Federal Ethics And Anti- Corruption Commission
9.92K subscribers
10.3K photos
244 videos
32 files
3.04K links
Download Telegram
ሌብነትና ብልሹ አሰራርን በማስወገድ ረገድ በቀጣይ ትኩረት ሰጥተን መስራት እንዳለብን ተስማምተናል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

****************

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 14/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ሌብነትና ብልሹ አሰራርን በማስወገድ ረገድ በቀጣይ ትኩረት ሰጥተን መስራት እንዳለብን ተስማምተናል ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ከከተማ እስከ ወረዳ ካሉ አመራሮቻችን ጋር ስናደርግ የነበረው የስራ አፈጻጸም ግምገማችንን ትላንት ምሽት አጠናቅቀናል ብለዋል።

አመራራችን ተቀናጅቶ ያሳካቸው ስራዎች መልካም ቢሆንም በቀሪ ወራት ከህዝብ ችግር እና ጥያቄ አንፃር ለመረጠን ህዝብ የምንሰጠውን አገልግሎት ለማሻሻል በሰው ሃይል እና በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን በፍጥነት ማጠናቀቅ እንዲሁም ሌብነትና ብልሹ አሰራርን በማስወገድ ረገድ በቀጣይ ትኩረት ሰጥተን መስራት እንዳለብን ተስማምተናል ብለዋል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
በሙስና ወንጀል ክስ ከቀረበባቸው መዝገቦች መካከል ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ የመንግስትና የህዝብ ሀብት ማስመለስ መቻሉን ቢሮው ገለፀ

****

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 14/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) በሙስና ወንጀል ክስ ከቀረበባቸው መዝገቦች መካከል ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ የመንግስትና የህዝብ ሀብት ማስመለስ መቻሉን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ በቡታጅራ ከተማ ባካሄደው የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ ላይ አስታውቋል።

በመድረኩ ላይ የቀረበው የሴክተሩ ሪፖርት እንደሚያሳየው የሙስና ወንጀል መዝገቦች ለዐቃቤ ህግ የቀረቡ ሲሆን፥ ከነዚህ ውስጥ 4, 820 የሚሆኑት ውሳኔ ተሰጥቶባቸዋል።

በሙስና ወንጀል ክስ ከቀረበባቸው መዝገቦች መካከል ከ11 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ የተመዘበረ ሀብት የተገኘ ሲሆን፥ ከዚህ ውስጥ 6 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር የሚሆነውን ገንዘብ ማስመለስ መቻሉ ተገልጿል።

በሌላ በኩልም በክልሉ በተጭበረበረ ታክስ ለመንግሥት መመለስና ገቢ መደረግ ከነበረበት ህገ ወጥ ንብረት መካከል ግምቱ 21 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር ውስጥ 15 ነጥብ 6 የሚጠጋውንም በድርድር እንዲመለስ መደረጉን ከክልሉ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ የማህበራዊ ትስስር ገፅ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ቤተሰብ የልጆች ስብዕና መሠረት ነው!

****************

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
የሀረሪ ፖሊስ ኮሚሽን የዲሲፕሊን ግድፈት በተገኘባቸው 81 አመራሮችና አባላት ላይ እርምጃ ወሰደ

****************

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 15/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የሀረሪ ፖሊስ ኮሚሽን የዲሲፕሊን ግድፈት በተገኘባቸው 81 የፖሊስ አመራሮችና አባላት ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ።

የህግ የበላይነት ሳይሸራረፍ ፍትህ ለማስፈን እየተሰሩ ያሉ ተግባራትን አጠናክሮ ለማስቀጠል ኮሚሽኑ ለ15 ቀናት የአመራርና የአባላት ግምገማ ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡

የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ነስሪ ዘከሪያ እንደገለፁት በመድረኩ በፖሊስ አመራርና አባላት ላይ በሚታዩ የሥነ-ምግባርና የአገልግሎት አሰጣጥ ክፍተቶች ምክንያት ሁሉም አመራርና አባላት በግምገማው እንዲያልፉ ተደርጓል።

