Federal Ethics And Anti- Corruption Commission
9.93K subscribers
10.3K photos
244 videos
32 files
3.04K links
Download Telegram
ኮሚሽኑ ሀብት ላስመዘገቡ የምክር ቤቱ አመራሮችና የፅ/ቤቱ ሰራተኞች የምስክር ወረቀት ሰጠ

****************

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 25/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአዲስ አበባ ከተማ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ሀብታቻውን ላስመዘገቡ የአዲስ አበባ ምክር ቤት አመራሮችና ለጽ/ቤቱ ሠራተኞች የምስክር ወረቀት ሰጥቷል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሪት ፋይዛ መሐመድ በሰርተፊኬት አሰጣጥ ሥነስርዓቱ ላይ ተገኝተው እንደተናገሩት ሌብነትና ብልሹ አሰራር አገር አጥፊ እንደመሆኑ መጠን እኛ እንደአመራር ሆነ እንደ መንግስት ሠራተኛ ለሌላው ማህበረሰብ አርዓያ በመሆን በጋራ እጅ ለእጅ ተያይዘን መታገል ይጠበቅብናል ብለዋል።

በአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ማናዬ በሥነምግባር የታነፀ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ለማፍራት በሚደረገው ርብርብ ሁሉም ዜጋ የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በዕለቱ ሀብታቸውን ያሳወቁና ያስመዘገቡ አመራሮች እና ሠራተኞች ሀብትን ያስመዝገቡበትን ምስክር ወረቀት ርክክብ በማካሄድ በተቋሙ የሥነምግባር ሰራዊት ማቋቋማቸውን ከአዲስ አበባ ምክር ቤት የህ/ግ/ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዘገባ ማወቁን ገልፆ ኮሚሽኑ በፌስቡክ ገፁ መረጃውን አጋርቷል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
የፌደራል ፖሊስ አባላትና ግብራበሮቻቸው በስራ ተግባር የሚፈፀም የመውሰድና የመሰወር ከባድ የሙሰና ወንጀል ተከሰሱ

****

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 26/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) አራት የፌደራል ፖሊስ አባላትና 4 በግል ስራ የተሰማሩ ግብራበሮቻቸው በስራ ተግባር የሚፈፀም የመውሰድና የመሰወር ከባድ የሙሰና ወንጀል መከሰሳቸው ተገለፀ።

ከተከሻቹ መካከል ሳጅን አሊ መሀመድ አሊ፣ ኮንስታብል መድ በሌ፣ መልካሙ ሽንኮራ እና ሀብታው ዳዲ ይገኙበታል።

በፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ወንጀሎች አቃቤህግ ዳይሬክቶሬት ጀነራል ክስ መዝገብ እንደሚያስረዳው ተከሳሾቹ ወንጀሉን የፈፀሙት በያዝነው የካቲት ወር ሌሊት 9 ሰዓት ነው።

ተከሳሾቹ የቱሉዲምቱ ካምፕ የአፍረፅዮን ኮንስትራክሽን ንብረት እንዲጠብቁ ተመድበው ሲሰሩ ወንጀሉን መፈፀማቸው ተገልጿል፡፡

ማንነቱ ለጊዜው ያልታወቀ አይሱዙ ተሸከርካሪ የኮንስትራክሸኑን 5 ሺህ 692 የውሃ ማስተላለፊያ መገጠጣሚያዎች ጭኖ ሲወስድ ቆመው ሽፋን በመስጠታቸው መከሰሳቸው ተገልጿል።

ከነርሱ ጋር የጥቅም ትስስር የነበራቸው 4ቱ ተከሳሾች ንብረቱን ሌሊት ጭነው ሲወጡ እጅ ከፍንጅ መያዛቸውንም ክሱ ያትታል።

በዚህም አቃቤ ህግ ሁሉንም በስራ ተግባር የሚፈፀም የመውሰድና የመሰወር ከባድ የሙስና ወንጀል ከሷቸዋል፡፡ በትላትናው ዕለት ሁሉም ተከሳሾች በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድቤት 1ኛ የሙስና ወንጀል ችሎት መቅረባቸውን ኢቢሲ ዘግቧል።

