Federal Ethics And Anti- Corruption Commission
9.89K subscribers
10.4K photos
246 videos
32 files
3.06K links
Download Telegram
በህገ-ወጥ ነጋዴዎች ላይ የሚስተዋለውን ብልሹ አሰራር በማጋለጥ የበኩላችን ድርሻ እንወጣ!

*****

በህገ-ወጥ ነጋዴዎች ላይ የሚስተዋለውን ብልሹ አሰራር ለህብረተሰቡ ግንዛቤ ለመፍጠር በአማራ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የተዘጋጀ አስተማሪ ማስታወቂያ ነው።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ ሶፍትዌር፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ፓስፖርትና ቪዛ ለውጭ ዜጎች በመስጠትና ግለሰቦችን ወደ ውጭ በመላክ ወንጀል የተከሰሱ 36 ተከሳሾች ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ሆነው እንዲከታተሉ ታዘዘ

******

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 19/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) ፓስፖርትና ቪዛ ለውጭ ሀገር ዜጎች በመስጠትና ሰነድ አልባ ግለሰቦችን ወደ ውጭ በመላክ የሙስና ወንጀል የተከሰሱ 36 ተከሳሾች በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ትዕዛዝ ተሰጠ።

ትዕዛዙን የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1 ኛ የሙስና ወንጀል ችሎት ነው።

የቀድሞ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ታምሩ ግንበቶ ከዚህ በፊት በነበረ የስራ ድርሻቸው ምክንያት ጥቃት ሊፈጸምባቸው እንደሚችል መስጋታቸውን በመግለጽ በማረሚያ ቤት በልዩ ሁኔታ ከለላ እንዲደረግላቸው አቤቱታ ማቅረባቸውን ተከትሎ ትዕዛዝ እስኪሰጥበት ድረስ በፌደራል ፖሊስ ጊዜያዊ ማቆያ እንዲቆዩ ችሎቱ አዟል።

ሌሎች ተከሳሾችን በሚመለከት ግን ማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ነው የታዘዘው።

የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዘርፍ ዐቃቤ ሕግ ባሳለፍነው ረቡዕ የተሳትፎ ደረጃ ጠቅሶ በ60 ግለሰቦች ላይ በየደረጃው 15 የሙስና ወንጀል ክስ መመስረቱ ይታወሳል።

ክሱ ከቀረበባቸው ተከሳሾች መካከል ቀደም ሲል በነበረ ቀጠሮ በዐቃቤ ሕግ በኩል 54ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሰ ፈራኦል የተባለ ተከሳሽ ክሱ እንዲቋረጥለት በቀረበ ጥያቄ መሰረት መቋረጡ ይታወቃል።

ሌሎች ሁለት ተከሳሾች ደግሞ ማለትም የኢሚግሬሽን ዜግነት አገልግሎት የኬላዎች ዘርፍ ቡድን መሪ የነበረው 5ኛ ተከሳሽ አይክፋው ጓሳዬ ገረመው እና አለሚቱ የኔ አየሁ የተባለች 49ኛ ተከሳሽን በሚመመከት የቀረበባቸው የክስ ድንጋጌ ዋስትና የማያስከለክል መሆኑን ተከትሎ በ10 እና በ20 ሺህ ብር ዋስ ከእስር ተፈተዋል።

በዛሬው ቀጠሮ በዋስ የተፈቱ ሁለት ግለሰቦች እና የቀድሞ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የምዝገባና ቁጥጥር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ታምሩ ግንበቶ አዋልሶ፣ የውጪ ዜጎች ቁጥጥርና ቆንስላ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጅላሉ በድሩ፣ በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ቡድን አስተባባሪ ከድር ሰዒድ ስሩር፣ የኬላዎች ማስተባበሪያ ዳይሬክተር ቴዎድሮስ ቦጋለ ጨምሮ አጠቃላይ 39 ተከሳሾች ፍርድ ቤት ቀርበው ጉዳያቸውን ተከታትለዋል።

ቀሪ 20 ተከሳሾች ግን ችሎት አልቀረቡም።

ችሎቱ ባለፈው ቀጠሮ ክሱን በንባብ ካሰማ በኋላ ከ5ኛ፣ ከ13ኛ እና ከ37ኛ ተራ ቁጥር ከተጠቀሱ ተከሳሾች ውጪ ያሉ የሌሎች ተከሳሾች በጠበቆቻቸው በኩል ክሱ ግልጽ እንዳልሆነ ገልጸው ክርክሩ ከመቀጠሉ በፊት የክስ ግልጽነት ላይ ጥያቄ አለን በማለት አቤቱታ አቅርበው ነበር።

