ማረሚያ ቤት በሚገኝ ግለሰብ ስም ሀሰተኛ ሊብሬና ከዕግድ ነጻ ሰነዶችን በመጠቀም ገንዘብ ተበድረዋል የተባሉ በሙስና ወንጀል ተከሰሱ
***************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 16/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ማረሚያ ቤት በሚገኝ ግለሰብ ስም ሀሰተኛ የቪ8 ተሽከርካሪ ሊብሬና ከዕግድ ነጻ ሰነዶችን በመጠቀም ገንዘብ ተበድረዋል የተባሉ 4 ግለሰቦች በሙስና ወንጀል ተከሰሱ።
ክሱ የተመሰረተው በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 5ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።
ተከሳሾቹ በወንጀል ተግባር ክስ ተመስርቶበት በማረሚያ ቤት የሚገኘው 1ኛ ተከሳሽ ሱራፌል በቀለ ደግፌ፣ 2ኛ ወ/ሮ ራኬብ መንግስቱ፣ 3ኛ ወ/ሮ ቤተልሄም መንግስቱ እና 4ኛ ወ/ሮ ማህሌት በቀለ ይባላሉ።
የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጀነራል ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾቹ ላይ የወንጀል ህግ አንቀጽ 32 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) እና የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 23 ንዑስ ቁጥር 2 (ሀ) እና ንዑስ ቁጥር 3 ስር የተመላከተውን ድንጋጌ ተላልፈዋል በማለት ክስ አቅርቦባቸዋል።
በዚህም ተከሳሾቹ ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ ከአ/አ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ከአዲስ ከተማ ቅርጫፍ ጽ/ቤት በማረሚያ ቤት በሚገኝ ሱራፌል በቀለ በሚባል ግለሰብ ስም የተመዘገበ በማስመሰል የቪ8 ተሽከርካሪ ማረጋገጫ ሊብሬና ከዕግድ ነጻ የሚል የተዘጋጁ ሀሰተኛ ሰነዶችን መጠቀማቸው በክስ ዝርዝሩ ላይ ተመላክቷል።
በዚህ ሀሰተኛ ሰነድ በመጠቀም በ2013 ዓ.ም በፀደቀ የብድር ውል ስምምነት መሰረት ሀርቡ ማይክሮ ፋይናንስ አ/ማ ከሚባል ህዝባዊ ድርጅት በተለያዩ መጠኖች በአጠቃላይ 4 ሚሊየን 575 ሺህ 547 ብር ገንዘብ ተበድረው ጥቅም አግኝተውበት ያልመለሱ መሆኑን ዐቃቤ ሕግ በክሱ ጠቅሶ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን ሀሰተኛ መንግስታዊ ሰነዶችን መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ አቅርቦባቸዋል።
ዐቃቤ ሕግ ገላጭና አስረጂ ያላቸውን የሰነድ ማስረጃዎችን የክስ ዝርዝሩ ላይ ጠቅሶ አቅርቧል።
ከአንደኛ ተከሳሽ ውጪ ያሉ ተከሳሾች ችሎት ቀርበው ክሰ እንዲደርሳቸው ተደርጓል።
አንደኛ ተከሳሽን በሚመለከት ግን ከማረሚያ ቤት አልቀረበም።
ፍርድ ቤቱም አንደኛ ተከሳሽ በቀጣይ ቀጠሮ እንዲቀርብ ትዕዛዝ በመስጠት ክሱን ለመመልከት ለጥር 27 ቀን 2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱን ኤፍቢሲ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
***************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 16/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ማረሚያ ቤት በሚገኝ ግለሰብ ስም ሀሰተኛ የቪ8 ተሽከርካሪ ሊብሬና ከዕግድ ነጻ ሰነዶችን በመጠቀም ገንዘብ ተበድረዋል የተባሉ 4 ግለሰቦች በሙስና ወንጀል ተከሰሱ።
ክሱ የተመሰረተው በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 5ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።
ተከሳሾቹ በወንጀል ተግባር ክስ ተመስርቶበት በማረሚያ ቤት የሚገኘው 1ኛ ተከሳሽ ሱራፌል በቀለ ደግፌ፣ 2ኛ ወ/ሮ ራኬብ መንግስቱ፣ 3ኛ ወ/ሮ ቤተልሄም መንግስቱ እና 4ኛ ወ/ሮ ማህሌት በቀለ ይባላሉ።
የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጀነራል ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾቹ ላይ የወንጀል ህግ አንቀጽ 32 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) እና የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 23 ንዑስ ቁጥር 2 (ሀ) እና ንዑስ ቁጥር 3 ስር የተመላከተውን ድንጋጌ ተላልፈዋል በማለት ክስ አቅርቦባቸዋል።
በዚህም ተከሳሾቹ ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ ከአ/አ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ከአዲስ ከተማ ቅርጫፍ ጽ/ቤት በማረሚያ ቤት በሚገኝ ሱራፌል በቀለ በሚባል ግለሰብ ስም የተመዘገበ በማስመሰል የቪ8 ተሽከርካሪ ማረጋገጫ ሊብሬና ከዕግድ ነጻ የሚል የተዘጋጁ ሀሰተኛ ሰነዶችን መጠቀማቸው በክስ ዝርዝሩ ላይ ተመላክቷል።
በዚህ ሀሰተኛ ሰነድ በመጠቀም በ2013 ዓ.ም በፀደቀ የብድር ውል ስምምነት መሰረት ሀርቡ ማይክሮ ፋይናንስ አ/ማ ከሚባል ህዝባዊ ድርጅት በተለያዩ መጠኖች በአጠቃላይ 4 ሚሊየን 575 ሺህ 547 ብር ገንዘብ ተበድረው ጥቅም አግኝተውበት ያልመለሱ መሆኑን ዐቃቤ ሕግ በክሱ ጠቅሶ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን ሀሰተኛ መንግስታዊ ሰነዶችን መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ አቅርቦባቸዋል።
