ሥነምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት በሚል መሪ ሀሳብ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አመራሮች በተለያዩ ዲስትሪክቶች ስልጠና ተሰጥቷል
*******************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 17/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ሥነምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት በሚል መሪ ሀሳብ በአዳማ እና በአሰላ ዲስትሪክት እንዲሁም በዋናው መስሪያ ቤት ለሚሰሩ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አመራሮች የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
ስልጠናው ሙስና እና ብልሹ አሰራር በሀገራዊ ኢኮኖሚ እድገት ላይ የሚያስከትለውን አስከፊ ጉዳት ለባንኩ መካከለኛ አመራሮች ግንዛቤ በማስጨበጥ ከተቋማቸው አልፈው ሀገራቸውን እንዲከላከሉ ለማስቻል ያለመ ነው።
በባንኩ ላይ የሚከሰቱ ሙስና እና የሙስና መከላከያ ስልቶች ላይ ትኩረት ያደረግው ስልጠና በዶ/ር በረከት ሰለሞን፣ በዶ/ር ይልቃል ሙሉአለም እና በዶ/ር እንድሪስ የባ እንዲሁም በዶ/ር ያሲን ሁሴን ለሁለት ቀናት ተሰጥቷል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
*******************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 17/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ሥነምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት በሚል መሪ ሀሳብ በአዳማ እና በአሰላ ዲስትሪክት እንዲሁም በዋናው መስሪያ ቤት ለሚሰሩ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አመራሮች የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
ስልጠናው ሙስና እና ብልሹ አሰራር በሀገራዊ ኢኮኖሚ እድገት ላይ የሚያስከትለውን አስከፊ ጉዳት ለባንኩ መካከለኛ አመራሮች ግንዛቤ በማስጨበጥ ከተቋማቸው አልፈው ሀገራቸውን እንዲከላከሉ ለማስቻል ያለመ ነው።
በባንኩ ላይ የሚከሰቱ ሙስና እና የሙስና መከላከያ ስልቶች ላይ ትኩረት ያደረግው ስልጠና በዶ/ር በረከት ሰለሞን፣ በዶ/ር ይልቃል ሙሉአለም እና በዶ/ር እንድሪስ የባ እንዲሁም በዶ/ር ያሲን ሁሴን ለሁለት ቀናት ተሰጥቷል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ወደ ራሱ አካውንት ብር ሲያስተላልፍ የነበረ የባንክ ሠራተኛ በቁጥጥር ስር ዋለ
*******************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 17/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ደቡበ ወሎ ዞን መቅደላ ወረዳ ዳሽን ባንክ ካሸር ላይ ሲሰራ የነበረ ሠራተኛ 3.2 ሚሊየን ብር ወደራሱ አካውንት ብር ሲያስተላልፍ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ በመጣራት ላይ መሆኑን የወረዳው ፖሊስ አስታውቋል፡፡
በመቅደላ ወረዳ የዳሽን ባንክ ሠራተኛው መጋቢት 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከሌሎች አካውንት ላይ 3 ሚልየን 200 ሺህ ብር ወደ ራሱ አካውንት ሲያስገባ የወረዳው ፖሊስ በደረሰው መረጃ መሠረት ግለሰቡን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራውን በማጣራት ላይ እንደሚገኝ ከአማራ ፖሊስ ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
የምርመራ ውጤቱን ተከታትሎ በቀጣይ እንደሚያሳውቅ ፖሊስ ገልጿል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
*******************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 17/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ደቡበ ወሎ ዞን መቅደላ ወረዳ ዳሽን ባንክ ካሸር ላይ ሲሰራ የነበረ ሠራተኛ 3.2 ሚሊየን ብር ወደራሱ አካውንት ብር ሲያስተላልፍ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ በመጣራት ላይ መሆኑን የወረዳው ፖሊስ አስታውቋል፡፡
በመቅደላ ወረዳ የዳሽን ባንክ ሠራተኛው መጋቢት 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከሌሎች አካውንት ላይ 3 ሚልየን 200 ሺህ ብር ወደ ራሱ አካውንት ሲያስገባ የወረዳው ፖሊስ በደረሰው መረጃ መሠረት ግለሰቡን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራውን በማጣራት ላይ እንደሚገኝ ከአማራ ፖሊስ ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