ፍርድ ቤቱም በቀረበው ጥያቄ ላይ ዐቃቤ ሕግ ለዛሬ መልስ እንዲያቀርብ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ባቀረበው የጽሁፍ መልስ የጠበቆቹ ጥያቄ ከክስ መቃወሚያ ጋር ተጠቃሎ መቅረብ እንዳለበት ጠቅሷል።

ለብቻው የግልጽነት ጥያቄ ላይ ፍርድ ቤቱ ብይን ሊሰጥበት አይገባም የሚል መልስና በጉዳዩ ላይ ፍርድ ቤቱ ብይን ወይም ትዕዛዝ ሊሰጥ ይገባል የሚል ከሆነ ደግሞ ክሱ መሰረታዊ ካልሆኑ የአሃዝ እና የስያሜ ስህተት ውጪ ግልጽ በመሆኑ ክሱ በቀረበበት አግባብ ሊቀጥል ይገባል በማለት ዐቃቤ ሕግ አስተያየት ሰጥቷል።

ፍርድ ቤቱም ጉዳዩን መርምሮ ብይን ለመስጠት ለታህሳስ 23 ቀን 2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

እነዚህ በሙስና ወንጀል ክስ የተመሰረተባቸው ተከሳሾች ላይ ዐቃቤ ሕግ ከተለያዩ ሀገራት ዜጎች ጋር በጥቅም በመመሳጠር፣ ከህግ ውጪ በጉቦ በዶላር እየተቀበሉ ለውጭ ዜጎች በመስጠት፣ ከህግ አሰራር ውጪ ቪዛ በመስጠት፣ ሰነድ አልባ ዜጎችኝ በጥቅም በህገወጥ መንገድ ከሀገር በማስወጣት፣ መንግስት ላይ ጉዳት ማድረስ የሚሉ ነጥቦች በየተሳትፎ ደረጃ ተጠቅሶ በክስ ዝርዝሩ መካተቱን ኤፍቢሲ ዘግቧል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ ሶፍትዌር፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
አብረን ነበርን አብረን ነን፤ አብረን እንኖራለን!

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ ድህረ ገጻችን፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች ሲሰጥ የነበረው የቴክኒክና የሥነባህሪ ብቃት ፈተና መጠናቀቁ ተገለፀ

******

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 20/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ የተዘጋጀው እና በዛሬው ዕለት ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች ሲሰጥ የነበረው የቴክኒክና የሥነባህሪ ብቃት ፈተና መጠናቀቁ ተገልጿል።

ይህ የቴክኒክና የሥነባህሪ ብቃት ፈተና 15 ሺሕ 592 ለሚሆኑ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፣ ባለሙያዎች እና ሰራተኞች የተሰጠ መሆኑም ተጠቅሷል፡፡

የሪፎርሙ ዋና ዓላማ በተቋማት የሚስተዋሉ የአሰራር ማነቆ፣ ሌብነት እና ብልሹ አሰራሮችን ለመዋጋት የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ለማስጠበቅ ፣ ተለማጭ የሆነ አደረጃጀት ለመፍጠር፣ አሰራሮችን ለማሻሻል፣ የስራ ተነሳሽነት እና ትጋት ያለው የሰው ኃይል ማፍራት ናቸው ተብሏል።

ቴክኖሎጂ መር አገልግሎቶችን ከመስጠት ባሻገር አገልግሎቶቹን ለሶስተኛ ወገን በማስተላለፍ ቀልጣፋ እና ተደራሽ ግልጋሎትን በመስጠት ጊዜ፣ ገንዘብ፣ እንግልት እና የመልካም አስተዳደር ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ እየተሰራ ስለመሆኑም የከንቲባ ፅህፈት ቤትን ዋቢ አድርጎ ኢቢሲ ዘግቧል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ ሶፍትዌር፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ ሶፍትዌር፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የጥቅም ግጭት (Conflict of interest) ምንነት

******************

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ መተግበሪያ፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ውጭ አገር ለመላክ ከግለሰቦች ገንዘብ የተቀበለችው ግለሰብ በጽኑ እስራት ተቀጣች

******************

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 22/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ) በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፍ የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጀኔራል ዐቃቤ ሕግ በህገ-ወጥ መንገድ ሰውን ለስራ ወደ ውጭ አገር ለመላክ ገንዘብ ከግለሰቦች ተቀብለሻል ባላት ግለሰብ ላይ ክስ መስርቶባት ክርክሩ ሲካሄድ ቆይቷል፡፡