ከጠበቆቻቸው ጋራ ተመካክረው ክሱ እንዲነበብላቸው ተለዋጭ ቀጠሮ ተይዟል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በፀረ-ሙስና ትግሉ የፖሊስ ሚና

****************

የአዲስ አበባ ከተማ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከአዲስ ሚዲያ ኔትውርክ ጋር በመተባበር በፀረ-ሙስና ትግሉ የፖሊስ ሚና በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ የተደረገ ፕሮግራም ነው፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
አሜሪካ በዚምባብዌ ፕሬዝዳንት ምናንጋግዋ እና በሌሎች መሪዎች ላይ ከሙስና ጋር በተያያዘ አዲስ ማዕቀብ ጣለች

****

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 26/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) አሜሪካ በዚምባብዌ ፕሬዝዳንት ኢመርሰን ምናንጋግዋ ላይ በሙስና እና በሰብአዊ መብት ረገጣ በሚል አዲስ ማዕቀብ ጣለች።

የማዕቀቡ ትዕዛዝ በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮችንም የሚነካ ሲሆን፥ በአሜሪካ ያሉ ንብረቶቻቸውን ማገድ ጨምሮ መደበኛ ያልሆነ ጉዞ እንዳያደርጉ ይከለክላል። አዲሱ ማዕቀብ ከሁለት አስርት አመታት በፊት የተጀመረውን ሰፊ ፕሮግራም ተክቷል ተብሏል።

ዋይት ሀውስ በመግለጫው “በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ እና በሰብአዊ መብቶች ላይ የሚፈጸሙ ከባድ ጥሰቶችን እያየን ነው” ብሏል። የሲቪል ማህበረሰቡን ኢላማ ማድረግ እና በፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ከፍተኛ እገዳዎች መሰረታዊ ነፃነቶችን ጨፍልቀዋል፣ የመንግስት መሪዎችን ጨምሮ ቁልፍ ተዋናዮች የህዝብን ሃብት ለግል ጥቅም በዝብዘዋል ሲል አክሏል።

እነዚህ ህገወጥ ተግባራት በዚምባብዌ፣ በደቡብ አፍሪካ እና በሌሎች የአለም ክፍሎች ያሉ ማህበረሰቦችን ለድህነት የሚዳርግ ጉቦ እና ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር አለም አቀፍ የወንጀል መረብን ለመደገፍ አስተዋፅኦ ያደርጋሉ ተብሏል።

በአሜሪካ ማዕቀብ ከተጣለባቸው ከፕሬዝዳንት ምናንጋግዋ በተጨማሪም ሌሎች 10 ሰዎች ላይ እና ሶስት የንግድ ድርጅቶችን እንዳሉበት ተገልጿል። በዝርዝሩ ውስጥ ከተካተቱት መካከል ቀዳማዊት እመቤት ኦክሲሊያ ምናንጋግዋ፣ ምክትል ፕሬዝዳንት ኮንስታንቲኖ ቺዌንጋ እና የመከላከያ ሚኒስትር ኦፓህ ሙቺንጉሪ ይገኙበታል።

የዚምባብዌ ብሄራዊ ፖሊስ እና የማዕከላዊ መረጃ ድርጅት (ሲአይኦ) አባላትን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የደህንነት ባለስልጣናት ኢላማ ተደርገዋል። የመንግስት ሙስናን ሲያመቻቹ የነበሩ ነጋዴዎችም ከማዕቀቡ አላመለጡም ተብሏል።
የዚምባብዌ መንግስት ቃል አቀባይ ኒክ ምናንጋግዋ የቀድሞው የማዕቀብ መርሃ ግብር መነሳት የፕሬዚዳንት ምናንጋግዋ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ትልቅ ማረጋገጫ ነው ሲሉ ገልጸው አዲሱን ማዕቀብ ግን "ህገ-ወጥ" ሲሉ ገልጸውታል።

