ሜ/ጀነራል ክንፈ ዳኘው ከኢንፔሪያልና ሪቨራል ሆቴል ግዢ ጋር በተያያዘ በቀረበባቸው የሙስና ወንጀል ክስ ጥፋተኛ ተባሉ
***
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 4/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው ከኢንፔሪያል እና ሪቨራል ሆቴል ግዢ ጋር ተያይዞ በቀረበባቸው የሙስና ወንጀል ክስ የጥፋተኝነት ፍርድ ተላለፈባቸው።
የጥፋተኝነት ፍርዱን የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።
የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት ጀነራል የቀድሞ የብረታ ብረትና ኢንጂነሪግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው ላይ በ2011 ዓ.ም ከህግ ውጪ በተፈጸመ ኢንፔሪያል እና ሪቨራል በተባሉ ሁለት ሆቴሎች ግዢ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል በማለት ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ አቅርቧል።
ይህንን ተከትሎ ተከሳሹ በክሱ ላይ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት አለመፈጸማቸውን ጠቅሰው በሰጡት የዕምነት ክህደት ቃል መነሻ ዐቃቤ ሕግ የተለያዩ የሰነድና የሰው ምስክሮችን በችሎት አቅርቦ አሰምቶ ነበር።
ፍርድ ቤቱ ዐቃቤ ሕግ ያቀረበውን ማስረጃ መርምሮ ሜጀር ጀነራል ክንፈ በተከሰሱበት ድንጋጌ እንዲከላከሉ ብይን የሰጠ ቢሆንም ተከሳሹ በተገቢው መከላከል አለመቻላቸውን ዛሬ ፍርድ ቤቱ ገልጾ፤ በወንጀል ህግ አንቀጽ 407 ንዑስ ቁጥር 1 ሀ እና ንዑስ ቁጥር 2 መሰረት የጥፋተኝነት ፍርድ አስተላልፎባቸዋል።
በተላለፈው የጥፋተኝነት ፍርድ በአንደኛው የሆቴል ግዢ በሙሉ ድምጽ ጥፋተኛ የተባሉ ሲሆን፣ በሌላኛው የሆቴል ግዢ ክስ ደግሞ በአብላጫ ድምጽ በአንድ ዳኛ የሀሳብ ልዩነት ጥፋተኛ ተብለዋል።
ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየትን መርምሮ የቅጣት ውሳኔ ለመስጠት ለመጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱን ኤፍቢሲ ዘግቧል።
ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው ከዚህ በፊት ከ111 የራዳር ግዢ ጋር ተያይዞ በ3 ዓመት ከ7 ወራት ጽኑ እስራት እንዲቀጡ በ4ኛ የሙስና ወንጀል ችሎት ውሳኔ መሰጠቱን መዘገባችን ይታወሳል።
በአሁን ወቅትም በሜጀር ጀነራል ክንፈ ላይ የመርከብ ግዢን ጨምሮ ሶስት ቀሪ የሙስና የክስ መዝገቦች በፍርድ ቤት በሂደት ላይ ይገኛሉ።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
***
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 4/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው ከኢንፔሪያል እና ሪቨራል ሆቴል ግዢ ጋር ተያይዞ በቀረበባቸው የሙስና ወንጀል ክስ የጥፋተኝነት ፍርድ ተላለፈባቸው።
የጥፋተኝነት ፍርዱን የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።
የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት ጀነራል የቀድሞ የብረታ ብረትና ኢንጂነሪግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው ላይ በ2011 ዓ.ም ከህግ ውጪ በተፈጸመ ኢንፔሪያል እና ሪቨራል በተባሉ ሁለት ሆቴሎች ግዢ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል በማለት ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ አቅርቧል።
