Federal Ethics And Anti- Corruption Commission
9.91K subscribers
10.4K photos
244 videos
32 files
3.04K links
Download Telegram
ለ25 ዘርፎች የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና አስፈፃሚዎችና ባለሙያዎች፣ ለኮሚሽኑ ዓላማ ፈፃሚ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች እየተሰጠ ያለው የዓቅም ግንባታ ስልጠና እንደቀጠለ ነው

****

(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 9/2016 ዓ.ም አዳማ) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ለ25 ዘርፎችና ለተጠሪ ተቋማት የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና አስፈፃሚዎችና ባለሙያዎች፣ ለኮሚሽኑ ዓላማ ፈፃሚ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ እየሰጠ ያለው የዓቅም ግንባታ ስልጠና እንደቀጠለ ይገኛል።

የዕለቱ ስልጠና በፌደራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የአስቸኳይ ሙስና መከላከል መሪ ሥራ አስፈፃሚ በአቶ ገዛኸኝ ጋሻው እየተሰጠ ሲሆን፥ በሙስና ወንጀል ሕጎች ምንነትና አስፈላጊነት ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።

ስልጠናዉ ለቀጣይ ሶስት ቀናት የሚቀጥል ሲሆን፥ በሃብት ምዝገባና ማሳወቅ አዋጅ እና በዋና ዋና ኮሚሽኑ በሚተገብራቸው ፕሮግራሞች ላይ ትኩረት አድርጎ በኮሚሽኑ ዓላማ ፈጻሚ መሪ ሥራ አስፈጻሚዎች የሚሰጥ ይሆናል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በአንዲት መንገደኛ ላይ ተፈፅሟል የተባለውን ሙስና እና እንግልት የፈፀሙት የጉምሩክ ኮሚሽን ሰራተኞች ናቸው ተባለ

****

(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 9/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) በቅርቡ በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በአንዲት መንገደኛ ላይ ተፈፅሟል የተባለውን ሙስና እና እንግልት የፈፀሙት የጉምሩክ ኮሚሽን ሰራተኞች መሆናቸውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ገለጸ፡፡

ድርጊቱን የፈፀሙት የኮሚሽኑ ሠራተኞችም በቁጥጥር ስር መዋላቸው ነው የተገለጸው፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው በሰሞነኛና በአየር መንገዱ እንቅስቃሴ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም፥ በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ ለሚፈፀሙ ወንጀሎች አየር መንገዱን ሙሉ በሙሉ ተጠያቂ ማድረግ ተቀባይነት የለውም ብለዋል።

በአውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ ከአየር መንገዱ በተጨማሪ የኢሚግሬሽን፣ የጉምሩክ፣ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት እንዲሁም የፌደራል ፖሊስ የራሳቸው ድርሻ እንዳላቸው አስረድተዋል።

በቅርቡ በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በአንዲት መንገደኛ ላይ ተፈፅሟል የተባለውን ሙስና እና እንግልት የፈፀሙት የጉምሩክ ኮሚሽን ሰራተኞች እንጅ የአየር መንገዱ ሰራተኞች አይደሉም ነው ያሉት፡፡

በአውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ መሰል ድርጊቶች እንዳይፈፀሙ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት እንደሚሰራም ተናግረዋል።

በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ ከ3 ሺህ በላይ የደህንነት ካሜራዎች እንዳሉም ነው የገለፁት።

አሁን ላይ 145 አውሮፕላኖች አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን አንስተው፥ በቅርቡ የአዳዲስ አውሮፕላኖች ግዥ ትዕዛዝ መሰጠቱንም ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ እያሳየች ያለው የላቀ ውጤትና እመርታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ማረጋገጣቸውን ኤፍቢሲ ዘግቧል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
በሀሰተኛ ሰነድ 300 ካሬ ሜትር ይዞታ ወስዶ ሸጧል የተባለው ግለሰብ ላይ ክስ ተመሰረተ

****

(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 9/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) በሀሰተኛ ሰነድ አርሶ አደር ነኝ በማለት 300 ካሬ ሜትር ይዞታ ወስዶ ሸጧል የተባለው የቴክኒክ ባለሙያና ግብረ አበሩ ላይ ክስ ተመሰረተ።

የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት ጀነራል በተከሳሾቹ ላይ የወንጀል የተሳትፎ ደረጃቸውን ጠቅሶ፤ ስልጣንን ያለአግባብ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት አቅርቦባቸዋል።

