በትምህርት ተቋማት የተደራጀ የግብረ ገብነትና ፀረ-ሙስና ክበባትን የማጠናከር ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለፀ
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 7/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአዲስ አበባ ከተማ የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የግብረ-ገብና ፀረ-ሙስና ክበባት አደረጃጀትና የሚከናወኑ ተግባራት ዙሪያ ለክበባቱ አስፈፃሚዎች ስልጠና መስጠቱን ገልጿል።
በስልጠናው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የኮሚሽኑ ም/ኮሚሽነር አቶ አሰፋ ቶላ እንደገለፁት በትምህርት ተቋማት የተደራጀ የግብረ-ገብነትና ፀረ-ሙስና ክበባትን በማጠናከር ውጤታማ ስራ እንደሚሰራ ተናግረዋል።
ም/ኮሚሽነሩ አክለውም የክበባት አስፈፃሚዎች የተጣለባቸውን ኃላፊነት ከልብ እንዲወጡ አሳስበው፥ የኮሚሽኑ ድጋፍም እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
በኮሚሽኑ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ስልጠና ዳ/ዳይሬክተር አቶ ጀንበሩ ኢርኮ በበኩላቸው በሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ክበባት አደረጃጀትና የሚከናወኑ ተግባራት ዙሪያ ስልጠና ሰጥተዋል። ኮሚሽኑ ካሉት ዓላማዎች አንዱ የትውልድ ሥነምግባርና የሞራል እሴቶችን መገንባት በመሆኑ የሞራልና ሥነምግባር ግንባታ ዋነኛ ማዕከል በሆነው ትምህርት ቤት ክበባትን የማጠናከር ስራ እንደሚሰራ አቶ ጀንበሩ ተናግረዋል።
በስልጠናው ታማኝነት፣ ፍታዊነት፣ ሰላማዊነት፣ ገለልተኛነት፣ እራስን መግዛት፣ ሀቀኝነት፣ ታታሪነት፣ የሀገር ፍቅር፣ ለህዝብ ንብረት ተቆርቋሪነት እና የቡድን መንፈስ መላበስ ተማሪዎች ሊያጎለብቷቸው የሚገቡ እሴቶች መሆናቸው መጠቀሱን ከኮሚሽኑ የትስስር ገፅ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በስልጠናው የተሳተፉ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ክበባት አመራር መምህራንና ተማሪዎች የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ክበባት የትምህርት ጥራትና ሥነምግባርን ለማሻሻል ወሳኝ በመሆኑ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ስልጠናው ግንዛቤ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
ከባለፈው ሳምንት በቀጠለው ስልጠና አቃቂ ቃሊቲ፣ ጉለሌ፣ ኮልፌ ቀራንዮ፣ ቦሌ፣ ለሚ ኩራ እና ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተሞች በመንግስት ትምህርት ቤቶች ላይ የሚገኙ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ክበባት አስፈፃሚዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 7/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአዲስ አበባ ከተማ የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የግብረ-ገብና ፀረ-ሙስና ክበባት አደረጃጀትና የሚከናወኑ ተግባራት ዙሪያ ለክበባቱ አስፈፃሚዎች ስልጠና መስጠቱን ገልጿል።
በስልጠናው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የኮሚሽኑ ም/ኮሚሽነር አቶ አሰፋ ቶላ እንደገለፁት በትምህርት ተቋማት የተደራጀ የግብረ-ገብነትና ፀረ-ሙስና ክበባትን በማጠናከር ውጤታማ ስራ እንደሚሰራ ተናግረዋል።
ም/ኮሚሽነሩ አክለውም የክበባት አስፈፃሚዎች የተጣለባቸውን ኃላፊነት ከልብ እንዲወጡ አሳስበው፥ የኮሚሽኑ ድጋፍም እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