ዐቃቤ ሕግ ገላጭና አስረጂ ያላቸውን የሰነድ ማስረጃዎችን የክስ ዝርዝሩ ላይ ጠቅሶ አቅርቧል።
ከአንደኛ ተከሳሽ ውጪ ያሉ ተከሳሾች ችሎት ቀርበው ክሰ እንዲደርሳቸው ተደርጓል።
አንደኛ ተከሳሽን በሚመለከት ግን ከማረሚያ ቤት አልቀረበም።
ፍርድ ቤቱም አንደኛ ተከሳሽ በቀጣይ ቀጠሮ እንዲቀርብ ትዕዛዝ በመስጠት ክሱን ለመመልከት ለጥር 27 ቀን 2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱን ኤፍቢሲ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
ኮሚሽኑ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ እንዲሁም ማጣራት ስራ እያካሄደ እንደሚገኝ ገለፀ
******
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 16/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአብክመ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በክልሉ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ እንዲሁም ማጣራት ስራ እያካሄደ ይገኛል።
በዛሬው ዕለት የኮሚሽኑ የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ ዳ/ዳይሬክተር አቶ ይልቃል ወርቅነህ በሀብት ማሳወቅና ምዝገባ እንዲሁም ማጣራት ላይ ለጋዜጠኞች መረጃ ሰጥተዋል።
አቶ ይልቃል በመግለጫቸው የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ ዋና ዓላማው የግልፀኝነትና ተጠያቂነት ስርዓት ለማስፈንና ተሿሚዎች ስልጣናቸውን ያለአግባብ መከታ አድርገው ከገቢ ምንጫቸው በላይ ሀብት ማካበት እንዳይችሉ እንዲሁም የጥቅም ግጭት ለመከላከል መሰረት ያደረገ ነው ብለዋል።
ሀብት ማስመዝገብ ያለባቸው አካላት የህዝብ ተመራጮች፣ በየትኛውም እርከን ላይ ያሉ የመንግስት ተሿሚዎች እና ለሙስና ተጋላጭ ከሆኑ መደቦች ላይ የተመደቡ/የተቀጠሩ ባለሙያዎችን መሆናቸውን ገልፀዋል።
ሀብት አስመዝጋቢዎች የመጀመሪያ ምዝገባ ሀብታቸውን ማስመዝገብ ያለባቸው የህዝብ ተመራጮች በተመረጡ፣ የመንግስት ተሿሚዎች በተሾሙ እና ባለሙያዎች በተቀጠሩ ወይም በተመደቡ በ45 ቀናት ውስጥ ሲሆን፥ ለእድሳት ደግሞ የመጀመሪያ ምዝገባ ካስመዘገቡ በኋላ በ2.5 (በሁለት ዓመት ከአምስት ወር) መሆኑን በመግለጫው አንስተዋል።
አቶ ይልቃል አክለውም ሀብት አስመዝጋቢዎች በተሰጣቸው የጊዜ ገደብ አሳማኝ ባልሆነ ምክንያት ሀብታቸውን ሳያስመዘግቡ ከቀሩ ለመጀመሪያ ጊዜ 1000 ብር ይቀጡና በ30 ቀናት ውስጥ ማስመዝገብ ይኖርባቸዋል ብለዋል። በመደበኛም ሆነ በተራዘመላቸው የጊዜ ገደብ ውስጥ ሀብታቸውን ያላስመዘገቡ እና ትክክለኛ ሀብት ያላስመዘገቡ ካሉ እስከ 5 ዓመት የሚደርስ እስራት የሚያስቀጣና ማንኛውም ያልተመዘገበ ሀብት የሚወረስ መሆኑን በመግለጫቸው ገልፀዋል።
በመጨረሻም አቶ ይልቃል የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ የሚካሄድባቸው ከወረዳ እስከ ክልል ባሉ ተቋማት በተመደቡ የሥነምግባር መኮንኖች፣ በደሴ፣ በጎንደርና ደብረ ብርሃን ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እና በክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የሚካሄድ ሲሆን፥ ለሀብት ምዝገባው በየደረጃው የሚገኛው የተቋማት አመራሮች እገዛ ወሳኝ በመሆኑ በቅርበት ለሥነምግባር መኮንኖች የሀብት ምዝገባውን ሊያግዙና ሊያማክሩ ይገባል በማለት መልክታቸውን ማስተላለፋቸውን ከኮሚሽኑ የፌስቡክ ገፅ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
******
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 16/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአብክመ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በክልሉ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ እንዲሁም ማጣራት ስራ እያካሄደ ይገኛል።
በዛሬው ዕለት የኮሚሽኑ የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ ዳ/ዳይሬክተር አቶ ይልቃል ወርቅነህ በሀብት ማሳወቅና ምዝገባ እንዲሁም ማጣራት ላይ ለጋዜጠኞች መረጃ ሰጥተዋል።
አቶ ይልቃል በመግለጫቸው የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ ዋና ዓላማው የግልፀኝነትና ተጠያቂነት ስርዓት ለማስፈንና ተሿሚዎች ስልጣናቸውን ያለአግባብ መከታ አድርገው ከገቢ ምንጫቸው በላይ ሀብት ማካበት እንዳይችሉ እንዲሁም የጥቅም ግጭት ለመከላከል መሰረት ያደረገ ነው ብለዋል።
ሀብት ማስመዝገብ ያለባቸው አካላት የህዝብ ተመራጮች፣ በየትኛውም እርከን ላይ ያሉ የመንግስት ተሿሚዎች እና ለሙስና ተጋላጭ ከሆኑ መደቦች ላይ የተመደቡ/የተቀጠሩ ባለሙያዎችን መሆናቸውን ገልፀዋል።
ሀብት አስመዝጋቢዎች የመጀመሪያ ምዝገባ ሀብታቸውን ማስመዝገብ ያለባቸው የህዝብ ተመራጮች በተመረጡ፣ የመንግስት ተሿሚዎች በተሾሙ እና ባለሙያዎች በተቀጠሩ ወይም በተመደቡ በ45 ቀናት ውስጥ ሲሆን፥ ለእድሳት ደግሞ የመጀመሪያ ምዝገባ ካስመዘገቡ በኋላ በ2.5 (በሁለት ዓመት ከአምስት ወር) መሆኑን በመግለጫው አንስተዋል።
