Federal Ethics And Anti- Corruption Commission
9.9K subscribers
10.4K photos
244 videos
32 files
3.04K links
Download Telegram
ለሚኒስቴር መ/ቤቱና ለተጠሪ ተቋማት አመራሮች ሥነምግባራዊ አመራርን የተመለከተ ስልጠና እየተሰጠ ነው

********

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 27/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ሥነምግባራዊ አመራርን የተመለከተ ስልጠና ቡድን መሪ እና ከዚያ በላይ ለሆኑ ለከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር እና ለተጠሪ ተቋማት አመራሮች እየተሰጠ ነው፡፡

የፌዴራል የሥነ-ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሥነምግባር መከታተያ ስራ አስፈጻሚ ጋር በመተባበር ለመስሪያ ቤቱ እና ለተጠሪ ተቋማት በየደረጃው ለሚገኙ አመራሮች ሥነምግባራዊ አመራርን ለመፍጠር የሚያስችል የአቅም ግንባታ ስልጠና በአለም ገና ከተማ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በምህንድስና የስልጠና ማዕከል እየተሰጠ ይገኛል፡፡

የስልጠናው ዓላማ በዘርፉ ለሚሰሩ ተግባራት ሥነምግባራዊ አመራርን በማጎልበት ከሙስና እና ከብልሹ አሰራር የጸዳ አመራርን እንዲከተሉ የሚያስችል የአቅም ግንባታ ስልጠና ነው፡፡

የስልጠናውን መድረክ በንግግር ያስጀመሩት የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ወንድሙ ሴታ(ኢንጂነር) እንደገለፁት የሥነምግባራዊ አመራር ጽንሰ ሀሳብን በመረዳት እና በተቋማችን ለማስተግበር ዘርፉ ሰፊ ሀብትና አገልገሎት የሚሰጥበት በመሆኑ የተመደበለትን ሀብት ለታለመለት ዓላማ ለማዋል ያለንን ግንዛቤ ለማዳበር ይረዳል ብለዋል፡፡

አያይዘውም በኮንስትራክሽን እና በመሠረተ ልማት ዘርፍ በጣም ብዙ አገልግሎቶች የሚሰጡበት በመሆኑ የህዝባችንን ጥያቄ ለመመለስ፣ የተጣሉብንን ሀላፊነቶች በአግባቡ ለመወጣት፣ በተቋማችን የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት እና የመንግስትን ሀብት ለተገቢው አገልግሎት ለማዋል ስልጠናውን በአግባቡ በመከታተል በተግባር ላይ ማዋል ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

በፌዴራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ስልጠና ክፍል ዴስክ ሀላፊ የሆኑት አቶ አንተነህ ኃይሌ በሥነምግባራዊ አመራር ጽንሰ ሀሳብ፣ አስፈላጊነት፣ ክህሎቶች እና መርሆዎች ላይ ገለጻ ሲያደርጉ እንደተናገሩት በተቋማቶች ሙስናን እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል አመራሮች ትልቁን ድርሻ እንደሚይዝ ገልፀው፥ የከተማና መሠረተ ልማት ዘርፍ ለሀገር እድገትና ልማት ቁልፍ የሆነና ከፍተኛ የሀገር ሀብት የሚፍስበት እንደመሆኑ መጠን ሥነምግባራዊ አመራር ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡

ስራን በእውቀትና በብልሃት መስራት የሚችል፣ ሰራተኛውን ግንባር ቀደም ተሳታፊ የሚያደርግ፣ የሰራተኛውን ችግር የሚያውቅና መፍትሔ የሚሰጥ፣ ውሳኔን በወቅቱ መስጠት የሚችልና ሙስና የሚፈጠርባቸው ቦታዎች ላይ አጥብቆ የሚመራ መሪ ያስፈልጋል ሲሉ ለተሳታፊ አመራሮች መግለፃቸውን ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