በኮሚሽኑ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ስልጠና ዳ/ዳይሬክተር አቶ ጀንበሩ ኢርኮ በበኩላቸው በሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ክበባት አደረጃጀትና የሚከናወኑ ተግባራት ዙሪያ ስልጠና ሰጥተዋል። ኮሚሽኑ ካሉት ዓላማዎች አንዱ የትውልድ ሥነምግባርና የሞራል እሴቶችን መገንባት በመሆኑ የሞራልና ሥነምግባር ግንባታ ዋነኛ ማዕከል በሆነው ትምህርት ቤት ክበባትን የማጠናከር ስራ እንደሚሰራ አቶ ጀንበሩ ተናግረዋል።
በስልጠናው ታማኝነት፣ ፍታዊነት፣ ሰላማዊነት፣ ገለልተኛነት፣ እራስን መግዛት፣ ሀቀኝነት፣ ታታሪነት፣ የሀገር ፍቅር፣ ለህዝብ ንብረት ተቆርቋሪነት እና የቡድን መንፈስ መላበስ ተማሪዎች ሊያጎለብቷቸው የሚገቡ እሴቶች መሆናቸው መጠቀሱን ከኮሚሽኑ የትስስር ገፅ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በስልጠናው የተሳተፉ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ክበባት አመራር መምህራንና ተማሪዎች የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ክበባት የትምህርት ጥራትና ሥነምግባርን ለማሻሻል ወሳኝ በመሆኑ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ስልጠናው ግንዛቤ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
ከባለፈው ሳምንት በቀጠለው ስልጠና አቃቂ ቃሊቲ፣ ጉለሌ፣ ኮልፌ ቀራንዮ፣ ቦሌ፣ ለሚ ኩራ እና ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተሞች በመንግስት ትምህርት ቤቶች ላይ የሚገኙ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ክበባት አስፈፃሚዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኮሚሽኑ ለ25 ዘርፎችና ለተጠሪ ተቋማት የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና አስፈፃሚዎችና ባለሙያዎች፣ ለኮሚሽኑ ዓላማ ፈፃሚ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች የዓቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 8/2016 ዓ.ም አዳማ) የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ለ25 ዘርፎችና ለተጠሪ ተቋማት የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና አስፈፃሚዎችና ባለሙያዎች፣ ለኮሚሽኑ ዓላማ ፈፃሚ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የዓቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።
በስልጠና መድረኩ ላይ የተገኙት የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር ክቡር አቶ ወዶ አጦ እንደገለፁት የአቅም ግንባታ ስልጠናው የተሻላ ግንዛቤ የምናገኝበትና ለተልኳችን አቅም የምንወስድበት ነዉ ብለዋል።
ም/ኮሚሽነሩ አክለውም የሥነምግባር ግንባታ እና የሙስና መከላከል ተግባራትን ለማከናወን ከዘርፍ ተቋማት ጋር የጋራ መግባባት በመፍጠር ወጥ የሆነ የአንድ እቅድ፣ የአንድ ሪፖርት አሰራርን በመከተል የምንሰራ ይሆናል ብለዋል።
የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር ክቡር አቶ እሸቴ አስፋው በበኩላቸው ሥልጠናዉ መንግሥት የጀመረዉን አገራዊ የፀረ-ሙስና ትግል በንቅናዌ መልክ መምራት እንዲያስችል ለማድረግ ያለመ መሆኑን በመገንዘብ፥ የስልጠና ተሳታፊዎች የአቅም ግንባታ ስልጠናውን ትኩረት መስጠት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ም/ኮሚሽነሩ አክለውም ሥልጠናው አለምዓቀፍ የፀረ-ሙስና ህጎችን በተጨባጭ ሁኔታ በመረዳት ተግባራዊነታቸውን ለመከታተል የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል።