ይህንን ተከትሎ ተከሳሹ በክሱ ላይ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት አለመፈጸማቸውን ጠቅሰው በሰጡት የዕምነት ክህደት ቃል መነሻ ዐቃቤ ሕግ የተለያዩ የሰነድና የሰው ምስክሮችን በችሎት አቅርቦ አሰምቶ ነበር።
ፍርድ ቤቱ ዐቃቤ ሕግ ያቀረበውን ማስረጃ መርምሮ ሜጀር ጀነራል ክንፈ በተከሰሱበት ድንጋጌ እንዲከላከሉ ብይን የሰጠ ቢሆንም ተከሳሹ በተገቢው መከላከል አለመቻላቸውን ዛሬ ፍርድ ቤቱ ገልጾ፤ በወንጀል ህግ አንቀጽ 407 ንዑስ ቁጥር 1 ሀ እና ንዑስ ቁጥር 2 መሰረት የጥፋተኝነት ፍርድ አስተላልፎባቸዋል።
በተላለፈው የጥፋተኝነት ፍርድ በአንደኛው የሆቴል ግዢ በሙሉ ድምጽ ጥፋተኛ የተባሉ ሲሆን፣ በሌላኛው የሆቴል ግዢ ክስ ደግሞ በአብላጫ ድምጽ በአንድ ዳኛ የሀሳብ ልዩነት ጥፋተኛ ተብለዋል።
ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየትን መርምሮ የቅጣት ውሳኔ ለመስጠት ለመጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱን ኤፍቢሲ ዘግቧል።
ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው ከዚህ በፊት ከ111 የራዳር ግዢ ጋር ተያይዞ በ3 ዓመት ከ7 ወራት ጽኑ እስራት እንዲቀጡ በ4ኛ የሙስና ወንጀል ችሎት ውሳኔ መሰጠቱን መዘገባችን ይታወሳል።
በአሁን ወቅትም በሜጀር ጀነራል ክንፈ ላይ የመርከብ ግዢን ጨምሮ ሶስት ቀሪ የሙስና የክስ መዝገቦች በፍርድ ቤት በሂደት ላይ ይገኛሉ።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
የክልሉ ምክር ቤት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ሀብትን ለማሳወቅና ለማስመዝገብ የወጣ አዋጅ ቁጥር 34/2016 ጨምሮ የቀረቡለትን 5 አዋጆች እና 1 ደንብ በሙሉ ድምፅ አፀደቀ
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 5/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የክልሉን ሀብትን ለማሳወቅና ለማስመዝገብ የወጣ አዋጅ ቁጥር 34/2016 ጨምሮ የቀረቡለትን 5 አዋጆች እና 1 ደንብ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።
የክልሉ ምክር ቤት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ሀብትን ለማሳወቅና ለማስመዝገብ የወጣ አዋጅ ቁጥር 34/2016፣ የአስተዳደር ሥነ-ሥርዓት አዋጅ ቁጥር 32/2016፣ የብሔረሰቦች ምክር ቤት ሥልጣንና ተግባር ለመዘርዘር የወጣ አዋጅ ቁጥር 33/2016፣ የህገ-መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ ስልጣንና ተግባሩን ለመደንገግ የወጣ አዋጅ ቁጥር 35/2016 እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የብሔረሰቦች ምክር ቤት ጽህፈት ቤት ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 36/2016 እንዲሁም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የፍርድ ቤቶች የአስተዳደር ሠራተኞች ደንብ መርምሮ በሙሉ ድምፅ ማፅደቁን ደ.ሬ.ቴ.ድ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 5/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የክልሉን ሀብትን ለማሳወቅና ለማስመዝገብ የወጣ አዋጅ ቁጥር 34/2016 ጨምሮ የቀረቡለትን 5 አዋጆች እና 1 ደንብ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።
