በሳውላ ከተማ ከ64 ሚሊዮን ብር በላይ ጉድለት ያሳዩ ግለሰቦች ለህግ እንዲቀርቡ ተደረገ
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 5/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የመንግስትን ህጋዊ አሰራር ባለመጠበቅ ከ64 ሚሊዮን ብር በላይ የህዝብና የመንግስት ገንዘብ ጉድለት ያሳዩ ግለሰቦች ለህግ እንዲቀርቡ መደረጉን የሳውላ ከተማ ገቢዎች ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
ጽህፈት ቤቱ የአሰራር ጉድለቶችን የማጥራት ሥራ እየሰራ የቆየ ሲሆን፥ በዚህም በኦዲት ሥራዎች ላይ የሰነድ ማበላለጥ፣ በተመሳሳይ ንምራ ቁጥር የተለያዩ የገቢ ርዕሶች እንዲሁም የገንዘብ መጠንና የከፋይ ስም በበራሪና በቀሪ ደረሰኝ ላይ አለመጣጣምና ማጭበርበር፣ ወደ ግል አካውንት ገንዘብ ማስገባት፣ ካርኒ አላግባቢ መቁረጥ ፣ ወጭ የሆኑ ደረሰኞችን ተመላሽ ያለማድረግ የተስተዋለ የአሰራር ችግሮች መሆኑን የሣውላ ከተማ ገቢዎች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌታሁን ኩማ ገልጸዋል። ።
በዚህ መነሻነት በሁለት ግለሰቦች የተስተዋለው የኦዲት ግኝት በጠቅላላው ስልሳ አራት ሚሊዮን አንድ መቶ ዘጠና አምስት ሺ ዘጠና አራት ብር ከስልሳ ዘጠኝ ሣንቲም ግኝት ሆኖ የተረጋገጠ ሲሆን ይህም ለህግ ቀርቦ ውሳኔ እንዲያገኝ እየተሰራ መሆኑን አቶ ጌታሁን አስረድተዋል ።
ይህን ተከትሎ በውስጥም በውጭም የሚስተዋሉ ሌብነቶችን በአሰራር ትግል በማድረግ የማጥራት ስራው ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው መረጃ በመስጠትና ደረሰኞችን በማቅረብ ትብብር ላደረጉ አካላት ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።
መንግሥት ሌብነትን በመታገል የጀመረውን ህግ የማስከበር ስራ ከፍፃሜ የሚያደርስ መሆኑን በመገንዘብ ግብር ከፋዮች የሚጠበቅባቸውን ግብር ያለምንም ስጋት እንዲከፍሉ ኃላፊው ጥሪያቸውን ማቅረባቸውን ደ.ሬ.ቴ.ድ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 5/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የመንግስትን ህጋዊ አሰራር ባለመጠበቅ ከ64 ሚሊዮን ብር በላይ የህዝብና የመንግስት ገንዘብ ጉድለት ያሳዩ ግለሰቦች ለህግ እንዲቀርቡ መደረጉን የሳውላ ከተማ ገቢዎች ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
ጽህፈት ቤቱ የአሰራር ጉድለቶችን የማጥራት ሥራ እየሰራ የቆየ ሲሆን፥ በዚህም በኦዲት ሥራዎች ላይ የሰነድ ማበላለጥ፣ በተመሳሳይ ንምራ ቁጥር የተለያዩ የገቢ ርዕሶች እንዲሁም የገንዘብ መጠንና የከፋይ ስም በበራሪና በቀሪ ደረሰኝ ላይ አለመጣጣምና ማጭበርበር፣ ወደ ግል አካውንት ገንዘብ ማስገባት፣ ካርኒ አላግባቢ መቁረጥ ፣ ወጭ የሆኑ ደረሰኞችን ተመላሽ ያለማድረግ የተስተዋለ የአሰራር ችግሮች መሆኑን የሣውላ ከተማ ገቢዎች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌታሁን ኩማ ገልጸዋል። ።
በዚህ መነሻነት በሁለት ግለሰቦች የተስተዋለው የኦዲት ግኝት በጠቅላላው ስልሳ አራት ሚሊዮን አንድ መቶ ዘጠና አምስት ሺ ዘጠና አራት ብር ከስልሳ ዘጠኝ ሣንቲም ግኝት ሆኖ የተረጋገጠ ሲሆን ይህም ለህግ ቀርቦ ውሳኔ እንዲያገኝ እየተሰራ መሆኑን አቶ ጌታሁን አስረድተዋል ።
ይህን ተከትሎ በውስጥም በውጭም የሚስተዋሉ ሌብነቶችን በአሰራር ትግል በማድረግ የማጥራት ስራው ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው መረጃ በመስጠትና ደረሰኞችን በማቅረብ ትብብር ላደረጉ አካላት ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።
