የዜጎችን የፍትህ ፍላጎት በማርካት በፍትህ በሥርዓቱ ላይ ያለውን ዕምነት ማሳደግ እንደሚገባ ተጠቆመ
***************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 23/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፍትሕ ሚኒስቴር ሚኒስትሩ ክቡር ጌዲዮና ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከምክር ቤቱ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ዝርዝር ምላሽ ሰጥተዋል።
የፍትህ ሥርዓቱን ዲጂታላይዝ ለማድረግና በቴክኖሎጂ ለማገዝ ምን ጥረት እየተደረገ ይገኛል፣ ለጠቋሚዎችና ለምስክሮች እየተሰጠ የሚገኝ የህግ ከለላ ምን ደረጃ ላይ ይገኛሉ እና ሌሎችም ጥያቄዎች ከምክር ቤቱ አባላትና ከህግና ፍትህ ቋሚ ኮሚቴ ተነስተዋል፡፡
ከህዝብና ከመንግስት የተመዘበሩና ወደ ሌሎች አገራት የሸሹ ሀብቶችን ለማስመለስ እየተሰሩ ያሉ ሥራዎች ምን ይመስላሉ፣ ባህላዊ የፍትሕ ሥርዓትን ወጥነት ባለው መልኩ ተግባራዊ ለማድረግ ምን ታስቧል፣ ለታራሚዎች የሚሰጥ ምህረት ለብልሹ አሰራር ተጋልጧል፣ በማረሚያ ቤቶች ውስጥ ያለው የመሰረታዊ አገልግሎት አቅርቦት ችግር አለባቸው የሚሉ ጥያቄዎች ቀርበዋል፡፡
ለተነሱ ጥያቄዎች የፍትህ ሚንስትሩ ምላሽ ሰጥተዋል። ዘርፉን በቴክኖሎጂ ከማዘመን አንፃር የሰነዶችን ምዝገባና ማረጋገጥ ፋይሎችን ማደራጀትን ክፍያዎችን የመፈፀም አገልግሎቶች መጀመራቸውን የገለፁት ሚንስትሩ፥ ፋይሎችን የፍትህ ሂደት መከታተያ ዘዴዎች በመበልፀግ ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡
ወደ ውጪ አገራት የአገር ሃብትን ይዘው የሚኮበልሉ ተጠርጣሪዎችን በብዛት የሚኮበሉልባቸውን አገራት በመለየት ከሀገራቱ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የማዕቀፍ ስምምነቶች እየተፈፀሙ ይገኛሉ ያሉ ሲሆን፥ የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስና ደቡብ አፍሪካ እንደሚገኙበት ጠቁመዋል፡፡
የኦዲት ግኝት ያለባቸውን ተቋማት ተጠያቂ ለማድርግ በዘርፉ ዕውቅና እና ልምድ ያለው የሰው ሃይል ዕጥረት መኖሩን የጠቆሙት ሚኒስትሩ፥ ለምስክሮችና ለጠቋሚዎች ከሚሰጥ የህግ ከለላ አንጻር አገራችን የህግ ክፍተት ባይኖርባትም የሃብት ዕጥረት መኖሩ ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ማድረግ አልተቻለም ብለዋል፡፡
የባህላዊ ፍትህ ሥርዓቱን ለመጠቀም ከየክልሎቹ ባህልና ዕሴት ጋር የተስማማ የፍትህ ሥርዓት ረቂቅ ሞዴል ተዘጋጅቶ ከክልሎች ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማጣጠም ወደ ስራ ለመግባት በዝግጅት ላይ እንሚገኝ ለምክር ቤቱ አብራርተዋል፡፡
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ ዕፀገነት መንግስቱ በበኩላቸው የፍትህ ሚኒስቴር ሰዎችን በህገ ወጥ መንገድ በማዘዋወር ለእንግልት በሚዳርጉ ህገ ወጥ ደላሎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ለሌሎች አስተማሪ መሆን ይገባዋል ብለዋል። ለታራሚዎች ምህረት የሚሰጥባቸው ዕድሎችን አሰራሮችን ግልፅ ማድረግ እንደሚገባ የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዋ አሳስበዋል፡፡
የማህበረሰቡን የፍትህ ፍላጎት ለማርካትና በሥርዓቱ ላይ ያለውን ዕምነት ማሳደግ እንደሚገባ የተከበሩ ወ/ሮ ዕፀገነት የጠቆሙ ሲሆን፤ አቅም ለሌላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች የሚሰጠው ነፃ የህግ ድጋፍ አገልግሎትም በስፋት ተደራሽ ሊደረግ እንደሚገባው መግለፃቸውን ከህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የፌስቡክ ገፅ የተገኘው መረጃ ያሳያል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
