ት/ቤቶች 21ኛውን ዓለምአቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን በተለያዩ ሁነቶች አክብረዋል
******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 24/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የደሴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት የሥነምግባር መከታተያ ክፍል ከመርሀ ጥበብ አጠቃላይ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጋር በመተባበር 21ኛውን ዓለምአቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን "ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፤ የነገን ስብዕና ይገነባል!" በሚል መሪ መልዕክት በተለያዩ ሁነቶች አክብረዋል።
በዓሉ በተማሪዎች መካከል በጥያቄና መልስ ውድድር፣ በድራማና ሥነፅሁፍ እንዲሁም በባህላዊ ጭፈራዎች በማወዳደር በደማቅ ሁኔታ የተከበረ መሆኑ ተገልጿል፡፡
በውድድሩም የተሻለ ውጤት በማምጣት አሸናፊ ለሆኑትና ከ1-4ኛ ደረጃ ለወጡት ተማሪዎች እና ለበዓሉ መሳካት አስተዋፅኦ ለአበረከቱ መምህራን በደሴ ከተማ አስስተዳደር ከንቲባ ፅ/ቤት የሥነምግባር መከታተያ ክፍል ባለሙያ አቶ ሰይድ እሸቱ የመጽሐፍት እና ሰርትፍኬት ሽልማት የተበረከተ መሆኑን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 24/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የደሴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት የሥነምግባር መከታተያ ክፍል ከመርሀ ጥበብ አጠቃላይ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጋር በመተባበር 21ኛውን ዓለምአቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን "ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፤ የነገን ስብዕና ይገነባል!" በሚል መሪ መልዕክት በተለያዩ ሁነቶች አክብረዋል።
በዓሉ በተማሪዎች መካከል በጥያቄና መልስ ውድድር፣ በድራማና ሥነፅሁፍ እንዲሁም በባህላዊ ጭፈራዎች በማወዳደር በደማቅ ሁኔታ የተከበረ መሆኑ ተገልጿል፡፡
በውድድሩም የተሻለ ውጤት በማምጣት አሸናፊ ለሆኑትና ከ1-4ኛ ደረጃ ለወጡት ተማሪዎች እና ለበዓሉ መሳካት አስተዋፅኦ ለአበረከቱ መምህራን በደሴ ከተማ አስስተዳደር ከንቲባ ፅ/ቤት የሥነምግባር መከታተያ ክፍል ባለሙያ አቶ ሰይድ እሸቱ የመጽሐፍት እና ሰርትፍኬት ሽልማት የተበረከተ መሆኑን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
አለምዓቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን ምክንያት በማድረግ የጥያቄና መልስ ውድድር ተካሄደ
******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 24/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) "ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፣ የነገን ስብዕና ይገነባል!" በሚል መሪ ሀሳብ 21ኛውን አለምዓቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በድሬዳዋ አስተዳደር በሚገኙ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በሚማሩ ተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር ተካሄዷል።
በዚሁ መርሀ-ግብር በመገኘት ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ፌኑስ አብዱልጀባር ሙስናን አውቆ የሚታገል ሀገር ተረካቢ ዜጋ ለማፍራት በሚደረገው ጥረት ሀገር ተረካቢ የሆኑ ተማሪዎች ላይ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
አቶ ፌኑስ አክለውም በትምህርት ቤቶች ውስጥ የሚገኙ ባለድርሻ አካላት የትውልድ ስብእና ግንባታ ላይ ያላቸው ተፅእኖ ከፍተኛ መሆኑን አውቀው በርካታ ስራዎችን መስራት እንደሚገባቸውም ገልፀዋል።
በቀጣይም አለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን ምክንያት በማድረግ በድሬዳዋ አስተዳደር በተለያዩ መርሀ-ግብሮች እንደሚከበር መገለፁን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 24/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) "ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፣ የነገን ስብዕና ይገነባል!" በሚል መሪ ሀሳብ 21ኛውን አለምዓቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በድሬዳዋ አስተዳደር በሚገኙ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በሚማሩ ተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር ተካሄዷል።
በዚሁ መርሀ-ግብር በመገኘት ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ፌኑስ አብዱልጀባር ሙስናን አውቆ የሚታገል ሀገር ተረካቢ ዜጋ ለማፍራት በሚደረገው ጥረት ሀገር ተረካቢ የሆኑ ተማሪዎች ላይ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
አቶ ፌኑስ አክለውም በትምህርት ቤቶች ውስጥ የሚገኙ ባለድርሻ አካላት የትውልድ ስብእና ግንባታ ላይ ያላቸው ተፅእኖ ከፍተኛ መሆኑን አውቀው በርካታ ስራዎችን መስራት እንደሚገባቸውም ገልፀዋል።
