ተቋማት የሥነምግባር ግንባታ እና የሙስና መከላከል ሥራን በዕቅድ አካተው እንዲሠሩ ተጠየቀ
******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 22/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በአማራ ክልል "ሥነምግባርን በማጎልበት እና ሙስናን በመከላከል ረገድ የምክር ቤቶች ሚና" በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀ ሰነድ ላይ የክልሉ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎችና አባላት፣ የኮሚሽኑ የሥራ ኀላፊዎች እና ባለሙያዎች ጋር ውይይት ተደርጓል።
የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሀብታሙ ሞገስ እንዳሉት በተቋማት ላይ የታዩ የአሠራር ችግሮች በሀገር አቀፍ ደረጃ በጥናት ተለይተዋል። ይሁን እንጅ ባለፉት ተከታታይ ዓመታት በተከስተው የጸጥታ ችግር ምክንያት በተቋማት የታዩ ብልሹ አሠራሮችን በሚፈለገው መንገድ ለመከላከል ፈታኝ አድርጎት ቆይቷል ብለዋል።
አሁን ላይ የተለዩ ችግሮችን ለመፍታት ወደ ሥራ መገባቱን ገልፀው፥ ብልሹ አሠራር በታየባቸው ተቋማት ላይ ጥናቶችን በማካሄድ እርምጃ እንዲወሰድ መደረጉን ጠቁመዋል።
በሌሎች ተቋማት ላይም ጥናቶች እየተደረጉ መኾኑን ጠቁመው፥ የሃብት ምዝገባ እና ሌሎች ሥራዎችም እየተሠሩ መኾኑን ተናግረዋል።
የትምህርት፣ የሃይማኖት እና የመንግስት ተቋማት በሥነምግባር ግንባታ ላይ አተኩረው እንዲሠሩ ሥራዎች መሠራታቸውን አንስተዋል። በቀጣይም ሌሎች ተቋማት የሥነምግባር ግንባታ እና የሙስና መከላከል ሥራን በዕቅድ አካተው እንዲሠሩ ጠይቀዋል።
ምክር ቤቶችም ተቋማት ለሥነምግባር ግንባታ እና ለሙስና መከላከል የሰጡትን ትኩረት የመከታተል እና የመቆጣጠር ኀላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።
በክልሉ ምክር ቤት የሕግ፣ ፍትሕ እና አሥተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሣቢ ደሴ ጥላሁን (ፒኤችዲ) ሙስናን የሚጸየፍ ትውልድ ለመፍጠር ከትምህርት ተቋማት ባለፈ ቤተሰብ፣ የሃይማኖት ተቋማት፣ የሲቪክ ሶሳይቲ፣ ሚዲያዎች እና መንግሥታዊ ያልኾኑ ተቋማት ግብረ ገብ ላይ ትኩረት ሰጥተው ሊሠሩ ይገባል ብለዋል።
የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴዎችም የሚከታተሏቸው ተቋማት ለሥነምግባር ግንባታ እና ለሙስና መከላከል ትኩረት መስጠታቸውን ክትትል እና ቁጥጥር እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።
አሁን ላይ የፀረ-ሙስና ትግሉ እንቅስቃሴ እየተጠና መኾኑን ገልፀው፥ ጥናቱ ይፋ ሲኾን በተገኙ ግኝቶች ላይ ግፊት ይደረጋል ብለዋል።
የክልሉ ምክር ቤት የበጀት እና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሣቢ ሀናን አብዱ እንዳሉት የበጀት እና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ የሚከታተላቸው ተቋማት አሠራርን መሠረት ያደረገ ግዥ እንዲፈጸም ክትትል እያደረገ ይገኛል። ሥልጠና ከመስጠት ባለፈ በዕቅድ እንዲመሩ እየተደረገ መኾኑንም ገልጸዋል።
ከአሠራር ውጭ ግዥ ፈጽመው በተገኙ ተቋማት ላይ ደግሞ የማስተካከያ ርምጃ እየተወሰደ ይገኛል ብለዋል። ባለፉት ዓመታት በክልሉ የተከሰተውን የጸጥታ መደፍረስ እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ያለአግባብ ተጠቃሚነቶች እንደነበሩ በተደረጉ ክትትሎች ማረጋገጥ መቻሉን ጠቁመዋል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በድርጊቱ ተሳትፈው በተገኙ የሥራ ኀላፊዎች እና ባለሙያዎች ላይ ሕጋዊ ርምጃ እየተወሰደ መኾኑን መናገራቸውን አሚኮ ዘግቧል።
በቀጣይም የቁጥጥሩ እና ተጠያቂነትን የማረጋገጥ ሥራው በምክር ቤቱ እና ምክር ቤቱ ባቋቋማቸው የፍትሕ ተቋማት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል።