መንግሥት ሌብነትን በመታገል የጀመረውን ህግ የማስከበር ስራ ከፍፃሜ የሚያደርስ መሆኑን በመገንዘብ ግብር ከፋዮች የሚጠበቅባቸውን ግብር ያለምንም ስጋት እንዲከፍሉ ኃላፊው ጥሪያቸውን ማቅረባቸውን ደ.ሬ.ቴ.ድ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
የኮሚሽኑ አመራሮችና ሠራተኞች በመንግስት የ2016 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የዘርፎች የእቅድ አፈፃፀም ላይ ውይይት አካሄዱ
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 5/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን አመራሮችና ሠራተኞች በመንግስት የ2016 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የዘርፎች የእቅድ አፈፃፀም ላይ ውይይት አካሄደዋል፡፡
በ2016 በጀት ዓመት የስድስት ወራት በመንግስት የተከናወኑ የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም፣ የኢኮኖሚ ዘርፎች፣ የመሰረተ ልማት እና የማህበራዊ ልማት ዘርፎች አፈፃፀም እንዲሁም የአስተዳደር ዘርፎች የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሄዶበታል፡፡
በቀረበው የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ በሥራ ኃላፊዎችና በሰራተኞች ሀሳብና አስተያየት እንዲሁም ጥያቄዎች ቀርበው በኮሚሽኑ የበላይ አመራሮች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 5/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን አመራሮችና ሠራተኞች በመንግስት የ2016 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የዘርፎች የእቅድ አፈፃፀም ላይ ውይይት አካሄደዋል፡፡
በ2016 በጀት ዓመት የስድስት ወራት በመንግስት የተከናወኑ የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም፣ የኢኮኖሚ ዘርፎች፣ የመሰረተ ልማት እና የማህበራዊ ልማት ዘርፎች አፈፃፀም እንዲሁም የአስተዳደር ዘርፎች የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሄዶበታል፡፡
በቀረበው የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ በሥራ ኃላፊዎችና በሰራተኞች ሀሳብና አስተያየት እንዲሁም ጥያቄዎች ቀርበው በኮሚሽኑ የበላይ አመራሮች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
የንግድ ሥርዓቱን ለማዘመን የተከናወኑ ተግባራት ብልሹ አሰራርን በማስቀረት አበረታች ውጤት አስመዝግበዋል - አቶ ገብረመስቀል ጫላ
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 5/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የኢትዮጵያን የንግድ ሥርዓት ለማዘመን የተከናወኑ ተግባራት የዘርፉ አሰራር በማቀላጠፍና ብልሹ አሰራርን በማስቀረት አበረታች ውጤት ማስመዝገባቸውን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ አቶ ገብረመስቀል ጫላ ገለጹ።
ሚኒስትሩ የኢትዮጵያን የንግድ ሥርዓት ለማዘመን የተከናወኑ ዓበይት ተግባራትን አስምልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን ማብራሪያ ሰጥተዋል።
የንግዱ ማህበረሰብ ካለበት ቦታ ሆኖ በተንቀሳቃሽ ስልኩ የንግድ ምዝገባ፣ ፈቃድና የግብር ከፋይ ማረጋገጫ አገልግሎት እንዲያገኝ እያደረገ መሆኑን አንስተዋል። አሰራሩም ጉቦ፣ ምልጃና ብልሹ አሰራሮችን ማስቀረት መቻሉንም ጠቅሰዋል።
