የፈተና ሥነምግባር ጥሰት የፈፀሙ 114 ተፈታኞች ውጤት መሰረዙን የትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 2/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) በመውጫ ፈተና ኩረጃና ሌሎች የፈተና ሥነምግባር ጥሰት የፈጸሙ 114 ተፈታኞች ውጤት ሙሉ በሙሉ መሰረዙን የትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡
በመውጫ ፈተና ሞባይል ስልክ ይዞ መግባት፣ መኮረጅና የተለያዩ የፈተና ሥነምግባር ጥሰት የፈጸሙ 114 ተፈታኞች ውጤት ሙሉ በሙሉ መሠረዙን ነው ሚኒስቴሩ ዛሬ ለሁሉም የመንግስትና የግል ዩኒቨርሲቲዎች በጻፈው ደብዳቤ ያስታወቀው፡፡
የፈተና ሥነምግባር ጥሰት የፈጸሙት 114 ተፈታኞች ውጤታቸው ሙሉ በሙሉ መሰረዙንና የሚወሰዱ ተጨማሪ እርምጃዎች በቀጣይ የሚገለጽ መሆኑ ተመልክቷል።
ከየካቲት 6 እስከ 11 ቀን 2016 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ የመንግስት ተቋማት በተሰጠው ሁለተኛ ዙር የመውጫ ፈተና 119 ሺህ 145 ተፈታኞች መፈተናቸውን ከሚኒስቴሩ የትስስር ገፅ የተገኘው መረጃ ያስረዳል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 2/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) በመውጫ ፈተና ኩረጃና ሌሎች የፈተና ሥነምግባር ጥሰት የፈጸሙ 114 ተፈታኞች ውጤት ሙሉ በሙሉ መሰረዙን የትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡
በመውጫ ፈተና ሞባይል ስልክ ይዞ መግባት፣ መኮረጅና የተለያዩ የፈተና ሥነምግባር ጥሰት የፈጸሙ 114 ተፈታኞች ውጤት ሙሉ በሙሉ መሠረዙን ነው ሚኒስቴሩ ዛሬ ለሁሉም የመንግስትና የግል ዩኒቨርሲቲዎች በጻፈው ደብዳቤ ያስታወቀው፡፡
የፈተና ሥነምግባር ጥሰት የፈጸሙት 114 ተፈታኞች ውጤታቸው ሙሉ በሙሉ መሰረዙንና የሚወሰዱ ተጨማሪ እርምጃዎች በቀጣይ የሚገለጽ መሆኑ ተመልክቷል።
ከየካቲት 6 እስከ 11 ቀን 2016 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ የመንግስት ተቋማት በተሰጠው ሁለተኛ ዙር የመውጫ ፈተና 119 ሺህ 145 ተፈታኞች መፈተናቸውን ከሚኒስቴሩ የትስስር ገፅ የተገኘው መረጃ ያስረዳል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ከኢንዶኔዥያ የሙስና ማስወገድ ኮሚሽን ጋር የተደረገው የልምድና የተሞክሮ ልውውጥ ላይ በቂ ግባቶች ተገኝተውበታል - የኮሚሽኑ የልዑካን ቡድን አባላት
****************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 3/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ፣ የፍትህ ሚኒስቴር ምክትል ዴኤታ እና የኦሮሚያ፣ የአማራና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽነሮች እንዲሁም የፌደራል አራት የሥራ ኃላፊዎችን የያዘ በኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር በአቶ ወዶ አጦ የተመራ ልዑካን ቡድን እ.ኤ.አ ከማርች 5 እስከ 9 ቀን 2024 ድረስ የኢንዶኔዥያ የሙስና መከላከል ኮሚሽን የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ልምድና ተሞክሮ በመቅሰም ተመልሷል፡፡
የተሞክሮና የልምድ ልውውጥ ዓላማው የሀገራችንን ብሔራዊ የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ፖሊሲ ዝግጅት የሚያግዙ ልምዶና ተሞክሮ ለመቅሰም ታሳቢ ያደረገ መሆኑ ተመላክቷል።