የክልሉ ምክር ቤት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ሀብትን ለማሳወቅና ለማስመዝገብ የወጣ አዋጅ ቁጥር 34/2016፣ የአስተዳደር ሥነ-ሥርዓት አዋጅ ቁጥር 32/2016፣ የብሔረሰቦች ምክር ቤት ሥልጣንና ተግባር ለመዘርዘር የወጣ አዋጅ ቁጥር 33/2016፣ የህገ-መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ ስልጣንና ተግባሩን ለመደንገግ የወጣ አዋጅ ቁጥር 35/2016 እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የብሔረሰቦች ምክር ቤት ጽህፈት ቤት ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 36/2016 እንዲሁም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የፍርድ ቤቶች የአስተዳደር ሠራተኞች ደንብ መርምሮ በሙሉ ድምፅ ማፅደቁን ደ.ሬ.ቴ.ድ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ሀሰተኛ ኦዲት ሪፖርት በመስራት ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች ፍርድ ቤት ቀረቡ
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 5/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ለተለያዩ ድርጅቶች ዓመታዊ ሀሰተኛ ኦዲት ሪፖርት በመስራትና ሀሰተኛ ሰነዶችን አዘጋጅተው በመጠቀም ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ፍርድ ቤት ቀረቡ።
ተጠርጣሪዎቹ ነጋሽ አህመድ እረሽድ፣ ቅድስት ሙሉጌታና ናርዶስ ብርሃኑ ናቸው።
ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ያዋለው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ምርመራ ዘርፍ ሲሆን÷ ተጠርጣሪዎቹን ፍርድ ቤት አቅርቦ የ14 ቀን የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል።
በተለይም ነጋሽ አህመድ እረሽድ በተባለው ተጠርጣሪ ላይ በተሰራው ኦፕሬሽን ስራ ግለሰቡ ‘የሂሳብ አዋቂ ነኝ’ በማለት ብቻ ከኢትዮጵያ ሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ ፍቃድ ሳያገኝ በቂርቆስ ክ/ከ ወረዳ 2 እና ወረዳ 8 ስር ቢሮ በመክፈት የተለያዩ ድርጅቶች ዓመታዊ ኦዲት ሪፖርት በመስራትና ለገቢዎች ቢሮ እንዲቀርብ በማድረግ በህዝብና በመንግስታዊ ድርጅቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ ሙስና ወንጀል መጠርጠሩን መርማሪ ፖሊስ ለችሎቱ አስረድቷል።
በተጠርጣሪው የስራ ቦታ በተደረገ ብርበራ በንብ ባንክ፣ በንግድና በኮንስትራክሽን ባንክ በሚል የተዘጋጀ ሀሰተኛ 3 ጥራዝ ቼክ፣ ከኢትዮጵያ ሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ ዳይሬክተር በነበሩት በአቶ የማነ ደስታ ስም ቲተርና ማህተም በማዘጋጀት፣ ሀሰተኛ ኦዲቶች እንደታደሱ ተብለው የተዘጋጁ ሰነዶች፣ ከ60 በላይ የተለያዩ ድርጅቶች ስም የተቀረጹ ማህተሞችና ቲተሮች፣ የተለያዩ የስራ ልምዶች፣ የዩኒቨርሲቲና በኮሌጆች ስም የትምህርት ማስረጃዎች ጭምር እንደተገኙ ፖሊስ ለጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ገልጿል።
ከተጠርጣሪው ጋር ሲሰሩ ነበር የተባሉ ግብረዓበሮች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ፖሊስ ለጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ አስታውቋል።
በተጨማሪም ቅድስት ሙሉጌታ የተባለች ተጠርጣሪን የሂሳብ ሰራተኛ ሆና የተለያዩ አመታዊ ኦዲቶች ለድርጅቶች በማድረስ ጭምር ተሳትፎ አላት በማለት መጠርጠሩን የገለጸው ፖሊስ፤ ናርዶስ ብርሃኑን በሚመለከት ደግሞ ለግል ድርጅት በሚል ኦዲት ሪፖርት በማሰራት ረገድ ተሳትፎ እንዳላት ተጠቅሷል።
