የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ባለሙያዎች ነፃና ገለልተኛ በመሆን የፀረ-ሙስና ህጎች እንዲከበሩ በቁርጠኝነት እንዲሰሩ ተገለፀ
****************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት ዐ9/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአዲስ አበባ ከተማ የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በየደረጃው ለሚገኙ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና አስፈፃሚዎች ለ4 ተከታታይ ቀናት ሲሰጠው የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ።
በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የኮሚሽኑ ም/ኮሚሽነር አሰፋ ቶላ ከማዕከል እስከ ወረዳ ድረስ ያሉ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ባለሙያዎች ነፃና ገለልተኛ በመሆን የፀረ-ሙስና ህጎች እንዲከበሩ በቁርጠኝነት እንዲሰሩ አሳስበዋል።
እያንዳንዱ ስራዎቻችን ትውልድ ግንባታ ላይ ማዕከል ያደረገ መሆን እንደሚገባውና የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና አስፈፃሚዎችም ከተለያዩ ተቋማት ጋር መስራት እንዳለባቸው ም/ኮሚሽነር አሰፋ ቶላ ተናግረዋል። ከሰልጣኞች ከሰው ኃይል ማሟላት፣ ከግብዓትና ሌሎች በተነሱ ጥያቄዎች ላይ ኮሚሽነሩ ሰፋ ያለ ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል።
የኮሚሽኑ ም/ኮሚሽነር አሰግደው ኃ/ጊዮርጊስ በበኩላቸው እንደ ኮሚሽን የውስጥ አቅምን መገንባት ስላለብን ቅድሚያ ለሥነምግባርና ፀረ-ሙስና አስፈፃሚዎች አቅም ሊሆኑ የሚችሉ ስልጠናዎች መሰጠቱ አስፈላጊም፣ ተገቢም ነው ብለዋል።
የኮሚሽኑ ተግባራት ከሆኑት ውስጥ አንዱ ሙስናን መከላከል ስለሆነ ሙስና ሊፈፀምባቸው ይችላሉ ተብለው የሚታሰቡ ጉዳዮችን በጥናት እየለየንና እየዘጋን መሄድ አለብን ሲሉ ም/ኮሚሽነር አሰግደው ተናግረዋል።
አክለውም ሙስና ተፈፅሞበታል ወይም ሙስና ሊፈፀምበት ነው ተብሎ በሚቀርብ ጥቆማ መሰረት በአስቸኳይ ሙስና መከላከል ማስቆም ይኖርብናል ብለዋል።
ስልጠናው በሙስና ተጋላጭነት አሰራር ጥናት፣ ምንነትና አዘገጃጀት፣ በጥቅም ግጭት፣ በሥነምግባር ግንባታና መልካም አስተዳደር በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገ ሲሆን፥ በሴክተር መ/ቤቶች፣ በኮሌጆች፣ በሆስፒታሎች፣ በቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች፣ በክፍለ ከተሞችና በወረዳዎች ላይ የሚገኙ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ክፍል ዳሬክተሮችና ቡድን መሪዎች የስልጠናው ተሳታፊ እንደነበሩ ከኮሚሽኑ የፌስቡክ ገፅ የተገኘው መረጃ ያስረዳል።
በስልጠናው የተሳተፉ ቡድን መሪዎችና ዳይሬክተሮችም ስልጠናው ለቀጣይ ስራዎቻቸው የተሻለ አቅም እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት ዐ9/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአዲስ አበባ ከተማ የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በየደረጃው ለሚገኙ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና አስፈፃሚዎች ለ4 ተከታታይ ቀናት ሲሰጠው የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ።
በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የኮሚሽኑ ም/ኮሚሽነር አሰፋ ቶላ ከማዕከል እስከ ወረዳ ድረስ ያሉ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ባለሙያዎች ነፃና ገለልተኛ በመሆን የፀረ-ሙስና ህጎች እንዲከበሩ በቁርጠኝነት እንዲሰሩ አሳስበዋል።
እያንዳንዱ ስራዎቻችን ትውልድ ግንባታ ላይ ማዕከል ያደረገ መሆን እንደሚገባውና የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና አስፈፃሚዎችም ከተለያዩ ተቋማት ጋር መስራት እንዳለባቸው ም/ኮሚሽነር አሰፋ ቶላ ተናግረዋል። ከሰልጣኞች ከሰው ኃይል ማሟላት፣ ከግብዓትና ሌሎች በተነሱ ጥያቄዎች ላይ ኮሚሽነሩ ሰፋ ያለ ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል።
የኮሚሽኑ ም/ኮሚሽነር አሰግደው ኃ/ጊዮርጊስ በበኩላቸው እንደ ኮሚሽን የውስጥ አቅምን መገንባት ስላለብን ቅድሚያ ለሥነምግባርና ፀረ-ሙስና አስፈፃሚዎች አቅም ሊሆኑ የሚችሉ ስልጠናዎች መሰጠቱ አስፈላጊም፣ ተገቢም ነው ብለዋል።
የኮሚሽኑ ተግባራት ከሆኑት ውስጥ አንዱ ሙስናን መከላከል ስለሆነ ሙስና ሊፈፀምባቸው ይችላሉ ተብለው የሚታሰቡ ጉዳዮችን በጥናት እየለየንና እየዘጋን መሄድ አለብን ሲሉ ም/ኮሚሽነር አሰግደው ተናግረዋል።