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 22/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በአማራ ክልል "ሥነምግባርን በማጎልበት እና ሙስናን በመከላከል ረገድ የምክር ቤቶች ሚና" በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀ ሰነድ ላይ የክልሉ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎችና አባላት፣ የኮሚሽኑ የሥራ ኀላፊዎች እና ባለሙያዎች ጋር ውይይት ተደርጓል።
የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሀብታሙ ሞገስ እንዳሉት በተቋማት ላይ የታዩ የአሠራር ችግሮች በሀገር አቀፍ ደረጃ በጥናት ተለይተዋል። ይሁን እንጅ ባለፉት ተከታታይ ዓመታት በተከስተው የጸጥታ ችግር ምክንያት በተቋማት የታዩ ብልሹ አሠራሮችን በሚፈለገው መንገድ ለመከላከል ፈታኝ አድርጎት ቆይቷል ብለዋል።
አሁን ላይ የተለዩ ችግሮችን ለመፍታት ወደ ሥራ መገባቱን ገልፀው፥ ብልሹ አሠራር በታየባቸው ተቋማት ላይ ጥናቶችን በማካሄድ እርምጃ እንዲወሰድ መደረጉን ጠቁመዋል።
በሌሎች ተቋማት ላይም ጥናቶች እየተደረጉ መኾኑን ጠቁመው፥ የሃብት ምዝገባ እና ሌሎች ሥራዎችም እየተሠሩ መኾኑን ተናግረዋል።
የትምህርት፣ የሃይማኖት እና የመንግስት ተቋማት በሥነምግባር ግንባታ ላይ አተኩረው እንዲሠሩ ሥራዎች መሠራታቸውን አንስተዋል። በቀጣይም ሌሎች ተቋማት የሥነምግባር ግንባታ እና የሙስና መከላከል ሥራን በዕቅድ አካተው እንዲሠሩ ጠይቀዋል።
ምክር ቤቶችም ተቋማት ለሥነምግባር ግንባታ እና ለሙስና መከላከል የሰጡትን ትኩረት የመከታተል እና የመቆጣጠር ኀላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።
በክልሉ ምክር ቤት የሕግ፣ ፍትሕ እና አሥተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሣቢ ደሴ ጥላሁን (ፒኤችዲ) ሙስናን የሚጸየፍ ትውልድ ለመፍጠር ከትምህርት ተቋማት ባለፈ ቤተሰብ፣ የሃይማኖት ተቋማት፣ የሲቪክ ሶሳይቲ፣ ሚዲያዎች እና መንግሥታዊ ያልኾኑ ተቋማት ግብረ ገብ ላይ ትኩረት ሰጥተው ሊሠሩ ይገባል ብለዋል።
የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴዎችም የሚከታተሏቸው ተቋማት ለሥነምግባር ግንባታ እና ለሙስና መከላከል ትኩረት መስጠታቸውን ክትትል እና ቁጥጥር እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።
አሁን ላይ የፀረ-ሙስና ትግሉ እንቅስቃሴ እየተጠና መኾኑን ገልፀው፥ ጥናቱ ይፋ ሲኾን በተገኙ ግኝቶች ላይ ግፊት ይደረጋል ብለዋል።
የክልሉ ምክር ቤት የበጀት እና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሣቢ ሀናን አብዱ እንዳሉት የበጀት እና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ የሚከታተላቸው ተቋማት አሠራርን መሠረት ያደረገ ግዥ እንዲፈጸም ክትትል እያደረገ ይገኛል። ሥልጠና ከመስጠት ባለፈ በዕቅድ እንዲመሩ እየተደረገ መኾኑንም ገልጸዋል።
ከአሠራር ውጭ ግዥ ፈጽመው በተገኙ ተቋማት ላይ ደግሞ የማስተካከያ ርምጃ እየተወሰደ ይገኛል ብለዋል። ባለፉት ዓመታት በክልሉ የተከሰተውን የጸጥታ መደፍረስ እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ያለአግባብ ተጠቃሚነቶች እንደነበሩ በተደረጉ ክትትሎች ማረጋገጥ መቻሉን ጠቁመዋል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በድርጊቱ ተሳትፈው በተገኙ የሥራ ኀላፊዎች እና ባለሙያዎች ላይ ሕጋዊ ርምጃ እየተወሰደ መኾኑን መናገራቸውን አሚኮ ዘግቧል።
በቀጣይም የቁጥጥሩ እና ተጠያቂነትን የማረጋገጥ ሥራው በምክር ቤቱ እና ምክር ቤቱ ባቋቋማቸው የፍትሕ ተቋማት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል።
