Federal Ethics And Anti- Corruption Commission
9.92K subscribers
10.3K photos
244 videos
32 files
3.04K links
Download Telegram
በክልሉ የተጀመረው ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎችን የማጣራት ሥራ ህዝብ በተደጋጋሚ ለሚያነሳቸው ቅሬታዎች ምላሽ የሚሰጥ ነው - የተከበሩ አብርሃም አለማየሁ (ዶ/ር)

****************

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 29/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተጀመረው ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎችን የማጣራት ሥራ ህዝብ በተደጋጋሚ ለሚያነሳቸው ቅሬታዎች ምላሽ የሚሰጥ መሆኑን የተከበሩ አብርሃም አለማየሁ (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፌደራል ፓርላማ እና የክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤቶች አባላት ከወከላቸው ህዝብ ጋር ያደረጉት የውይይት ግብረ-መልስ ማቅረቢያ መድረክ በሆሳዕና ከተማ መካሄዱ ተገልጿል፡፡

በክልሉ የሚኖሩ 20 ሺ ሰዎችን ማወያየት መቻሉን የተናገሩት በኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ የተከበሩ አብርሃም አለማየሁ (ዶ/ር) በውይይት መድረኩ የተነሱ ሀሳቦችን፣ አስተያየቶችን፣ ጥያቄዎችንና ለጥያቄዎቹ ምላሽ ለመስጠት የክልሉ መንግስት የሚያደርገውን ጥረት በተመለከተ ገለፃ አድርገዋል፡፡

ከህዝብ ጋር በተደረገው የውይይት መድረክ ላይ የሠላምና ፀጥታ፣ የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ፣ የፕሮጀክት አፈፃፀም፣ የሌብነት እና ብልሹ አሰራር እንዲሁም የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች መነሳታቸውን አስረድተዋል፡፡

የክልሉ ህዝብ ለሚያነሳቸው የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የክልሉ መንግስት የሚያደርገው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የተከበሩ አብርሃም አለማየሁ (ዶ/ር)ገልጸዋል::

ከሌብነትና ብሉሹ አሰራር ጋር ተያይዞ በተለይም የማዳበሪያ እዳ ጉዳይ ህዝብ በተለያዩ መድረኮች ላይ የሚያነሳው ነው ያሉት የተከበሩ አብርሃም አለማየሁ (ዶ/ር)፣ አሁን ችግሩን ለመፍታት ወረዳዎችና ዞኖች የኦዲት ሥራ መጀመራቸው ጥሩ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በክልሉ የተጀመረው ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎችን የማጣራት ሥራ ህዝብ በተደጋጋሚ ለሚያነሳቸው ቅሬታዎች ምላሽ የሚሰጥ ነው ማለታቸውን የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ዘግቧል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
የመጋዘን ኃላፊው ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ መድሃኒት በመሰወር የሙስና ወንጀል ክስ ቀረበበት

***

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 29/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የኢትዮጵያ የመድሃኒት አቅራቢ ድርጅት የመጋዘን ኃላፊው ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ መድሃኒት በመሰወር የሙስና ወንጀል ክስ ቀረበበት።

የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት ጀነራል በኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢ አገልግሎት የመጋዘን ኃላፊ በነበረው እና በተመሳሳይ ወንጀል ተከሶ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት የሚገኘው ሚካኤል ዘዉገ ተሰማ ላይ የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 31 ንዑስ ቁጥር 2 ስር የተመላከተውን ድንጋጌ ተላልፏል በማለት ክስ አቅርቦበታል።

በቀረበበት ክስ ዝርዝር ላይ እንደተመላከተው፥ ተከሳሹ በኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢ አገልግሎት ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚገኙ የሁለት መጋዘኖች ኃላፊ ሆኖ በሚያስተዳድርበት ወቅት የኢትዮጵያ መድሐኒት አቅራቢ አገልግሎት አንቲ አርኤችኦ (ዲ) ኢሚዩን ግሎቡሊን (Anti-Rho (D) Immune Globulin 300 Mg in 2ml Vial- Injection) መድሐኒት መጠኑ በብልቃጥ 46 ሺህ 560 የሆነ ከበሀራት ሰሩም እና ቫሲን ኤልቲዲ (Bharat Serum and Vaccine LTD) ከተባለ አቅራቢ በግዥ ትዕዛዝ ከዉጭ ሀገር ያስመጣውን መድሐኒት መጋቢት 15 ቀን 2012 ዓ.ም ፈርሞ ከትራንዚተር ተረክቧል።

ከዚህ በኋላ መድሐኒቱን ወደ ሌላ "ሜይን 3"ወደ ተሰኘ መጋዘን አብሮ ገቢ ካደረገ በኋላ ከተረከበው አጠቃላይ 46 ሺህ 560 ብልቃጥ ውስጥ አጠቃላይ የዋጋ ግምቱ 1 ሚሊየን 114 ሺህ 857 ብር ከ87 ሳንቲም የሚያወጣ 900 ብልቃጥ መድሐኒት ሳያስረክብ ለራሱ ወይም ለሌላ ሰው ያደረገ ወይም የሰወረ መሆኑ ተጠቅሶ በከባድ የእምነት ማጉደል የሙስና ወንጀል መከሰሱን ኤፍቢሲ ዘግቧል፡፡

የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ክሱን ለመመልከት ለመጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃን አስመልክቶ መግለጫ ሰጠ

***

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 29/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የዩኒቨርሲቲው ምሩቃን በሀገር አቀፍና በዓለምአቀፍ ተቋማት በሚቀጠሩበት ወይም ተቀጥረው እየሠሩ ባሉበት ጊዜ የሚቀርቡ የትምህርት ማስረጃ ትክክለኛነት ይጣራልን ጥያቄዎችን እየተቀበለ የትምህርት ማስረጃ አጣርቶ በማረጋገጥ በተከታታይ ምላሽ በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡

በዚህም መሠረት በ2015 ዓ.ም የቀረቡ የትምህርት ማስረጃ ማጣራት ጥያቄዎችን ተከትሎ በተደረገ የማጣራት ሂደት ከአንዳንድ ተቋማት የቀረቡ የዩኒቨርሲቲው ምሩቃን የትምህርት ማስረጃዎች በዩኒቨርሲቲው በተሰጣቸው የተማሪ ውጤት ኮፒ ላይ የአጠቃላይ ነጥብ ለውጥ የተደረገባቸው እንዲሁም ፈጽሞ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ያልተማሩባቸው ሀሰተኛ ዲግሪ ማስረጃዎች ሆነው የተገኙ መሆኑን ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡

በመሆኑም መሰል ኃላፊነት የጎደላቸው ተግባራት እንዳይበረታቱ ብሎም ሕዝብና መንግሥት ሙያዊ ብቃት በሌላቸውና ኃላፊነት በጎደላቸው ዜጎች ለጉዳት እንዳይጋለጥ በማሰብ በዩኒቨርሲቲው የትምህርት ማስረጃ ላይ የዘመኑን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ በማስመሰልና በመቀየር እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው ስምና ሎጎ ያልተማሩበትን ዲግሪ ይዘው የማጭበርበር ተግባር ላይ የተሠማሩና ወደ ፊትም የሚሠማሩ ቢኖሩ ለሕዝብ የማጋለጥ ሥራ በተከታታይነት እንዲሠራ ዩኒቨርሲቲው ወስኗል፡፡

ስለሆነም ከዚህ መግለጫ ጋር በፎቶ በተያያዘው የሀሰተኛ ማስረጃ ማጣራት ሪፖርት ላይ ስማቸው የተጠቀሱ ግለሰቦች በእነዚህ የትምህርት ማስረጃዎች በየትኛውም ተቋም ቢቀጠሩ ማስረጃዎቻቸው ሕጋዊነት የሌላቸው መሆኑን ጠቅሶ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ መረጃውን በፌስቡክ ገፁ አጋርቷል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ተማሪዎች ግብረ ገባዊ እና ሀገራዊ ግዴታቸውን ለመወጣት ሥነምግባራዊ እሴቶችን ማጎልበት ይኖርባቸዋል - ም/ኮሚሽነር አሰፋ ቶላ

****

(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 30/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአዲስ አበባ ከተማ የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከአራዳ፣ ቂርቆስ፣ አዲስ ከተማና ልደታ ክፍለ ከተሞች ለተውጣጡ የመንግስት ትምህርት ቤት የግብረ ገብና የፀረ-ሙስና ክበባት ስራ አስፈፃሚ ተማሪዎች ስልጠና ሰጥቷል።

የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር አሰፋ ቶላ የመክፈቻ ንግግር ባደረጉበት ወቅት እንደተናገሩት በሀገራችን ብሎም በከተማችን እየተንሰራፋ የሚገኘውን የሥነምግባር ዝቅጠትና የግብረ ገብነት ችግሮችን ለመቅረፍ በትውልድ ላይ መስራት አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል።

ኮሚሽኑ በትውልድ ሥነምግባር ግንባታ ላይ በከተማው የሚገኙ የመንግስት ትምህርት ቤቶች ላይ የግብረ ገብነና የፀረ-ሙስና ክበባትን በአዲስ አደራጅቶ ወደ ስራ የገባ መሆኑን ም/ኮሚሽነር አሰፋ ገልፀው፥ ተማሪዎች ግብረ ገባዊና ሀገራዊ ግዴታቸውን ለመወጣት ሥነምግባራዊ እሴቶችን እንዲያጎለብቱ ክበባቱ መቋቋማቸው የማይተካ ሚና አላቸው ብለዋል።

የኮሚሽኑ የስልጠና ክፍል ኃላፊ አቶ ጀንበሩ ኢርኮ ስልጠናውን የሰጡ ሲሆን፥ ትምህርት ቤቶች የትውልድ ሥነምግባር መገንቢያ ማዕከል እንደመሆናቸው ነገ ሀገር ሊረከቡ የሚችሉ ተማሪዎችን ማፍራት እንደሚጠበቅባቸው ገለፃ አድርገዋል።

ኮሚሽኑ በትውልድ ሥነምግባር ግንባታ ላይ በመንግስት ትምህርት ቤቶች የጀመራቸውን ስራዎች አጠናክሮ ለመቀጠል የትምህርት ማህበረሰቡን ባሳተፈ መልኩ ስራዎች ሊሰሩ እንደሚገባ በስልጠናው ማብራራታቸውን ከኮሚሽኑ የፌስቡክ ገፅ የተገኘው መረጃ ያስረዳል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