Federal Ethics And Anti- Corruption Commission
9.93K subscribers
10.3K photos
244 videos
32 files
3.04K links
Download Telegram
ለማዕድን ዘርፍ አመራሮች በሥነምግባራዊ አመራርነት ዙሪያ ስልጠና እየተሰጠ ነው

****************

(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 19/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ለማዕድን ሚኒስቴር እና ለተጠሪ ተቋማት አመራሮች በሥነምግባራዊ አመራርነት ዙሪያ ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡

በስልጠናው ንግግር ያደረጉት የማዕድን ሚኒስቴር ሚኒስትር ሀብታሙ ተገኘ (ኢ/ር) እንደገለፁት በማዕድኑ ሴክተር በሥነምግባር ላይ ያተኮሩ ተግባራትን ለመስራት ስልጠናው ጠቀሜታው የጎላ ነው፡፡ አመራሩም በዚህ ርዕሰ ጉዳይ ላይ ስልጠና መውሰዱ ትልቅ ፋይዳ አለው ብለዋል፡፡

ሚኒስትሩ አክለውም ዘርፉ ለሙስና እና ብልሹ አሰራር ተጋላጭ በመሆኑ ስልጠናው አስፈላጊ መሆኑን ገለፀው፤ በቀጣይም በየደረጃው ላሉ የዘርፉ አመራሮች ተመሳሳይ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልፀዋል፡፡

በፌደራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ስልጠና መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግም አላምረው በበኩላቸው የስልጠናው ዓላማ በማዕድን ዘርፉ ሥነምግባራዊ አመራርን በማጎልበት ሙስና እና ብልሹ አሰራርን እንዲከላከሉ ያለመ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

ስልጠናው በፌደራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ስልጠና ባለሙያ በአቶ ፍሬሁን መለስ እየተሰጠ ሲሆን፣ በሥነምግባራዊ አመራርነት፣ ሥነምግባር ለአመራሩ ያለው አስፈላጊነት፣ የሥነምግባራዊ አመራርነት ክህሎቶች፣ መርሆዎች እና መገለጫ ባህሪያት ላይ ያተኮረ ነው፡፡

ስልጠናው ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚሰጥ ሲሆን፤ በነገው ዕለትም ሥነምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥና በዘርፉ ሙስና አና ብልሹ አሰራርን ከመከላከል አኳያ የአመራሩ ሚና በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የሚቀጥል ይሆናል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ሀሰተኛ ሊብሬና ታርጋ በማውጣት ከ30 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት ያደረሱ እስከ 25 ዓመት በሚደርስ እስራትና በገንዘብ ተቀጡ

****************

(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 19/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የጉሙሩክ ስርዓት ሳይፈጽሙ ሀሰተኛ የተሽከርካሪ ሊብሬና ታርጋ በማወጣት ከ30 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት ያደረሱ ግለሰቦች እስከ 25 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራትና በገንዘብ ተቀጡ።

የቅጣት ውሳኔውን የወሰነው የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ወንጀል ችሎት ተከሳሾቹ ጥፋተኛ በተባሉባቸው ተደራራቢ ክሶች መነሻ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየት መርምሮ ነው ዛሬ በዋለው የችሎት ቀጠሮ ተከሳሾቹን በጽኑ እስራትና በገንዘብ እንዲቀጡ የወሰነው።

ተከሳሾች የኦሮሚያ ክልል የመንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ሰበታ ቅርጫፍ ሰራተኛ የነበሩት ለሚ በየነ እና ያይላል ንጋቱ እንዲሁም በግል ስራ የሚተዳደሩት መሪማ ጀማል፣ ጌታቸው ንጉሴ እና ቃልኪዳን አሰፋ ናቸው።

የኦሮሚያ ክልል የፍትህ ቢሮ የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾቹ ላይ የተሳትፎ ደረጃ ጠቅሶ ተደራራቢ ክሶችን አቅርቦባቸው ነበር።

ይህም ያቀረበው ክስ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀጽ 32 ንዑስ ቁጥር 1 እና አንቀጽ 33 እና የሙስና አዋጅ 881/2007 አንቀጽ 9 ንዑስ ቁጥር 1 እና 2፣ አንቀጽ 33 እና የጉሙሩክ አዋጅን አንቀጽ 167 ንዑስ ቁጥር 1፣ አንቀጽ 168 ንዑስ ቁጥር 1 እንዲሁም አዋጅ ቁጥር 780/2005 አንቀጽ 29 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) እና ንዑስ ቁጥር 2 (ለ) ስር የተመላከተውን ድንጋጌ ተላልፈዋል የሚል ነበር።