የምርመራ ውጤቱን ተከታትሎ በቀጣይ እንደሚያሳውቅ ፖሊስ ገልጿል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ሠራተኞች በቁጥጥር ስር ዋሉ
*******
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 17/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በወረዳ 2 በሰላምና ፀጥታ ኃላፊ የሚመራው የክትትል ቡድን በማደራጀት ከአያት እስከ ጣፎ አደባባይ ድረስ መንግስትና ህዝብ የሰጣቸውን ኃላፊነት ወደ ጎን በመተው ለራስ ያልተገባ ጥቅም በማዋል መኪናዎችን በማስቆም ገንዘብ ሲቀበሉ የነበሩ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ገቢዎች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሠራተኞች ላይ እርምጃ ተወስዷል።
ይህንን ወንጀል ሲፈፅሙ እጅ ከፈንጅ የተያዙት ተጠርጣሪ ወንጀለኞች 1ኛ ዳኛቸው ጎንፋ ዋቅጅራ ባለሙያ፣ 2ኛ ዳዊት ፍቅሬ እና 3ኛ ይልቃል ጌጤ (ሹፌር) በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፥ ግለሰቦቹ በፈፀሙት ያልተገባ ወንጀል ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
*******
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 17/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በወረዳ 2 በሰላምና ፀጥታ ኃላፊ የሚመራው የክትትል ቡድን በማደራጀት ከአያት እስከ ጣፎ አደባባይ ድረስ መንግስትና ህዝብ የሰጣቸውን ኃላፊነት ወደ ጎን በመተው ለራስ ያልተገባ ጥቅም በማዋል መኪናዎችን በማስቆም ገንዘብ ሲቀበሉ የነበሩ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ገቢዎች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሠራተኞች ላይ እርምጃ ተወስዷል።
ይህንን ወንጀል ሲፈፅሙ እጅ ከፈንጅ የተያዙት ተጠርጣሪ ወንጀለኞች 1ኛ ዳኛቸው ጎንፋ ዋቅጅራ ባለሙያ፣ 2ኛ ዳዊት ፍቅሬ እና 3ኛ ይልቃል ጌጤ (ሹፌር) በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፥ ግለሰቦቹ በፈፀሙት ያልተገባ ወንጀል ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ሥነምግባርን ያልተላበሰ አመራር የተቋሙን ተልዕኮ ሊያሳካ አይችልም - ም/ኮሚሽነር አቶ ፍቃዱ ሰቦቃ
****************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 18/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ሥነምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት በሚል መሪ ሀሳብ ለኢትዮጵያ ኤሌትሪክ አገልግሎት አመራሮች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።
የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የሥነምግባር ግንባታ ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ክቡር አቶ ፍቃዱ ሰቦቃ ሥነምግባርን ያልተላበሰ አመራር የተቋሙን ተልዕኮ ሊያሳካ አይችልም ብለዋል።
ኢትዮጵያ ኤሌትሪክ አገልግሎት ኤሌክትሪክን ለሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ የሚያከፋፍል ከዜጎች የዕለት ተዕለት ኑሮ ጋር ከፍተኛ ቁርኝት ያለው ትልቅ ተቋም ቢሆንም በዚሁ ልክ የዜጎችን ብሶት እና እሮሮ የሚበዛበት ተቋም መሆኑን ገልፀዋል።
ተቋሙ ላይ የሚስተዋሉ ከቆጣሪ ንባብ ጋር፣ መብራት አውቆ በማጥፋት ተገልጋዩን በማስገደድ ገንዘብ አምጡ ከማለት እና የኤሌትሪክ መቆራረጥ በሚፈጠርበት ወቅት ለጥገና የሚፈፀሙ የሙስና ወንጀሎች ህብረተሰቡ የሚማረርባቸው ብልሹ አሰራሮች የግዙፉን ተቋም ስም የሚያጠለሹ በአንዳንድ ሥነምግባር የጎደላቸው ሠራተኞች እና አመራሮች የሚፈፀም በመሆኑ አመራሩ በቁርጠኝነት ሊታገል ይገባዋል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢ/ር ጌቱ ገረመው በበኩላቸው ሙስና በመንግስትና በህዝብ ሃብትና ንብረት ላይ ስርቆት መፈጸም፣ ዝርፊያ ማካሄድ፣ ማጭበርበር፣ ህግና ሥርዓትን ተከትሎ ከመሥራት ይልቅ በዝምድና፣ በትውውቅ፣ በፖለቲካ ወገንተኝነት፣ በጐሰኝነት፣ በኃይማኖት ትስስር ላይ ተመርኩዞ በመሥራት አድሎ መፈፀም፣ ፍትህን ማጓደል፣ ስልጣንና ኃላፊነትን በህገወጥ መንገድ የግል ጥቅም ማግኛ የማድረግ እኩይ ተግባር ነው ብለዋል፡፡