አቶ ይልቃል አክለውም ሀብት አስመዝጋቢዎች በተሰጣቸው የጊዜ ገደብ አሳማኝ ባልሆነ ምክንያት ሀብታቸውን ሳያስመዘግቡ ከቀሩ ለመጀመሪያ ጊዜ 1000 ብር ይቀጡና በ30 ቀናት ውስጥ ማስመዝገብ ይኖርባቸዋል ብለዋል። በመደበኛም ሆነ በተራዘመላቸው የጊዜ ገደብ ውስጥ ሀብታቸውን ያላስመዘገቡ እና ትክክለኛ ሀብት ያላስመዘገቡ ካሉ እስከ 5 ዓመት የሚደርስ እስራት የሚያስቀጣና ማንኛውም ያልተመዘገበ ሀብት የሚወረስ መሆኑን በመግለጫቸው ገልፀዋል።
በመጨረሻም አቶ ይልቃል የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ የሚካሄድባቸው ከወረዳ እስከ ክልል ባሉ ተቋማት በተመደቡ የሥነምግባር መኮንኖች፣ በደሴ፣ በጎንደርና ደብረ ብርሃን ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እና በክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የሚካሄድ ሲሆን፥ ለሀብት ምዝገባው በየደረጃው የሚገኛው የተቋማት አመራሮች እገዛ ወሳኝ በመሆኑ በቅርበት ለሥነምግባር መኮንኖች የሀብት ምዝገባውን ሊያግዙና ሊያማክሩ ይገባል በማለት መልክታቸውን ማስተላለፋቸውን ከኮሚሽኑ የፌስቡክ ገፅ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
ከ9 ሚሊየን ብር በላይ መንግስትን አሳጥተዋል የተባሉ ግለሰቦች በእስራትና በገንዘብ ተቀጡ
****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 16/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ከ9 ሚሊየን ብር በላይ ዓመታዊ ግብር ክፍያ መንግስትን አሳጥተዋል የተባሉ ግለሰቦች በቀረበባቸው የሙስና ወንጀል ክስ እስከ 13 አመት በሚደርስ ጽኑ እስራትና በገንዘብ እንዲቀጡ የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወንጀል ችሎት ወሰነ።
የቅጣት ውሳኔ የተላለፈባቸው ተከሳሾቹ 1ኛ በግል የስራ ተቋራጭ የሆኑት አብይ አማረ ዋሴ እና የኦሮሚያ ገቢዎች ቢሮ የሒሳብ ባለሙያ የነበሩት ተረፈ ቦጃ ናቸው።
የኦሮሚያ ፍትህ ቢሮ የሙስና ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾቹ ላይ የተሳትፎ ደረጃቸውን ጠቅሶ ሁለት የወንጀል ክሶችን በ2015 ዓ.ም መጨረሻ ባጠቃላይ በ3 ተከሳሾች ላይ ክስ መመስረቱን መዘገባችን ይታወሳል።
ዐቃቤ ሕግ ያቀረበው ክስ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32 ንዑስ ቁጥር 1 እና አንቀጽ 33 እንዲሁም ሙስናን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 13 ንዑስ ቁጥር 2 ላይ የተመላከተውን ድንጋጌ እና የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 203/2009 አንቀጽ 118 ንዑስ ቁጥር 1 ስር የተመላከተውን ድንጋጌ ተላልፈዋል የሚል ነበር።
በዚህም በአንደኛ ክስ በሁሉም ተከሳሾች ላይ የቀረበ ሲሆን፥ በሁለተኛው ክስ ላይ ደግሞ በአንደኛ ተከሳሽ ላይ ብቻ ነው የቀረበው።
በክሱ እንደተመላከተው 1ኛ ተከሳሽ የታክስ አስተዳደር አዋጁን በመተላለፍ ዓመታዊ የግብር ገቢ መክፈል ሲገባቸው የከፈሉ ለማስመሰል ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጠመንጃ ያዥ ቅርንጫፍ የተሰጠ የሚመስል ሀሰተኛ የኦሮሚያ ገቢዎች ሒሳብ ያልሆነ የባንክ ስሊፕ ማቅረባቸው በክስ መዝገቡ ላይ ተመላክቷል፡፡
2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች ደግሞ ከ1ኛ ተከሳሽ ጋር በመመሳጠር ያቀረቡትን ሐሰተኛ የባንክ ስሊፕ ሕጋዊነት ማረጋገጥ ሲገባቸው÷ ሳያረጋግጡ ሀሰተኛ ስሊፑን እና ሌሎች ሰነዶችን ትክክለኛነት ሳያረጋግጡ በመቀበል የገቢ ግብር ከፍለዋል በማለት የገቢ ደረሰኝ መስጠታቸው ተጠቅሷል፡፡
ከዚህም በኋላ ደግሞ ስራ ተቋራጩ ዓመታዊ ግብር ከነቅጣቱ እንደከፈሉ በማስመሰል ዓመታዊ ግብር ባለመክፈላቸው ምክንያት የተጣለባቸው የንብረት እግድ እንዲነሳላቸው በ3ኛ ተከሳሽ በኩል ለህግ ክፍል መጻፉም በክሱ ተጠቅሷል።
በአጠቃላይ ተከሳሾቹ መንግስትን 9 ሚሊየን 292 ሺህ 127 ብር ከ83 ሳንቲም ገቢ አሳጥተዋል በማለት ዐቃቤ ሕግ ክስ አቅርቦባቸዋል።
ተከሳሾቹ የቀረበባቸውን ክስ ዝርዝር ደርሷቸውና በችሎት በንባብ ከተሰማ በኋላ በክስ ዝርዝሩ ላይ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት አለመፈጸማቸውን ጠቅሰው የዕምነት ክህደት ቃላቸው ሰጥተዋል።
ይህን ተከትሎ ዐቃቤ ሕግ ከ3 በላይ የሰው ምስክሮችን እና ሌሎች ገላጭና አስረጂ የሰነድ ማስረጃዎችን አቅርቧል።
የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን የመረመረው ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ እንዲከላከሉ በሰጠው ብይን የመከላከያ ማስረጃ ያቀረቡ ሲሆን፥ 1ኛ እና 2ኛ ተከሳሾች ባቀረቡት የመከላከያ ማስረጃ የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው አላስተባበሉም በማለት በፍርድ ቤቱ የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎባቸዋል።