በቀጣይም አለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን ምክንያት በማድረግ በድሬዳዋ አስተዳደር በተለያዩ መርሀ-ግብሮች እንደሚከበር መገለፁን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 21ኛው አለምዓቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት እየተከበረ ነው
*******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 25/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አመራር፣ ዳኞችና ሰራተኞች በአለም አቀፍ ደረጃ ለ21ኛ ጊዜ የሚከበረዉን የፀረ-ሙስና ቀን “ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፤ የነገን ስብዕና ይገነባል!” በሚል መሪ ቃል በድምቀት መከበሩ ተገልጿል።
የዉይይት መድረኩን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ሠንበታ ቀጀላ እና የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ነጅመዲን አልማሃዲ በጋራ መርተውታል።
በመድረኩ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ሠንበታ ቀጀላ ሙስና እድገትን የሚያቀጭጭ በህዝቦች መካከል መተማመንን የሚሸረሽር እኩይ ተግባር ነው ብለዋል።
ይህንን እኩይ ተግባር አምርሮ መታገል እንደሚገባ አስታዉሰዉ፥ በተለይም በመልካም ሥነ-ምግባር የታነፀ እና ሙስናን የሚፀየፍ ትዉልድ ማፍራት ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
በዉይይቱ ላይም የፀረ-ሙስና ቀንን አስመልክቶ የመስሪያቤቱ የሥነ-ምግባር መከታተያ ባለሙያ ወ/ሪት ሰሚራ ኡስማን ሠነድ አቅርበው ዉይይት መደረጉን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በዉይይቱ ሙስና የመንግስትን ሥራን ሥነምግባራዊ እና ህጋዊ መሠረት ባለዉ መመሪያና ደንብ ላይ ተመርኩዞ ማከናወን አለመቻል የሚፈጠር የሞራል ዝቅጠት፣ የመልካም አስተዳደር ጉድለት፣ ስግብግብነት፣ ራስወዳድነት እና በአቋራጭ የመበልፀግ አባዜ ሲሆን፣ የሀገርን ዕድገት የሚገታ መርዛማ በሽታ በመሆኑ በጋራ መከላከል እንደሚገባ መነሳቱ ተገልጿል።
ሙስና እና ብልሹ አሰራር የመንግስትን የአገልግሎት አሰጣጥ ቅልጥፍና፣ ታማኝነት እና ፍትሃዊነትን በእጅጉ የሚጎዳ፣ የዕድገት ነቀርሳ መሆኑን በመገንዘብ የመንግስት ሠራተኞች እና አመራሮች እነዚህን ተግዳሮቶች በመዋጋትና በመታገል አገልግሎቶችን ግልጽ እና ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ተግባራዊ ማድረግ ይገባልም ተብሏል።
የዉይይቱ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት አንዱ የሙስና አይነት የመንግስት ስራ ሰዓት አለማክበርና አድሎዊ አሰራር በመሆኑ ሁሉም ሠራተኞች በአግባቡ የመንግስት ስራ ሰዓት በማክበር በተመደቡበት ሙያ ፍትሃዊ አገልግሎት ለማህብረሰቡ መስጠት ይገባል ብለዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
*******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 25/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አመራር፣ ዳኞችና ሰራተኞች በአለም አቀፍ ደረጃ ለ21ኛ ጊዜ የሚከበረዉን የፀረ-ሙስና ቀን “ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፤ የነገን ስብዕና ይገነባል!” በሚል መሪ ቃል በድምቀት መከበሩ ተገልጿል።
የዉይይት መድረኩን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ሠንበታ ቀጀላ እና የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ነጅመዲን አልማሃዲ በጋራ መርተውታል።
በመድረኩ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ሠንበታ ቀጀላ ሙስና እድገትን የሚያቀጭጭ በህዝቦች መካከል መተማመንን የሚሸረሽር እኩይ ተግባር ነው ብለዋል።
ይህንን እኩይ ተግባር አምርሮ መታገል እንደሚገባ አስታዉሰዉ፥ በተለይም በመልካም ሥነ-ምግባር የታነፀ እና ሙስናን የሚፀየፍ ትዉልድ ማፍራት ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
በዉይይቱ ላይም የፀረ-ሙስና ቀንን አስመልክቶ የመስሪያቤቱ የሥነ-ምግባር መከታተያ ባለሙያ ወ/ሪት ሰሚራ ኡስማን ሠነድ አቅርበው ዉይይት መደረጉን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በዉይይቱ ሙስና የመንግስትን ሥራን ሥነምግባራዊ እና ህጋዊ መሠረት ባለዉ መመሪያና ደንብ ላይ ተመርኩዞ ማከናወን አለመቻል የሚፈጠር የሞራል ዝቅጠት፣ የመልካም አስተዳደር ጉድለት፣ ስግብግብነት፣ ራስወዳድነት እና በአቋራጭ የመበልፀግ አባዜ ሲሆን፣ የሀገርን ዕድገት የሚገታ መርዛማ በሽታ በመሆኑ በጋራ መከላከል እንደሚገባ መነሳቱ ተገልጿል።
ሙስና እና ብልሹ አሰራር የመንግስትን የአገልግሎት አሰጣጥ ቅልጥፍና፣ ታማኝነት እና ፍትሃዊነትን በእጅጉ የሚጎዳ፣ የዕድገት ነቀርሳ መሆኑን በመገንዘብ የመንግስት ሠራተኞች እና አመራሮች እነዚህን ተግዳሮቶች በመዋጋትና በመታገል አገልግሎቶችን ግልጽ እና ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ተግባራዊ ማድረግ ይገባልም ተብሏል።
የዉይይቱ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት አንዱ የሙስና አይነት የመንግስት ስራ ሰዓት አለማክበርና አድሎዊ አሰራር በመሆኑ ሁሉም ሠራተኞች በአግባቡ የመንግስት ስራ ሰዓት በማክበር በተመደቡበት ሙያ ፍትሃዊ አገልግሎት ለማህብረሰቡ መስጠት ይገባል ብለዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319