የፕሬዝዳንት ምናንጋግዋ ገዥው የዛኑ ፒኤፍ ፓርቲ ቃል አቀባይ ፋራይ ሙሮይዋ ማራፒራ በበኩላቸዉ ፕሬዚዳንቱ "የሁሉም ወዳጅ እና የማንም ጠላት የመሆን ፖሊሲ እና በራችን ለሁሉም ክፍት እንዲሆን መደረጉ መራራ ውጤት አስገኝቷል" ብለዋል። "ፕሬዝዳንቱ፣ ቀዳማዊት እመቤት እና ከፍተኛ ባለስልጣናት ማዕቀብ ከተጣለባቸው ዚምባብዌ በዚህ ህገ-ወጥነት ማዕቀብ እና ሸክም እንዳለባት ትቀጥላለች" ሲል በቀድሞው ትዊተር በአሁኑ ኤክስ ገፃቸው ላይ ጽፏል።

አሜሪካ በ1990ዎቹ መጀመሪያ ላይ በዚምባብዌ ላይ የኢኮኖሚ እና የጉዞ ማዕቀብ ጥላ እንደነበር ተገልጿል፡፡ የቀድሞ የዚምባብዌ ፕሬዝዳንት ሮበርት ሙጋቤ እና በደርዘን የሚቆጠሩ ሌሎች የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ዋሽንግተን የሀገሪቱን ዲሞክራሲን ያናጋሉ በማለት መክሰሳቸዉ ይታወሳል፡፡

የዩናይትድ ኪንግደም እና የአውሮፓ ህብረት አባላትን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት በዚምባብዌ ላይ ማዕቀብ ጥለዋል። ባለፈው አመት ለሁለተኛ ጊዜ ቃለ መሃላ የፈፀሙት ፕሬዚደንት ምናንጋግዋ የኢኮኖሚ ታሪፍ የሀገሪቱን እድገት እያሽመደመደው ገልፆ ቢቢሲ አፍሪካ ኒውስ ዘግቧል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
በኮሚሽኑ አመራሮች የተመራ የልዑካን ቡድን እና የኢንዶኔዥያ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽኖች የልምድና ተሞክሮ ልውውጥ አደረጉ

****

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 26/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል፣ የክልልና ከተማ አስተዳደር የሥነምነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን አመራሮች እና የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ እውነቴ አለነ እንዲሁም የፍትህ ሚኒስቴር ዴኤታ ክቡር ተስፋዬ ዳባን ያካተተ ልዑካን ቡድን በኢንዶኔዥያ ጃካርታ ከተማ ከሚገኘው የሙስና መከላከል ኮሚሽን የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ጋር የተሞክሮና የልምድ ልውውጥ አካሄዱ፡፡

በኢሲያ ሀገራት ውስጥ በፀረ-ሙስና ትግል ውጤታማ ተግባራትን በማከናወን ከሚገኙ ተቋማት መካከል አንዱ ከሆነው የኢንዶኔዥያ የሙስና መከላከል ኮሚሽን/KPK/ እንደገና ከተቋቋመበት እ.ኤ.አ ከ2003 ጀምሮ ተጠሪነቱን ለኢንዶኔዥያ ህዝብ በማድረግ፣ ከማኛውም አካል ነፃና ገለልተኛ በሆነ ሁኔታ( Type A) የራሱን አቅም በሰው ኃይልና በበጀት በማሳደግ ሶስቱን የሙስና መታገያ ስልቶችን ከተለያዩ የባለድርሻ አካላት ጋር በትስስር የሥነምግባር ግንባታን፣ የሙስና መከላከል እና የምርመራና ክስ ሥራዎችን ስትራቴጂ በመንደፍና በማከናወን ላይ የሚገኝ ኮሚሽን መሆኑ ተመላክቷል፡፡