ክሱ የቀረበባቸው ከሳሾች በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ መሬት ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት የቴክኒክ ጉዳዮች አጣሪና ወሳኝ ባለሙያ የነበረች እህተማርያም መላኩ ፀጋዬ እና በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ መሬት ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት የቴክኒክ ባለሙያ የነበረው ተስፋዬ እጀታ ዲማ ናቸው።

በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀጽ 32 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) እና አንቀጽ 33 እንዲሁም የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 9 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) እና ንዑስ ቁጥር (2) ስር የተመለከተውን ድንጋጌ ተላልፈዋል ተብለው ስልጣንን ያለአግባብ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ቀርቦባቸዋል።

በዚህም በአንደኛ ክስ ዝርዝር ላይ እንደተመላከተው 1ኛ ተከሳሽ በአዲስ አበባ ከተማ መሬት አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ መሬት ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት የቴክኒክ አጣሪና ወሳኝ ባለሙያ ሆና በምትሰራበት ወቅት ከ2ኛ ተከሳሽ ጋር በጥቅም በመመሳጠር የማይገባ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለሌሎች ለማስገኘት በማሰብ 2ኛ ተከሳሽ አርሶ አደር ሳይሆን ሀሰተኛ የአርሶ አደር ኮሚቴ አባላት እንደሆነ በማስመሰል ሀሰተኛ የገጠር መሬት መጠቀሚያ ክፍያ እና የእርሻ ስራ ግብር ደረሰኝ በማዘጋጀት፣ ከንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ ወረዳ 2 አስተዳደር ጽ/ቤት ለንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ መሬት ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት ሳይላክ እንደተላከ በማስመሰል በክ/ከተማው መሬት አስተዳደር ማህደር እንዲዘጋጅለት በማድረግ 2ኛ ተከሳሽ ምንም አይነት ቤት ሳይኖረው ቤት እንዳለው በማስመሰል በይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ላይ ንድፍ እንዲዘጋጅለት ተደርጓል።

በዚህ መልኩ አንደኛ ተከሳሽ ሚያዝያ 30 ቀን 2012 ዓ.ም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ ወረዳ 02 ውስጥ ጠቅላላ የሊዝ ጨረታ ዋጋው 6 ሚሊየን 301 ሺህ 638 ብር የሆነ አጠቃላይ 300 ካሬ ሜትር ይዞታን ሁለተኛ ተከሳሽ እንዲወስድ በማድረግ በዋና እና ልዩ ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን ስልጣንን ያለአግባብ የመገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ በሁለቱም ግለሰቦች ላይ ቀርቧል።

በሁለተኛ ተከሳሽ ላይ ብቻ በቀረበ ክስ ደግሞ ተከሳሹ አርሶ አደር ሳይሆን አርሶ አደር እንደሆነ በማስመሰል ከ1ኛ ተከሳሽ ጋር በመመሳጠር በህገ ወጥ መንገድ ሀሰተኛ ሰነዶችን በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ ወረዳ 02 የ300 ካሬ ሜትር ይዞታ ከወሰደ በኋላ የንብረቱን ህገወጥ ምንጭ ለመደበቅ ወይም ለመሸፈን በማሰብ ንብረቱን አቶ አለማየሁ ለሚ ለተባለ ግለሰብ ነሃሴ 12 ቀን 2014 ዓ.ም በተደረገ ውል በ1 ሚሊየን 400 ሺህ ብር በሽያጭ ያስተላለፈ መሆኑ ተጠቅሶ በፈፀመው በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብን ወይም ንብረት ህጋዊ አስመስሎ በማቅረብ ወንጀል ተከሷል፡፡

2ኛ ተከሳሽ ዛሬ ችሎት ቀርቦ ክሱ እንዲደርሰው ከተደረገና በንባብ ከተሰማ በኋላ በክሱ ላይ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት አለመፈጸሙን ጠቅሶ የዕምነት ክህደት ቃሉን መስጠቱን ኤፍቢሲ ዘግቧል።

ዐቃቤ ሕግ ለወንጀሉ መፈጸም የሚያስረዱ ምስክሮች እንዲሰሙለት መጠየቁን ተከትሎ ፍርድ ቤቱ የዐቃቤ ህግ ምስክሮችን ለመጠባበቅና እና አንደኛ ተከሳሽ በመጥሪያ እንድትቀርብ በማዘዝ ለመጋቢት 18 ቀን 2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል በተቋማት ላይ የግልፀኝነትና የተጠያቂነት ሥርዓት መዘርጋት ያስፈልጋል!