***************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 23/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፍትሕ ሚኒስቴር ሚኒስትሩ ክቡር ጌዲዮና ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከምክር ቤቱ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ዝርዝር ምላሽ ሰጥተዋል።
የፍትህ ሥርዓቱን ዲጂታላይዝ ለማድረግና በቴክኖሎጂ ለማገዝ ምን ጥረት እየተደረገ ይገኛል፣ ለጠቋሚዎችና ለምስክሮች እየተሰጠ የሚገኝ የህግ ከለላ ምን ደረጃ ላይ ይገኛሉ እና ሌሎችም ጥያቄዎች ከምክር ቤቱ አባላትና ከህግና ፍትህ ቋሚ ኮሚቴ ተነስተዋል፡፡
ከህዝብና ከመንግስት የተመዘበሩና ወደ ሌሎች አገራት የሸሹ ሀብቶችን ለማስመለስ እየተሰሩ ያሉ ሥራዎች ምን ይመስላሉ፣ ባህላዊ የፍትሕ ሥርዓትን ወጥነት ባለው መልኩ ተግባራዊ ለማድረግ ምን ታስቧል፣ ለታራሚዎች የሚሰጥ ምህረት ለብልሹ አሰራር ተጋልጧል፣ በማረሚያ ቤቶች ውስጥ ያለው የመሰረታዊ አገልግሎት አቅርቦት ችግር አለባቸው የሚሉ ጥያቄዎች ቀርበዋል፡፡
ለተነሱ ጥያቄዎች የፍትህ ሚንስትሩ ምላሽ ሰጥተዋል። ዘርፉን በቴክኖሎጂ ከማዘመን አንፃር የሰነዶችን ምዝገባና ማረጋገጥ ፋይሎችን ማደራጀትን ክፍያዎችን የመፈፀም አገልግሎቶች መጀመራቸውን የገለፁት ሚንስትሩ፥ ፋይሎችን የፍትህ ሂደት መከታተያ ዘዴዎች በመበልፀግ ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡
ወደ ውጪ አገራት የአገር ሃብትን ይዘው የሚኮበልሉ ተጠርጣሪዎችን በብዛት የሚኮበሉልባቸውን አገራት በመለየት ከሀገራቱ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የማዕቀፍ ስምምነቶች እየተፈፀሙ ይገኛሉ ያሉ ሲሆን፥ የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስና ደቡብ አፍሪካ እንደሚገኙበት ጠቁመዋል፡፡
የኦዲት ግኝት ያለባቸውን ተቋማት ተጠያቂ ለማድርግ በዘርፉ ዕውቅና እና ልምድ ያለው የሰው ሃይል ዕጥረት መኖሩን የጠቆሙት ሚኒስትሩ፥ ለምስክሮችና ለጠቋሚዎች ከሚሰጥ የህግ ከለላ አንጻር አገራችን የህግ ክፍተት ባይኖርባትም የሃብት ዕጥረት መኖሩ ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ማድረግ አልተቻለም ብለዋል፡፡
የባህላዊ ፍትህ ሥርዓቱን ለመጠቀም ከየክልሎቹ ባህልና ዕሴት ጋር የተስማማ የፍትህ ሥርዓት ረቂቅ ሞዴል ተዘጋጅቶ ከክልሎች ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማጣጠም ወደ ስራ ለመግባት በዝግጅት ላይ እንሚገኝ ለምክር ቤቱ አብራርተዋል፡፡
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ ዕፀገነት መንግስቱ በበኩላቸው የፍትህ ሚኒስቴር ሰዎችን በህገ ወጥ መንገድ በማዘዋወር ለእንግልት በሚዳርጉ ህገ ወጥ ደላሎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ለሌሎች አስተማሪ መሆን ይገባዋል ብለዋል። ለታራሚዎች ምህረት የሚሰጥባቸው ዕድሎችን አሰራሮችን ግልፅ ማድረግ እንደሚገባ የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዋ አሳስበዋል፡፡
የማህበረሰቡን የፍትህ ፍላጎት ለማርካትና በሥርዓቱ ላይ ያለውን ዕምነት ማሳደግ እንደሚገባ የተከበሩ ወ/ሮ ዕፀገነት የጠቆሙ ሲሆን፤ አቅም ለሌላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች የሚሰጠው ነፃ የህግ ድጋፍ አገልግሎትም በስፋት ተደራሽ ሊደረግ እንደሚገባው መግለፃቸውን ከህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የፌስቡክ ገፅ የተገኘው መረጃ ያሳያል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
ከ1 ሚሊዮን ብር በላይና የተለያዩ ሀገራት ገንዘብ በመኖሪያ ቤቱ በህገ ወጥ መንገድ አከማችቶ የተገኘ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ
***************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 23/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ከ1 ሚሊየን ብር በላይና በርካታ ዶላርና የተለያዩ ሀገራት ገንዘብ በመኖሪያ ቤቱ በህገ ወጥ መንገድ አከማችቶ የተገኘ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ማዋሉን አዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር ለመቆጣጠር እያደረገ ያለውን ክትትል አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡
የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ነዋሪነቱ በክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ነዋሪ የሆነ አንድ ግለሰብ በህገ-ወጥ መንገድ ገንዘብ ያከማቸ መሆኑን ባሰባሰበው መረጃ ማረጋገጡን ተከትሎ ከፍርድ ቤት የመበርበሪያ ትእዛዝ በማውጣት በተጠርጣሪው መኖሪያ ቤት ጥር 23 ቀን 2016 ዓ/ም ባደረገው ብርበራ 1ሚሊዮን 199ሺህ 290 ብር ፣ 26ሺህ 405 የአሜሪካ ዶላር ፣ 5ሺህ 100 የካናዳ ዶላር ፣ 34 ሺህ 150 ዮሮ እና 1ሺህ 635 የሳውዲ ሪያል እና 27 ጥይት በኤግዚቢትነት ይዟል፡፡
ህገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያደርሰው ጫና ከፍተኛ በመሆኑ እና ለወንጀል መፈፀም መንስኤ በመሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ ክትትሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡
ህብረተሰቡም በተመሳሳይ የወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦችን በመጠቆም እና መረጃ በመስጠት ለፖሊስ ተባባሪ መሆን እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክቱን አስተላልፏል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
***************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 23/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ከ1 ሚሊየን ብር በላይና በርካታ ዶላርና የተለያዩ ሀገራት ገንዘብ በመኖሪያ ቤቱ በህገ ወጥ መንገድ አከማችቶ የተገኘ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ማዋሉን አዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር ለመቆጣጠር እያደረገ ያለውን ክትትል አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡
የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ነዋሪነቱ በክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ነዋሪ የሆነ አንድ ግለሰብ በህገ-ወጥ መንገድ ገንዘብ ያከማቸ መሆኑን ባሰባሰበው መረጃ ማረጋገጡን ተከትሎ ከፍርድ ቤት የመበርበሪያ ትእዛዝ በማውጣት በተጠርጣሪው መኖሪያ ቤት ጥር 23 ቀን 2016 ዓ/ም ባደረገው ብርበራ 1ሚሊዮን 199ሺህ 290 ብር ፣ 26ሺህ 405 የአሜሪካ ዶላር ፣ 5ሺህ 100 የካናዳ ዶላር ፣ 34 ሺህ 150 ዮሮ እና 1ሺህ 635 የሳውዲ ሪያል እና 27 ጥይት በኤግዚቢትነት ይዟል፡፡
ህገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያደርሰው ጫና ከፍተኛ በመሆኑ እና ለወንጀል መፈፀም መንስኤ በመሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ ክትትሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡
ህብረተሰቡም በተመሳሳይ የወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦችን በመጠቆም እና መረጃ በመስጠት ለፖሊስ ተባባሪ መሆን እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክቱን አስተላልፏል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
ከ30 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት አድርሰዋል በተባሉ ግለሰቦች የጥፋተኝነት ፍርድ ተላለፈ
****************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 24/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የጉምሩክ ሥርዓት ባልተፈፀመባቸው ተሽከርካሪዎች ሐሰተኛ ሊብሬና ታርጋ በማውጣት ከ30 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት አድርሰዋል በተባሉ ግለሰቦች ላይ የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ወንጀል ችሎት የጥፋተኝነት ፍርድ አስተላለፈ።
ተከሳሾቹ የክልሉ የመንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ሰበታ ቅርንጫፍ ሠራተኛ የነበሩት ለሚ በየነ እና ያይላል ንጋቱ እንዲሁም በግል ሥራ የሚተዳደሩት መሪማ ጀማል፣ ጌታቸው ንጉሴ እና ቃልኪዳን አሰፋ ናቸው።
በተከሳሾቹ ላይ የኦሮሚያ ክልል የፍትሕ ቢሮ የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ ተደራራቢ ክሶችን አቅርቦባቸው ነበር።
ክሱም÷ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32 ንዑስ ቁጥር 1 እና አንቀጽ 33 እና የሙስና አዋጅ 881/2007 አንቀጽ 9 ንዑስ ቁጥር 1 እና 2፣ አንቀጽ 33 እና የጉምሩክ አዋጅን አንቀጽ 167 ንዑስ ቁጥር 1፣ አንቀጽ 168 ንዑስ ቁጥር 1 እንዲሁም አዋጅ ቁጥር 780/2005 አንቀጽ 29 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) እና ንዑስ ቁጥር 2 (ለ) ሥር የተመላከተውን ድንጋጌ ተላልፈዋል የሚል ነው።
1ኛና 2ኛ ተከሳሾች በ2015 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል የመንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ሰበታ ቅርንጫፍ ባለሙያነት ሲሠሩ ከ3ኛ እስከ 5ኛ ተራ ቁጥር ከተጠቀሱ ግለሰቦች ጋር በመመሳጠር ከሕግና አሠራር ውጪ የጉምሩክ ሥርዓት ያልተፈጸመባቸው በአካል ባልቀረቡ ሦስት የV8 ተሽከርካሪዎች የታርጋ ቁጥር፣ ሊብሬና ቦሎ የተለያዩ የማረጋገጫ ሠነዶች እንዲወጣላቸው ማድረጋቸውን ዐቃቤ ሕግ በክሱ አመላክቷል።
ጌታቸው ንጉሴና ቃልኪዳን አሰፋ የተባሉ ተከሳሾች ደግሞ የጉምሩክ ሥርዓት ያልተፈጸሙባቸው በተጠቀሱና ከሰበታ ቅርንጫፍ የመንገድ ትራንስፖርት ቢሮ በሕገ ወጥ መንገድ የወሰዱትን የተሽከርካሪ የማረጋገጫ ሠነዶች ለባንክ በማቅረብ 26 ሚሊየን ብር ብድር መውሰዳቸው በክሱ ተጠቅሷል፡፡
ግለሰቦቹ ፈጽመዋል በተባለው ሕገ-ወጥ ተግባር በመንግሥት ላይ ከ30 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት አድርሰዋል ተብለው በዐቃቤ ሕግ ተደራራቢ ክሶች ተመስርቶባቸው ነበር።
ተከሳሾቹ ፍርድ ቤት ቀርበው ክሱ ከደረሳቸውና በንባብ ከተሰማ በኋላ ወንጀሉን አልፈጸምንም በማለት የሰጡትን የዕምነት ክህደት ቃል ተከትሎ ዐቃቤ ሕግ ስድስት የሰው ምስክር ቃልና የተለያየ የሠነድ ማስረጃዎችን ለፍርድ ቤቱ ማቅረቡን ፋና ዘግቧል።
ፍርድ ቤቱም የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን መርምሮ ተከሳሾቹ በተከሰሱባቸው ድንጋጌዎች እንዲከላከሉ ብይን የሰጠ ቢሆንም÷ ተከሳሾቹ የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው መንገድ መከላከል ባለመቻላቸው ተከላከሉ በተባሉበት ድንጋጌ የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎባቸዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 24/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የጉምሩክ ሥርዓት ባልተፈፀመባቸው ተሽከርካሪዎች ሐሰተኛ ሊብሬና ታርጋ በማውጣት ከ30 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት አድርሰዋል በተባሉ ግለሰቦች ላይ የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ወንጀል ችሎት የጥፋተኝነት ፍርድ አስተላለፈ።