በኢንዶኔዥያ የሙስና ማስወገድ ኮሚሽን ቆይታ የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ተደራሽ የሚያደርጋቸውን የሥነምግባር ሥልጠናና ትምህርት አሰጣጥ፣ የፀረ-ሙስና ትግልና የህብረተሰብ ትስስርና አጋዥነት፣ ዘርፈ ብዙ የሙስና መከላከል ዘዴዎች፣ የሀብት ምዝገበና ትክክለኛነት ማጣራት፣ የጥቅም ግጭት መከላከል፣ በፀረ-ሙስና ትግል የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት ፋይዳ፣ የሙስና ወንጀል ቅድመ ምርመራ፣ የሙስና ወንጀል ምርመራ እንዲሁም የማስቀጣት ምጣኔ፣ በፀረ-ሙስና ትግል የባለድርሻ አካላት ትስስርና ሚና እንዲሁም በሙስና የተመዘበረ ሀብት ለማስመለስ ከሀገር ውስጥና ከውጪ አገር ስለሚደረገው ትስስር፣ በሙስና የተመዘበረ ሀብትና ንብረት የማሳገድ፣ የመንከባከብና የማስመለስ ሂደቶች ላይ ያተረኮሩ መሆኑን ከልዑካን ቡድኑ አባላት የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
የተገኙ መልካም ልምዶችና ተሞክሮዎች ለሀገራችን የፀረ-ሙስና ትግል በሚያመች መልኩ በመቀመርና በማስፋፋት እንዲሁም ይህንኑ በዝግጅት ሂደት የሚገኘውን የብሔራዊ የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ፖሊሲ አካል በማድረግ ለማስፀደቅ እንደሚሠራ የልዑካን ቡድኑ ተልዕኮ ማሳካት እንደሆነም ግንዛቤ የተወሰደ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
በተጨማሪም ልምዶችና ተሞክሮዎች ለኮሚሽኑ የፀረ-ሙስና ትግሉን ውጤታማ ለማድረግ ተግባራዊ ለሚያደርጋቸው የሪፎርም ሥራዎች ዕገዛ እንዳለውም ተገልጿል፡፡
የልዑካን ቡድኑ አባላት ተልዕኳቸውን ለማሳካት ሚና ለነበራቸው የኢንዶኔዥያ የሙስና ማስወገድ ኮሚሽን የበላይ አመራሮችና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም በኢንዶኔዥያ ለኢትዮጵያ ኢምባሲ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 3/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ፣ የፍትህ ሚኒስቴር ምክትል ዴኤታ እና የኦሮሚያ፣ የአማራና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽነሮች እንዲሁም የፌደራል አራት የሥራ ኃላፊዎችን የያዘ በኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር በአቶ ወዶ አጦ የተመራ ልዑካን ቡድን እ.ኤ.አ ከማርች 5 እስከ 9 ቀን 2024 ድረስ የኢንዶኔዥያ የሙስና መከላከል ኮሚሽን የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ልምድና ተሞክሮ በመቅሰም ተመልሷል፡፡
የተሞክሮና የልምድ ልውውጥ ዓላማው የሀገራችንን ብሔራዊ የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ፖሊሲ ዝግጅት የሚያግዙ ልምዶና ተሞክሮ ለመቅሰም ታሳቢ ያደረገ መሆኑ ተመላክቷል።
በኢንዶኔዥያ የሙስና ማስወገድ ኮሚሽን ቆይታ የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ተደራሽ የሚያደርጋቸውን የሥነምግባር ሥልጠናና ትምህርት አሰጣጥ፣ የፀረ-ሙስና ትግልና የህብረተሰብ ትስስርና አጋዥነት፣ ዘርፈ ብዙ የሙስና መከላከል ዘዴዎች፣ የሀብት ምዝገበና ትክክለኛነት ማጣራት፣ የጥቅም ግጭት መከላከል፣ በፀረ-ሙስና ትግል የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት ፋይዳ፣ የሙስና ወንጀል ቅድመ ምርመራ፣ የሙስና ወንጀል ምርመራ እንዲሁም የማስቀጣት ምጣኔ፣ በፀረ-ሙስና ትግል የባለድርሻ አካላት ትስስርና ሚና እንዲሁም በሙስና የተመዘበረ ሀብት ለማስመለስ ከሀገር ውስጥና ከውጪ አገር ስለሚደረገው ትስስር፣ በሙስና የተመዘበረ ሀብትና ንብረት የማሳገድ፣ የመንከባከብና የማስመለስ ሂደቶች ላይ ያተረኮሩ መሆኑን ከልዑካን ቡድኑ አባላት የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
