Federal Ethics And Anti- Corruption Commission
9.88K subscribers
10.4K photos
245 videos
32 files
3.05K links
Download Telegram
በሙስና ወንጀል የተከሰሱት የቀድሞ የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት የመረጃ ክትትልና ትንተና ቡድን መሪ አቤል ጌታቸው በጽኑ እስራትና በገንዘብ ተቀጡ

****************

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 14/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የቀድሞ የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት የመረጃ ክትትል እና ትንተና ቡድን መሪ አቤል ጌታቸው እና በግል ሥራ የሚተዳደሩት አቶ ፉፋ ዳባ ጥፋተኛ በተባሉበት ድንጋጌ በእስራትና በገንዘብ እንዲቀጡ ተወሰነ።

የቅጣት ውሳኔውን ያስተላለፈው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።

የፍትሕ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾቹ ላይ ሁለት ክሶችን አቅርቦ ነበር።

አቤል ጌታቸው በተባለው ግለሰብ ላይ የቀረበው ክስ ተከሳሹ የሙስና ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 9 ንዑስ ቁጥር 1 እና ንዑስ ቁጥር 2 ስር የተጠቀሰውን ድንጋጌ ተላልፏል የሚል ነው።

ሁለተኛ ተከሳሽን ፋፋ ዳባን በሚመለከት ደግሞ በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብን ወይም ንብረትን ሕጋዊ አድርጎ ማቅረብና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 780/2005 አንቀጽ 29 ንዑስ ቁጥር 1 ሀ ፣ ስር ያለውን ድንጋጌ በመተላለፍ የሚል ክስ ነው የቀረበው።

አቶ አቤል ጌታቸው የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ውስጥ የመረጃ ክትትልና ትንተና ቡድን መሪ ሆነው ሲሰሩ የተቋሙን አሰራር ባልተከተለ መልኩ የባለሃብቶችንና የድርጅቶችን የባንክ ሒሳብ አስቀድሞ በማጥናትና መረጃ በመውሰድ በተለያዩ ጊዜያት ለባለሃብቶች ስልክ በመደወል በአካል በማግኘት ገንዘብ እንዲከፍሉ በመጠየቅ የማይከፍሉ ከሆነ ደግሞ የፋይናንስ እንቅስቃሴያቸውን በተመለከተ ለፖሊስ በማስተላለፍ የወንጀል ክስ እንደሚመሰረትባቸው በመግለጽ አስፈራርተዋል በማለት ነው ዐቃቤ ሕግ በክሱ የጠቀሰው።

በዚህ መልኩ ተከሳሹ በ2013 እና በ2014 ዓ.ም በተለያዩ ጊዜያት ባለሃብቶችን በማስፈራራት ከ3 ግለሰቦች 3 ሚሊየን 70 ሺህ ብር ገንዘብ ፉፋ ዳባ በተባለው 2ኛ ተከሳሽ ስም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ገንዘቡ ገቢ እንዲደረግ በማድረግ በዋና ወንጀል አድራጊነት ስልጣንን ያለአግባብ መገልገል ከባድ ሙስና ወንጀል ክስ ቀርቦበት ነበር።

ሁለተኛ ተከሳሽ ፉፋ ዳባን በሚመለከት ደግሞ በወንጀል የተገኘ 3 ሚሊየን 70 ሺህ ብር የወንጀል ፍሬ መሆኑን እያወቁ የገንዘቡን ምንጭ ለመደበቅ በስሙ በባንክ የገባውን ገንዘብ በተለያዩ መጠን በመጠቀም ሕገ ወጥ ገንዘብን ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብ የሚል ክስ በዐቃቤ ሕግ ቀርቦበታል።

በዚህ መልኩ ክሱ ለተከሳሾች የክስ ዝርዝሩ ደርሷቸው በችሎት በንባብ ተሰምቷል።

ከዚህም በኋላ ተከሳሾች የሰጡትን የዕምነት ክህደት ቃል ተከትሎ ፍርድ ቤቱ በዐቃቤ ሕግ የቀረቡ አምስት የሰው ምስክሮችን ቃል እና የሰነድ ማስረጃ መርምሮ ተከሳሾቹ እያንዳንዳቸው በተከሰሱበት ድንጋጌ እንዲከላከሉ ብይን ሰጥቷል።

ይሁንና ተከሳሾቹ የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው መከላከል አለመቻላቸውን ጠቅሶ ፍርድ ቤቱ የጥፋተኝነት ፍርድ አስተላልፎባቸዋል።