በዚህ ሂደትም በመንግስትና በህዝብ የተሰጣቸውን የስራ ኃላፊነት ተጠቅመው ህብረተሰቡን ከማገልገል ይልቅ ለግል ጥቅማቸው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ አመራሮችና አባላት ላይ በጥፋታቸው ልክ የዲሲፕሊን እርምጃ መወሰዱን አስታውቀዋል፡፡

በዚህም የስራ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ያልተወጡ አመራሮች ከቦታቸው እንዲነሱ መደረጉን ጠቅሰው፤ በተደረገው ግምገማ 51 የፖሊስ አባላት እርምጃ እንደተወሰደባቸው ተናግረዋል፡፡

ከነዚህ ውስጥ 17 በህግ እንዲጠየቁ፣ 15 አባላት ለ1 ወር ከስራና ደመወዝ እንዲታገዱ፣ 8 አባላት ለ2 ወር ከስራና ደመወዝ እንዲታገዱ፣ 7 የፖሊስ አባላት ደግሞ ለ1 እና 2 ወር ከስራና ደመወዝ ታግደው ከማዕረግ ዝቅ በማድረግ ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ መደረጉን ኮሚሽነሩ ጨምረው ገልፀዋል።

በግምገማው ችግሮችን በመለየትና የመፍትሔ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ በዘርፉ የተጀመረውን የሪፎርም ስራ ከማሳካት ባሻገር በአገልግሎት አሰጣጥ የህብረተሰቡን እርካታ ለማሳደግ እንደሚሰራ መጠቆማቸውን የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
በመሬት ልማት እና አስተዳደር ላይ የሚታየውን ሌብነትና ብልሹ አሰራር ለማስተካከል የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታወቁ

****************

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 16/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ጉባኤውን በዓድዋ ድል መታሰቢያ የምክር ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ አካሄዷል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የከተማ አስተዳደሩን የ2016 የ6 ወራት እቅድ አፈፃፀም ለምክር ቤቱ በዝርዝር አቅርበዋል፡፡

በመሬት አገልግሎት ላይ የሚታየውን ሌብነት እና ብልሹ አሰራር ለማስተካከል በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ከንቲባዋ አስታውቀዋል፡፡

በለሚ ኩራ እና በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የመሬት ይዞታ ማህደር ኦዲት የማድረግ ስራ መከናወኑን የገለጹት ከንቲባዋ፥ በኦዲት ውጤቱ መሰረት ዝርዝር መረጃ ተጠናክሮ ለሚመለከተው አካልና ለፀረ-ሙስና ኮሚሽን መተላለፉን አብራርተዋል፡፡

በተቋሙ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ የተጀመረው ስራ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡

በዘርፉ የሚታየውን ብልሹ አሰራር እና ችግር ከመሰረቱ ለመፍታት በተቋሙ ያለው የሰው ኃይል አስተዳደር ብልሹ አሰራርን ለመከላከል እንዲያስችል የሰራተኛ አስተዳደር ደንብ ፀድቆ ወደ ጠንካራ ሪፎርም መገባቱን ጠቁመዋል፡፡

ለመልካም አስተዳደር እና ለብልሹ አሰራር ችግር ምክንያት ሊሆኑ የሚችሉ 14 የመሬት ደንቦችና መመርያዎችን ሙሉ በሙሉ የማሻሻል ስራ ተሰርቷልም ብለዋል፡፡

በተጨማሪም ከዚህ ቀደም ተበታትነው የነበሩ መመርያዎችና ሰርኩላሮችን በማጠቃለልና በማደራጀት ወደ ሁለት ደንብ መጠቃለሉን አንስተዋል፡፡