****

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
የሙስና ወንጀል ድንጋጌዎችን መሰረት በማድረግ ለፀረ-ሙስና ትግሉ የበኩላችን ሚና እንወጣ!

********

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ባለቤቱ ሳያውቅ ባለ 3 መኝታ የጋራ መኖሪያ ቤትን በሀሰተኛ ሰነድ የሸጡ ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ

****

(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 11/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ባለቤቱ ሳያውቅ ባለ 3 መኝታ የጋራ መኖሪያ ቤትን በሀሰተኛ ሰነድ በ2 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር ሸጠዋል የተባሉ ግለሰቦች በጽኑ እስራት እንዲቀጡ የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 5ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ውሳኔ ሰጠ።

የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት ጀነራል በጳውሎስ ገለጠው፣ ዳዊት ግርማ እና ፋሲል እሸቱ ላይ በጥር 16 ቀን 2015 ዓ.ም ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ መስርቶባቸው ነበር።

በተለይም በአንደኛ እና ሁለተኛው ክስ በ1ኛ ተከሳሽ ጳውሎስ ገለጠው ላይ የሙስና ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 23 ንዑስ አንቀጽ 1 ሀ፣ 2 እና 3 ላይ የተደነገገውን ድንጋጌን በመተላለፍ እንዲሁም የወሳኝ ኩነት ምዝገባና ብሔራዊ መታወቂያ አዋጅ ቁጥር 760/2004 አንቀጽ 66/1 በመተላለፍ፤ በተመሳሳይ ስም በተዘጋጀ ሀሰተኛ መታወቂያ እና ሀሰተኛ ሰነዶችን በመጠቀም በብድር ውል በኮዬ ፈጬ ሳይት በሚገኝ ባለ 3 መኝታ ቤትን የእኔ ነው በማለት የቤቱ ህጋዊ ባለቤት ሳይሰማና ሳያውቅ ቤቱን ሸጧል ተብሎ የቀረበ ነው።

3ኛው ክስ ደግሞ በ1ኛ እና በ2ኛ ተከሳሾች ላይ ብቻ የቀረበ ሲሆን በዚህም 1ኛ ተከሳሽ የእኔ ቤት ነው ብሎ በብድር ውል በህገ ወጥ መንገድ የቤቱ ህጋዊ ባለቤት ሳያውቅ በ2 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በሸጠበት ወቅት 2ኛ ተከሳሽ ለቤቱ ገዢ 1ኛ ተከሳሽ የቤቱ ባለቤት ነው ብሎ በሀሰት አሻሽጧል ሲል ዐቃቤ ሕግ በክሱ ላይ ዘርዝሯል።

በሌላኛው ክስ ደግሞ በሁሉም ተከሳሾች ላይ በቀረበው ክስ ላይ እንደተመላከተው ተከሳሾቹ ቤቱን ከተሸጠ በኋላ ገንዘቡን በተለያየ መጠን በባንክ ሂሳባቸው በማዘዋወር ለግል ጥቅማቸው አውለውታል በማለት ነበር ዐቃቤ ሕግ በህገወጥ መንገድ የተገኘ ንብረትን ወይም ገንዘብን ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ ሙስና ወንጀል ክስ ያቀረበው።

ተከሳሾቹ ችሎት ከቀረቡና ክሱ ከደረሳቸው በኋላ ወንጀሉን አለመፈጸማቸውን ጠቅሰው የሰጡትን የዕምነት ክህደት ቃል ተከትሎ ዐቃቤ ሕግ የሰነድና የሰው ማስረጃ አሰምቷል።

ፍርድ ቤቱ የቀረበውን ማስረጃ መርምሮ ተከሳሾቹ እንዲከላከሉ በሰጠው ብይን መሰረት ተከሳሾቹ በተገቢው መንገድ መከላከል ባለመቻላቸው የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎባቸዋል።

ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየት በመያዝ 1ኛ ተከሳሽ ጳውሎስ ገለጠው ያቀረበውን 6 የቅጣት ማቅለያን በመያዝ በዕርከን 27 መሰረት በ8 ዓመት ከ5 ወራት ጽኑ እስራትና በ5 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ መወሰኑን ኤፍቢሲ ዘግቧል።

2ኛ ተከሳሽ ዳዊት ግርማን ደግሞ በ6 ዓመት ጽኑ እስራትና በ3 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲሁም 3ኛ ተከሳሽ ፋሲካ እሸቱ ደግሞ በ5 ዓመት ጽኑ እስራት በ2 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ ወስኗል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