ከዚህ ባሻገርም ለኢትዮጵዊያን ብቻ ክፍት የነበረውን የንግድ ምህዳር በነፃ የንግድ መርህ የውጭ ባለሃብቶች የሚሳተፉበትን ዕድል በመፍጠር የንግድ ሥርዓቱን እያዘመነ መሆኑን አብራርተዋል።
በዚህም በጥናት ላይ በመመስረት ከ3 ሺህ 300 በላይ የደላላ የንግድ ፈቃድ በመሰረዝ ህብረተሰቡ በዕለት የሚጠቀማቸው የምርት አይነቶች ቀጥታ ለገበያ እንዲቀርቡ እየተደረገ ነው ብለዋል።
በንግድ ሥርዓቱ ላይ ሳንካ ሲፈጥሩ በነበሩ ደላሎች ላይ የንግድ ፈቃድ እግድ መደረጉም ምርትና አገልግሎትን ለሸማቹ በቀጥታ እንዲቀርብ ያስቻለ መሆኑን ገልጸዋል።
ምንም እንኳን የህገ-ወጥ ደላላ እንቅስቃሴን ከመሰረቱ ማጥፋት ባይቻልም የምርት ፍላጎትና አቅርቦቱን ለማጣጣም በሚደረጉ ጥረቶች የህብረተሰቡ እገዛ አይተኬ ነው ብለዋል።
የህገ-ወጥ ደላሎችን እንቅስቃሴ ለመግታትም ከወረዳ ጀምሮ በአገር አቀፍ ደረጃ የሸማቾች ጥበቃ ማህበር በማቋቋም ወደ ሥራ ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ማህበሩም በግንዛቤ ፈጠራና ህገ-ወጥ ቁጥጥር ላይ ህብረሰተቡን በማስገንዘብ ውጤታማ ተግባር መሥራት እንደሚያስችል አንስተዋል።
ህብረተሰቡም በህገ-ወጥ ቁጥጥር ላይ በነፃ የስልክ ጥሪ ጭምር የራሱን ገንቢ ሚና መወጣት እንደሚጠበቅበት አስገንዝበዋል። ጎን ለጎንም የንግዱንና የሸማቹን ማህበረሰብ ተጠቃሚነት የሚሳድጉ ማሻሻያዎች እየተደረጉ ነው ብለዋል።
የንግዱ ማህበረሰብም ለተገልጋዮቻቸው የዋጋ ዝርዝር በማሳወቅ ለሕጋዊ የንግድ ሥርዓት መጎልበት የራሳቸውን አዎንታዊ ሚና መወጣት እንደሚጠበቅባቸው ማስገንዘባቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 5/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የኢትዮጵያን የንግድ ሥርዓት ለማዘመን የተከናወኑ ተግባራት የዘርፉ አሰራር በማቀላጠፍና ብልሹ አሰራርን በማስቀረት አበረታች ውጤት ማስመዝገባቸውን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ አቶ ገብረመስቀል ጫላ ገለጹ።
ሚኒስትሩ የኢትዮጵያን የንግድ ሥርዓት ለማዘመን የተከናወኑ ዓበይት ተግባራትን አስምልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን ማብራሪያ ሰጥተዋል።
የንግዱ ማህበረሰብ ካለበት ቦታ ሆኖ በተንቀሳቃሽ ስልኩ የንግድ ምዝገባ፣ ፈቃድና የግብር ከፋይ ማረጋገጫ አገልግሎት እንዲያገኝ እያደረገ መሆኑን አንስተዋል። አሰራሩም ጉቦ፣ ምልጃና ብልሹ አሰራሮችን ማስቀረት መቻሉንም ጠቅሰዋል።
ከዚህ ባሻገርም ለኢትዮጵዊያን ብቻ ክፍት የነበረውን የንግድ ምህዳር በነፃ የንግድ መርህ የውጭ ባለሃብቶች የሚሳተፉበትን ዕድል በመፍጠር የንግድ ሥርዓቱን እያዘመነ መሆኑን አብራርተዋል።
በዚህም በጥናት ላይ በመመስረት ከ3 ሺህ 300 በላይ የደላላ የንግድ ፈቃድ በመሰረዝ ህብረተሰቡ በዕለት የሚጠቀማቸው የምርት አይነቶች ቀጥታ ለገበያ እንዲቀርቡ እየተደረገ ነው ብለዋል።
በንግድ ሥርዓቱ ላይ ሳንካ ሲፈጥሩ በነበሩ ደላሎች ላይ የንግድ ፈቃድ እግድ መደረጉም ምርትና አገልግሎትን ለሸማቹ በቀጥታ እንዲቀርብ ያስቻለ መሆኑን ገልጸዋል።
ምንም እንኳን የህገ-ወጥ ደላላ እንቅስቃሴን ከመሰረቱ ማጥፋት ባይቻልም የምርት ፍላጎትና አቅርቦቱን ለማጣጣም በሚደረጉ ጥረቶች የህብረተሰቡ እገዛ አይተኬ ነው ብለዋል።
የህገ-ወጥ ደላሎችን እንቅስቃሴ ለመግታትም ከወረዳ ጀምሮ በአገር አቀፍ ደረጃ የሸማቾች ጥበቃ ማህበር በማቋቋም ወደ ሥራ ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ማህበሩም በግንዛቤ ፈጠራና ህገ-ወጥ ቁጥጥር ላይ ህብረሰተቡን በማስገንዘብ ውጤታማ ተግባር መሥራት እንደሚያስችል አንስተዋል።
