መልካም ሥነምግባር ያለውና ሙስናን የሚፀየፍ ማህበረሰብ ለመፍጠር የሃይማኖት አባቶች በማስተማርም ሆነ በግል ህይወታቸው አርአያ መሆን እንዳለባቸው ተገለፀ
****************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 28/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ ) የአዲስ አበባ የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከሃይማኖት አባቶችና መምህራን ጋር በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ በሚስተዋሉ ችግሮችና መፍትሔዎቻቸው ላይ የምክክር መድረክ አካሂዷል።
በምክክር መድረኩ ላይ የአዲስ አበባ የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀማል ረዲ እንደገለፁት ሀገራችን ኢትዮጵያ የአማኞች ሀገር በመሆኗ የሃይማኖት ተቋማት፣ አባቶችና መምህራን የሚያስተምሩት አስተምህሮ ታማኝነትን፣ ርህራሄን፣ ትዕግስትን፣ አብሮነትን፣ ደግነትን እና ይቅርታን የተላበሰ መሆን አለበት ብለዋል።
የሙስና እና ብልሹ አሰራር ችግሮች መነሻቸው የአስተሳሰብ ጉደለት ነው ያሉት ኮሚሽነሩ፥ የሃይማኖት አባቶች እሴቶች ለማስረፅ ጠንካራ ስራ መስራት እንዳለባቸው ገልጸዋል።
የኮሚሽኑ ም/ኮሚሽነር አሰፋ ቶላ በበኩላቸው የሃይማኖት ተቋማት ማህበራዊ ትስስርን፣ አብሮነትንና በጎነትን የሚያጠናክሩ እሴቶችን የሚሰብኩ መሆን እንዳለባቸው ገልፀው፥ ማህበረሰቡ ጠንካራ የሥነምግባር እሴቶች እንዲላበስና ፈታኝ በሆኑ ሁኔታዎች ውስጥ ጭምር ሥነምግባራዊና ከጥላቻ የራቁ ንግግሮችን እንዲያደርጉ እና መልካም ውሳኔዎችን እንዲወስኑ የሚያስችሉ መሆን አለባቸው ብለዋል።
በሥነምግባራቸው ተምሳሌት የሆኑ የሃይማኖት አባቶችና መምህራን በመልካም ባህሪ የታነፀ ትውልድ ለመፍጠር ያላቸው ሚና የላቀ መሆኑን አመላክተዋል።
በውይይቱ ላይ የተሳተፉ የሃይማኖት አባቶችና መምህራን በሥነምግባር የታነፀና ሙስናን የሚፀየፍ ትውልድ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ሚናቸውን እንደሚወጡ ገልፀዋል። አክለውም መንግስት ለሌብነትና ብልሹ አሰራር በር የሚከፍቱ አሰራሮችን ተከታትሎ በማረም እና ተጠያቂነትን በማጠናከር የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
"የሃይማኖት ተቋማት መልካም ባህሪ ያለውና ሙስና የሚፀየፍ ትውልድ ከመገንባት አንፃር ያላቸው ሚና" የሚል የመወያያ ሰነድ በኮሚሽኑ የስልጠና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጀንበሩ ኢርኮ ቀርቦ ውይይት መካሄዱን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 28/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ ) የአዲስ አበባ የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከሃይማኖት አባቶችና መምህራን ጋር በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ በሚስተዋሉ ችግሮችና መፍትሔዎቻቸው ላይ የምክክር መድረክ አካሂዷል።
በምክክር መድረኩ ላይ የአዲስ አበባ የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀማል ረዲ እንደገለፁት ሀገራችን ኢትዮጵያ የአማኞች ሀገር በመሆኗ የሃይማኖት ተቋማት፣ አባቶችና መምህራን የሚያስተምሩት አስተምህሮ ታማኝነትን፣ ርህራሄን፣ ትዕግስትን፣ አብሮነትን፣ ደግነትን እና ይቅርታን የተላበሰ መሆን አለበት ብለዋል።
የሙስና እና ብልሹ አሰራር ችግሮች መነሻቸው የአስተሳሰብ ጉደለት ነው ያሉት ኮሚሽነሩ፥ የሃይማኖት አባቶች እሴቶች ለማስረፅ ጠንካራ ስራ መስራት እንዳለባቸው ገልጸዋል።
የኮሚሽኑ ም/ኮሚሽነር አሰፋ ቶላ በበኩላቸው የሃይማኖት ተቋማት ማህበራዊ ትስስርን፣ አብሮነትንና በጎነትን የሚያጠናክሩ እሴቶችን የሚሰብኩ መሆን እንዳለባቸው ገልፀው፥ ማህበረሰቡ ጠንካራ የሥነምግባር እሴቶች እንዲላበስና ፈታኝ በሆኑ ሁኔታዎች ውስጥ ጭምር ሥነምግባራዊና ከጥላቻ የራቁ ንግግሮችን እንዲያደርጉ እና መልካም ውሳኔዎችን እንዲወስኑ የሚያስችሉ መሆን አለባቸው ብለዋል።
በሥነምግባራቸው ተምሳሌት የሆኑ የሃይማኖት አባቶችና መምህራን በመልካም ባህሪ የታነፀ ትውልድ ለመፍጠር ያላቸው ሚና የላቀ መሆኑን አመላክተዋል።
በውይይቱ ላይ የተሳተፉ የሃይማኖት አባቶችና መምህራን በሥነምግባር የታነፀና ሙስናን የሚፀየፍ ትውልድ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ሚናቸውን እንደሚወጡ ገልፀዋል። አክለውም መንግስት ለሌብነትና ብልሹ አሰራር በር የሚከፍቱ አሰራሮችን ተከታትሎ በማረም እና ተጠያቂነትን በማጠናከር የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
"የሃይማኖት ተቋማት መልካም ባህሪ ያለውና ሙስና የሚፀየፍ ትውልድ ከመገንባት አንፃር ያላቸው ሚና" የሚል የመወያያ ሰነድ በኮሚሽኑ የስልጠና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጀንበሩ ኢርኮ ቀርቦ ውይይት መካሄዱን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