3ኛ ተከሳሽ የነበሩት የኦሮሚያ ገቢዎች ቢሮ የግብር ክትትል ቡድን መሪ መንግስቱ ሙሉነህን በሚመለከት የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን አስተባብለዋል በሚል ከቀረበባቸው ክስ ነጻ ተብለዋል።
ከዚህም በኋላ ፍርድ ቤቱ 1ኛ እና 2ኛ ተከሳሾች ያቀረቡትን የቅጣት ማቅለያ እንዲሁም ዐቃቤ ሕግ ያቀረበውን የቅጣት ማክበጃ አስተያየትን መርምሮ ዛሬ በዋለው የችሎት ቀጠሮ የቅጣት ውሳኔ ሰጥቷል።
በዚህም የተከሳሾችን የቅጣት አስተያየት በመያዝ 1ኛ ተከሳሽን ጥፋተኛ በተባሉበት ድንጋጌ በዕርከን 32 መሰረት በ13 ዓመት ጽኑ እስራትና በ85 ሺህ ብር እንዲቀጡ ወስኗል።
2ኛ ተከሳሽን በሚመለከት ፍርድ ቤቱ በአንድ አመት እስራትና በ2 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ የወሰነ ቢሆንም በዐቃቤ ሕግ በኩል ይግባኝ እንደሚጠይቅ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት አስታውቋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 16/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ከ9 ሚሊየን ብር በላይ ዓመታዊ ግብር ክፍያ መንግስትን አሳጥተዋል የተባሉ ግለሰቦች በቀረበባቸው የሙስና ወንጀል ክስ እስከ 13 አመት በሚደርስ ጽኑ እስራትና በገንዘብ እንዲቀጡ የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወንጀል ችሎት ወሰነ።
የቅጣት ውሳኔ የተላለፈባቸው ተከሳሾቹ 1ኛ በግል የስራ ተቋራጭ የሆኑት አብይ አማረ ዋሴ እና የኦሮሚያ ገቢዎች ቢሮ የሒሳብ ባለሙያ የነበሩት ተረፈ ቦጃ ናቸው።
የኦሮሚያ ፍትህ ቢሮ የሙስና ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾቹ ላይ የተሳትፎ ደረጃቸውን ጠቅሶ ሁለት የወንጀል ክሶችን በ2015 ዓ.ም መጨረሻ ባጠቃላይ በ3 ተከሳሾች ላይ ክስ መመስረቱን መዘገባችን ይታወሳል።
ዐቃቤ ሕግ ያቀረበው ክስ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32 ንዑስ ቁጥር 1 እና አንቀጽ 33 እንዲሁም ሙስናን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 13 ንዑስ ቁጥር 2 ላይ የተመላከተውን ድንጋጌ እና የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 203/2009 አንቀጽ 118 ንዑስ ቁጥር 1 ስር የተመላከተውን ድንጋጌ ተላልፈዋል የሚል ነበር።
በዚህም በአንደኛ ክስ በሁሉም ተከሳሾች ላይ የቀረበ ሲሆን፥ በሁለተኛው ክስ ላይ ደግሞ በአንደኛ ተከሳሽ ላይ ብቻ ነው የቀረበው።
በክሱ እንደተመላከተው 1ኛ ተከሳሽ የታክስ አስተዳደር አዋጁን በመተላለፍ ዓመታዊ የግብር ገቢ መክፈል ሲገባቸው የከፈሉ ለማስመሰል ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጠመንጃ ያዥ ቅርንጫፍ የተሰጠ የሚመስል ሀሰተኛ የኦሮሚያ ገቢዎች ሒሳብ ያልሆነ የባንክ ስሊፕ ማቅረባቸው በክስ መዝገቡ ላይ ተመላክቷል፡፡
2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች ደግሞ ከ1ኛ ተከሳሽ ጋር በመመሳጠር ያቀረቡትን ሐሰተኛ የባንክ ስሊፕ ሕጋዊነት ማረጋገጥ ሲገባቸው÷ ሳያረጋግጡ ሀሰተኛ ስሊፑን እና ሌሎች ሰነዶችን ትክክለኛነት ሳያረጋግጡ በመቀበል የገቢ ግብር ከፍለዋል በማለት የገቢ ደረሰኝ መስጠታቸው ተጠቅሷል፡፡
ከዚህም በኋላ ደግሞ ስራ ተቋራጩ ዓመታዊ ግብር ከነቅጣቱ እንደከፈሉ በማስመሰል ዓመታዊ ግብር ባለመክፈላቸው ምክንያት የተጣለባቸው የንብረት እግድ እንዲነሳላቸው በ3ኛ ተከሳሽ በኩል ለህግ ክፍል መጻፉም በክሱ ተጠቅሷል።
በአጠቃላይ ተከሳሾቹ መንግስትን 9 ሚሊየን 292 ሺህ 127 ብር ከ83 ሳንቲም ገቢ አሳጥተዋል በማለት ዐቃቤ ሕግ ክስ አቅርቦባቸዋል።
ተከሳሾቹ የቀረበባቸውን ክስ ዝርዝር ደርሷቸውና በችሎት በንባብ ከተሰማ በኋላ በክስ ዝርዝሩ ላይ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት አለመፈጸማቸውን ጠቅሰው የዕምነት ክህደት ቃላቸው ሰጥተዋል።
ይህን ተከትሎ ዐቃቤ ሕግ ከ3 በላይ የሰው ምስክሮችን እና ሌሎች ገላጭና አስረጂ የሰነድ ማስረጃዎችን አቅርቧል።
የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን የመረመረው ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ እንዲከላከሉ በሰጠው ብይን የመከላከያ ማስረጃ ያቀረቡ ሲሆን፥ 1ኛ እና 2ኛ ተከሳሾች ባቀረቡት የመከላከያ ማስረጃ የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው አላስተባበሉም በማለት በፍርድ ቤቱ የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎባቸዋል።
3ኛ ተከሳሽ የነበሩት የኦሮሚያ ገቢዎች ቢሮ የግብር ክትትል ቡድን መሪ መንግስቱ ሙሉነህን በሚመለከት የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን አስተባብለዋል በሚል ከቀረበባቸው ክስ ነጻ ተብለዋል።
ከዚህም በኋላ ፍርድ ቤቱ 1ኛ እና 2ኛ ተከሳሾች ያቀረቡትን የቅጣት ማቅለያ እንዲሁም ዐቃቤ ሕግ ያቀረበውን የቅጣት ማክበጃ አስተያየትን መርምሮ ዛሬ በዋለው የችሎት ቀጠሮ የቅጣት ውሳኔ ሰጥቷል።