ህብረተሰቡም በህገ-ወጥ ቁጥጥር ላይ በነፃ የስልክ ጥሪ ጭምር የራሱን ገንቢ ሚና መወጣት እንደሚጠበቅበት አስገንዝበዋል። ጎን ለጎንም የንግዱንና የሸማቹን ማህበረሰብ ተጠቃሚነት የሚሳድጉ ማሻሻያዎች እየተደረጉ ነው ብለዋል።
የንግዱ ማህበረሰብም ለተገልጋዮቻቸው የዋጋ ዝርዝር በማሳወቅ ለሕጋዊ የንግድ ሥርዓት መጎልበት የራሳቸውን አዎንታዊ ሚና መወጣት እንደሚጠበቅባቸው ማስገንዘባቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ባለፉት ስድስት ወራት ህገወጥ ተግባር ሲፈፅሙ የነበሩ 205 ሠራተኞች ላይ እርምጃ ተወስዷል - የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 5/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ከደላሎች ጋር በመመሳጠር ህገወጥ ተግባር ሲፈፅሙ የነበሩ 205 ሠራተኞች ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ።
የደንበኞችን ጥያቄ ሙሉ ለሙሉ ለመመለስ ከ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን በላይ የፓስፖርት ህትመት መከናወኑንም ነው አገልግሎቱ የገለጸው።
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት የአገልግሎቱን የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የስራ አፈፃፀም አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል።
ባለፋት ስድስት ወራት 205 ከውጭ አገር ደላሎች ጋር ተመሳጥረው በህገወጥ ተግባር ላይ ተሰማርተው የነበሩ የአገልግሎቱ ሰራተኞች ከስራ እስከማባረር የደረሰ እርምጃ እንደተወሰደባቸውም ገልጸዋል።
በተጨማሪም ህጋዊ ሰነድ ሳይኖራቸውና ባልተፈቀደላቸው ስራ ላይ የተሰማሩ ከ10 ሺህ በላይ የውጭ አገር ዜጎች ላይ ምርመራ በማድረግ እንደ ጥፋት መጠናቸው ተጠያቂ እንዲሆኑ መደረጉንም አንስተዋል። ህጋዊ ሰነድ የሌላቸው የውጭ አገር ዜጎች ሰነድ አሟልተው እንዲመዘገቡ መደረጉንም አገልግሎቱ መግለፁን ኢዜአ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 5/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ከደላሎች ጋር በመመሳጠር ህገወጥ ተግባር ሲፈፅሙ የነበሩ 205 ሠራተኞች ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ።
የደንበኞችን ጥያቄ ሙሉ ለሙሉ ለመመለስ ከ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን በላይ የፓስፖርት ህትመት መከናወኑንም ነው አገልግሎቱ የገለጸው።
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት የአገልግሎቱን የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የስራ አፈፃፀም አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል።
ባለፋት ስድስት ወራት 205 ከውጭ አገር ደላሎች ጋር ተመሳጥረው በህገወጥ ተግባር ላይ ተሰማርተው የነበሩ የአገልግሎቱ ሰራተኞች ከስራ እስከማባረር የደረሰ እርምጃ እንደተወሰደባቸውም ገልጸዋል።
በተጨማሪም ህጋዊ ሰነድ ሳይኖራቸውና ባልተፈቀደላቸው ስራ ላይ የተሰማሩ ከ10 ሺህ በላይ የውጭ አገር ዜጎች ላይ ምርመራ በማድረግ እንደ ጥፋት መጠናቸው ተጠያቂ እንዲሆኑ መደረጉንም አንስተዋል። ህጋዊ ሰነድ የሌላቸው የውጭ አገር ዜጎች ሰነድ አሟልተው እንዲመዘገቡ መደረጉንም አገልግሎቱ መግለፁን ኢዜአ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