በአጠቃላይ በተጠረጠሩበት ወንጀል የጣት አሻራ የማስነሳት ስራ ማከናወኑን የጠቀሰው መርማሪ ፖሊስ ቀሪ ማለትም ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት የምስክርነት ቃል መቀበልና ቀሪ ማስረጃ የማቅረብ ስራ እንደሚቀረው ጠቅሶ፤ ከወንጀሉ ውስብስብነትና ከምርመራው ስፋት አንጻር ፍርድ ቤቱ ተገንዝቦ በወ/መ/ስ/ህ ቁጥር 59/2 መሰረት የ14 ቀን የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።
ተጠርጣሪዎቹም ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ ሊሰጥ እንደማይገባ ገልጸው የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድላቸው መጠየቃቸውን ኤፍቢሲ ዘግቧል።
የግራ ቀኝ ክርክሩን እና የፖሊስ ምርመራ መዝገብን የተመለከተው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ተጨማሪ የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፖሊስ እንደሚያስፈልገው ከግምት ውስጥ በማስገባት የተጠርጣሪዎችን የዋስትና ጥያቄ ለጊዜው በማለፍ ለፖሊስ የ14 ቀን የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዷል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 5/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ለተለያዩ ድርጅቶች ዓመታዊ ሀሰተኛ ኦዲት ሪፖርት በመስራትና ሀሰተኛ ሰነዶችን አዘጋጅተው በመጠቀም ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ፍርድ ቤት ቀረቡ።
ተጠርጣሪዎቹ ነጋሽ አህመድ እረሽድ፣ ቅድስት ሙሉጌታና ናርዶስ ብርሃኑ ናቸው።
ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ያዋለው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ምርመራ ዘርፍ ሲሆን÷ ተጠርጣሪዎቹን ፍርድ ቤት አቅርቦ የ14 ቀን የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል።
በተለይም ነጋሽ አህመድ እረሽድ በተባለው ተጠርጣሪ ላይ በተሰራው ኦፕሬሽን ስራ ግለሰቡ ‘የሂሳብ አዋቂ ነኝ’ በማለት ብቻ ከኢትዮጵያ ሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ ፍቃድ ሳያገኝ በቂርቆስ ክ/ከ ወረዳ 2 እና ወረዳ 8 ስር ቢሮ በመክፈት የተለያዩ ድርጅቶች ዓመታዊ ኦዲት ሪፖርት በመስራትና ለገቢዎች ቢሮ እንዲቀርብ በማድረግ በህዝብና በመንግስታዊ ድርጅቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ ሙስና ወንጀል መጠርጠሩን መርማሪ ፖሊስ ለችሎቱ አስረድቷል።
በተጠርጣሪው የስራ ቦታ በተደረገ ብርበራ በንብ ባንክ፣ በንግድና በኮንስትራክሽን ባንክ በሚል የተዘጋጀ ሀሰተኛ 3 ጥራዝ ቼክ፣ ከኢትዮጵያ ሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ ዳይሬክተር በነበሩት በአቶ የማነ ደስታ ስም ቲተርና ማህተም በማዘጋጀት፣ ሀሰተኛ ኦዲቶች እንደታደሱ ተብለው የተዘጋጁ ሰነዶች፣ ከ60 በላይ የተለያዩ ድርጅቶች ስም የተቀረጹ ማህተሞችና ቲተሮች፣ የተለያዩ የስራ ልምዶች፣ የዩኒቨርሲቲና በኮሌጆች ስም የትምህርት ማስረጃዎች ጭምር እንደተገኙ ፖሊስ ለጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ገልጿል።
ከተጠርጣሪው ጋር ሲሰሩ ነበር የተባሉ ግብረዓበሮች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ፖሊስ ለጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ አስታውቋል።
በተጨማሪም ቅድስት ሙሉጌታ የተባለች ተጠርጣሪን የሂሳብ ሰራተኛ ሆና የተለያዩ አመታዊ ኦዲቶች ለድርጅቶች በማድረስ ጭምር ተሳትፎ አላት በማለት መጠርጠሩን የገለጸው ፖሊስ፤ ናርዶስ ብርሃኑን በሚመለከት ደግሞ ለግል ድርጅት በሚል ኦዲት ሪፖርት በማሰራት ረገድ ተሳትፎ እንዳላት ተጠቅሷል።