በዚህም የተከሳሾችን የቅጣት አስተያየት በመያዝ 1ኛ ተከሳሽን ጥፋተኛ በተባሉበት ድንጋጌ በዕርከን 32 መሰረት በ13 ዓመት ጽኑ እስራትና በ85 ሺህ ብር እንዲቀጡ ወስኗል።
2ኛ ተከሳሽን በሚመለከት ፍርድ ቤቱ በአንድ አመት እስራትና በ2 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ የወሰነ ቢሆንም በዐቃቤ ሕግ በኩል ይግባኝ እንደሚጠይቅ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት አስታውቋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
ተፈናቃይ ነን በማለት በሀሰተኛ ሰነድ ከ8 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት አድርሰዋል የተባሉ ግለሰቦች እንዲከላከሉ ብይን ተሰጠ
****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 17/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ከሶማሌ ክልል ተፈናቃይ ነን በማለት በሀሰተኛ ሰነድ በመንግስት ላይ ከ8 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት አድርሰዋል የተባሉ 20 ግለሰቦች እንዲከላከሉ የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወንጀል ችሎት ብይን ሰጠ።
የክልሉ ፍትህ ቢሮ የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በነሃሴ ወር 2015 ዓ.ም ሶስት ክሶችን ካቀረበባቸው 50 ተከሳሾች መካከል ብርሃኑ ግርማ፣ ደረጄ ጌታቸው፣ ዱቦ ፉፋ፣ ሙሳ አብዲን ጨምሮ ሌሎች የሚገኙበት ሲሆን በቁጥጥር ስር ውለው ፍርድ ቤት የቀረቡት ግን 21 ብቻ ናቸው።
ዐቃቤ ሕግ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀጽ 32 ንዑስ ቁጥር 1 ሀ እና አንቀጽ 696 (ሐ) ስር የተመለከተውን እንዲሁም የሙስና አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 4 ንዑስ ቁጥር 4፣ አንቀጽ 23 (2.3) እና አንቀጽ 32 (3.2) ላይ የተመላከተውን ድንጋጌ ተላልፈዋል በማለት የክስ ዝርዝር አቅርቦባቸዋል።
በቀረበው በአንደኛው ክስ ላይ እደተመላከተው ከ1ኛ እስከ 5ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት ተከሳሾች ከሶማሌ ክልል በግጭት ምክንያት ከኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ አካባቢ የተፈናቀሉ 1 ሺህ 854 ዜጎች የተፈናቃይ ኮሚቴ ሆነው ሲሰሩ ከአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን በተጻፈ የእርዳታና ድጎማ ደብዳቤ መነሻ የአ/አ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በወቅቱ በኮዬ ፌጬ አካባቢ ለተፈናቃዮች ቤት እንዲሰራ በወሰነው ውሳኔ መሰረት ለተፈናቃዮች የድጋፍና ድጎማ ስራ ሲጀምር በጥር 16 ቀን 2010 ዓ.ም
ተፈናቃይ ያልሆኑ ግለሰቦች በሀሰተኛ ጊዜያዊ መታወቂያና ሰነድ ዝርዝር እንዲካተት አድርገዋል በሚል ተጠቅሷል።
በተለይም ተፈናቃይ ዜጎችን የመደጎምና የመኖሪያ ቤት የመስጠት ሂደት ውስጥ ከ5ኛ እስከ 30ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱ ተከሳሾች ተፈናቃይ ነን በማለት ሀሰተኛ የተፈናቃይ ጊዜያዊ መታወቂያና የተለያዩ ሀሰተኛ ሰነዶችን በማቅረብ በማጭበርበር በእርዳታ ድጎማው ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደረጉ በክሱ ዝርዝር ተመላክቷል።
በሌላኛው ክስ ደግሞ ከ31ኛ እስከ 50ኛ ተራ ቁጥር የተካተቱ ተከሳሾች በተለያየ ጊዜ ሀሰተኛ የተፈናቃይ መታወቂያዎችን እና ከሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ካንፓስ የተሰጡ የሚመስሉ ሀሰተኛ ሰነዶችን በተለያዩ ስም ዝርዝሮች በማቅረብ ተሳትፎ ያላቸው ተከሳሾች መኖራቸው ተጠቅሷል።
በዚህ መልኩ ተከሳሾቹ በጥቅም በመመሳጠር ተፈናቃይ ሳይሆኑ ነን በማለት እና ተፈናቃይ እንደሆኑ የሚገልጹ ቅጾችን በመሙላት እና በማስሞላት ጭምር ባደረጉት ተሳትፎ በኮዬ ፈጬ አካባቢ እያንዳንዳቸው 705 ሺህ 225 ብር ከ04 ሳንቲም የሚገመት መኖሪያ ቤት በመውሰድ እንዲሁም 19 ሺህ 600 ብር ድጎማ እያንዳንዳቸው በተለያየ ጊዜ በመቀበል በተፈጸመ የማጭበርበር የሙስና ወንጀል ድርጊት በመንግስት ላይ 8 ሚሊየን 697 ሺህ 876 ብር ከ08 ሳንቲም ጉዳት አድርሰዋል በማለት ዐቃቤ ሕግ የተከሳሾቹን ሚና ጠቅሶ ክስ መስርቶባቸው ነበር።
ይሁንና ፍርድ ቤት የቀረቡና ክሱ እንዲደርሳቸው የተደረጉ 21 ተከሳሾች በክሱ ላይ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት አለመፈጸማቸውን ጠቅሰው የዕምነት ክህደት ቃላቸውን በመስጠታቸው ዐቃቤ ሕግ 14 የሰው ምስክሮችና ለወንጀሉ መፈፀም ያስረዳሉ ያላቸውን የተቋማት እና የተለያዩ የሰነድ ማስረጃዎችን አቅርቧል።
ፍርድ ቤቱ የዐቃቤ ሕግ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን ከመረመረ በኋላ 20 ተከሳሾች በቀረቡባቸው የክስ ድንጋጌዎች እንዲከላከሉ ዛሬ በዋለው ችሎት ብይን መስጠቱን ኤፍቢሲ ዘግቧል።
በክስ መዝገቡ ላይ በ21ኛ ተራ ቁጥር ላይ የተጠቀሰው ተከሳሽ ግን በነጻ ተሰናብቷል።
ፍርድ ቤቱ የሁለተኛ ክስ ጭብጥ ከአንደኛ ክስ ጋር ተመሳሳይነት ያለው መሆኑን ጠቅሶ ሁለተኛ ክስ ከአንደኛው ክስ ጋር እንዲጠቃለል አድርጓል።