አክለውም ሙስና ተፈፅሞበታል ወይም ሙስና ሊፈፀምበት ነው ተብሎ በሚቀርብ ጥቆማ መሰረት በአስቸኳይ ሙስና መከላከል ማስቆም ይኖርብናል ብለዋል።
ስልጠናው በሙስና ተጋላጭነት አሰራር ጥናት፣ ምንነትና አዘገጃጀት፣ በጥቅም ግጭት፣ በሥነምግባር ግንባታና መልካም አስተዳደር በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገ ሲሆን፥ በሴክተር መ/ቤቶች፣ በኮሌጆች፣ በሆስፒታሎች፣ በቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች፣ በክፍለ ከተሞችና በወረዳዎች ላይ የሚገኙ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ክፍል ዳሬክተሮችና ቡድን መሪዎች የስልጠናው ተሳታፊ እንደነበሩ ከኮሚሽኑ የፌስቡክ ገፅ የተገኘው መረጃ ያስረዳል።
በስልጠናው የተሳተፉ ቡድን መሪዎችና ዳይሬክተሮችም ስልጠናው ለቀጣይ ስራዎቻቸው የተሻለ አቅም እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዶናልድ ትራምፕ በማጭበርበር ክስ ለኒውዮርክ ግዛት 355 ሚሊዮን ዶላር እንዲከፍሉ ተወሰነ
****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 10/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በማጭበርበር ክስ ለኒውዮርክ ግዛት 355 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ እንዲከፍሉ መወሰኑ ተገልጿል።
ትራምፕ ያላቸውን ንብረት በተመለከተ ለባንኮች ሐሰተኛ መረጃዎችን ሰጥተዋል የሚለውን ጨምሮ ሌሎች ክሶች ቀርበውባቸው ነበር።
ብያኔውን ያስተላለፉት ዳኛ አርተር ኢንጎሮን ከገንዘብ ቅጣቱ በተጨማሪም ትራምፕም ሆነ ድርጅታቸው ለሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት በኒውዮርክ ከሚገኙ የፋይናንስ ተቋማት ብድር እንዳይጠይቁ እንዲሁም በኒውዮርክ በሚገኙ ኩባንያወቻቸው ዳይሬክተር ሆነው እንዳያገለግሉም እግድ አስተላልፈውባቸዋል።
ከሳቸው በተጨማሪም ሁለቱ ልጆቻቸው ኤሪክ ትራምፕ እና ዶናልድ ትራምፕ ጁኒየር በኒውዮርክ በሚገኙ በትራምፕ ድርጅቶች ላይ በሥራ ኃላፊነት እንዳይቀመጡም እግድ ተጥሎባቸዋል።
ትራምፕ ከቀረቡባቸው ክሶች መካከል ተደጋጋሚ ማጭበርበሮች፣ ሐሰተኛ የንግድ መዝገቦችን በማቅረብ፣ ሀሰተኛ የፋይናንስ ሪፖርቶችን በማቅረብ እና የኢንሹራንስ ማጭበርበር ክሶች ይገኙባቸዋል።
በተጨማሪም ትራምፕ እና ኩባንያቸው ለባንኮች እና ኢንሹራንስ ላይ ባቀረቡት ሪፖርት ላይ የትራምፕ ንብረት ላይ ከፍተኛ የዋጋ ግሽበትን ያካተተ ተመን አቅርበዋል የሚልም ተካቶበታል።
በኒውዮርክ ሪል ስቴት ዘርፍ ከፍተኛ ሀብት ያፈሩት ትራምፕ በበኩላቸው በብያኔው ላይ ይግባኝ እንደሚጠይቁም መናገራቸውን ቢቢሲን ዋቢ አድርጎ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 10/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በማጭበርበር ክስ ለኒውዮርክ ግዛት 355 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ እንዲከፍሉ መወሰኑ ተገልጿል።
ትራምፕ ያላቸውን ንብረት በተመለከተ ለባንኮች ሐሰተኛ መረጃዎችን ሰጥተዋል የሚለውን ጨምሮ ሌሎች ክሶች ቀርበውባቸው ነበር።
ብያኔውን ያስተላለፉት ዳኛ አርተር ኢንጎሮን ከገንዘብ ቅጣቱ በተጨማሪም ትራምፕም ሆነ ድርጅታቸው ለሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት በኒውዮርክ ከሚገኙ የፋይናንስ ተቋማት ብድር እንዳይጠይቁ እንዲሁም በኒውዮርክ በሚገኙ ኩባንያወቻቸው ዳይሬክተር ሆነው እንዳያገለግሉም እግድ አስተላልፈውባቸዋል።
ከሳቸው በተጨማሪም ሁለቱ ልጆቻቸው ኤሪክ ትራምፕ እና ዶናልድ ትራምፕ ጁኒየር በኒውዮርክ በሚገኙ በትራምፕ ድርጅቶች ላይ በሥራ ኃላፊነት እንዳይቀመጡም እግድ ተጥሎባቸዋል።
ትራምፕ ከቀረቡባቸው ክሶች መካከል ተደጋጋሚ ማጭበርበሮች፣ ሐሰተኛ የንግድ መዝገቦችን በማቅረብ፣ ሀሰተኛ የፋይናንስ ሪፖርቶችን በማቅረብ እና የኢንሹራንስ ማጭበርበር ክሶች ይገኙባቸዋል።
በተጨማሪም ትራምፕ እና ኩባንያቸው ለባንኮች እና ኢንሹራንስ ላይ ባቀረቡት ሪፖርት ላይ የትራምፕ ንብረት ላይ ከፍተኛ የዋጋ ግሽበትን ያካተተ ተመን አቅርበዋል የሚልም ተካቶበታል።
በኒውዮርክ ሪል ስቴት ዘርፍ ከፍተኛ ሀብት ያፈሩት ትራምፕ በበኩላቸው በብያኔው ላይ ይግባኝ እንደሚጠይቁም መናገራቸውን ቢቢሲን ዋቢ አድርጎ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ሲቪል ማህበራት የፀረ-ሙስና ትግሉ አጋር መሆን ይጠበቅባቸዋል!
****************
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****************
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