በአጠቃላይ በተጠረጠሩበት ወንጀል የጣት አሻራ የማስነሳት ስራ ማከናወኑን የጠቀሰው መርማሪ ፖሊስ ቀሪ ማለትም ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት የምስክርነት ቃል መቀበልና ቀሪ ማስረጃ የማቅረብ ስራ እንደሚቀረው ጠቅሶ፤ ከወንጀሉ ውስብስብነትና ከምርመራው ስፋት አንጻር ፍርድ ቤቱ ተገንዝቦ በወ/መ/ስ/ህ ቁጥር 59/2 መሰረት የ14 ቀን የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።
ተጠርጣሪዎቹም ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ ሊሰጥ እንደማይገባ ገልጸው የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድላቸው መጠየቃቸውን ኤፍቢሲ ዘግቧል።
የግራ ቀኝ ክርክሩን እና የፖሊስ ምርመራ መዝገብን የተመለከተው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ተጨማሪ የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፖሊስ እንደሚያስፈልገው ከግምት ውስጥ በማስገባት የተጠርጣሪዎችን የዋስትና ጥያቄ ለጊዜው በማለፍ ለፖሊስ የ14 ቀን የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዷል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
በሳውላ ከተማ ከ64 ሚሊዮን ብር በላይ ጉድለት ያሳዩ ግለሰቦች ለህግ እንዲቀርቡ ተደረገ
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 5/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የመንግስትን ህጋዊ አሰራር ባለመጠበቅ ከ64 ሚሊዮን ብር በላይ የህዝብና የመንግስት ገንዘብ ጉድለት ያሳዩ ግለሰቦች ለህግ እንዲቀርቡ መደረጉን የሳውላ ከተማ ገቢዎች ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
ጽህፈት ቤቱ የአሰራር ጉድለቶችን የማጥራት ሥራ እየሰራ የቆየ ሲሆን፥ በዚህም በኦዲት ሥራዎች ላይ የሰነድ ማበላለጥ፣ በተመሳሳይ ንምራ ቁጥር የተለያዩ የገቢ ርዕሶች እንዲሁም የገንዘብ መጠንና የከፋይ ስም በበራሪና በቀሪ ደረሰኝ ላይ አለመጣጣምና ማጭበርበር፣ ወደ ግል አካውንት ገንዘብ ማስገባት፣ ካርኒ አላግባቢ መቁረጥ ፣ ወጭ የሆኑ ደረሰኞችን ተመላሽ ያለማድረግ የተስተዋለ የአሰራር ችግሮች መሆኑን የሣውላ ከተማ ገቢዎች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌታሁን ኩማ ገልጸዋል። ።
በዚህ መነሻነት በሁለት ግለሰቦች የተስተዋለው የኦዲት ግኝት በጠቅላላው ስልሳ አራት ሚሊዮን አንድ መቶ ዘጠና አምስት ሺ ዘጠና አራት ብር ከስልሳ ዘጠኝ ሣንቲም ግኝት ሆኖ የተረጋገጠ ሲሆን ይህም ለህግ ቀርቦ ውሳኔ እንዲያገኝ እየተሰራ መሆኑን አቶ ጌታሁን አስረድተዋል ።
ይህን ተከትሎ በውስጥም በውጭም የሚስተዋሉ ሌብነቶችን በአሰራር ትግል በማድረግ የማጥራት ስራው ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው መረጃ በመስጠትና ደረሰኞችን በማቅረብ ትብብር ላደረጉ አካላት ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።
መንግሥት ሌብነትን በመታገል የጀመረውን ህግ የማስከበር ስራ ከፍፃሜ የሚያደርስ መሆኑን በመገንዘብ ግብር ከፋዮች የሚጠበቅባቸውን ግብር ያለምንም ስጋት እንዲከፍሉ ኃላፊው ጥሪያቸውን ማቅረባቸውን ደ.ሬ.ቴ.ድ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 5/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የመንግስትን ህጋዊ አሰራር ባለመጠበቅ ከ64 ሚሊዮን ብር በላይ የህዝብና የመንግስት ገንዘብ ጉድለት ያሳዩ ግለሰቦች ለህግ እንዲቀርቡ መደረጉን የሳውላ ከተማ ገቢዎች ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