ተከሳሽ ደመቀች ማጉጄ አቤቱ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የወንጀል ሕግ አንቀጽ 27/1/ እና በሰው የመነገድና ሰውን በሕገ-ወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣ አዋጅ ቁጥር 1178/2012 አንቀጽ 11/1/ ስር የተመለከተውን በመተላለፍ በዐቃቤ ሕግ ስድስት ክስ ቀርቦባታል፡፡

ተከሳሽ ወደ ውጭ አገር ሰውን ለስራ ለመላክ ፍቃድ ሳይኖራት ቀኑ በውል ተለይቶ ባልታወቀ ከሀምሌ ወር 2013 እስከ መስከረም ወር 2014 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ የተለያዩ 6 ተበዳዮችን ወደ ጆርዳን አገር ልኬ ስራ አስቀጥራችኋለሁ፣ ለዝግጅቱ እንደዚሁም ለህክምና ምርመራ ብር ትከፍላላችሁ በማለት ፓስፖርት እና ፎቶግራፍ በመቀበል፣ ከ1ኛ ተበዳይ 29 ሺህ 500 ብር፣ ከ2ኛ ተበዳይ 32 ሺህ 500 ብር፣ ከ3ኛ ተበዳይ 33 ሺህ 500 ብር፣ ከ4ኛ ተበዳይ 39 ሺህ ብር፣ ከ5ኛ ተበዳይ 25 ሺህ ብር፣ ከ6ኛ ተበዳይ 23 ሺህ ብር ተቀብላለች፡፡

ቀጥሎም ታህሳስ 12 ቀን 2014 ዓ.ም ከምሽቱ 4፡30 ሰዓት ጆርዳን አገር ስለምትሄዱ ቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ቀድማችሁ መድረስ አለባችሁ ብላ በመንገር እና ከሌሎች የግል ተበዳዮች ጋር ታክሲ በማሳፈር ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ሲሆን ቦሌ አየር ማረፊያ ካደረሰቻቸው በኋላ ግብረ-አበሯ የሆነውና ለጊዜው በቁጥጥር ስር ያልዋለ ግለሰብ የበረራ ትኬት ይዞ እየመጣ ነው በሚል ሲጠብቁ ሳይመጣ ቀርቶ የበረራ ሰዓት አልፎ ከምሽቱ 5፡00 ሰዓት ሲሆን ነገ ትሄዳላችሁ አሁን አልጋ ይዘን ታድራላችሁ በማለት እየተመለሱ እያለ በጸጥታ አካላት የተያዙ በመሆኑ ተከሳሽ በፈፀመችው በህገ-ወጥ መንገድ ሰውን ለስራ ወደ ውጭ አገር መላክ ሙከራ ወንጀል ዐቃቤ ህግ ክስ መስርቶባት ክርክር ሲደረግ ቆይቷል፡፡

ተከሳሽ በፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 20ኛ ወንጀል ችሎት ቀርባ የተከሰሰችበት ክስ በችሎት ተነቦላት ድርጊቱን አልፈፀምኩም በማለቷ የዐቃቤ ሕግ ማስረጃ ከተሰማ በኋላ ተከሳሽ እንድትከላከል ብይን ተሰጥቶ ተከሳሽ የመከላከያ ምስክሮችን አቅርባ ያሰማች ቢሆንም በዐቃቤ ሕግ የቀረበባትን ክስ መከላከል ባለመቻሏ ምክንያት ፍርድ ቤቱ በተከሳሿ ላይ የጥፋተኛነት ፍርድ በመስጠትና የቅጣት ውሳኔ በማሳረፍ በ14 ዓመት ጽኑ እስራት እና በ30 ሺ ብር የገንዘብ መቀጮ እንድትቀጣ እንዲሁም ከህዝባዊ መብቶቿ ለ5 ዓመት ታግዳ እንድትቆይ ሲል መወሰኑን ፍትህ ሚኒስቴር በፌስቡክ ገፁ መረጃውን አጋርቷል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ ሶፍትዌር(መተግበሪያ)፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀትና መገልገል የሚያስከትለው ተጠያቂነት

******************

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የጥቆማ ሶፍትዌር(መተግበሪያ)፡- https://epfs.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
የጥቆማ ኢሜል፡- CorruptionReportEthiopia@feacc.gov.et
ዩትዩብ፡- https://youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