ይህን የሥነምግባር ግንባታና የሙስና መከላከል ልምድና ተሞክሮ ከኢትዮጵያ የፀረ-ሙስና ትግል በሚጣጣም መልኩ በመቀመር ጥቅም ላይ ለማዋል እንዲቻል በኮሚሽኑ አመራሮች የተመራ ልዑኳን ቡድን ኢንዶኔዥያ ጃካርታ ከተማ በሚገኘው የሙስና መከላከል ኮሚሽን/KPK/ የሥራ ኃላፊና ባለሙያዎች በተገኙበት ልምድና ተሞክሯቸውን መለዋወጥ መቻሉ ተገልጿል፡፡

በኢንዶኔዥያ የሙስና መከላከል ኮሚሽን አደረጃጀት፣ የሚያከናውናቸው ስትራቴጂዎች፣ ውጤታማነትና ተግዳሮቶች ላይ ለልኡካን ቡድን አባላት ግንዛቤ ተፈጥሯል፡፡ ልኡካን ቡድኑም የኢትዮጵያ አጠቃላይ የፀረ-ሙስና ትግል እንቅስቃሴን በማብራራት በቀጣይ ልምድና ተሞክሮ የሚወስድባቸው ጉዳዮችን ትኩረት በማስቀመጥ ለብሔራዊ ሥነምግባር ግንባታና የሙስና መከላከል ፖሊሲ ዝግጅት የሚያግዙ የመነሻ ሀሳቦች መፀባረቃቸው ተመላክቷል፡፡

የኢንዶኔዥያ የሙስና መከላከል ኮሚሽን ኮሚሽነሮችም በተደረገው የተሞክሮና ልምድ ልውውጥ ሂደት በኮሚሽኑ የሙስና መከላከል ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ ተሞክሮ ሊሆኑ በሚችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡

እንዲሁም የሙስና ወንጀል ምርመራና ክስ ላይ የተሞክሮና ልምድ ልውውጥ የተደረገ ሲሆን፤ የልኡካን ቡድን አባላት ባነሷቸው ጉዳዮች ላይ በቂ ማብራሪያ መሰጠቱና በቀጣይ ቀናትም የልምድ ልውውጡ የሚቀጥል መሆኑን ከሥፍራው ያገኘነው መረጃ ያስረዳል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ልጆቼ ዳኞች በመሆናቸው የፍርድ ቤት ክርክራችሁን እኔ አስጨርስላችኃለሁ በማለት ጉቦ የተቀበለችው ግለሰብ በእስራት ተቀጣች

****

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 26/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) በምስራቅ ሀረርጌ ዞን ጉልሱም ወረዳ ሁኛን በሪ ከተማ ውስጥ ልጆቼ ዳኞች ስለሆኑ የፍርድ ቤት ክርክራችሁን እኔ አስጨርስላችኃለሁ በማለት ገንዘብ የተቀበለች ግለሰብ በእስራት መቀጣቷን የጉልሱም ወረዳ ዓቃቤ ህግ ፅ/ቤት አስታውቋል።

የጉልሱም ወረዳ ዓቃቤ ህግ ፅ/ቤት የተለያዩ ወንጀሎች ምርመራ ክፍል ለብስራት ሬድዮና ቴሌቪዥን በላከው መረጃ ተከሳሽ አስናቀች ወጋየው የተባለች ግለሰብ ልጆቼ በከፍተኛና በወረዳ ፍርድ ቤት ሰራተኛ ናቸው በማለት መረጃ ስትሰጥ ቆይታለች። በዚህም መሰረት አባትህን ከእስር አስፈታልኻለው በማለት 20 ሺ ብር ከአንድ ግለሰብ መቀበሏ ተገልጿል።