ፍርድ ቤቱ ከዚህም በኋላ የግራ ቀኝ የቀረቡ የቅጣት ማክበጃና የቅጣት ማቅለያ አስተያየቶችን መርምሯል።

በዚህም አንደኛ ተከሳሽ አቶ አቤልን በሚመለከት በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ በሰላም ማስከበር ረገድ እንዲሁም በበጎ አድራጎት ድርጅት ውስጥ ያበረከቱትን አስተዋጽኦ ጨምሮ አጠቃላይ ያቀረበውን የቅጣት ማቅለያ አስተያየቶችን በወንጀል ሕግ አንቀጽ 86 እና በአንቀጽ 82 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) መሰረት አጠቃላይ 7 የቅጣት ማቅለያ አስተያየቶችን ፍርድ ቤቱ ይዞላቸዋል።

ሁለተኛ ተከሳሽ ፉፋ ዳባን በሚመለከት ደግሞ ለሕዳሴ ግድብ ያበረከቱትን የቦንድ ግዢ ጨምሮ አጠቃላይ 5 የቅጣት ማቅለያ አስተያየቶች ተይዞላቸዋል።

ዐቃቤ ሕግ በበኩሉ የቅጣት ማክበጃ አስተያየት ያቀረበ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ በዝቅተኛ ደረጃ በመያዝ አንደኛ ተከሳሽን በዕርከን 16 መሰረት በ3 ዓመት ጽኑ እስራትና በ1 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ ወስኗል።

ሁለተኛ ተከሳሽ ፉፋ ዳባ ደግሞ በዕርከን 22 መሰረት በ5 ዓመት ከ 6 ወራት ጽኑ እስራት እና በ6 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ መወሰኑን ኤፍቢሲ ዘግቧል።

ዐቃቤ ሕግ በበኩሉ ይግባኝ እንደሚጠይቅ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ገልጿል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ሥነምግባርን የተላበሰ አመራር የግልፀኝነትንና የተጠያቂነትን መርህ ተግባራዊ በማድረግ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን የሚታገልና ለሀገር እድገት በትኩረት የሚሰራ ነው!

****************

ሥነምግባርን የተላበሰ አመራር መገለጫዎች

 ህጎችን በትክክል ተግባራዊ ያደርጋል፥
 ሌብነትንና አግበስባሽነትን ይፀየፋል፥
 ለሥሙ ይጠነቀቃል፥
 የእኔ ይቅደም ከማለት ይልቅ የሀገር ጉዳይን ያስቀድማል፥
 ለሐገር እድገት በትኩረት ይሰራል፥
 ሰዎችን በአግባቡ ያገለግላል፥
 የግልጽነትና የተጠያቂነት መርህን፥ ተግባራዊ የደርጋል፥
 የተቋሙን አላማ በትክክል ያስፈጽማል፥
 ሙስናን በጽኑ ይታገላል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኮሚሽኑ የሙስና ሥጋት ባለባቸው ስድስት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሲያካሄድ የቆየዉን የሙስና መከላከል ጥናት ግኝት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር አካሄደ

****

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 14/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የሙስና ሥጋት ባለባቸው ስድስት ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ባካሄደዉ የሙስና መከላከል ጥናት ግኝት ላይ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በይርጋለም ከተማ ምክክር አድርጓል፡፡

ጥናቱ የተካሄደባቸው ስድስቱ ርዕሰ ጉዳዮች በክልሉ በስራ እድል ፈጠራ፣ በገቢ አሰባሰብ ሂደት፣ በሰራተኞች ዝዉዉርና ቅጥር፣ በፋይናንስና ግዢ፣ በትምህርት ቤቶች ገቢ አሰባሰብና አጠቃቀም እንዲሁም የመድሀኒት አቅርቦትና ስርጭት ለሙስና እና ብልሹ አሰራር ያላቸዉን ተጋላጭነት ለይቶ ይፋ ያደረገ ሲሆን፤ ለችግሩም መንስኤ የሆኑትን መለየት መቻሉ ተገልጿል፡፡

የምክክር መድረኩን በንግግር የከፈቱት የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካ አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አስፋዉ ጎነሳ መንግስት የጀመረዉን የኢኮኖሚ፣ የእድገት፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጉዞ ለማስቀጠል በየደረጃዉ ካሉ አካላት ጋር ሰፋፊ ስራ እየተከናወነ መቆየቱን ገልፀዋል።

አቶ አስፋዉ አያይዘዉም እንደሀገር ሙስና እና ብልሹ አሰራር በሀገር ላይ የሚያደርሰዉን አሉታዊ ተጽእኖ ለመታገል ሰፊ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልፀዉ፤ እንደክልላችንም ኮሚቴ በማዋቀር የህዝብንና የመንግስትን ሀብት ለመመዝበር በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ላይ ጠንካራ ህጋዊ፣ አስተዳደራዊና ፖለቲካዊ የእርምት እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ተናግረዋል።

አቶ አስፋው የሀገር ልማትና እድገት አደናቃፊ የሆነዉን ሙስና እና ብልሹ አሰራርን በህብረት ልንታገል ይገባል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የክልሉ የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ወ/ሮ ዘላለም ለማ በበኩላቸዉ ኮሚሸኑ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል ግንዛቤ ከማስጨበጥ ጀምሮ የሙስና ወንጀል ተከስቶ ሲገኝ ጥቆማዎችን መነሻ በማድረግ የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ የበኩሉን ሲወጣ መቆየቱን ተናግረዋል።