በተለይም 1ኛ እና 2ኛ ተከሳሾች በ2015 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል የመንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ሰበታ ቅርጫፍ ባለሙያነት ሲሰሩ ከ3ኛ እስከ 5ኛ ተራ ቁጥር ከተጠቀሱ ግለሰቦች ጋር በመመሳጠር ከህግና አሰራር ውጪ የጉሙሩክ ስርዓት ያልተፈጸመባቸው በአካል ያልቀረቡ ሶስት ቪ 8 ተሽከርካሪዎች የታርጋ ቁጥር፣ ሊብሬና ቦሎ የተለያዩ የማረጋገጫ ሰነዶች እንዲወጣላቸው ማድረጋቸውን ዐቃቤ ሕግ በክሱ አመላክቷል።

ጌታቸው ንጉሴና ቃልኪዳን አሰፋ የተባሉ ተከሳሾች ደግሞ የጉሙሩክ ስርዓት ያልተፈጸሙባቸው፣ ከሰበታ ቅርንጫፍ የመንገድ ትራንስፖርት ቢሮ በህገወጥ መንገድ የወሰዱትን የተሽከርካሪ የማረጋገጫ ሰነዶችን ለባንክ በማቅረብ 26 ሚሊየን ብር ብድር መውሰዳቸው በክሱ ላይ በዝርዝር ሰፍሯል።

በአጠቃላይ በተጠቀሰው መልኩ በተፈጸመ ህገወጥ ተግባር መንግስት ላይ ከ30 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት አድርሰዋል ተብለው በዐቃቤ ሕግ ተደራራቢ ክስ ተመስርቶባቸው ነበር።

ተከሳሾቹ ፍርድ ቤት ቀርበው ክሱ ከደረሳቸውና በንባብ ከተሰማ በኋላ ወንጀሉን አልፈጸምንም በማለት የሰጡትን የዕምነት ክህደት ቃል ተከትሎ ዐቃቤ ሕግ ስድስት የሰው ምስክር ቃልና የተለያዩ የሰነድ ማስረጃዎችን ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል።

ፍርድ ቤቱም የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን መርምሮ ተከሳሾቹ በተከሰሱባቸው ድንጋጌዎች እንዲከላከሉ ብይን የሰጠ ቢሆንም ተከሳሾቹ የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢ መንገድ መከላከል ባለመቻላቸው ተከላከሉ በተባሉበት ድንጋጌ የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎባቸዋል።

ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየትን ከግምት ውስጥ በማስገባት ተከሳሾቹን በጽኑ እስራትና በገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ መወሰኑን ኤፍቢሲ ዘግቧል።

በዚህም የኦሮሚያ ክልል የመንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ሰበታ ቅርጫፍ ሰራተኛ የነበሩት 1ኛ ተከሳሽ ለሚ በየነን በ23 ዓመት ከ6 ወራት ጽኑ እስራትና በ225 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ የተወሰነ ሲሆን፥ 2ኛ ተከሳሽ ያይላል ንጋቱን ደግሞ በ18 ዓመት ጽኑ እስራትና በ3 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ተወስኗል።

በግል ስራ የሚተዳደሩት 3ኛ ተከሳሽ መሪማ ጀማልን በሚመለከት በ22 ዓመት ከ6 ወራት ጽኑ እስራትና 335 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ የወሰነው ፍርድ ቤቱ፥ 4ኛ ተከሳሽ ጌታቸው ንጉሴ ደግሞ በ25 ዓመት ጽኑ እስራትና በ175 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል።

ፍርድ ቤቱ 7ኛ ተከሳሽ ቃልኪዳን አሰፋን በሚመለከት በ12 ዓመት ጽኑ እስራትና በ60 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል።

ከተከሳሾች ላይ የተያዙ ተሽከርካሪዎች ለመንግስት ገቢ እንዲሆኑ ትዕዛዝ ተሰጥቷል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
መልካም ሥነምግባርን የተላበሰ አመራር ሙስና እና ብልሹ አሰራርን በመከላከል ለሀገር እድገት የሚኖረው ሚና የጎላ ነው!

