Federal Ethics And Anti- Corruption Commission
9.88K subscribers
10.4K photos
245 videos
32 files
3.05K links
Download Telegram
ስልጠናው በሥነምግባር የታነፀ አገልግሎት ለመስጠት እንዳነሳሳቸው የትራፊክ ፖሊስ አመራርና አባላት ተናገሩ

*******

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 15/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ስልጠናው በሥነምግባር የታነፀ አገልግሎት ለመስጠት እንዳነሳሳቸው የአዲስ አበባ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በሰጠው ስልጠና የተሳተፉ የትራፊክ ፖሊስ አመራርና አባላት መናገራቸው ተገልጿል።

ኮሚሽኑ ለሁሉም ክፍለ ከተማ የትራፊክ ፖሊስ ዲቭዥን አመራርና አባላት በሙያ ሥነምግባር እና ሙስና መከላከል ዙሪያ ለ13 ዙር ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል።

የትራፊክ ፖሊሲ አመራርና አባላት ሙያዊ ብቃትን ያረጋገጠና በህዝብ ዘንድ ታማኝ የሆነ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ ስልጠናውን የሰጡት በኮሚሽኑ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ስልጠና ዳ/ዳይሬክተር አቶ ጀንበሩ ኢርኮ ገልጸዋል።

የሥነምግባር ጉድለት ታማኝነትን ይሸረሽራል፣ ማህበራዊ ተቀባይነትን ያሳጣል፣ ጤናማ የሥራ ግንኙነትን ይቀንሳል እንዲሁም የጥቅም ግጭት ይፈጥራል ብለዋል።

ስልጠናው በሁሉም ክፍለ ከተማ ለሚገኙ የትራፊክ ፖሊስ አመራርና አባላት በዙር ሲሰጥ የነበረው ስልጠና በስኬት መጠናቀቁን አቶ ጀንበሩ ጠቅሰዋል።

በስልጠናው የተሳተፉት የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ትራፊክ ፖሊስ ዲቭዥን ዋና ኢንስፔክተር ጌቱ ግርማ ስልጠናው በሥነምግባር የታነፀ አገልግሎት ለመስጠት እንዳነሳሳቸው ተናግረዋል።

በስልጠናው ያገኙትን እውቀት ወደ ተግባር በመቀየር ህብረተሰባችንን በመልካም ሥነምግባር ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን መግለፃቸውን ከኮሚሽኑ የማህበራዊ ትስስር ገፅ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

ስልጠናው ከፍተኛ እውቀትና ልምድ ባለው አሰልጣኝ የተሰጠ በመሆኑ በመልካም ሥነምግባር ማገልገል የሚያስገኘውን ጠቀሜታ በመረዳት ለተሻለ ሥራ ያነሳሳ መሆኑን በስልጠናው የተሳተፉት ኢንስፔክተር እሌኒ ሙሴ ተናግረዋል።

የወሰድነው ስልጠና በግል ህይወታችንና በሥራችን ለውጥ የሚያመጣ መሆኑን ተረድተን ህዝብና ሀገርን ሙያዊ ሥነምግባርን በተላበሰ መልኩ ለማገልገል እንደተነሳሱ በስልጠናው የተሳተፉት ዋና ሳጅን ትዕግስት ታየው ገልፀዋል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

#NCRS ሞባይል መተግበሪያ

#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details

#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
የንብረት ማስመለስ አዋጁ አስፈላጊነት እና ይዞ የመጣው አዲስ ነገር (ክፍል ሶስት)

********************

1. የንብረት ማስመለስ ሥራ ኃላፊነትን በተመለከተ የተሰጠ ስልጣን ወይም ኃላፊነት፡- የንብረት ማስመለስ ሥራ የብዙ ተቋማት ቅንጅትን/ትብብርን የሚፈልግ ሥራ ሆኖ በተማከለ ሁኔታ በአንድ የህግ ማስከበር ተቋም/ዐቃቤ ህግ የሚመራ ስራ ነው፡፡ የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽንም ለንብረት ማስመለስ አዋጁ አጋዥና መነሻ የሚሆን የሀብት ማወቅና ምዝገባ እንዲሁም የማጣራት ሥራ እየሰራ ይገኛል፡፡ ይህም ለንብረት ማስመለስ አዋጁ ጉልህ አስተዋጽኦ አለው፡፡