በመድረኩም ሁሉም የሙስና መከላከል ጥናት ግኝቶች ቀርበው ከመድረኩ ተሳታፊዎች ጋር ምክክር በማካሄድ ጥናቱ ከተካሄደባቸው ተቋማት ጋር የትግበራ የዉል ስምምነት መካሄዱን ከኮሚሽኑ የፌስቡክ ገፅ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
በሥነምግባር ያልታነጸ አመራር የግልፀኝነትንና የተጠያቂነትን መርህ ተግባራዊ የማያደርግ፥ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን የማይታገልና ለሀገር እድገት በትኩረት የማይሰራ ይሆናል!

****

በሥነ-ምግባር ያልታነጸ አመራር መገለጫዎች

o የግል ጥቅሙን ያስቀድማል፥
o የሐገርን እድገት ማየት አይፈልግም፥
o ራዕይ የለውም፥
o ህግን አጣምሞ ይተረጉማል፥
o የግልጽነትና የተጠያቂነት መርህን ተግባራዊ አያደርግም፥
o የአገልጋይነት መንፈስ አይታይበትም፥
o ብልሹ አሰራሮችን አይከላከልም፥
o ሙስናን ከመከላከል ይልቅ እንዲስፋፋ እድሎችን ይፈጥራል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
በአዳማ ከተማ በሀሰተኛ ሰነድ የሌላ ሰው መሬት የሸጡ ግለሰቦች እያንዳንዳቸው በፅኑ እስራት ተቀጡ

****************

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 15/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) በአዳማ ከተማ በሀሰተኛ ሰነድ የሌላ ሰው መሬት የሸጡ አራት ግለሰቦች እያንዳንዳቸው በ6 አመት ከ6 ወራት ፅኑ እስራት ተቀጥተዋል፡፡

ወንጀለኞቹ ደለለኝ ግርማ፣ ምትኩ ደያሳ፣ አለም ተስፋዬ እና ብርቱካን ደገፋ ናቸው፡፡

አንደኛው ተከሳሽ ደለለኝ ግርማ በሌላ ሰው መሬት ባለዕርስት ነኝ በማለትና ሁለተኛው ተከሰሽ ምትኩ ደያሳ ደላላ በመሆን እና ሦስተኛው ተከሳሽ አለም ተስፋዬ በአዳማ የሉጎ ክፍለ ከተማ መሬት ጽህፈት ቤት ባልደረባ ነኝ በማለት ሳይሆኑ ሆነናል ብለው ነው ንጉሤ አበራ ለተሰኘ የግል ተበዳይ እንዲሁ አንድ ቦታ አሳይተውት ወደ ግብይት የገቡት፡፡

የግል ተበዳዩ እንዲያምናቸው ላሳዩት ቦታ ሀሰተኛ ካርታ አዘጋጅተው 750 ሺህ ብር ሊሸጡለት ተስማምተው 250 ሺህ ብር መቀበላቸው የአቃቤ ህግ ክስ ያመለክታል፡፡

ከዚህ በመነሳት የአዳማ ከተማ አቃቤ ህግ ወንጀለኞቹ ያልሆኑትን ሆነናል በማለት ሀሰተኛ ሰነድ በመጠቀም ገንዘብ በማጭርበራቸው፤ የአዳማ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሾቹ ጥፋተኛ በተባሉበት የማታለልና በሀሰተኛ ሰነድ መገልገል በሁለት ክሶች እያንዳንዳቸውን በ6 ዓመት ከ6 ወር እና በገንዘብ መቀጣታቸውን ኢቢሲ ዘግቧል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
የኮሚሽኑ አመራሮች እና ሠራተኞች የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያዘጋጀውን የዲፕሎማሲ አውደ ርዕይ ጎበኙ

****************

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 15/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን አመራሮች እና ሠራተኞች የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያዘጋጀውን የዲፕሎማሲ አውደ ርዕይ ጎብኝተዋል፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር "የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ሳምንት" በሚል መሪ ቃል በሳይንስ ሙዚየም የተዘጋጀዉን የሀገራችንን የዲፕሎማሲ ታሪክ፣ ወቅታዊ የዲፕሎማሲ ክንውኖች እና የመጪውን ዘመን ርዕይ እንዲሁም በመስኩ ሀገራችን ለዓለም ያበረከተችውን አስተዋፅኦ ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ እና ለህዝብ ለማስተዋወቅ ባዘጋጀው የዲፕሎማሲ አውደ ርዕይ ላይ የኮሚሽኑ አመራሮች እና ሠራተኞች ጉብኝት አድርገዋል::

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@feac1993?_t=8jEyU0ouURa&_r=1
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