በተጨማሪም ጥር 27 ቀን 2016 ዓ.ም 20 ሺህ ብር አይበቃም በማለት ተጨማሪ 10 ሺህ ብር በመቀበል በአጠቃላይ 30 ሺህ ከአንድ ግለሰብ መቀበሏን በማስረጃ ተረጋግጧል።

ተከሳሿ በልጆቿ ስም በመጠቀም ማጭበርበሯን ፖሊስ በተገቢው ማስረጃ በማረጋገጥ የምርመራ መዝገቡንም ለዓቃቤህግ ልኳል። ዓቃቤህግም የምርመራ መዝገቡን በመመልከትና አንቀጽ በመጥቀስ ክስ መስርቶባታል።

ክሱን የተመለከተው የጉልሱም ወረዳ ፍርድ ቤትም በፍትህ አካላት ስም የማጭበርበር ድርጊት የፈፀመችው ግለሰብን በ2 ዓመት እስርና በ3 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንድትቀጣ መወሰኑን የጉልሱም ወረዳ ዓቃቤ ህግ ፅ/ቤት ጨምሮ ገልጿል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ጉቦ ሲቀበል ተይዟል የተባለ ዐቃቤ ሕግ ላይ ክስ ተመሰረተ

****

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 27/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ከግለሰብ ጉቦ ሲቀበል ተይዟል የተባለ የፌደራል ዐቃቢ ሕግ ላይ ክስ ተመሰረተ።

የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት ጀነራል ናሆም ጌታቸው በተባለ ዐቃቤ ሕግ ላይ የሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 10 (1) ስር የተመለከተውን በመተላለፍ የተፈፀመ ጉቦ መቀበል የሙስና ወንጀል ክስ መስርቶበታል።

በክሱ ላይ እንደተመላከተው፤ ተከሳሹ በፌደራል ፍትህ ሚኒስቴር ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ በአራዳ ክፍለ ከተማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በዐቃቤ ህግነት ተመድቦ በማገልገል ላይ እያለ የማይገባውን ብልፅግና ለማግኘት በማሰብ የግል ተበዳይ አማኑኤል ገነሜ የተባለ ግለሰብ በወንጀል ተጠርጥሮ እና ክስ ተመስርቶ በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 6ኛ ወንጀል ችሎት ጉዳዩ በመታየት ላይ እያለ ተከሳሽ በስራ ግዴታው ማድረግ የማይገባውን ለማድረግ በማሰብ "ጉዳዩ በቀላሉ እንዲያልቅለትና ቅጣቱ በገንዘብ መቀጮ እንዲሆን አደርጋለሁ" በማለት የ60 ሺህ ብር ጉቦ እንዲከፍል ተበዳይን በመጠየቅ ድርድር ሲያደርግ ቆይቷል።

ድርድር ካደረገ በኋላም በጥር 30 ቀን 2016 ዓ.ም በአራዳ ክፍለ ከተማ ሰሜን ሆቴል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በመገናኘት 40 ሺህ ብር ለመቀበል በመስማማትና ከተስማሙት ገንዘብ ላይ በተከሳሽ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር በቅድሚያ 10 ሺህ ብር ተላልፎለት የተቀበለ በመሆኑ በቀረበበት ክስ ላይ በዝርዝር ሰፍሯል።

ከዚህም በኋላ ደግሞ በየካቲት 12 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 10፡10 አካባቢ በአራዳ ክፍለ ከተማ ሰሜን ሆቴል አካባቢ በሚገኝ ካፌ ውስጥ በመገኘት ብር 10 ሺህ ከግለሰብ ተቀብሎ ሲሄድ እጅ ከፍንጅ የተያዘ መሆኑ ተጠቅሶ ጉቦ በመቀበል የሙስና ወንጀል ተከሷል፡፡ ከክስ ዝርዝሩ ጋር የሰውና የሰነድ ገላጭና አስረጂ ማስረጃዎች መያያዛቸውን ኤፍቢሲ ዘግቧል።

የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት የክሱ ዝርዝር ለተከሳሽ እንዲደርስ በማድረግ ክሱን ለመመልከት ለመጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
የሚዲያ ተቋማት ህፃናትና ወጣቶች በመልካም ሥነምግባር ታንጸው ሙስና እና ብልሹ አሰራርን መከላከል እንዲችሉ ግንዛቤ የመፍጠር ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል!