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
በማዕድኑ ዘርፍ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮች መታረም እንዳለባቸው ኮሚሽኑ አስታወቀ
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 22/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በማዕድኑ ዘርፍ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮች መንግስት በዘርፉ የሚያገኘውን ጥቅም የሚያሳጣ፣ ለሃገርና ለማህበረስብ ዕድገት እንቅፋት የሚፈጥር መሆኑን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር መንግስቱ ላሎ ገልፀዋል፡፡
ዘርፉ የግልጸኝነት መጓደሎች የነበሩበት በመሆኑ በጠንካራ የሥራ ሥነምግባር በመመራት ክፍተቶችን መሙላት እንደሚገባ ኮሚሽነሩ ተናግረዋል፡፡
የክልሉ የማዕድን ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አድማሱ ሞርካ በበኩላቸው ተቋሙ በፊት በኤጀንሲ ደረጃ ከነበረበት ሁኔታ በርካታ መሻሻሎች መኖራቸውን ገልፀዋል ።
አሁንም በአሰራር ሂደት የሚስተዋሉ ችግሮችን ቢሮው እንደሚፈትሽና የማስተካከያ ስራዎችንም እንደሚሰራ ጠቁመዋል፡፡
ኃላፊው አክለውም ማማለያ ገንዘቦችን እምቢ የሚል ስብዕና ከተሰጠን አደራ ጋር አያይዘን መገንባት እስከምንችል እራሳችንን መፈተሸና መገምገም እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ቢሮው መሰል ክፍተቶችንም ለመሙላት ከክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ጋር በቅርበት በመስራት የአገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡
የቢሮው ሠራተኞች 21ኛውን አለምዓቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን “ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፥ የነገን ስብዕና ይገነባል!” በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ሁነቶች አክብረዋል።
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 22/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በማዕድኑ ዘርፍ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮች መንግስት በዘርፉ የሚያገኘውን ጥቅም የሚያሳጣ፣ ለሃገርና ለማህበረስብ ዕድገት እንቅፋት የሚፈጥር መሆኑን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር መንግስቱ ላሎ ገልፀዋል፡፡
ዘርፉ የግልጸኝነት መጓደሎች የነበሩበት በመሆኑ በጠንካራ የሥራ ሥነምግባር በመመራት ክፍተቶችን መሙላት እንደሚገባ ኮሚሽነሩ ተናግረዋል፡፡
የክልሉ የማዕድን ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አድማሱ ሞርካ በበኩላቸው ተቋሙ በፊት በኤጀንሲ ደረጃ ከነበረበት ሁኔታ በርካታ መሻሻሎች መኖራቸውን ገልፀዋል ።
አሁንም በአሰራር ሂደት የሚስተዋሉ ችግሮችን ቢሮው እንደሚፈትሽና የማስተካከያ ስራዎችንም እንደሚሰራ ጠቁመዋል፡፡
ኃላፊው አክለውም ማማለያ ገንዘቦችን እምቢ የሚል ስብዕና ከተሰጠን አደራ ጋር አያይዘን መገንባት እስከምንችል እራሳችንን መፈተሸና መገምገም እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ቢሮው መሰል ክፍተቶችንም ለመሙላት ከክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ጋር በቅርበት በመስራት የአገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡
የቢሮው ሠራተኞች 21ኛውን አለምዓቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን “ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፥ የነገን ስብዕና ይገነባል!” በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ሁነቶች አክብረዋል።
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባልደረባ ወድቆ ያገኙትን 50 ሺህ ዶላር ለባለቤቱ አስረከቡ
******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 23/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሴኪዩሪቲ ክፍል ባልደረባ ፍሬዘር በቀለ ወድቆ ያገኙትን 50 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ለባለቤቱ አስረከቡ፡፡
ገንዘቡን አቶ ፍሬዘር ሕዳር 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከመንገደኛ ወድቆ ማግኘታቸውን አየር መንገዱ አስታውቋል፡፡
ግለሰቡ በኢትዮጵያዊ ጨዋነትና ሲቀጠሩ በገቡት ቃል መሰረት አየር መንገዱ የሚመራበትን መርህና ሥነ-ምግባር እንዲሁም ሙያዊ ታማኝነታቸውን በብቃት መወጣታቸውንም አስታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለምአቀፍ ደረጃውን የጠበቀ እና ሥነ-ምግባር የተላበሰ የደንበኞች አገልግሎት ለመስጠት ሁሌም እንደሚተጋ ነው በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ያስታወቀው፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 23/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሴኪዩሪቲ ክፍል ባልደረባ ፍሬዘር በቀለ ወድቆ ያገኙትን 50 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ለባለቤቱ አስረከቡ፡፡
ገንዘቡን አቶ ፍሬዘር ሕዳር 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከመንገደኛ ወድቆ ማግኘታቸውን አየር መንገዱ አስታውቋል፡፡
ግለሰቡ በኢትዮጵያዊ ጨዋነትና ሲቀጠሩ በገቡት ቃል መሰረት አየር መንገዱ የሚመራበትን መርህና ሥነ-ምግባር እንዲሁም ሙያዊ ታማኝነታቸውን በብቃት መወጣታቸውንም አስታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለምአቀፍ ደረጃውን የጠበቀ እና ሥነ-ምግባር የተላበሰ የደንበኞች አገልግሎት ለመስጠት ሁሌም እንደሚተጋ ነው በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ያስታወቀው፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ለፀረ-ሙስና ትግሉ የሁሉም ማህበረሰብ አስተዋፅኦ ወሳኝ እንደሆነ ተገለፀ
******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 23/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ለ21ኛ ግዜ የሚከበረውን ዓለምአቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን ምክንያት በማድረግ የክፍለ ከተማው የሀይማኖት አባቶች፣ የኪነ-ጥበብ እና የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲሁም በጎ-ፈቃደኛ የሚዲያ አንቂዎች በተገኙበት የፓናል ውይይት ተካሂዷል፡፡
በፓናል ውይይቱም የሙስና ምንነት፣ ባህሪያት፣ ሙስናን ለመከላከል የተሰሩ አሁናዊ፣ አለም አቀፋዊና ሀገራዊ ሁኔታዎች፣ በፀረ-ሙስና ትግል ላይ የዜጎች ሚና እና ኃላፊነት ዙሪያ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