****************

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ከ1 ሺህ ግራም በላይ ወርቅ በህገ-ወጥ መንገድ ይዞ ተገኝቷል በተባለ ግለሰብ ላይ ክስ ተመሰረተ

****

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 20/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ከ 3 ሚሊየን ብር በላይ ዋጋ ያለው 1 ሺህ 10 ነጥብ 95 ግራም ወርቅ በህገ-ወጥ መንገድ ይዞ ተገኝቷል በተባለ ግለሰብ ላይ ክስ ተመሰረተ።

ክሱ የተመሰረተው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።

የፍትሕ ሚኒስቴር የኢኮኖሚ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጀነራል ዐቃቤ ሕግ በተከሳሹ አማረ ዮሐንስ ተ/ጊዮርጊስ ላይ ሁለት ክሶችን መስርቷል።

አንደኛው ክስ የሙስና አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 21 ንዑስ ቁጥር 2 ስር የተመላከተውን ድንጋጌ በመተላለፍ ተከሳሹ የካቲት 4 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:40 ላይ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የሀገር ውስጥ በረራ አካባቢ በተደረገ ፍተሻ በለበሰው ጃኬት ውስጥ 3 ሚሊየን 189 ሺህ 506 ብር ከ32 ሳንቲም የሚገመት 1 ሺህ 10 ነጥብ 95 ግራም የሚመዝን ጥፍጥፍ ወርቅ ይዞ ተገኝቷል የሚል ነው፡፡

በተያዘበት ጊዜም ፈቃድ እንደሌለውና ነጋዴ እንዳልሆነ ገልጾ በወቅቱ ለነበረው ፖሊስ አዛዥ ከያዘው ወርቅ ላይ ግማሹን "ልስጥህና ልቀቀኝ" በማለት ጉቦ ያቀረበ መሆኑን ዐቃቤ ህግ ጠቅሶ ተገቢ ያልሆነ ጉቦ ወይም ጥቅም መስጠት የሙስና ወንጀል ክስ ማቅረቡን ኤፍቢሲ ዘግቧል።

እንዲሁም ሁለተኛው ክስ የማዕድን አዋጅ ቁጥር 678/2002 አንቀጽ 7 ንዑስ ቁጥር 2 ስር እና አንቀጽ 78 ንዑስ 2 ስር የተመላከተውን ድንጋጌ መተላለፍ የፀና ፈቃድ ሳይኖረው የተፈጥሮ ማዕድን መያዝ የሚል ነው፡፡

ተከሳሹ ችሎት ቀርቦ የክስ ዝርዝሩ እንዲደርሰው ከተደረገ በኋላ ከጠበቃ ጋር ተማክሮ እንዲቀርብ በይደር ተቀጥሯል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ለውጭ ጉዳይ ዘርፍ አመራሮች በሥነምግባራዊ አመራርነት ዙሪያ ስልጠና እየተሰጠ ነው

****************

(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 20/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ለተጠሪ ተቋማት አመራሮች በሥነምግባራዊ አመራርነት ዙሪያ ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡

በስልጠናው ንግግር ያደረጉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፅህፈት ቤት ኃላፊ አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን (ዶ/ር) እንዳሉት የስልጠናው አላማ የአመራሮችን የሞራል ብቃት ማሳደግ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ወዶ አጦ በበኩላቸው ኮሚሽኑ ከተለያዩ ተቋማት ጋር የተቀናጀ የሙስና መከላከል ስትራቴጂን በተቋማት ተግባራዊ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልፀው፣ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን መከላከል የሁላችንም ኃላፊነት ነው ብለዋል።

ስልጠናው በፌደራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ስልጠና መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግም አላምረው እየተሰጠ ሲሆን፣ በሥነምግባራዊ አመራርነት፣ ሥነምግባር ለአመራሩ ያለው አስፈላጊነት፣ የሥነምግባራዊ አመራርነት ክህሎቶች፣ መርሆዎች እና መገለጫ ባህሪያት ላይ ያተኮረ ነው፡፡

ስልጠናው ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚሰጥ ሲሆን፤ በነገው ዕለትም ሥነምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥና በዘርፉ ሙስና አና ብልሹ አሰራርን ከመከላከል አኳያ የአመራሩ ሚና በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የሚቀጥል ይሆናል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ከ10 ሚሊየን ብር በላይ ምንጩን ደብቆ ለሌሎች ግለሰቦች አስተላልፏል የተባለው ተከሳሽ በ13 ዓመት እስራት ተቀጣ

****

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 21/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ከባንክ ደንበኞች ሂሳብ ተቀንሶ ገቢ የተደረገለትን ከ10 ሚሊየን ብር በላይ ገንዘብ ምንጩን ደብቆ ለሌሎች ግለሰቦች አስተላልፏል የተባለው ተከሳሽ በ13 ዓመት ጽኑ እስራትና በገንዘብ ተቀጣ።

የቅጣት ውሳኔውን የወሰነው የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ወንጀል ችሎት ነው።

የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ጀነራል ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ ጌትነት አማረ በተባለው ተከሳሽ ላይ የሙስና አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 9 ንዑስ ቁጥር 1 (ለ) እና ንዑስ ቁጥር 2 የተመለከተውን ድንጋጌ በመተላለፍ እና በህገወጥ መንገድ የተገኘ ንብረትን ወይም ገንዘብን ምንጩን በመደበቅ ህጋዊ አድርጎ ማቅረብ አዋጅ ቁጥር 780/2005 አንቀጽ 29 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) ስር የተመላከተውን ድንጋጌ ተላልፏል የሚል ክስ አቅርቦበት ነበር።

በዚህ ክስ ዝርዝር ላይ እንደተመላከተው፤ በዚሁ መዝገብ ቀደም ብሎ ጉዳያቸው ታይቶ ቅጣት ውሳኔ የተላለፈባቸው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሞጣ ቀራንዮ ቅርጫፍ የባንኩ ሰራተኞች በነበሩ ሁለት ግለሰቦች አማካኝነት በርሔ ወልዴና ሸዊት አለማየሁ ከተባሉ የባንኩ ደንበኞች ፍቃድ ውጪ የአሰራርና መመሪያን በመተላለፍ በተለያዩ ቀናቶች 10 ሚሊየን 400 ሺህ ብር በመቀነስና በማጽደቅ ተሳትፎ በጥቅምት 26 ቀን በ2015 ዓ.ም በአዳማ ዲስትሪክት ሃዩ ቅርጫፍ በሀሰተኛ ማንነትና የነዋሪነት መታወቂያ በተከሳሹ ስም በተከፈተ ሂሳብ ገቢ እንዲሆን መደረጉ ተጠቅሷል።

ተከሳሹ ደግሞ ጥቅምት 17 ቀን 2015 ዓ.ም ከለሚ ኩራ ክ/ከ ወረዳ 8 በሀሰተኛ ማንነት ባወጣው ሀሰተኛ የነዋሪነት መታወቂያ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዳማ ዲስትሪክት ሃዩ ቅርጫፍ በከፈተው ሂሳብ ውስጥ ገቢ የተደረገለትን 10 ሚሊየን 400 ሺህ ብር ወደ ተለያዩ ግለሰቦች ሂሳብ ማስተላለፉ በክሱ ላይ ተመላክቷል።

ተከሳሹ በቀረበበት ክስ ዝርዝር ላይ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት አለመፈጸሙን ጠቅሶ የሰጠውን የዕምነት ክህደት ቃል ተከትሎ ዐቃቤ ሕግ የሰውና የሰነድ ማስረጃ አቅርቧል።

የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን የመረመረው ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ በተከሰሰበት ድንጋጌ እንዲከላከል ብይን የሰጠ ቢሆንም የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን መከላከል ባለመቻሉ የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎበታል።

ፍርድ ቤቱ በቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 2/2006 አንቀጽ 29 ንዑስ ቁጥር 3 መሰረት የወንጀል አፈጻጸምና የደረሰውን ጉዳት ከግንዛቤ በማስገባት፣ ተከሳሹ ከለሚ ኩራ ክ/ከ ወረዳ 8 በሀሰተኛ ማንነት የነዋሪነት መታወቂያ በመውሰድ በአዳማ ሃዩ ቅርጫፍ የባንክ ሂሳብ በመክፈት 10 ሚሊዮን 400 ሺህ ብር ገቢ የተደረገለትና ገንዘቡን ወደተለያዩ ግለሰቦች ያስተላለፈ መሆኑን በመገንዘብ የወንጀል ደረጃውን መካከለኛ የወንጀል ደረጃ በመመደብ ተከሳሹ ያቀረበው የተለያዩ የቅጣት ማቅለያ አስተያየቶች በመያዝ ከሌላ የወንጀል ድርጊት እንዲቆጠብ ለማስተማር በሚል በሁለቱም ክስ በ13 ዓመት ጽኑ እስራት እና በዕርከን 8 መሰረት በ20 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ወስኗል።

የአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት ተከሳሹ እጁ ከተያዘበት ከታህሳስ 25 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ታሳቢ በማድረግ የተወሰነበትን የእስራት ቅጣት እንዲያስፈጽም መታዘዙን ኤፍቢሲ ዘግቧል ።

ተከሳሹ የተጣለበትን የገንዘብ ቅጣት ለመንግስት ገቢ እንዲያደርግ የፍትህ ሚኒስቴር ተከታትሎ እንዲያስፈጽም ትዕዛዝ ተሰጥቷል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