በአሁኑ ወቅት ህብረተሰቡ አገልግሎቶችን ለማግኘት የእጅ መንሻ እየሰጠ መቀጠል የለበትም ያሉት ም/ኮምሽነሩ፥ በተሰማራችሁበት የሥራ ዘርፍ ህብረተሰቡ ለብልሹ አሰራር እንዳይጋለጥ የበኩላችሁን ድርሻ መወጣት ይኖርባችኃል ብለዋል።
ስልጠናው በፌደራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ሥልጠና መሪ ሥራ አስፈፃሚ በአቶ ሀረጎት አብርሃ እየተሰጠ ሲሆን፥ የአለምዓቀፍ እና አህጉራዊ የፀረ-ሙስና ሥምምነቶች አፈፃፀም በኢትዮጵያ ምን እንደሚመስልና አተገባበራቸው ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።
ስልጠናዉ ለቀጣይ አራት ቀናት የሚሰጥ ሲሆን፥ በሙስና ወንጀል ሕጎች እና በሃብት ምዝገባና ማሳወቅ አዋጅ እንዲሁም በዋና ዋና ኮሚሽኑ በሚተገብራቸው ፕሮግራሞች ላይ ትኩረት አድርጎ በኮሚሽኑ የዓላማ ፈጻሚ መሪ ሥራ አስፈጻሚዎች የሚሰጥ ይሆናል። በስልጠናው ከ700 በላይ የሚሆኑ ሰልጣኞች እየተሳተፋ ይገኛል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 8/2016 ዓ.ም አዳማ) የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ለ25 ዘርፎችና ለተጠሪ ተቋማት የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና አስፈፃሚዎችና ባለሙያዎች፣ ለኮሚሽኑ ዓላማ ፈፃሚ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የዓቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።
በስልጠና መድረኩ ላይ የተገኙት የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር ክቡር አቶ ወዶ አጦ እንደገለፁት የአቅም ግንባታ ስልጠናው የተሻላ ግንዛቤ የምናገኝበትና ለተልኳችን አቅም የምንወስድበት ነዉ ብለዋል።
ም/ኮሚሽነሩ አክለውም የሥነምግባር ግንባታ እና የሙስና መከላከል ተግባራትን ለማከናወን ከዘርፍ ተቋማት ጋር የጋራ መግባባት በመፍጠር ወጥ የሆነ የአንድ እቅድ፣ የአንድ ሪፖርት አሰራርን በመከተል የምንሰራ ይሆናል ብለዋል።
የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር ክቡር አቶ እሸቴ አስፋው በበኩላቸው ሥልጠናዉ መንግሥት የጀመረዉን አገራዊ የፀረ-ሙስና ትግል በንቅናዌ መልክ መምራት እንዲያስችል ለማድረግ ያለመ መሆኑን በመገንዘብ፥ የስልጠና ተሳታፊዎች የአቅም ግንባታ ስልጠናውን ትኩረት መስጠት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ም/ኮሚሽነሩ አክለውም ሥልጠናው አለምዓቀፍ የፀረ-ሙስና ህጎችን በተጨባጭ ሁኔታ በመረዳት ተግባራዊነታቸውን ለመከታተል የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል።
በአሁኑ ወቅት ህብረተሰቡ አገልግሎቶችን ለማግኘት የእጅ መንሻ እየሰጠ መቀጠል የለበትም ያሉት ም/ኮምሽነሩ፥ በተሰማራችሁበት የሥራ ዘርፍ ህብረተሰቡ ለብልሹ አሰራር እንዳይጋለጥ የበኩላችሁን ድርሻ መወጣት ይኖርባችኃል ብለዋል።
ስልጠናው በፌደራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ሥልጠና መሪ ሥራ አስፈፃሚ በአቶ ሀረጎት አብርሃ እየተሰጠ ሲሆን፥ የአለምዓቀፍ እና አህጉራዊ የፀረ-ሙስና ሥምምነቶች አፈፃፀም በኢትዮጵያ ምን እንደሚመስልና አተገባበራቸው ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።
ስልጠናዉ ለቀጣይ አራት ቀናት የሚሰጥ ሲሆን፥ በሙስና ወንጀል ሕጎች እና በሃብት ምዝገባና ማሳወቅ አዋጅ እንዲሁም በዋና ዋና ኮሚሽኑ በሚተገብራቸው ፕሮግራሞች ላይ ትኩረት አድርጎ በኮሚሽኑ የዓላማ ፈጻሚ መሪ ሥራ አስፈጻሚዎች የሚሰጥ ይሆናል። በስልጠናው ከ700 በላይ የሚሆኑ ሰልጣኞች እየተሳተፋ ይገኛል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