የተገኙ መልካም ልምዶችና ተሞክሮዎች ለሀገራችን የፀረ-ሙስና ትግል በሚያመች መልኩ በመቀመርና በማስፋፋት እንዲሁም ይህንኑ በዝግጅት ሂደት የሚገኘውን የብሔራዊ የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ፖሊሲ አካል በማድረግ ለማስፀደቅ እንደሚሠራ የልዑካን ቡድኑ ተልዕኮ ማሳካት እንደሆነም ግንዛቤ የተወሰደ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
በተጨማሪም ልምዶችና ተሞክሮዎች ለኮሚሽኑ የፀረ-ሙስና ትግሉን ውጤታማ ለማድረግ ተግባራዊ ለሚያደርጋቸው የሪፎርም ሥራዎች ዕገዛ እንዳለውም ተገልጿል፡፡
የልዑካን ቡድኑ አባላት ተልዕኳቸውን ለማሳካት ሚና ለነበራቸው የኢንዶኔዥያ የሙስና ማስወገድ ኮሚሽን የበላይ አመራሮችና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም በኢንዶኔዥያ ለኢትዮጵያ ኢምባሲ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ሁለት ሲኖ ትራኮች እንዲሰረቁና እንዲሰወሩ አድርገዋል የተባሉ የቀድሞ የፖሊስ አባላት እንዲከላከሉ ብይን ተሰጠ
****************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 3/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ሁለት ሲኖ ትራክ ተሽከርካሪዎች እንዲሰረቁና እንዲሰወሩ አድርገዋል የተባሉ ሶስት የአዲስ አበባ የቀድሞ ፖሊስ አባላትን ጨምሮ ስድስት ተከሳሾች በተከሰሱበት ስልጣንን ያለአግባብ መጠቀም ከባድ የሙስና ወንጀል እንዲከላከሉ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት ብይን ሰጠ።
ችሎቱ በክስ መዝገቡ የተካተቱ ሌሎች ሶስት ተከሳሾችን በሚመለከት ደግሞ የጥፋተኝነት ፍርድ አስተላልፏል።
ተከሳሾቹ 1ኛ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የአራዳ ክ/ከተማ አራት ኪሎ ፖሊስ ጣቢያ የቀድሞ የፖሊስ አባልና የወንጀል መከላከል ቡድን መሪ የነበረው ዋና ሳጅን ትግሉ ሰቦቃ፣ 2ኛ እና 3ኛ ደግሞ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ የጊቢ ጥበቃ አባላት የነበሩት ኮ/ብል ዘነበ ኩማ እና ኮ/ብል መንግስቱ እንቻሌ እንዲሁም 4ኛ አቶ ላዕከ ተስፋ ገ/ስላሴ፣ 5ኛ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ድርጅት ውስጥ የቦሌ አራብሳ ፕሮጀክት 13 ጥበቃ የነበረው መልካሙ አያና፣ 6ኛ መላኩ ካላዩ፣ 7ኛ ከበደ ገ/እየሱስ፣ 8ኛ ወንዶሰን ወይም ኢብራሂም ረጋሳ ገለታ እና 9ኛ ሮቤል ሙሉአለም ሃይሉ ናቸው።
የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት ጀነራል በ2015 ዓ.ም በተከሳሾች ላይ የተሳትፎ ደረጃ ጠቅሶ ስልጣንን ያለአግባብ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ አቅርቦባቸው ነበር።