ተከላከሉ የተባሉ 20 ተከሳሾችን በሚመለከት የመከላከያ ማስረጃ ካላቸው ለመጠባበቅ ለየካቲት 11 ቀን 2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 17/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ከሶማሌ ክልል ተፈናቃይ ነን በማለት በሀሰተኛ ሰነድ በመንግስት ላይ ከ8 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት አድርሰዋል የተባሉ 20 ግለሰቦች እንዲከላከሉ የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወንጀል ችሎት ብይን ሰጠ።
የክልሉ ፍትህ ቢሮ የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በነሃሴ ወር 2015 ዓ.ም ሶስት ክሶችን ካቀረበባቸው 50 ተከሳሾች መካከል ብርሃኑ ግርማ፣ ደረጄ ጌታቸው፣ ዱቦ ፉፋ፣ ሙሳ አብዲን ጨምሮ ሌሎች የሚገኙበት ሲሆን በቁጥጥር ስር ውለው ፍርድ ቤት የቀረቡት ግን 21 ብቻ ናቸው።
ዐቃቤ ሕግ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀጽ 32 ንዑስ ቁጥር 1 ሀ እና አንቀጽ 696 (ሐ) ስር የተመለከተውን እንዲሁም የሙስና አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 4 ንዑስ ቁጥር 4፣ አንቀጽ 23 (2.3) እና አንቀጽ 32 (3.2) ላይ የተመላከተውን ድንጋጌ ተላልፈዋል በማለት የክስ ዝርዝር አቅርቦባቸዋል።
በቀረበው በአንደኛው ክስ ላይ እደተመላከተው ከ1ኛ እስከ 5ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት ተከሳሾች ከሶማሌ ክልል በግጭት ምክንያት ከኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ አካባቢ የተፈናቀሉ 1 ሺህ 854 ዜጎች የተፈናቃይ ኮሚቴ ሆነው ሲሰሩ ከአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን በተጻፈ የእርዳታና ድጎማ ደብዳቤ መነሻ የአ/አ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በወቅቱ በኮዬ ፌጬ አካባቢ ለተፈናቃዮች ቤት እንዲሰራ በወሰነው ውሳኔ መሰረት ለተፈናቃዮች የድጋፍና ድጎማ ስራ ሲጀምር በጥር 16 ቀን 2010 ዓ.ም
ተፈናቃይ ያልሆኑ ግለሰቦች በሀሰተኛ ጊዜያዊ መታወቂያና ሰነድ ዝርዝር እንዲካተት አድርገዋል በሚል ተጠቅሷል።
በተለይም ተፈናቃይ ዜጎችን የመደጎምና የመኖሪያ ቤት የመስጠት ሂደት ውስጥ ከ5ኛ እስከ 30ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱ ተከሳሾች ተፈናቃይ ነን በማለት ሀሰተኛ የተፈናቃይ ጊዜያዊ መታወቂያና የተለያዩ ሀሰተኛ ሰነዶችን በማቅረብ በማጭበርበር በእርዳታ ድጎማው ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደረጉ በክሱ ዝርዝር ተመላክቷል።
በሌላኛው ክስ ደግሞ ከ31ኛ እስከ 50ኛ ተራ ቁጥር የተካተቱ ተከሳሾች በተለያየ ጊዜ ሀሰተኛ የተፈናቃይ መታወቂያዎችን እና ከሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ካንፓስ የተሰጡ የሚመስሉ ሀሰተኛ ሰነዶችን በተለያዩ ስም ዝርዝሮች በማቅረብ ተሳትፎ ያላቸው ተከሳሾች መኖራቸው ተጠቅሷል።
በዚህ መልኩ ተከሳሾቹ በጥቅም በመመሳጠር ተፈናቃይ ሳይሆኑ ነን በማለት እና ተፈናቃይ እንደሆኑ የሚገልጹ ቅጾችን በመሙላት እና በማስሞላት ጭምር ባደረጉት ተሳትፎ በኮዬ ፈጬ አካባቢ እያንዳንዳቸው 705 ሺህ 225 ብር ከ04 ሳንቲም የሚገመት መኖሪያ ቤት በመውሰድ እንዲሁም 19 ሺህ 600 ብር ድጎማ እያንዳንዳቸው በተለያየ ጊዜ በመቀበል በተፈጸመ የማጭበርበር የሙስና ወንጀል ድርጊት በመንግስት ላይ 8 ሚሊየን 697 ሺህ 876 ብር ከ08 ሳንቲም ጉዳት አድርሰዋል በማለት ዐቃቤ ሕግ የተከሳሾቹን ሚና ጠቅሶ ክስ መስርቶባቸው ነበር።
ይሁንና ፍርድ ቤት የቀረቡና ክሱ እንዲደርሳቸው የተደረጉ 21 ተከሳሾች በክሱ ላይ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት አለመፈጸማቸውን ጠቅሰው የዕምነት ክህደት ቃላቸውን በመስጠታቸው ዐቃቤ ሕግ 14 የሰው ምስክሮችና ለወንጀሉ መፈፀም ያስረዳሉ ያላቸውን የተቋማት እና የተለያዩ የሰነድ ማስረጃዎችን አቅርቧል።
ፍርድ ቤቱ የዐቃቤ ሕግ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን ከመረመረ በኋላ 20 ተከሳሾች በቀረቡባቸው የክስ ድንጋጌዎች እንዲከላከሉ ዛሬ በዋለው ችሎት ብይን መስጠቱን ኤፍቢሲ ዘግቧል።
በክስ መዝገቡ ላይ በ21ኛ ተራ ቁጥር ላይ የተጠቀሰው ተከሳሽ ግን በነጻ ተሰናብቷል።
ፍርድ ቤቱ የሁለተኛ ክስ ጭብጥ ከአንደኛ ክስ ጋር ተመሳሳይነት ያለው መሆኑን ጠቅሶ ሁለተኛ ክስ ከአንደኛው ክስ ጋር እንዲጠቃለል አድርጓል።
ተከላከሉ የተባሉ 20 ተከሳሾችን በሚመለከት የመከላከያ ማስረጃ ካላቸው ለመጠባበቅ ለየካቲት 11 ቀን 2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ
*****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 18/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ልዩ ልዩ ሐሰተኛ ሰነዶችንና ዘዴዎችን በመጠቀም ህብረተሰቡን ሲያጭበረብሩና ሲያታልሉ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ፡፡
ተጠርጣሪዎቹ የመንግስት ባለስልጣናትን ስም በማንሳት ''እነ እከሌን እናውቃለን፤ ጉዳያችሁን እንጨርስላችኋለን'' በማለት የተለያዩ ሰዎችን በማጭበርበር ገንዘብ እየተቀበሉ ባሉበት ወቅት ከማስረጃ ጋር በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ ባለሃብትና ከፍተኛ ገንዘብ እንዳላቸው ለማስመሰል በርካታ የአሜሪካን ዶላር በሳምሶናይት ይዘው ፎቶግራፍ በመነሳት እና እራሳቸውን በማሳየት ሲያጨብረብሩ መቆታቸው ተመላክቷል፡፡
በተጨማሪም የመከላከያ ሠራዊት እና የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት መሥሪያ ቤት የስራ ባልደረባ አባል ነን በሚል በሐሰተኛ መታወቂያ ህብረተሰቡን ሲያጭበረብሩና ሲያታልሉ እንደቆዩ ፖሊስ ገልጿል።
ፖሊስ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አካባቢ በሚገኘው የአንደኛው ተጠርጣሪ ሞቱማ ደለሳ ቦሮቃ መኖሪያ ቤት ውስጥ ባደረገው ብርበራ ለወንጀል ተግባር ማስፈፀሚያ የሚገለገሉበት 90 ሺህ ብር፣ አንድ ሽጉጥ ከ24 መሠል ጥይቶች እና ከ2 ካዝና ጋር፣ አይፎንና ሳምሳንግ ሞባይል፣ አንድ አፒድ ላፕቶፕ እና ሦስት ፍላሾች ተይዘዋል፡፡
ህብረተሰቡ በተመሳሳይ የወንጀል ተግባር የተሰማሩ ግለሰቦችንና ቡድኖችን በሚመለከትበት ጊዜ በማጋለጥ እና አሳልፎ ለፖሊስ በመስጠት እንዲተባበር የፌዴራል ፖሊስ ጥሪውን አቅርቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
*****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 18/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ልዩ ልዩ ሐሰተኛ ሰነዶችንና ዘዴዎችን በመጠቀም ህብረተሰቡን ሲያጭበረብሩና ሲያታልሉ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ፡፡
ተጠርጣሪዎቹ የመንግስት ባለስልጣናትን ስም በማንሳት ''እነ እከሌን እናውቃለን፤ ጉዳያችሁን እንጨርስላችኋለን'' በማለት የተለያዩ ሰዎችን በማጭበርበር ገንዘብ እየተቀበሉ ባሉበት ወቅት ከማስረጃ ጋር በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ ባለሃብትና ከፍተኛ ገንዘብ እንዳላቸው ለማስመሰል በርካታ የአሜሪካን ዶላር በሳምሶናይት ይዘው ፎቶግራፍ በመነሳት እና እራሳቸውን በማሳየት ሲያጨብረብሩ መቆታቸው ተመላክቷል፡፡
በተጨማሪም የመከላከያ ሠራዊት እና የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት መሥሪያ ቤት የስራ ባልደረባ አባል ነን በሚል በሐሰተኛ መታወቂያ ህብረተሰቡን ሲያጭበረብሩና ሲያታልሉ እንደቆዩ ፖሊስ ገልጿል።
ፖሊስ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አካባቢ በሚገኘው የአንደኛው ተጠርጣሪ ሞቱማ ደለሳ ቦሮቃ መኖሪያ ቤት ውስጥ ባደረገው ብርበራ ለወንጀል ተግባር ማስፈፀሚያ የሚገለገሉበት 90 ሺህ ብር፣ አንድ ሽጉጥ ከ24 መሠል ጥይቶች እና ከ2 ካዝና ጋር፣ አይፎንና ሳምሳንግ ሞባይል፣ አንድ አፒድ ላፕቶፕ እና ሦስት ፍላሾች ተይዘዋል፡፡
ህብረተሰቡ በተመሳሳይ የወንጀል ተግባር የተሰማሩ ግለሰቦችንና ቡድኖችን በሚመለከትበት ጊዜ በማጋለጥ እና አሳልፎ ለፖሊስ በመስጠት እንዲተባበር የፌዴራል ፖሊስ ጥሪውን አቅርቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በልጆች ሥነምግባር ግንባታ የቤተሰብ ሚና (ክፍል ሁለት)
***************
የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በበይነመረብ አማካኝነት የትውልድ ሥነምግባር ግንባታ እና የሙስና መከላከል ክህሎት ሥልጠና እና ግንዛቤ ማጎልበቻ ፕሮግራም ሥራዎችን እያቀረበ ሲሆን ‹‹ለልጆች የሥነምግባር ግንባታ የቤተሰብ ሚና›› በሚል ርዕስ ክፍል ሁለት እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
***************
የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በበይነመረብ አማካኝነት የትውልድ ሥነምግባር ግንባታ እና የሙስና መከላከል ክህሎት ሥልጠና እና ግንዛቤ ማጎልበቻ ፕሮግራም ሥራዎችን እያቀረበ ሲሆን ‹‹ለልጆች የሥነምግባር ግንባታ የቤተሰብ ሚና›› በሚል ርዕስ ክፍል ሁለት እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
በሙስና ወንጀል በተጠረጠሩት እነ ኤልቤቴል ሀብቴ ላይ የክስ መመስረቻ ጊዜ ተሰጠ
*****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 20/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአ/አ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ የቀድሞ የፕሮቶኮል ዳይሬክተር እነ ኤልቤቴል ሀብቴ ላይ በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል የክስ ለመመስረት የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ለዐቃቤ ሕግ 15 ቀን ሰጠ።
ተጠርጣሪዎቹ የአ/አ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ የቀድሞ የፕሮቶኮል ዳይሬክተር ኤልቤቴል ሀብቴ፣ የፍትህ ሚኒስቴር ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ ሀብት አስተዳደር ዳይሬክተር ፍቅሩ ኦላና እንዲሁም በግል ስራ ይተዳደራሉ የተባሉት ቅዱስ መስፍን፣ አማኑኤል መስፍንና ተክሌ ከቡ የተባሉ ግለሰቦች ናቸው።