በውይይቱ የተገኙት የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ምክርቤት ዋና አፈጉባኤ ክብርት ቦጋለች ተድላ እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ የክፍለ ከተማው አስተዳደር የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻል፣ የብልሹ አሰራር እና መልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት እየሰራ ባለው ስራ ሚናችሁ ከፍተኛ ነው፥ የፀረ-ሙስና ትግሉ ላይም ይህንን አስተዋፅኦ ማስቀጠል እንደሚገባቸው ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የክፍለ ከተማው የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ያሲን መሃመድ የኃማኖት አባቶች ትውልድን በሥነምግባር ከመቅረፅ ባሻገር ህብረተሰቡ ሌብነትን እንዲጠየፍ በየኃይማኖት አስተምሮዎቻቸው የሚሰጡትን ትምህርት አጠናክረው መቀጠል አለባቸው ሲሉ አስታውቀዋል፡፡
የክፍለ ከተማው የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና መከታታያ ክፍል ቡድን መሪ ወ/ሮ ስንታየሁ ወዳጆ በፀረ-ሙስና ትግሉ ሁሉም የማህበረሰብ አካላት የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የበዓሉን የውይይት መድረክ የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን፣ ባህል ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም፣ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ፅ/ቤቶች በጋራ ማዘጋጀታቸውን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 23/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ለ21ኛ ግዜ የሚከበረውን ዓለምአቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን ምክንያት በማድረግ የክፍለ ከተማው የሀይማኖት አባቶች፣ የኪነ-ጥበብ እና የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲሁም በጎ-ፈቃደኛ የሚዲያ አንቂዎች በተገኙበት የፓናል ውይይት ተካሂዷል፡፡
በፓናል ውይይቱም የሙስና ምንነት፣ ባህሪያት፣ ሙስናን ለመከላከል የተሰሩ አሁናዊ፣ አለም አቀፋዊና ሀገራዊ ሁኔታዎች፣ በፀረ-ሙስና ትግል ላይ የዜጎች ሚና እና ኃላፊነት ዙሪያ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
በውይይቱ የተገኙት የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ምክርቤት ዋና አፈጉባኤ ክብርት ቦጋለች ተድላ እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ የክፍለ ከተማው አስተዳደር የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻል፣ የብልሹ አሰራር እና መልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት እየሰራ ባለው ስራ ሚናችሁ ከፍተኛ ነው፥ የፀረ-ሙስና ትግሉ ላይም ይህንን አስተዋፅኦ ማስቀጠል እንደሚገባቸው ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የክፍለ ከተማው የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ያሲን መሃመድ የኃማኖት አባቶች ትውልድን በሥነምግባር ከመቅረፅ ባሻገር ህብረተሰቡ ሌብነትን እንዲጠየፍ በየኃይማኖት አስተምሮዎቻቸው የሚሰጡትን ትምህርት አጠናክረው መቀጠል አለባቸው ሲሉ አስታውቀዋል፡፡
የክፍለ ከተማው የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና መከታታያ ክፍል ቡድን መሪ ወ/ሮ ስንታየሁ ወዳጆ በፀረ-ሙስና ትግሉ ሁሉም የማህበረሰብ አካላት የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የበዓሉን የውይይት መድረክ የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን፣ ባህል ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም፣ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ፅ/ቤቶች በጋራ ማዘጋጀታቸውን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