2. ዐቃቤ ህግ ራሱ በሚመረምርበት ጉዳይ ላይ ዕግድ ትዕዛዝ በራሱ ማውጣቱ ከማረጋገጥ፣ ሚዛናዊነት እንዲሁም ከገለልተኛነት አንፃር የማይጋጭ ስለመሆኑ፤ በተመሳሳይ እንደማንኛውም የመንግስት ሥራ ስራው ለብልሹ አሰራር ሊጋለጥ ይችላል፡፡ ነገር ግን ዋናው ቁምነገር ዜጎች ላልተገባ የመብት ጥሰት እንዳይዳረጉ ምን መንገድ አለ የሚለው ጉዳይ ነው፡፡ በመሠረቱ በዚህ አዋጅ ዐቃቤ ህግ ተቋም አንድም አስተዳደራዊ በሆነ መልኩ ውርስ ሊፈፅም የሚችልበት ምንም መብት አልሰጠም፡፡ የትኛውም ክርክርም ሆነ ውርስ ትዕዛዝ መስጠት የሚችለው ፍርድ ቤት ነው፡፡ በፍርድ ቤት ደግሞ አንዱ ፍርድ ቤት ላይ የተፈፀመን የትኛውንም አይነት ስህተት የማስተካከያ የይግባኝ ስርዓት መኖሩ የታወቀ ነው፡፡

ስለዚህ ከምርመራ የይግባኝ ደረጃውን አልፎ እንስከሚሰጥ የመጨረሻ ውሳኔ ድረስ ሊደርሱ የሚችሉ የሥነምግባር ግድፈቶችን የሚጣሩበት እና ሊስተካከሉ የሚችልበትን ሥርዓት አለው፡፡ ከዚህ ወጪ ፍትህ ሚኒስቴር ግልፀኝነት የሚፈጥር እና ይህ ስርዓት የሚመራበትን ውስጣዊ የአሠራር ስርዓቶችን በህግ የሚዘረጋ ይሆናል፡፡ ይህም ጠንካራ የሥነምግባር ክትትል እና አቤቱታ መቀበያ ስርዓትንም ያካትታል፡፡

3. ዐቃቤ ህግ ራሱ በሚመረምርበት ጉዳይ ላይ ዕግድ ትዕዛዝ በራሱ ማውጣቱ ከማረጋገጥ፣ ሚዛናዊነት እንዲሁም ከገለልተኛነት አንፃር የማይጋጭ ስለመሆኑ፤ ይህ ጉዳይ በዐቃቤ ህግ ለ72 ሰዓት አስተዳደራዊ ዕግድ የሚሰጥበትን ጉዳይ በተመለከተ ሲሆን፣ ይህም በተመሳሳይ በዚህ ህግ አዲስ የመጣ አይደለም፡፡ በህግ ስርዓታችን ውስጥ ቀድሞም የነበረ ነው፡፡ በፊት ዐቃቤ ህግ ኃላፊ 48 ሰዓት የማገድ ስልጣኑን በዚህ ህግ ወደ 72 ሰዓት ከፍ እንዲል አድርጓል፡፡ በመሰረቱ ይህ የዕግድ ሁኔታ መርህ ሳይሆን ልዩ ሁኔታ ነው፡፡ ስለዚህ በጠባቡ ነው ስራ ላይ የሚውለው፡፡

አንደኛ ይህን ዕግድ ዐቃቤ ህግ ሳይሆን የተቋሙ/የዘርፉ የበላይ ኃላፊ ብቻ ነው ሊሰጥ የሚችለው፡፡ ስለዚህ በዘፈቀደ ለሁሉም ባለሙያ የተሰጠ ስልጣን አለመሆኑን ማስተዋል ያስፈልጋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ይህ ዕግድ ግዜያዊ እንጂ ገደብ አልባ እና እስከመጨረሻው ጸንቶ የሚቆይ አይደለም፡፡ ዐቃቤ ህግ ይህን ዕግድ ካሰጠ በኋላ መደበኛ ዕግድ ለፍርድ ቤት አቅረቦ ማስቀየር አለበት፡፡ ይህ ካልሆነ ግን በአዋጁ የተቀመጡትን የጊዜ ገደቦች ውስጥ ዕግዱ ቀሪ የሚሆንበትን አግባብ ተመላክቷል፡፡ ወደ 72 ሰዓት ከፍ ያለው ከዚህ በፊት የነበረው የ48 ሰዓት ዕግድ በተግባር ውጤታማነቱ ላይ ተግዳሮት ስለገጠመው ነው፡፡

4. የመያዝና የዕግድ ትዕዛዝ የማያርፍባቸው የንብረት አይነቶች፤ የእለት መተዳደሪያ ወይም ሙያዊ ሥራ ለመስራት የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶች፣ የቤት ውስጥ መገልገያ የሆኑ ዕቃዎች፣ ለእለት ኑሮ የሚሆን እና የስድስት ወር ወይም ፍርድ ቤቱ በልዩ ሁኔታ ለሚወስነው ጊዜ የሚቆይ ስንቅ (ለምግብነት የሚውል) ንብረቶች በመርህ ደረጃ ሊያዙ ወይም ሊታገዱ አይችሉም፡፡ ሆኖም ቁሳቁሶቹ ውድ ከሆኑ ማዕድናት ወይም ከፍተኛ ዋጋ ካለው የእደ ጥበብ ሥራዎች የተሰሩ ከሆነ ወይም ንብረቱ የወንጀል ፍሬ መሆኑ በግልጽ ከታወቀ በምንም ዓይነት ሁኔታ ተጠርጣሪው ወይም ተከሳሹ ከወንጀል ፍሬው የመጠቀም መብት ስለማይኖረው የዕግድ ወይም የመያዝ ትዕዛዝ ያርፍበታል፡፡