ይህን አስነዋሪ ድርጊት በዘላቂነት መፍታት እና ከሙስና የጸዳ አገልገሎት መስጠት የሚቻለው ለህግ፣ ለሥርዓት እና አሠራር ተገዢ በመሆን፣ ሥራን በግልፅነትና በተጠያቂነት በመፈጸም፣ የሥነምግባር እና የሞራል ዕሴቶችን በማክበር፣ ራስን ከሙስና እና ብልሹ አሰራር በማራቅ፣ ሌብነትን በመዋጋት፣ አገልጋይና ለሌሎች አርዓያ መሆንን በተግባር ማረጋገጥ እንደሚገባ ገልፀዋል።
ኢ/ር ጌቱ ገረመው አክለውም ተቋማችን ሙስናንና ብልሹ አሰራርን ለማክሰም ከመቼውም ጊዜ በላይ ቁርጠኛ መሆኑን ለማረጋገጥ በቅርቡ አበልጽጎ ተግባራዊ ያደረገው የሞባይል መተግበሪያ አንዱ ማረጋገጫ መሆኑን ገልፀው፤ በየደረጃው የሚገኙ የተቋማችን አመራሮችና ፈጻሚዎች ሙስና እና ብልሹ አሰራርን በፅናት በመታገል የተጀመረውን ተቋማዊ የለውጥ ሥራ በውጤታማነት ማስቀጠል እንደሚገባ አሳስበዋል።
ስልጠናው በዶ/ር ይልቃል ሙሉአለም እና በዶ/ር እንድሪስ የባ እየተሰጠ ሲሆን፣ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
****************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 18/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ሥነምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት በሚል መሪ ሀሳብ ለኢትዮጵያ ኤሌትሪክ አገልግሎት አመራሮች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።
የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የሥነምግባር ግንባታ ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ክቡር አቶ ፍቃዱ ሰቦቃ ሥነምግባርን ያልተላበሰ አመራር የተቋሙን ተልዕኮ ሊያሳካ አይችልም ብለዋል።
ኢትዮጵያ ኤሌትሪክ አገልግሎት ኤሌክትሪክን ለሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ የሚያከፋፍል ከዜጎች የዕለት ተዕለት ኑሮ ጋር ከፍተኛ ቁርኝት ያለው ትልቅ ተቋም ቢሆንም በዚሁ ልክ የዜጎችን ብሶት እና እሮሮ የሚበዛበት ተቋም መሆኑን ገልፀዋል።
ተቋሙ ላይ የሚስተዋሉ ከቆጣሪ ንባብ ጋር፣ መብራት አውቆ በማጥፋት ተገልጋዩን በማስገደድ ገንዘብ አምጡ ከማለት እና የኤሌትሪክ መቆራረጥ በሚፈጠርበት ወቅት ለጥገና የሚፈፀሙ የሙስና ወንጀሎች ህብረተሰቡ የሚማረርባቸው ብልሹ አሰራሮች የግዙፉን ተቋም ስም የሚያጠለሹ በአንዳንድ ሥነምግባር የጎደላቸው ሠራተኞች እና አመራሮች የሚፈፀም በመሆኑ አመራሩ በቁርጠኝነት ሊታገል ይገባዋል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢ/ር ጌቱ ገረመው በበኩላቸው ሙስና በመንግስትና በህዝብ ሃብትና ንብረት ላይ ስርቆት መፈጸም፣ ዝርፊያ ማካሄድ፣ ማጭበርበር፣ ህግና ሥርዓትን ተከትሎ ከመሥራት ይልቅ በዝምድና፣ በትውውቅ፣ በፖለቲካ ወገንተኝነት፣ በጐሰኝነት፣ በኃይማኖት ትስስር ላይ ተመርኩዞ በመሥራት አድሎ መፈፀም፣ ፍትህን ማጓደል፣ ስልጣንና ኃላፊነትን በህገወጥ መንገድ የግል ጥቅም ማግኛ የማድረግ እኩይ ተግባር ነው ብለዋል፡፡
ይህን አስነዋሪ ድርጊት በዘላቂነት መፍታት እና ከሙስና የጸዳ አገልገሎት መስጠት የሚቻለው ለህግ፣ ለሥርዓት እና አሠራር ተገዢ በመሆን፣ ሥራን በግልፅነትና በተጠያቂነት በመፈጸም፣ የሥነምግባር እና የሞራል ዕሴቶችን በማክበር፣ ራስን ከሙስና እና ብልሹ አሰራር በማራቅ፣ ሌብነትን በመዋጋት፣ አገልጋይና ለሌሎች አርዓያ መሆንን በተግባር ማረጋገጥ እንደሚገባ ገልፀዋል።
ኢ/ር ጌቱ ገረመው አክለውም ተቋማችን ሙስናንና ብልሹ አሰራርን ለማክሰም ከመቼውም ጊዜ በላይ ቁርጠኛ መሆኑን ለማረጋገጥ በቅርቡ አበልጽጎ ተግባራዊ ያደረገው የሞባይል መተግበሪያ አንዱ ማረጋገጫ መሆኑን ገልፀው፤ በየደረጃው የሚገኙ የተቋማችን አመራሮችና ፈጻሚዎች ሙስና እና ብልሹ አሰራርን በፅናት በመታገል የተጀመረውን ተቋማዊ የለውጥ ሥራ በውጤታማነት ማስቀጠል እንደሚገባ አሳስበዋል።
ስልጠናው በዶ/ር ይልቃል ሙሉአለም እና በዶ/ር እንድሪስ የባ እየተሰጠ ሲሆን፣ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319