በክስ ዝርዝሩ ላይ እንዳመላከተው፤ ተከሳሾቹ የማይገባቸውን ብልጽግና ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ በጥቅም በመመሳጠር በዋና እና በልዩ ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን ጥር 30 ቀን 2015 ዓ.ም ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ላይ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱ የፖሊስ አባላት ፖሊሳዊ ኃላፊነታቸውን ያለአግባብ በመገልገል በአዲስ አበባ በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ቦሌ አራብሳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ቦሌ አራብሳ ሳይት ውስጥ በመግባት በጥበቃ ስራ ላይ የነበረ (የዐቃቤ ሕግ ምስክር) ግለሰብን “ለወንጀል ምርመራ ትፈለጋለህ" በማለት 1ኛ ተከሳሽ ከ3ኛ ተከሳሽ ጋር በመሆን ከጥበቃ ስፍራው ወደ ሌላ ቦታ ወስደዋል።
2ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች ደግሞ በቦታው የነበሩ ንብረቶችን እንዲያወጡ በመርዳት 11 ሚሊየን ብር የሚያወጡ ሁለት ማለትም የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 03-95058 ኢት የሆነ እና የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 03-16409 ኢት የሆኑ ሁለት ሲኖ ትራክ ተሽከርካሪዎችን 6ኛ ተከሳሽ ሞተሩን በካቻቢቴ በማስነሳት ከ9ኛ ተከሳሽ ጋር ተሽከርካሪዎችን ይዘውና ሌሎቹ ደግሞ አጅበው ወደ አዳማ በመውሰድና በመሰወር፣ 8ኛ ተከሳሽ ደግሞ ከሌሎች ግብረዓበሮቹ ጋር በመሆን አንደኛውን ተሽከርካሪ ለግለሰብ በ600 ሺህ ብር በመሸጥና ገንዘቡን በ7ኛ ተከሳሽ ስም በተከፈተ በአዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ ሂሳብ በማስገባትና በተለያዩ መጠኖች ገንዘቡን መከፋፈላቸው ተጠቅሶ ስልጣንን ያለአግባብ መገልገል ከባድ ሙስና ወንጀል ተከሰው ነበር።
ከተከሳሾቹ መካከል ስድስቱ ችሎት ቀርበው ክስ ዝርዝሩ የደረሳቸው ሲሆን÷ ቀሪ ሶስት ተከሳሾች ግን በተደጋጋሚ መጥሪያ ተደርጎላቸው ሳይቀርቡ መቅረታቸውን ተከትሎ ጉዳያቸው በሌሉበት እንዲታይ ተደርጓል።
ችሎት የቀረቡ ስድስቱ ተከሳሾች የወንጀል ድርጊቱን አልፈጸምንም ብለው የዕምነት ክህደት ቃላቸውን በመስጠታቸው ዐቃቤ ሕግ የተለያዩ ገላጭ ማስረጃዎችን እና ስምንት የሰው ምስክሮችን ቃል አሰምቷል።
ፍርድ ቤቱም የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን መርምሮ ዛሬ በዋለው ችሎት 1ኛ፣ 2ኛ፣ 3ኛ፣ 4ኛ፣ 6ኛ እና 7ኛ ተከሳሾችን በሚመለከት በዐቃቤ ሕግ የቀረበባቸውን ማስረጃ በወንጀል ህግ አንቀጽ 32 ንዑስ ቁጥር 1 ሀ እና ለ፣ አንቀጽ 33 እንዲሁም የሙስና አዋጅን ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 9 ንዑስ ቁጥር 2 መሰረት እንዲከላከሉ በሙሉ ድምጽ ብይን ሰጥቷል።
5ኛ፣ 8ኛ እና 9ኛ ተከሳሾችን ደግሞ በዚሁ ድንጋጌ ስር በሌሉበት የጥፋተኝነት ፍርድ መተላለፈባቸውን ኤፍቢሲ ዘግቧል።
ተከላከሉ የተባሉ ተከሳሾችን የመከላከያ ማስረጃ ለመጠባበቅ ለሚያዚያ 9 ቀን 2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ የተሰጠ ሲሆን÷ በዚህ ቀን ዐቃቤ ሕግ የጥፋተኝነት ፍርድ የተላለፈባቸው ሶስት ተከሳሾችን በሚመለከት የቅጣት አስተያየት እንዲያቀርብ ቀጠሮ ተሰጥቷል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 3/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ሁለት ሲኖ ትራክ ተሽከርካሪዎች እንዲሰረቁና እንዲሰወሩ አድርገዋል የተባሉ ሶስት የአዲስ አበባ የቀድሞ ፖሊስ አባላትን ጨምሮ ስድስት ተከሳሾች በተከሰሱበት ስልጣንን ያለአግባብ መጠቀም ከባድ የሙስና ወንጀል እንዲከላከሉ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት ብይን ሰጠ።