5. የተወረሰ ንብረት በተመለከተ (እጣ ፈንታ)፤ በወንጀል የተገኘ ሀብትን ከማስመለስ አንጻር በአለምዓቀፍ ደረጃ የተቀመጡ ስምምነቶች እና የአፈጻጸም ግምገማ ሰነዶች እንዳስቀመጡት አንድ ሀገር በጣም ተጋላጭ የሆነባቸውን የተደራጁና ኢኮኖሚያዊ ወንጀሎች የሚለይበትን ጥናት ማከናወን እንዳለበት እና በዚህ መንገድ የተለዩ ወንጀሎችን በመለየት፣ በመመርመር፣ በመክሰስ፣ ተገቢውንና አስተማሪ ቅጣት በመጣል እንዲሁም የተመዘበረውን ሀብት በማስመለስ ተገቢውን የህግ ማስከበር ስራ መስራት እንዳለበት ሲያስገነዝቡ፣ ከዚህ አሠራር ጀርባ ያለው ምክንያት ደግሞ ውስን የሆነውን ሀብት ለህግ የበላይነት እና የፍትህ ስራ ለማዋል ቅድሚያ የሚሰጠው በጣም ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ለሚያደርሰው ወንጀል አይነት ነው በሚል ነው፡፡

ስለሆነም ሁሉንም ወንጀል መርምሮ ክስ ለማቅረብ እና ወደ ፍርድ ቤት ለመውሰድ በቂ ሀብት እንደማይኖር የታወቀ በመሆኑ ምክንያት አንዳንድ ሀገራት በወንጀል የተገኘ ነው በሚል መርምረውና ክስ አቅርበው በፍርድ ቤት እንዲወረስ ውሳኔ የሚያሰጡበትን ንብረት መልሰው ለወንጀል ፍትህ አስተዳደር ተግባር ያውላሉ፡፡ በዚህ አግባብ ይህ የንብረት ማስመለስ አዋጅ ተመሳሳይ አቋም በመያዝ ከፋይናንስ ሚኒስቴር ጋር በመነጋገር የተወሰነውን የተወረሰ ሀብት ለወንጀል ፍትህ አስተዳደር ለማዋል የሚቻልበትን ሁኔታ አስቀምጧል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

#NCRS ሞባይል መተግበሪያ

#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details

#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ኮሚሽነር ሳሙኤል ኡርቃቶ (ፒኤችዲ) በሥነምግባር ግንባታ እና ሙስና መከላከል ዙሪያ ከአዘርባጃን አምባሳደር ሩስላን ናስቦቭ ጋር ተወያዩ

***************

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 16/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሳሙኤል ኡርቃቶ (ፒኤችዲ) በሥነምግባር ግንባታ እና ሙስና መከላከል ዙሪያ ከአዘርባጃን አምባሳደር ሩስላን ናስቦቭ ጋር ውይይት አካሂደዋል፡፡

በውይይቱ የአዘርባጃን የመልካም ሥነምግባር እና የሙስና መከላከል ባህል ግንባታ ዙሪያ የተገኙ ውጤቶች እንደመልካም ተሞክሮ የሚወሰዱ መሆኑ ተመላክቷል።

በቀጣይም በአገራችን የተጀመረውን የሥነምግባር ግንባታ፣ የሙስና ቅድመ-መከላከል እና የሙስና ወንጀል ሕግ የማስከበር ሥራዎችን ለማሻሻል የሚያስችል የልምድ ልውውጥ የሚደረግ መሆኑ ተገልጿል።

ይህን ትብብር ለማጠናከር በቀጣይ በኢትዮጵያ እና አዛርባጃን የፀረ-ሙስና ተቋማት መካከል የትብብር ስምምነት ለመፈራረም ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

#NCRS ሞባይል መተግበሪያ

#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details

#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
የሙስና ወንጀል ህግ የማስከበር ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራርን ማዘመን አስፈላጊ ነው - ም/ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

*******************

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 16/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የሙስና ወንጀል ሕግ የማስከበር ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራርን ማዘመን አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።

የሙስና ወንጀል ሕግ የማስከበር ሥራዎች የባለድርሻ ተቋማት የምክክር መድረክ ዛሬ ተካሂዷል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ የትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ፤ በውይይታችን የባለድርሻ አካላቱ ቅንጅታዊ አሰራርና የስራ አፈጻጸም ምን እንደሚመስል ምክክር አድርገናል ብለዋል።

ተቋማቱ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ቅንጅታዊ አሰራርን በማዘመን፣ በፀረ-ሙስና ትግል ሀገራዊ የጋራ ተልዕኮን ማዕከል በማድረግ የሚያከናውኗቸውን ተግባራት አጠናክረው እንዲቀጥሉ አቅጣጫ መቀመጡንም አመላክተዋል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

#NCRS ሞባይል መተግበሪያ

#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details

#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319