ተከሳሾቹ የክልሉ የመንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ሰበታ ቅርንጫፍ ሠራተኛ የነበሩት ለሚ በየነ እና ያይላል ንጋቱ እንዲሁም በግል ሥራ የሚተዳደሩት መሪማ ጀማል፣ ጌታቸው ንጉሴ እና ቃልኪዳን አሰፋ ናቸው።
በተከሳሾቹ ላይ የኦሮሚያ ክልል የፍትሕ ቢሮ የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ ተደራራቢ ክሶችን አቅርቦባቸው ነበር።
ክሱም÷ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32 ንዑስ ቁጥር 1 እና አንቀጽ 33 እና የሙስና አዋጅ 881/2007 አንቀጽ 9 ንዑስ ቁጥር 1 እና 2፣ አንቀጽ 33 እና የጉምሩክ አዋጅን አንቀጽ 167 ንዑስ ቁጥር 1፣ አንቀጽ 168 ንዑስ ቁጥር 1 እንዲሁም አዋጅ ቁጥር 780/2005 አንቀጽ 29 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) እና ንዑስ ቁጥር 2 (ለ) ሥር የተመላከተውን ድንጋጌ ተላልፈዋል የሚል ነው።
1ኛና 2ኛ ተከሳሾች በ2015 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል የመንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ሰበታ ቅርንጫፍ ባለሙያነት ሲሠሩ ከ3ኛ እስከ 5ኛ ተራ ቁጥር ከተጠቀሱ ግለሰቦች ጋር በመመሳጠር ከሕግና አሠራር ውጪ የጉምሩክ ሥርዓት ያልተፈጸመባቸው በአካል ባልቀረቡ ሦስት የV8 ተሽከርካሪዎች የታርጋ ቁጥር፣ ሊብሬና ቦሎ የተለያዩ የማረጋገጫ ሠነዶች እንዲወጣላቸው ማድረጋቸውን ዐቃቤ ሕግ በክሱ አመላክቷል።
ጌታቸው ንጉሴና ቃልኪዳን አሰፋ የተባሉ ተከሳሾች ደግሞ የጉምሩክ ሥርዓት ያልተፈጸሙባቸው በተጠቀሱና ከሰበታ ቅርንጫፍ የመንገድ ትራንስፖርት ቢሮ በሕገ ወጥ መንገድ የወሰዱትን የተሽከርካሪ የማረጋገጫ ሠነዶች ለባንክ በማቅረብ 26 ሚሊየን ብር ብድር መውሰዳቸው በክሱ ተጠቅሷል፡፡
ግለሰቦቹ ፈጽመዋል በተባለው ሕገ-ወጥ ተግባር በመንግሥት ላይ ከ30 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት አድርሰዋል ተብለው በዐቃቤ ሕግ ተደራራቢ ክሶች ተመስርቶባቸው ነበር።
ተከሳሾቹ ፍርድ ቤት ቀርበው ክሱ ከደረሳቸውና በንባብ ከተሰማ በኋላ ወንጀሉን አልፈጸምንም በማለት የሰጡትን የዕምነት ክህደት ቃል ተከትሎ ዐቃቤ ሕግ ስድስት የሰው ምስክር ቃልና የተለያየ የሠነድ ማስረጃዎችን ለፍርድ ቤቱ ማቅረቡን ፋና ዘግቧል።
ፍርድ ቤቱም የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን መርምሮ ተከሳሾቹ በተከሰሱባቸው ድንጋጌዎች እንዲከላከሉ ብይን የሰጠ ቢሆንም÷ ተከሳሾቹ የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው መንገድ መከላከል ባለመቻላቸው ተከላከሉ በተባሉበት ድንጋጌ የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎባቸዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
ከ13 ሺህ በላይ የመንግሥት ሠራተኞች ሃብታቸውን ማስመዝገባቸው ተገለጸ