ችሎቱ በክስ መዝገቡ የተካተቱ ሌሎች ሶስት ተከሳሾችን በሚመለከት ደግሞ የጥፋተኝነት ፍርድ አስተላልፏል።
ተከሳሾቹ 1ኛ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የአራዳ ክ/ከተማ አራት ኪሎ ፖሊስ ጣቢያ የቀድሞ የፖሊስ አባልና የወንጀል መከላከል ቡድን መሪ የነበረው ዋና ሳጅን ትግሉ ሰቦቃ፣ 2ኛ እና 3ኛ ደግሞ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ የጊቢ ጥበቃ አባላት የነበሩት ኮ/ብል ዘነበ ኩማ እና ኮ/ብል መንግስቱ እንቻሌ እንዲሁም 4ኛ አቶ ላዕከ ተስፋ ገ/ስላሴ፣ 5ኛ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ድርጅት ውስጥ የቦሌ አራብሳ ፕሮጀክት 13 ጥበቃ የነበረው መልካሙ አያና፣ 6ኛ መላኩ ካላዩ፣ 7ኛ ከበደ ገ/እየሱስ፣ 8ኛ ወንዶሰን ወይም ኢብራሂም ረጋሳ ገለታ እና 9ኛ ሮቤል ሙሉአለም ሃይሉ ናቸው።
የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት ጀነራል በ2015 ዓ.ም በተከሳሾች ላይ የተሳትፎ ደረጃ ጠቅሶ ስልጣንን ያለአግባብ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ አቅርቦባቸው ነበር።
በክስ ዝርዝሩ ላይ እንዳመላከተው፤ ተከሳሾቹ የማይገባቸውን ብልጽግና ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ በጥቅም በመመሳጠር በዋና እና በልዩ ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን ጥር 30 ቀን 2015 ዓ.ም ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ላይ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱ የፖሊስ አባላት ፖሊሳዊ ኃላፊነታቸውን ያለአግባብ በመገልገል በአዲስ አበባ በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ቦሌ አራብሳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ቦሌ አራብሳ ሳይት ውስጥ በመግባት በጥበቃ ስራ ላይ የነበረ (የዐቃቤ ሕግ ምስክር) ግለሰብን “ለወንጀል ምርመራ ትፈለጋለህ" በማለት 1ኛ ተከሳሽ ከ3ኛ ተከሳሽ ጋር በመሆን ከጥበቃ ስፍራው ወደ ሌላ ቦታ ወስደዋል።
2ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች ደግሞ በቦታው የነበሩ ንብረቶችን እንዲያወጡ በመርዳት 11 ሚሊየን ብር የሚያወጡ ሁለት ማለትም የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 03-95058 ኢት የሆነ እና የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 03-16409 ኢት የሆኑ ሁለት ሲኖ ትራክ ተሽከርካሪዎችን 6ኛ ተከሳሽ ሞተሩን በካቻቢቴ በማስነሳት ከ9ኛ ተከሳሽ ጋር ተሽከርካሪዎችን ይዘውና ሌሎቹ ደግሞ አጅበው ወደ አዳማ በመውሰድና በመሰወር፣ 8ኛ ተከሳሽ ደግሞ ከሌሎች ግብረዓበሮቹ ጋር በመሆን አንደኛውን ተሽከርካሪ ለግለሰብ በ600 ሺህ ብር በመሸጥና ገንዘቡን በ7ኛ ተከሳሽ ስም በተከፈተ በአዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ ሂሳብ በማስገባትና በተለያዩ መጠኖች ገንዘቡን መከፋፈላቸው ተጠቅሶ ስልጣንን ያለአግባብ መገልገል ከባድ ሙስና ወንጀል ተከሰው ነበር።
ከተከሳሾቹ መካከል ስድስቱ ችሎት ቀርበው ክስ ዝርዝሩ የደረሳቸው ሲሆን÷ ቀሪ ሶስት ተከሳሾች ግን በተደጋጋሚ መጥሪያ ተደርጎላቸው ሳይቀርቡ መቅረታቸውን ተከትሎ ጉዳያቸው በሌሉበት እንዲታይ ተደርጓል።
