Federal Ethics And Anti- Corruption Commission
9.88K subscribers
10.4K photos
245 videos
32 files
3.05K links
Download Telegram
ከሙስና የፀዳ ሀገራዊ መስተንግዶ ለቱሪዝም ዘርፍ ወሳኝ ነው - ሚኒስትር ዴኤታ ስለሺ ግርማ

******

(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 24/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ከሙስና የፀዳ ሀገራዊ መስተንግዶ ለቱሪዝም ዘርፍ ወሳኝ መሆኑን የኢፌዴሪ ቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ስለሺ ግርማ ገልፀዋል።

ለቱሪዝም ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት አመራሮች "ሥነምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት" በሚል መሪ ቃል ዘርፍ ተኮር የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ስልጠና በዶ/ር ምህረተአብ አብርሃም እየተሰጠ ይገኛል።

በመድረኩ የተገኙት የኢፌዲሪ ቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ስለሺ ግርማ ከሙስና የፀዳ ሀገራዊ መስተንግዶ ለቱሪዝም ዘርፍ ወሳኝ በመሆኑ በሥነምግባራዊ አመራርነት ጎልቶ ሊታይ እንደሚገባ ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት ሙስና በጣም ፈታኝ የሆነበት ጊዜ እንደመሆኑ በቱሪዝሙ ዘርፍ ሊያስከትል ከሚችለው ጉዳት አንፃር ሀገሪቷ ማግኘት ያለባትን ገቢ ሊያሳጣ እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡

በመድረኩ የተገኙት የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ፈቃዱ ሰቦቃ በበኩላቸው ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል በጥናት በመደገፍ ዘርፍ ተኮር የስልጠና ሞጁል በማዘጋጀትና የመከላከያ ስልቶች በመለየት በዘርፎች ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።

ስልጠናው ለኢፌዴሪ ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ ለኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን እና ለኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን አመራሮችና የሥራ ኃላፊዎች በቱሪዝም ዘርፍ የሚስተዋሉ የሙስና እና ብልሹ አሰራሮች መከላከያ ስልቶች ላይ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚሰጥ ይሆናል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

#NCRS ሞባይል መተግበሪያ

#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details

#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ሙስና ሀገርን እና ዜጎችን የሚጎዳ የህዝብ ጠላት ድንበር ዘለል ወንጀል በመሆኑ በጋራ መታገል ይገባል

******

(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 24/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት አመራሮችና ሰራተኞች 21ኛው አለምዓቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል።

አለምዓቀፍ የፀረ-ሙስና ቀኑን አስመልክቶ የከንቲባ ጽ/ቤት ፋይናንስና አስተዳደር ዘርፍ ሃላፊ አቶ ፍቃዱ አዱኛ ሙስና አገርን እና ዜጎችን የሚጎዳ የህዝብ ጠላትና ድንበር ዘለል ወንጀል በመሆኑ በጋራ መታገል ይገባል ብለዋል።

የከንቲባ ጽ/ቤት የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ፀጋዬ ዳንደና ሙሰኝነት ከሥነ-ምግባር ውድቀት እና ከሞራል ዝቅጠት የሚመነጭ ዜጎችን ለረሃብ፣ ለኑሮ ውድነት፣ ለስደት የሚዳርግ አደገኛ ወንጀል በመሆኑ ጠንካራ የአሰራር ሥርዓት በመፍጠር ልንከላከለው እንደሚገባ አመልክተዋል፡፡

በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኮተቤ ዩኒቨርሲቲ መምህር ዶክተር የሺጥላ መንግስቴ የውይይት ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን፥ በፕሮግራሙ ላይ ግንባር ቀደም የሆኑና ሰናይ ሥነ-ምግባር ያላቸው ሰራተኞች በጽ/ቤቱ የዘርፍ ሃላፊዎች ተመርጠው በጥያቄና መልስ ውድድር በማሳተፍ ከአንድ እስከ አምስት ለወጡ ተወዳዳሪዎች የሞባይል ሽልማት መሰጠቱ ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

#NCRS ሞባይል መተግበሪያ

#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details

#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ኮሚሽኑ የ2017 ዓ.ም አለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን በደማቅ ሁኔታ አከበረ

******

(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 24/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የሲዳማ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን አመራሮችና ሥራተኞች "ወጣቱን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፣ የነገን ስብዕናን ለመገንባት!" በሚል መሪ ቃል 21ኛውን ዓለምአቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን በተለያዩ ዝግጅቶች በደማቅ ሁኔታ አክብሯል።

በዓሉን በንግግር የከፈቱት የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ክብርት ወ/ሮ ዘላለም ለማ ሙስና ለሁሉም ህብረተሰብ ክፍል የሚያደርሰዉ ተፅዕኖ ከፍተኛ ነው ብለዋል።

በተለይ በወጣቱ ላይ እያደረሰ ያለዉ ተፅዕኖና አደጋ ከፍተኛ በመሆኑ ወጣቱን በፀረ-ሙስና ትግሉ ላይ በማሣተፍ ድርሻውን እንዲወጣና ከሙስና ተፅዕኖ ራሱን መከላከል እንዲችል ማድረግ የሁሉም ኃላፊነት መሆኑን አሳስበዋል።

በመድረኩ ወጣቱን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፣ የነገ ስብዕናን ለመገንባት! የሚል ሰነድ በኮሚሽኑ ሥልጠና ዳይረክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ወኔ ሀመሶ ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን፥ ከመድረኩ የተለያዩ ምላሾችና አቅጣጫዎች መቀመጡን ከኮሚሽኑ የማህበራዊ ትስስር ገፅ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

#NCRS ሞባይል መተግበሪያ

#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details

#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319