Federal Ethics And Anti- Corruption Commission
9.88K subscribers
10.4K photos
246 videos
32 files
3.06K links
Download Telegram
ሀሰተኛ ሰነዶችን ሲያዘጋጁ የነበሩ ሁለት ተጠርጣሪዎች መያዛቸው ተገለፀ

****************

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 1/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ሀሰተኛ ሰነድ በሚያዘጋጁ ግለሰቦች ላይ ባደረገው ክትትል ልዩ ልዩ ሀሰተኛ ሠነዶችንና ሰነዶቹን ለማዘጋጀት የሚገለገሉባቸውን ቁሳቁሶች ከሁለት ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ ገለፀ።

ፖሊስ በወረዳ 3 አብነት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሀሰተኛ ሰነድ በሚዘጋጅበት መኖሪያ ቤት ውስጥ በህግ አግባብ ባደረገው ብርበራ 13 ሀሰተኛ የመኪና ሊብሬ፣ 10 ሀሰተኛ የቤት ካርታ፣ 2 ሀሰተኛ የጋብቻ ሰርተፍኬት፣ 18 የእጅ በእጅ የሽያጭ ደረሰኞች እና 6 ሀሰተኛ የባንክ ቤት ደረሰኞች ማግኘቱን አስታውቋል፡፡

በተጨማሪም የተለያዩ የዲግሪ፣ የዲፕሎማ እና የስምንተኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃዎች ፣ የፌዴራል ፖሊስ እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ሀሰተኛ የስራ ልምድ እንዲሁም የተለያዩ የመንግስት እና የግል ተቋማት ሀሰተኛ አርማዎች (ሎጎ) መገኘታቸውን የጌጃ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ሃላፊ ኮማንደር በልሁ ክፍሌ ገልፀዋል።

ሀሰተኛ ሰነድ በሀገር ላይ የሚስከትለውን ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳት በመረዳት ሀሰተኛ ሰነዶችን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ውስጥ ሁሉም ዜጋ የበኩሉን አበርክቶ ሊወጣ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክቱን ማስተላለፉን ጠቅሶ ኢቢሲ ዘግቧል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኤጀንሲው አገልግሎት በመስጠት ሂደት ላይ ያልተገባ ጥቅም የሚያገኙ አካላት ላይ ተጠያቂነትን ለማስፈን እየሰራ ነው

****************

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 1/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አገልግሎት በመስጠት ሂደት ላይ ያልተገባ ጥቅም የሚያገኙ አካላት ላይ ተጠያቂነትን ለማስፈን እየሰራ መሆኑን ገለፀ።
የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ በስድስት ወራት ውስጥ በህገወጥነትና ተጠያቂነት ላይ በተሰሩ ስራዎች ላይ መግለጫ ሰጥቷል።

የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ ዓለማየሁ እንደለፁት፤ ኤጀንሲው ከሌብነት የፀዳ አገልግሎት ለመስጠት እየሰራ ነው።

በ6 ወራት ውስጥ በአገልግሎት አሰጣጥ እና በኦዲት ግኝት ላይ ክትትሎች ተደርገዋል። በዚህም የአገልግሎት ኦዲትን በተመለከተ በጠቅላላው 63 ሰዎች ተጠያቂ ሲሆኑ 12 በወንጀል እና 41 በዲሲፕሊን ተጠያቂ ናቸው። ቀሪ 10 የጽ/ቤት አመራሮች ስራን በአግባቡ ባለመምራት ተጠያቂ የሚሆኑ መሆናየውን ገልፀዋል።

እንዲሁም በአገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተ 47 ባለሙያዎች ተጠያቂ የተደረጉ ሲሆን ከዚህም 34 በከባድ እና ቀላል ዲሲፕሊን እንዲሁም 9 ባለሙያዎች በወንጀል ተከሰዋል ብለዋል።

በተጨማሪም 36 ሃሰተኛ ሰነድ ይዘው የተገኙ ተገልጋዮች በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ የተደረገ መሆኑን አስታውቀው፤ 4ቱ በወረዳ ጽ/ቤት፣ 34ቱ በኤጀንሲው ዋና መስሪያ ቤት መሆናቸውን ገልፀዋል። ከዚህም ውስጥ 3ቱ ፍርድ መሰጠታቸውን ኢፕድ ዘግቧል፡፡
ለግብርና ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት አመራሮች ሥነምግባራዊ አመራር ላይ ያተኮረ ስልጠና እየተሰጠ ነው

******

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 1/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ለግብርና ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት አመራሮች በሥነምግባራዊ አመራር ጽንሰ ሀሳብ እና መገለጫ ባህርያት እንዲሁም ውሳኔ አሰጣጥ ላይ ያተኮረ ስልጠና እየተሰጠ ነው።

በፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የሥልጠና ዴስክ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች እየተሰጠ የሚገኘው ስልጠና በነገው ዕለትም እንደሚቀጥል ከግብርና ሚኒስቴር የፌስቡክ ገፅ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በመልካም ሥነምግባር አርዓያ የሆነ፣ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን የሚጸየፍ ትውልድ በመፍጠር ረገድ የመምህራን ሚና የጎላ ነው!