በተቋሙ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ወደ ቴክኖሎጂ ለማሸጋገር የሚያስችል መሰረት መጣሉንም ከንቲባዋ ማብራራታቸውን አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ዘግቧል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
6 ሺ ብር ከግለሰቦች አካዉንት ወደ ራሱ አካዉንት ያዘዋወረ የዩንቨርሲቲ ተማሪ በ4 ዓመት ከ8 ወር በእስር እንዲቀጣ መወሰኑ ተገለፀ

****************

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 16/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወልቂጤ ቅርንጫፍ ከሁለት የግል ተበዳዮች አካዉንት ወደ እራሱ አካዉንት ገንዘብ አዘዋዉሯል የተባለ የወልቂጤ ዩንቨርሲቲ የ3ኛ አመት ተማሪ በተመሰረተበት የማታለል የወንጀል ክስ በ4 ዓመት ከ8 ወር እስራት እንዲቀጣ የተወሰነበት መሆኑን ፖሊስ ገልጿል።

በወልቂጤ ዩንቨርሲቲ የ3ኛ ዓመት ተማሪ የሆነዉ የ23 ዓመቱ ወጣት ዘነበ መኮንን አባቡ በ2016 ዓ.ም በተለያየ ቀንና ሰአት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወልቂጤና በኩር ሁለት የባንኩ ቅርንጫፎች ቀርቦ ከግል አካዉንቱ ወደሌላ ሰዉ አካዉንት ገንዘብ ለማስተላለፍ ወደ ባንክ መምጣቱን ለባንክ ሰራተኞች በመንገር መንገደኛ መሆኑና የተሳፈረበት ተሽከርካሪ ጥሎት ሊሄደ ጉዞ መጀመሩንና መቸኮሉን በመግለፅ አስቀድሞ ያዘጋጀዉን ገንዘብ ማስተላለፊያ ቅፅ ለባንክ ሰራተኞች በአደራ በመስጠት ገንዘቡን አስተላልፉልኝ ሲል የባንኩን ሰራተኞች ትብብር እየጠየቀ ከሁለቱም ባንኮች እየተጣደፈ ወጥቶ መሄዱ ተገልጿል።

ተከሳሹ ከአካዉንቴ ወደ ሌላ ሰዉ አካዉንት ገንዘብ አስተላልፉልኝ ሲል ለባንክ ሰራተኞች በቃል ይናገር እንጂ ቀደም ሲል ያዘጋጀዉ የገንዘብ ማስተላለፊያ ቅፁ ላይ በፅሁፍ ያሰፈረዉ መረጃ ከሌሎች ሁለት የግል ተበዳዮች አካዉንት ወደ እራሱ አካዉንት ገንዘብ ለማስተላለፍ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።

በዚህም ከሁለት የግል ተበዳዮች አካዉንት 6,000 (ስድስት ሺህ) ብር ወደ እራሱ አካዉንት ማዘዋወሩን ፖሊስ ገልጿል።

ከግል አካዉንታችን ላይ ከእኛ እዉቅና ገንዘብ ወጪ ተደርጓል በማለት ከግል ተበዳዮች ለባንኩ በቀረበ አቤቱታ መነሻ ግለሰቡ የማታለል ወንጀል መፈፀሙ በመረጋገጡ በዚህም መነሻ በተከሳሹ ላይ ምርመራ ማጣራታቸዉ የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ዋና ሳጂን ስንታየሁ አበበ ተናግረዋል።

የተከሳሹን የክስ መዝገብ የተመለከተዉ የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የግለሰቡ አድራጎት ወንጀል መሆኑ በቀረበለት የሰዉና የሰነድ ማስረጃ በማረጋገጡ በተከሳሹ ላይ የጥፋተኝነት ዉሳኔ ሰጥቷል።

ፍርድ ቤቱ የካቲት 14 ቀን 2016 ዓ.ም ባዋለዉ የወንጀል ችሎት ተከሳሽ ዘነበ መኮንን በ4 ዓመት ከ8 ወር ጽኑ እስራት እንዲቀጣ መወሰኑን ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን የማህበራዊ ትስስር ገፅ የተገኘዉ መረጃ ያስረዳል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