Federal Ethics And Anti- Corruption Commission
9.92K subscribers
10.3K photos
244 videos
32 files
3.04K links
Download Telegram
ከሕገ-ወጥ የገንዘብ ምንዛሪና ክምችት ጋር በተያያዘ 23 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

****************

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 13/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ከሕገ-ወጥ የገንዘብ ምንዛሪ እና ክምችት ጋር በተያያዘ በአዲስ አበባ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች ባከናወነው ሥራ 23 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፖሊስ አስታወቀ፡፡

ከተጠርጣሪዎቹ በተጨማሪ ከ3 ሚሊየን ብር በላይ እና የተለያዩ ሀገራት ገንዘብ መያዙንም ነው የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ያስታወቀው፡፡

የሀገርን ኢኮኖሚ ለማዳከም የሚፈፀሙ ወንጀሎችን መነሻ በማድረግ በተለይም ሕገ-ወጥ የውጪ ሀገራት ገንዘብ ምንዛሪ በሚከናወንባቸው ቦታዎች እና ገንዘብን ከብሔራዊ ባንክ መመሪያ ውጪ በመኖሪያ ቤታቸው በሚያከማቹ ግለሰቦች ላይ ጥናት ሲያደርግ መቆየቱንም ጠቅሷል፡፡

ጥናቱን እና የሕዝብ ጥቆማን መነሻ በማድረግም 3 ሚሊየን 24 ሺህ 180 ብር፣ 20 ሺህ ሪያል፣ 3ሺህ 758 የአሜሪካ ዶላር እና የተለያዩ ሀገራት ገንዘብ ከብሐየራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ጋር በመተባበር መያዙን አስታውቋል፡፡

በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ጋንዲ ሆስፒታል አካባቢ፣ በወረዳ 2 ሸዋ ዳቦ እና መስቀል ፍላወር አካባቢ እንዲሁም ከሕገ-ወጥ የውጭ ሀገራት ገንዘብ ምንዛሪ ጋር በተያያዘ በጥናቱ በተካተቱ አራት ንግድ ቤቶች ላይ በተደረገ ብርበራ 350 ሺህ ብር፣ 2 ሺህ 803 ዶላር እና 20 ሺህ ሪያል መያዙን ገልጿል፡፡

በተጨማሪም መስቀል ፍላወር አካባቢ በሚገኝ አንድ ፔንሲዮን ውስጥ ብርበራ ሲደረግ በወረቀት ተጠቅልሎ ለሽያጭ የተዘጋጀ አደንዛዥ ዕፅ መገኘቱን ጠቁሟል፡፡

በቦሌ ክፍለ ከተማ እና በጥናት በተለዩ 15 ንግድ ቤቶች ላይ በተደረገ ብርበራ የተያዘው 1 ሚሊየን 305 ሺህ ብር እና የተለያዩ ሀገራት ገንዘብ መሆኑን አብራርቷል፡፡

ፖሊስ ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ጋር በመተባበር ባከናወነው ሥራ ከገንዘብ በተጨማሪ ሐሰተኛ ገንዘብ ለማዘጋጀት በብር መጠን ተቆርጠው የተቀመጡ ወረቀቶች፣ የነዋነት መታወቂያዎች፣ ፓስፖርቶች እና የተለያዩ የባንክ ሠነዶች አግኝቻለው ብሏል፡፡

በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ቀራንዮ የሺ ደበሌ አካባቢ አንድ ግለሰብ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያን በመተላለፍ በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ የተለያዩ ሀገራት ገንዘብ እና ከተፈቀደው መጠን ባላይ ብር ስለማከማቸቱ በደረሰ ጥቆማ ባደረኩት ክትትል በቁጥጥር ስር ውሏል ነው ያለው፡፡

በፍርድ ቤት ትዕዛዝም በተጠርጣሪው መኖሪያ ቤት በተከናወነ ብርበራ 955 ዶላር፣ 2 ሺህ 270 የኤርትራ ናቅፋ እና 300 ሺህ የኢትዮጵያ ብር መገኘቱን ጠቅሷል፡፡

በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 መነን አደባባይ አካባቢ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ በግለሰብ መኖሪያ ቤት በተደረገ ብርበራ 1 ሚሊየን 69 ሺህ 180 ብር ተከማችቶ በመገኘቱ መያዙን ጠቁሟል፡፡

በ23ቱ ተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን ያሳወቀው ፖሊስ÷ ሕገ-ወጥ ተግባር የሚፈፅሙ ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ እና ሕብረተሰቡም ጥቆማውን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በልጆች ሥነምግባር ግንባታ የቤተሰብ ሚና (ክፍል አራት)

***************

የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በበይነመረብ አማካኝነት የትውልድ ሥነምግባር ግንባታ እና የሙስና መከላከል ክህሎት ሥልጠና እንዲሁም የግንዛቤ ማጎልበቻ ፕሮግራም ሥራዎችን እያቀረበ ሲሆን ‹‹ለልጆች የሥነምግባር ግንባታ የቤተሰብ ሚና›› በሚል ርዕስ ክፍል አራት እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ሌብነትና ብልሹ አሰራርን በማስወገድ ረገድ በቀጣይ ትኩረት ሰጥተን መስራት እንዳለብን ተስማምተናል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