ጽህፈት ቤቱ የአሰራር ጉድለቶችን የማጥራት ሥራ እየሰራ የቆየ ሲሆን፥ በዚህም በኦዲት ሥራዎች ላይ የሰነድ ማበላለጥ፣ በተመሳሳይ ንምራ ቁጥር የተለያዩ የገቢ ርዕሶች እንዲሁም የገንዘብ መጠንና የከፋይ ስም በበራሪና በቀሪ ደረሰኝ ላይ አለመጣጣምና ማጭበርበር፣ ወደ ግል አካውንት ገንዘብ ማስገባት፣ ካርኒ አላግባቢ መቁረጥ ፣ ወጭ የሆኑ ደረሰኞችን ተመላሽ ያለማድረግ የተስተዋለ የአሰራር ችግሮች መሆኑን የሣውላ ከተማ ገቢዎች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌታሁን ኩማ ገልጸዋል። ።
በዚህ መነሻነት በሁለት ግለሰቦች የተስተዋለው የኦዲት ግኝት በጠቅላላው ስልሳ አራት ሚሊዮን አንድ መቶ ዘጠና አምስት ሺ ዘጠና አራት ብር ከስልሳ ዘጠኝ ሣንቲም ግኝት ሆኖ የተረጋገጠ ሲሆን ይህም ለህግ ቀርቦ ውሳኔ እንዲያገኝ እየተሰራ መሆኑን አቶ ጌታሁን አስረድተዋል ።
ይህን ተከትሎ በውስጥም በውጭም የሚስተዋሉ ሌብነቶችን በአሰራር ትግል በማድረግ የማጥራት ስራው ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው መረጃ በመስጠትና ደረሰኞችን በማቅረብ ትብብር ላደረጉ አካላት ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።
መንግሥት ሌብነትን በመታገል የጀመረውን ህግ የማስከበር ስራ ከፍፃሜ የሚያደርስ መሆኑን በመገንዘብ ግብር ከፋዮች የሚጠበቅባቸውን ግብር ያለምንም ስጋት እንዲከፍሉ ኃላፊው ጥሪያቸውን ማቅረባቸውን ደ.ሬ.ቴ.ድ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
የኮሚሽኑ አመራሮችና ሠራተኞች በመንግስት የ2016 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የዘርፎች የእቅድ አፈፃፀም ላይ ውይይት አካሄዱ
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 5/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን አመራሮችና ሠራተኞች በመንግስት የ2016 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የዘርፎች የእቅድ አፈፃፀም ላይ ውይይት አካሄደዋል፡፡
በ2016 በጀት ዓመት የስድስት ወራት በመንግስት የተከናወኑ የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም፣ የኢኮኖሚ ዘርፎች፣ የመሰረተ ልማት እና የማህበራዊ ልማት ዘርፎች አፈፃፀም እንዲሁም የአስተዳደር ዘርፎች የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሄዶበታል፡፡
በቀረበው የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ በሥራ ኃላፊዎችና በሰራተኞች ሀሳብና አስተያየት እንዲሁም ጥያቄዎች ቀርበው በኮሚሽኑ የበላይ አመራሮች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 5/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን አመራሮችና ሠራተኞች በመንግስት የ2016 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የዘርፎች የእቅድ አፈፃፀም ላይ ውይይት አካሄደዋል፡፡
በ2016 በጀት ዓመት የስድስት ወራት በመንግስት የተከናወኑ የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም፣ የኢኮኖሚ ዘርፎች፣ የመሰረተ ልማት እና የማህበራዊ ልማት ዘርፎች አፈፃፀም እንዲሁም የአስተዳደር ዘርፎች የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሄዶበታል፡፡
በቀረበው የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ በሥራ ኃላፊዎችና በሰራተኞች ሀሳብና አስተያየት እንዲሁም ጥያቄዎች ቀርበው በኮሚሽኑ የበላይ አመራሮች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