ችሎት የቀረቡ ስድስቱ ተከሳሾች የወንጀል ድርጊቱን አልፈጸምንም ብለው የዕምነት ክህደት ቃላቸውን በመስጠታቸው ዐቃቤ ሕግ የተለያዩ ገላጭ ማስረጃዎችን እና ስምንት የሰው ምስክሮችን ቃል አሰምቷል።
ፍርድ ቤቱም የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን መርምሮ ዛሬ በዋለው ችሎት 1ኛ፣ 2ኛ፣ 3ኛ፣ 4ኛ፣ 6ኛ እና 7ኛ ተከሳሾችን በሚመለከት በዐቃቤ ሕግ የቀረበባቸውን ማስረጃ በወንጀል ህግ አንቀጽ 32 ንዑስ ቁጥር 1 ሀ እና ለ፣ አንቀጽ 33 እንዲሁም የሙስና አዋጅን ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 9 ንዑስ ቁጥር 2 መሰረት እንዲከላከሉ በሙሉ ድምጽ ብይን ሰጥቷል።
5ኛ፣ 8ኛ እና 9ኛ ተከሳሾችን ደግሞ በዚሁ ድንጋጌ ስር በሌሉበት የጥፋተኝነት ፍርድ መተላለፈባቸውን ኤፍቢሲ ዘግቧል።
ተከላከሉ የተባሉ ተከሳሾችን የመከላከያ ማስረጃ ለመጠባበቅ ለሚያዚያ 9 ቀን 2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ የተሰጠ ሲሆን÷ በዚህ ቀን ዐቃቤ ሕግ የጥፋተኝነት ፍርድ የተላለፈባቸው ሶስት ተከሳሾችን በሚመለከት የቅጣት አስተያየት እንዲያቀርብ ቀጠሮ ተሰጥቷል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ከተቋማት የተደወለ በማስመሰል “የማጭበርበር ወንጀል ሲፈጽሙ ነበሩ” ባላቸው ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ ሊመሰርት መሆኑን ፖሊስ አስታወቀ
****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 3/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ከባንክ፣ ከኢትዮ-ቴሌኮም እና ከሌሎች ተቋማት የተደወለ በማስመሰል የማጭበርበር ወንጀል ፈጽመዋል ባላቸው 11 ተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራውን ጨምረ የክስ መዝገብ ለአቃቤ ህግ መላኩን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ የማጭበርበር ወንጀሉን ሲፈጽሙ የነበሩት “በይቆጥቡ ይሸለሙ” የሎተሪ ገንዘብ እና ሌሎች ሽልማቶች “አሸንፈዋል” በሚል ማሳሳቻ መሆኑ ተገልጿል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ ከግለሰቦች የባንክ አካውንት ገንዘብ ሲመዘብሩ የቆዩት “ሽልማቶቹን እንድታገኙ ሲቢኢ ዋሌት/CBE wallet / ክፈቱ“ ፣ “የሞባይል ባንኪንግ ኮዳችሁን ንገሩን“ እና “የምንልከውን ኮድ ያስገቡ“ በሚሉ ማጭበርበሪያዎች መሆኑም ተጠቁሟል፡፡
ፖሊስ ከህብረተሰቡ የደረሰውን አቤቱታ መነሻ በማድረግ በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ታቦት ማደሪያ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ 3 ወንድማማቾችን ጨምሮ 6 ተጠርጣሪዎችን በመኖሪያ ቤት ውስጥ ወንጀሉን ሲፈፅሙ እጅ ከፍንጅ ያያዛቸው ሲሆን የተቀሩትን ሁለት ተጠርጣሪዎችን ደግሞ በክትትል መያዙን አስታውቋል፡፡
ግለሰቦቹ ወንጀል ሲፈፅሙበት ነበረ የተባለ 176 ሲም ካርድ፣ 33 የሞባይል ቀፎዎች አንድ ተንቀሳቃሽ ዋይፋይ ራውተር፣ አንድ ተሽከርካሪ እና የተለያዩ የባንክ ደብተሮች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተጠቁሟል፡፡