****************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 24/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአማራ ክልል የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ደብረብርሃን ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሙስናን ለመከላከል በተሠራው ሥራ ከ13 ሺህ በላይ የመንግሥት ሠራተኞች ሃብታቸውን እንዲያስመዘግቡ ማስቻሉን ገልጿል።
የአማራ ክልል መንግሥት ለሙስና ተጋላጭ የኾኑ የሥራ መስኮችን በመለየት የሃብት ምዝገባ እንዲካሄድ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ አሠራሩ ግለጽነት እና ተጠያቂነት እንዲሰፍን ለማስቻል ታሳቢ ተደርጎ የመንግሥት ሠራተኞች የሃብት ምዝገባ እንዲካሄድ በአዋጅ ቁጥር 187/2003 ወሳኔ በማሳለፍ ወደ ሥራ ከገባ ዓመታት ተቆጥረዋል።
በአማራ ክልል የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የደብረብርሃን ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የሃብት ማሳወቅ እና ማስመዝገብ ቡድን መሪ ራሄል ወርቁ የመንግሥት ተሿሚዎች፣ ተመራጮች እና የመንግሥት ሠራተኞች ሃብታቸውን እንዲያስመዘግቡ የወጣዉ አዋጅ ያስገድዳል ብለዋል።
ሃብት እንዲያስመዘግቡ ተጠይቀው ኾን ብለው የማያስመዘግቡ ግለሰቦች ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸው 1 ሺህ ብር በመክፍል ሃብት እንዲያስመዘግቡ አሊያም እንደ ሙስና ተጋላጭነታቸው ክብደት እና ቅለት ታይቶ እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ አዋጁ እንደሚያስገድድም ነው ያስገነዘቡት።
የሃብት ማስመዝገብ ሂደቱ በየሁለት ዓመት ተኩል እንደሚታደስ ያነሱት ቡድን መሪዋ፥ የሙስና ወንጀል ሲፈጸም ዜጎች በስልክ ቁጥር 011 637 59 64 በመደወል አለያም በሰሜን ሸዋ ዞን አሥተዳደር በደብረብርሃን ከተማ ባለው መሥሪያ ቤት በአካል በመገኘት ጥቆማ መስጠት እንደሚቻልም ማሳሰባቸውን አሚኮ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 24/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአማራ ክልል የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ደብረብርሃን ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሙስናን ለመከላከል በተሠራው ሥራ ከ13 ሺህ በላይ የመንግሥት ሠራተኞች ሃብታቸውን እንዲያስመዘግቡ ማስቻሉን ገልጿል።
የአማራ ክልል መንግሥት ለሙስና ተጋላጭ የኾኑ የሥራ መስኮችን በመለየት የሃብት ምዝገባ እንዲካሄድ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ አሠራሩ ግለጽነት እና ተጠያቂነት እንዲሰፍን ለማስቻል ታሳቢ ተደርጎ የመንግሥት ሠራተኞች የሃብት ምዝገባ እንዲካሄድ በአዋጅ ቁጥር 187/2003 ወሳኔ በማሳለፍ ወደ ሥራ ከገባ ዓመታት ተቆጥረዋል።
በአማራ ክልል የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የደብረብርሃን ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የሃብት ማሳወቅ እና ማስመዝገብ ቡድን መሪ ራሄል ወርቁ የመንግሥት ተሿሚዎች፣ ተመራጮች እና የመንግሥት ሠራተኞች ሃብታቸውን እንዲያስመዘግቡ የወጣዉ አዋጅ ያስገድዳል ብለዋል።
ሃብት እንዲያስመዘግቡ ተጠይቀው ኾን ብለው የማያስመዘግቡ ግለሰቦች ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸው 1 ሺህ ብር በመክፍል ሃብት እንዲያስመዘግቡ አሊያም እንደ ሙስና ተጋላጭነታቸው ክብደት እና ቅለት ታይቶ እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ አዋጁ እንደሚያስገድድም ነው ያስገነዘቡት።
የሃብት ማስመዝገብ ሂደቱ በየሁለት ዓመት ተኩል እንደሚታደስ ያነሱት ቡድን መሪዋ፥ የሙስና ወንጀል ሲፈጸም ዜጎች በስልክ ቁጥር 011 637 59 64 በመደወል አለያም በሰሜን ሸዋ ዞን አሥተዳደር በደብረብርሃን ከተማ ባለው መሥሪያ ቤት በአካል በመገኘት ጥቆማ መስጠት እንደሚቻልም ማሳሰባቸውን አሚኮ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.