍተኛ ሥራ እያከናወነ መሆኑን አንስተዋል፡፡
በቀጣይም የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ባለሙያዎችን በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በማሰልጠንና የተለያዩ ምርምርና ጥናቶችን በማካሄድ ድጋፍ እንደሚደረግ ገልፀዋል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319