***************

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ማረሚያ ቤት በሚገኝ ግለሰብ ስም ሐሰተኛ ሊብሬና ከዕግድ ነጻ ሰነዶችን በመጠቀም ገንዘብ ተበድረዋል በተባሉ ግለሰቦች የክስ መመስረቻ ጊዜ ተፈቀደ

******

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 2/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ማረሚያ ቤት በሚገኝ ግለሰብ ስም ሀሰተኛ የቪ8 ተሽከርካሪ ሊብሬና ከዕግድ ነጻ የሚሉ ሰነዶችን በመጠቀም ገንዘብ ተበድረዋል ተብለው በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት የክስ መመስረቻ ጊዜ ፈቀደ።

ተጠርጣሪዎቹ ወ/ሮ ራኬብ መንግስቱ እና ወ/ሮ ቤተልየም መንግስቱ በማረሚያ ቤት በሚገኝ ሱራፌል በቀለ በሚባል ግለሰብ ስም ከአ/አ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፍቃና ቁጥጥር ባለስልጣን ከአዲስ ከተማ ቅርጫፍ ጽ/ቤት የተሰጠ በማስመሰል የቪ8 ተሽከርካሪ ማረጋገጫ ሊብሬና ከዕግድ ነጻ የሚል ሀሰተኛ ማስረጃዎችን በመጠቀም ሀርቡ ማይክሮ ፋይናንስ አ/ማ ከተባለ ህዝባዊ ድርጅት እያንዳንዳቸው 1 ሚሊዮን 76 ሺህ 74 ብር ገንዘብ ተበድረዋል ተብለው የተጠረጠሩ ግለሰቦች ናቸው።

የአ/አ ፖሊስ ኮሚሽን መርማሪ ተጠርጣሪዎች ላይ ሲያከናውን የቆየውን የምርመራ ስራ አጠናቆ የምርመራ መዝገቡን ለዐቃቤ ሕግ ማስረከቡን ለጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ገልጿል።

ዛሬ መዝገቡን እንደተረከበ የገለጸው የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ ደግሞ መዝገቡን ተመልክቶ ለመወሰን እንዲያስችለው በወ/መ/ስ/ህ/ቁ 109/1 መሰረት የ15 ቀን ክስ መመስረቻ ጊዜ ጠይቋል።

በተጨማሪም ዐቃቤ ሕግ በወንጀል ድርጊቱ የተገኘው ጉዳት ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሶ ተጠርጣሪዎቹ ላይ ክስ የሚመሰርት ከሆነ ከ10 ዓመት በላይ በሚያስቀጣ ድንጋጌ እንደሚሆን በመጠቆም ይህም ድንጋጌ ዋስትና የሚያስከለክል በመሆኑ ክስ እስኪመሰርት ተጠርጣሪዎቹ በእስር ይቆዩ የሚል ጥያቄ አንስቷል።

በተጠርጣሪ ጠበቃ በኩል ደግሞ የዐቃቤ ሕግ የክስ መመስረቻ ጊዜ ጥያቄን በመቃወም ተከራክሯል።

ከ10 ዓመት በላይ የሚያስቀጣ ድንጋጌ ዋስትና ሊያስከስስ ይችላል በሚል ምክንያት ብቻ የተጠርጣሪዎች የዋስትና መብት ሊገደብ አይገባም የሚል የመከራከሪያ ነጥብ መነሳቱን ጠቅሶ ኤፍቢሲ ዘግቧል።

የግራ ቀኙን ክርክር የመረመረው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ የምርመራ መዝገቡን ተመልክቶ ለመወሰን ጊዜ እንደሚያስፈልግ በማመን ዐቃቤ ሕግ የጠየቀውን የክስ መመስረቻ ጊዜ በመፍቀድ ውጤቱን ለመጠባበቅ ለጥር 16 ቀን 2016 ዓ.ም ቀጥሯል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