ህብረተሰብ ከባንክ አካውንት ጋር የተገናኘ ጥሪ ሲደርሰው ትክክለኝነቱን ደንበኛ ከሆነበት ባንክ ማረጋገጥ እና ጥርጣሬ ሲኖር ለፀጥታ አካላት ጥቆማ መስጠት እንዳለበትም ፖሊስ ማሳሰቡን ጠቅሶ ኢቢሲ ዘግቧል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 3/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ከባንክ፣ ከኢትዮ-ቴሌኮም እና ከሌሎች ተቋማት የተደወለ በማስመሰል የማጭበርበር ወንጀል ፈጽመዋል ባላቸው 11 ተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራውን ጨምረ የክስ መዝገብ ለአቃቤ ህግ መላኩን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ የማጭበርበር ወንጀሉን ሲፈጽሙ የነበሩት “በይቆጥቡ ይሸለሙ” የሎተሪ ገንዘብ እና ሌሎች ሽልማቶች “አሸንፈዋል” በሚል ማሳሳቻ መሆኑ ተገልጿል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ ከግለሰቦች የባንክ አካውንት ገንዘብ ሲመዘብሩ የቆዩት “ሽልማቶቹን እንድታገኙ ሲቢኢ ዋሌት/CBE wallet / ክፈቱ“ ፣ “የሞባይል ባንኪንግ ኮዳችሁን ንገሩን“ እና “የምንልከውን ኮድ ያስገቡ“ በሚሉ ማጭበርበሪያዎች መሆኑም ተጠቁሟል፡፡
ፖሊስ ከህብረተሰቡ የደረሰውን አቤቱታ መነሻ በማድረግ በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ታቦት ማደሪያ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ 3 ወንድማማቾችን ጨምሮ 6 ተጠርጣሪዎችን በመኖሪያ ቤት ውስጥ ወንጀሉን ሲፈፅሙ እጅ ከፍንጅ ያያዛቸው ሲሆን የተቀሩትን ሁለት ተጠርጣሪዎችን ደግሞ በክትትል መያዙን አስታውቋል፡፡
ግለሰቦቹ ወንጀል ሲፈፅሙበት ነበረ የተባለ 176 ሲም ካርድ፣ 33 የሞባይል ቀፎዎች አንድ ተንቀሳቃሽ ዋይፋይ ራውተር፣ አንድ ተሽከርካሪ እና የተለያዩ የባንክ ደብተሮች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተጠቁሟል፡፡
ህብረተሰብ ከባንክ አካውንት ጋር የተገናኘ ጥሪ ሲደርሰው ትክክለኝነቱን ደንበኛ ከሆነበት ባንክ ማረጋገጥ እና ጥርጣሬ ሲኖር ለፀጥታ አካላት ጥቆማ መስጠት እንዳለበትም ፖሊስ ማሳሰቡን ጠቅሶ ኢቢሲ ዘግቧል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
የሙስና ወንጀል ልማትን የሚያደናቅፍ ፍትህን የሚያዛባ በመሆኑ በጋራ ልንከላከለው ይገባል
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 3/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የሙስና ወንጀል ልማትን የሚያደናቅፍ እና ፍትህን የሚያዛባ በመሆኑ አንድ ተቋም ብቻ ሳይሆን ሁሉም አካል በጋራ ሊከላከል እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን።
ኮሚሽኑ የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 6 ወራት አፈፃፀም ግምገማና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ የምክክር መድረክ አካሄዷል።
የሙስና ወንጀል ልማትን የሚያደናቅፍ፣ ፍትህን የሚያዛባ፣ የህግ የበላይነትን የሚሸረሽር፣ የሰብአዊ መብት ጥሰትን የሚያስከትልና ዲሞክራሲ እውን እንዳይሆን ማነቆ ከሆኑ ጉዳዮች ዋነኛዉ እንደሆነ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የህግ የፍትህና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ስብሳቢ አቶ ንጉሴ ወ/ሚካኤል ተናግረዋል።
የሙስና ወንጀሉን በመከላከል እረገድ የሁሉም ባለድርሻ አካላት የተደራጀ ትብብርና ቅንጅት የሚፈልግ እንደሆነ ተገልጿል።