ተጠርጣሪዎቹ ከ17 ነጋዴዎች ከውጭ ሀገር እቃ ለማስመጣት በሚል ከተወሰደ ከ46 ሚሊየን ብር በላይ ገንዘብ ጋር ተያይዞ ስልጣንን ያለአግባብ በመገልገል እና ከማታለል ተግባር ጋር ተያይዞ በወንጀል ተጠርጥረው ምርመራ ሲከናወንባቸው ቆይቷል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን መርማሪ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ሲያከናውን የቆየውን የምርመራ ስራ ማጠናቀቁንና የምርመራ መዝገቡን ለዐቃቤ ሕግ ማስረከቡን አስታውቋል።
የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጀነራል ዐቃቤ ሕግ በበኩሉ የምርመራ መዝገቡን ተመልክቶ ለመወሰንና ክስ ለመመስረት እንዲያስችለው በወ/መ/ስ/ህ/ ቁጥር 109/1 መሰረት የ15 ቀን ክስ የመመስረቻ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።
የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች የዐቃቤ ሕግ የክስ መመስረቻ ጥያቄን በመቃወም የተጠረጠሩበት ወንጀል ተራ መሆኑን ጠቅሰው የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድ ጠይቀዋል።
ዐቃቤ ሕግ በተፈፀመው የወንጀል ድርጊት ከ46 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት የደረሰ መሆኑን በመጥቀስ ዋስትናን በሚያስነፍግ እና ከ10 ዓመት በላይ በሚያስቀጣ በከባድ የሙስና ድንጋጌ ሊከሰሱ እንደሚችሉ ገልጾ፤ የዋስትና ጥያቄው ውድቅ እንዲደረግለት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።
የግራ ቀኝ ክርክሩን የተከታተለው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ የዋስትና ጥያቄውን ውድቅ በማድረግ ለዐቃቤ ሕግ ክስ የመመስረቻ ጊዜ መስጠት አስፈላጊነትን በማመን 15 ቀናትን መፍቀዱን ኤፍቢሲ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
*****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 20/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአ/አ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ የቀድሞ የፕሮቶኮል ዳይሬክተር እነ ኤልቤቴል ሀብቴ ላይ በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል የክስ ለመመስረት የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ለዐቃቤ ሕግ 15 ቀን ሰጠ።
ተጠርጣሪዎቹ የአ/አ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ የቀድሞ የፕሮቶኮል ዳይሬክተር ኤልቤቴል ሀብቴ፣ የፍትህ ሚኒስቴር ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ ሀብት አስተዳደር ዳይሬክተር ፍቅሩ ኦላና እንዲሁም በግል ስራ ይተዳደራሉ የተባሉት ቅዱስ መስፍን፣ አማኑኤል መስፍንና ተክሌ ከቡ የተባሉ ግለሰቦች ናቸው።
ተጠርጣሪዎቹ ከ17 ነጋዴዎች ከውጭ ሀገር እቃ ለማስመጣት በሚል ከተወሰደ ከ46 ሚሊየን ብር በላይ ገንዘብ ጋር ተያይዞ ስልጣንን ያለአግባብ በመገልገል እና ከማታለል ተግባር ጋር ተያይዞ በወንጀል ተጠርጥረው ምርመራ ሲከናወንባቸው ቆይቷል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን መርማሪ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ሲያከናውን የቆየውን የምርመራ ስራ ማጠናቀቁንና የምርመራ መዝገቡን ለዐቃቤ ሕግ ማስረከቡን አስታውቋል።
የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጀነራል ዐቃቤ ሕግ በበኩሉ የምርመራ መዝገቡን ተመልክቶ ለመወሰንና ክስ ለመመስረት እንዲያስችለው በወ/መ/ስ/ህ/ ቁጥር 109/1 መሰረት የ15 ቀን ክስ የመመስረቻ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።
የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች የዐቃቤ ሕግ የክስ መመስረቻ ጥያቄን በመቃወም የተጠረጠሩበት ወንጀል ተራ መሆኑን ጠቅሰው የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድ ጠይቀዋል።
ዐቃቤ ሕግ በተፈፀመው የወንጀል ድርጊት ከ46 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት የደረሰ መሆኑን በመጥቀስ ዋስትናን በሚያስነፍግ እና ከ10 ዓመት በላይ በሚያስቀጣ በከባድ የሙስና ድንጋጌ ሊከሰሱ እንደሚችሉ ገልጾ፤ የዋስትና ጥያቄው ውድቅ እንዲደረግለት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።
የግራ ቀኝ ክርክሩን የተከታተለው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ የዋስትና ጥያቄውን ውድቅ በማድረግ ለዐቃቤ ሕግ ክስ የመመስረቻ ጊዜ መስጠት አስፈላጊነትን በማመን 15 ቀናትን መፍቀዱን ኤፍቢሲ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.