****************

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 14/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ሌብነትና ብልሹ አሰራርን በማስወገድ ረገድ በቀጣይ ትኩረት ሰጥተን መስራት እንዳለብን ተስማምተናል ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ከከተማ እስከ ወረዳ ካሉ አመራሮቻችን ጋር ስናደርግ የነበረው የስራ አፈጻጸም ግምገማችንን ትላንት ምሽት አጠናቅቀናል ብለዋል።

አመራራችን ተቀናጅቶ ያሳካቸው ስራዎች መልካም ቢሆንም በቀሪ ወራት ከህዝብ ችግር እና ጥያቄ አንፃር ለመረጠን ህዝብ የምንሰጠውን አገልግሎት ለማሻሻል በሰው ሃይል እና በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን በፍጥነት ማጠናቀቅ እንዲሁም ሌብነትና ብልሹ አሰራርን በማስወገድ ረገድ በቀጣይ ትኩረት ሰጥተን መስራት እንዳለብን ተስማምተናል ብለዋል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
በሙስና ወንጀል ክስ ከቀረበባቸው መዝገቦች መካከል ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ የመንግስትና የህዝብ ሀብት ማስመለስ መቻሉን ቢሮው ገለፀ

****

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 14/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) በሙስና ወንጀል ክስ ከቀረበባቸው መዝገቦች መካከል ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ የመንግስትና የህዝብ ሀብት ማስመለስ መቻሉን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ በቡታጅራ ከተማ ባካሄደው የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ ላይ አስታውቋል።

በመድረኩ ላይ የቀረበው የሴክተሩ ሪፖርት እንደሚያሳየው የሙስና ወንጀል መዝገቦች ለዐቃቤ ህግ የቀረቡ ሲሆን፥ ከነዚህ ውስጥ 4, 820 የሚሆኑት ውሳኔ ተሰጥቶባቸዋል።

በሙስና ወንጀል ክስ ከቀረበባቸው መዝገቦች መካከል ከ11 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ የተመዘበረ ሀብት የተገኘ ሲሆን፥ ከዚህ ውስጥ 6 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር የሚሆነውን ገንዘብ ማስመለስ መቻሉ ተገልጿል።

በሌላ በኩልም በክልሉ በተጭበረበረ ታክስ ለመንግሥት መመለስና ገቢ መደረግ ከነበረበት ህገ ወጥ ንብረት መካከል ግምቱ 21 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር ውስጥ 15 ነጥብ 6 የሚጠጋውንም በድርድር እንዲመለስ መደረጉን ከክልሉ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ የማህበራዊ ትስስር ገፅ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ቤተሰብ የልጆች ስብዕና መሠረት ነው!

****************

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
የሀረሪ ፖሊስ ኮሚሽን የዲሲፕሊን ግድፈት በተገኘባቸው 81 አመራሮችና አባላት ላይ እርምጃ ወሰደ

****************

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 15/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የሀረሪ ፖሊስ ኮሚሽን የዲሲፕሊን ግድፈት በተገኘባቸው 81 የፖሊስ አመራሮችና አባላት ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ።

የህግ የበላይነት ሳይሸራረፍ ፍትህ ለማስፈን እየተሰሩ ያሉ ተግባራትን አጠናክሮ ለማስቀጠል ኮሚሽኑ ለ15 ቀናት የአመራርና የአባላት ግምገማ ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡

የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ነስሪ ዘከሪያ እንደገለፁት በመድረኩ በፖሊስ አመራርና አባላት ላይ በሚታዩ የሥነ-ምግባርና የአገልግሎት አሰጣጥ ክፍተቶች ምክንያት ሁሉም አመራርና አባላት በግምገማው እንዲያልፉ ተደርጓል።

በዚህ ሂደትም በመንግስትና በህዝብ የተሰጣቸውን የስራ ኃላፊነት ተጠቅመው ህብረተሰቡን ከማገልገል ይልቅ ለግል ጥቅማቸው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ አመራሮችና አባላት ላይ በጥፋታቸው ልክ የዲሲፕሊን እርምጃ መወሰዱን አስታውቀዋል፡፡

በዚህም የስራ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ያልተወጡ አመራሮች ከቦታቸው እንዲነሱ መደረጉን ጠቅሰው፤ በተደረገው ግምገማ 51 የፖሊስ አባላት እርምጃ እንደተወሰደባቸው ተናግረዋል፡፡

ከነዚህ ውስጥ 17 በህግ እንዲጠየቁ፣ 15 አባላት ለ1 ወር ከስራና ደመወዝ እንዲታገዱ፣ 8 አባላት ለ2 ወር ከስራና ደመወዝ እንዲታገዱ፣ 7 የፖሊስ አባላት ደግሞ ለ1 እና 2 ወር ከስራና ደመወዝ ታግደው ከማዕረግ ዝቅ በማድረግ ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ መደረጉን ኮሚሽነሩ ጨምረው ገልፀዋል።

በግምገማው ችግሮችን በመለየትና የመፍትሔ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ በዘርፉ የተጀመረውን የሪፎርም ስራ ከማሳካት ባሻገር በአገልግሎት አሰጣጥ የህብረተሰቡን እርካታ ለማሳደግ እንደሚሰራ መጠቆማቸውን የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