ኮምሽኑና በየደረጃው ያሉ የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች በዋናነት ሙስና እና ብልሹ አሰራር የማይሸከም ህብረተሰብ በመፍጠርና የግንዛቤ ስራዎችን በማስፋት ለሙስና እና ለብልሹ አሰራር የሚያጋልጡ ሁኔታዎችን በጥናት መዝጋት እንደሚኖርባቸው አሳስበዋል።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በፍትህና ልማት ዕቅድ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ግርማ ግዥ እንደተናገሩት አስቸኳይ ሙስና መከላከል ተግባራትን በመስራት የመንግስትና የህዝብ ሀብት ከብክነት ማዳን እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ቅንጅታዊ ስራዎችን በማጠናከር ሙስና እና ብልሹ አሰራርን በመከላከል ክልላዊ የልማት ግቦቻችንን ወደማያደናቅፍ ደረጃ ማድረስ ይኖርብናል ማለታቸውን ሚዛን አማን ፋና ኤፍ ኤም ዘግቧል።
በኮሚሽኑና በየደረጃው ባሉ የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች የሚሰሩ የስራ አፈፃፀሞች ከጊዜ ወደ ግዜ መሻሻሎች እንዳሉት በአፈፃፀም ግምገማው ላይ ተገልጿል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 3/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የሙስና ወንጀል ልማትን የሚያደናቅፍ እና ፍትህን የሚያዛባ በመሆኑ አንድ ተቋም ብቻ ሳይሆን ሁሉም አካል በጋራ ሊከላከል እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን።
ኮሚሽኑ የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 6 ወራት አፈፃፀም ግምገማና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ የምክክር መድረክ አካሄዷል።
የሙስና ወንጀል ልማትን የሚያደናቅፍ፣ ፍትህን የሚያዛባ፣ የህግ የበላይነትን የሚሸረሽር፣ የሰብአዊ መብት ጥሰትን የሚያስከትልና ዲሞክራሲ እውን እንዳይሆን ማነቆ ከሆኑ ጉዳዮች ዋነኛዉ እንደሆነ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የህግ የፍትህና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ስብሳቢ አቶ ንጉሴ ወ/ሚካኤል ተናግረዋል።
የሙስና ወንጀሉን በመከላከል እረገድ የሁሉም ባለድርሻ አካላት የተደራጀ ትብብርና ቅንጅት የሚፈልግ እንደሆነ ተገልጿል።
ኮምሽኑና በየደረጃው ያሉ የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች በዋናነት ሙስና እና ብልሹ አሰራር የማይሸከም ህብረተሰብ በመፍጠርና የግንዛቤ ስራዎችን በማስፋት ለሙስና እና ለብልሹ አሰራር የሚያጋልጡ ሁኔታዎችን በጥናት መዝጋት እንደሚኖርባቸው አሳስበዋል።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በፍትህና ልማት ዕቅድ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ግርማ ግዥ እንደተናገሩት አስቸኳይ ሙስና መከላከል ተግባራትን በመስራት የመንግስትና የህዝብ ሀብት ከብክነት ማዳን እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ቅንጅታዊ ስራዎችን በማጠናከር ሙስና እና ብልሹ አሰራርን በመከላከል ክልላዊ የልማት ግቦቻችንን ወደማያደናቅፍ ደረጃ ማድረስ ይኖርብናል ማለታቸውን ሚዛን አማን ፋና ኤፍ ኤም ዘግቧል።
በኮሚሽኑና በየደረጃው ባሉ የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች የሚሰሩ የስራ አፈፃፀሞች ከጊዜ ወደ ግዜ መሻሻሎች እንዳሉት በአፈፃፀም ግምገማው ላይ ተገልጿል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ሙስናን በጽናት በመታገል መልካም አስተዳደርን እናረጋግጥ!
****
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