የአዲስ አበባ ፖሊስ ሀሰተኛ ሰነድ አዘጋጅቷል የተባለውን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ እንደሚገኝ ገለፀ
*****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 23/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) አቶ በህረዲን ጀማል የተባለው ግለሰብ ሃሰተኛ ሰነድ በማዘጋጀት ተጠርጥሮ በቁጥጥር ስር የዋለው በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 አካባቢ መሆኑ ተገልጿል።
ተጠርጣሪው ሰዎችን ወደ ውጭ ሀገር የመላክ ምንም አይነት ህጋዊ ፍቃድ ሳይኖረው አንድን ግለሰብ “ሁሉንም ነገር እኔ አስጨርሼ ወደ ዱባይ እልክሃለሁ” ብሎ ከ297 ሺህ በር በላይ እንደተቀበለው የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል፡፡
ጉዳይህ አልቆልሃል ተብሎ ከተጠርጣሪው የጉዞ ሰነድ የተሰጠው የግል ተበዳይም ወደ ዱባይ ለመሄድ ቦሌ አለምዓቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተገኘበት ወቅት ሰነዱ ሀሰተኛ መሆኑ እንደተገለፀለትና ከአየር መንገድ እንደተመለሰ ፖሊስ መምሪያው ጠቅሷል።
የግል ተበዳይን አቤቱታ የተቀበለው የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ ባደረገው ክትትል ተጠርጣሪውን በቁጥጥር አውሎ የፍርድ ቤት የመበርበሪያ ትዕዛዝ በማውጣት በመኖሪያ ቤቱ ባደረገው ብርበራ ሀሰተኛ ሰነዶችና ሰነዶቹን ለማዘጋጀት የሚጠቀምበትን ኮምፒውተር በኤግዚቢትነት ተይዞ ምርመራ እየተጣራ ይገኛል ተብሏል።
በተጠርጣሪው ተመሳሳይ የማታለል ወንጀል ተፈፅሞብናል የሚሉ ግለሰቦች ወደ ክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ ቀርበው ተጨማሪ መረጃ መስጠት እንደሚችሉ መገለፁን ከአዲስ አበባ ፖሊስ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
*****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 23/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) አቶ በህረዲን ጀማል የተባለው ግለሰብ ሃሰተኛ ሰነድ በማዘጋጀት ተጠርጥሮ በቁጥጥር ስር የዋለው በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 አካባቢ መሆኑ ተገልጿል።
ተጠርጣሪው ሰዎችን ወደ ውጭ ሀገር የመላክ ምንም አይነት ህጋዊ ፍቃድ ሳይኖረው አንድን ግለሰብ “ሁሉንም ነገር እኔ አስጨርሼ ወደ ዱባይ እልክሃለሁ” ብሎ ከ297 ሺህ በር በላይ እንደተቀበለው የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል፡፡
ጉዳይህ አልቆልሃል ተብሎ ከተጠርጣሪው የጉዞ ሰነድ የተሰጠው የግል ተበዳይም ወደ ዱባይ ለመሄድ ቦሌ አለምዓቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተገኘበት ወቅት ሰነዱ ሀሰተኛ መሆኑ እንደተገለፀለትና ከአየር መንገድ እንደተመለሰ ፖሊስ መምሪያው ጠቅሷል።
የግል ተበዳይን አቤቱታ የተቀበለው የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ ባደረገው ክትትል ተጠርጣሪውን በቁጥጥር አውሎ የፍርድ ቤት የመበርበሪያ ትዕዛዝ በማውጣት በመኖሪያ ቤቱ ባደረገው ብርበራ ሀሰተኛ ሰነዶችና ሰነዶቹን ለማዘጋጀት የሚጠቀምበትን ኮምፒውተር በኤግዚቢትነት ተይዞ ምርመራ እየተጣራ ይገኛል ተብሏል።
በተጠርጣሪው ተመሳሳይ የማታለል ወንጀል ተፈፅሞብናል የሚሉ ግለሰቦች ወደ ክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ ቀርበው ተጨማሪ መረጃ መስጠት እንደሚችሉ መገለፁን ከአዲስ አበባ ፖሊስ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319