****************

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
የተለያዩ ማታለያዎችን በመጠቀም ከ300 ሺህ ብር በላይ የወሰደው ተከሳሽ በፅኑ እስራትና በገንዘብ ተቀጣ

****

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 28/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የተለያዩ ማታለያዎችን በመጠቀም ወደ ግል ተበዳዮች ስልክ በመደወል የሚነገራቸውን ቁጥር በመንካት ገንዘብ እንዲያስተላልፉለት በማድረግ ከ300 ሺህ ብር በላይ የወሰደው ተከሳሽ በፅኑ እስራትና በገንዘብ መቀጣቱ ተገልጿል።

በዐቃቤ ሕግ የክስ መዝገብ ላይ ሜጋ ማንዴላ ማለቆ የተባለው ተከሳሽ በተለያዩ 6 ክሶች የተከሰሰ ሲሆን፤ በክሱ ዝርዝርም ተከሳሽ የሌላን ሰው የተሳሳተ እምነት በመጠቀም ካልተያዙ ግብረ-አበሮቹ ጋር በመሆን ከህዳር 22 ቀን 2015 ዓ.ም እስከ የካቲት 4 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ በተለያዩ 6 ቀናት ለተለያዩ ግለሰቦች በተንቀሳቃሽ ስልካቸው ላይ በመደወል ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እንደደወሉ በማስመሰል የተለያዩ ማታለያዎችን በመጠቀም እነሱ የሚነግሯቸውን ቁጥር በስልካቸው እንዲነኩ በማድረግ በ1ኛ ክሱ ላይ 11 ሺህ 10 ብር፣ በ2ኛ ክሱ ላይ 64 ሺህ 900 ብር፣ በ3ኛ ክሱ ላይ 8 ሺህ 300 ብር፣ በ4ኛ ክሱ ላይ 199 ሺህ 400 ብር፣ በ5ኛ ክሱ ላይ 68 ሺህ ብር፣ በ6ኛ ክሱ ላይ 19 ሺህ 600 ብር ከተበዳዮች ሂሳብ ቁጥር ላይ ተቀናሽ ሆኖ ተከሳሽ ሀሰተኛ ስም እና መታወቂያ ተጠቅሞ ወደከፈተው ሂሳብ ቁጥር እንዲያስተላልፉ አድርጓል።

ተከሳሽም የገባውን ብር ከአካውንቱ ላይ ያወጣው በመሆኑ በፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጀኔራል ዐቃቤ ሕግ በ1996 ዓ.ም በወጣው የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32/1/ሀ/ መሰረት በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ልዩ ልዩ ወንጀል ችሎት ተከሳሽ በፈፀመው በኮምፒዩተር አማካኝነት የሚፈፀም የማታለል ወንጀል ክስ ቀርቦበት ክርክር ሲደረግ ቆይቷል፡፡

በክርክሩ ሂደትም የዐቃቤ ሕግ ማስረጃ ከተሰማ በኋላ ተከሳሽ እንዲከላከል ብይን ተሰጥቶ የመከላከያ ምስክር የለኝም በማለቱና በዐቃቤ ሕግ የቀረበበትን ክስ መከላከል ባለመቻሉ ምክንያት ፍርድ ቤቱ በተከሳሽ ላይ የጥፋተኛነት ፍርድ በመስጠትና የቅጣት ውሳኔ በማሳረፍ በ6 ዓመት ከ6 ወር ጽኑ እስራትና በ6 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ መወሰኑን በፍትህ ሚኒስቴር የፌስቡክ ገፅ የተገኘው መረጃ ያስረዳል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