በ26 ዘርፎች ላይ የተጀመሩ የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ስራዎችን አጠናክረን እንቀጥላለን - ክቡር አቶ እሸቴ አስፋው
********
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 13/2017 ዓ.ም አዳማ) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በዘርፎች የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወር የሥራ አፈፃፀም እና በኮሚሽኑ በሁሉም ዘርፎች ላይ በተደረገ የሱፐርቪዥን ሪፖርትና ግብረ-መልስ ላይ የግምገማ መድረክ አካሄዷል።
በመድረኩ የተገኙት በኮሚሽኑ የሙስና መከላከል ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ክቡር አቶ እሸቴ አስፋው በ26 ዘርፎች ላይ የተጀመሩ የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ስራዎችን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።
ሙስና እና ብልሹ አሠራርን ለመከላከል በተቋማት ላይ ያሉ የውስጥ ኦዲት፣ ህግ አገልግሎት፣ ተቋማዊ ለውጥ እና የሥነምግባር መከታተያ ክፍል ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተቀናጅተው መስራት እንዳለባቸው ገልፀዋል።
በቀጣይም ለህብረተሰቡ እሮሮ የሆኑ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚስተዋሉ ብልሹ አሠራሮችን መከላከል ላይ በማተኮር እንሰራለን ብለዋል።
የኮሚሽኑ የሥነምግባር ግንባታ ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ክቡር አቶ ፍቃዱ ሰቦቃ በበኩላቸው የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች ከተቋማት አመራሮች ጋር ያላችሁን ግንኙነት፣ ቅንጅትና ትብብር በማጠናከር የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ሥራዎችን ውጤታማ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በቀጣይ የሱፐርቪዥን ሥራን አንዱ ዘርፍ ሌላውን የሚያይበት አሠራርን በመከተል እርስ በርዕስ ልምድ የምትለዋወጡበትና አቅም የምትገነባቡበት ይሆናል ብለዋል።
የተጀመረውን ዘርፍ ተኮር የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ሥልጠናውን አጠናክረን በማስቀጠል ሁሉንም ዘርፎች ተደራሽ እንደሚሆን ተናግረዋል።
በመድረኩ የዘርፎች የ6 ወር የሥራ አፈፃፀም እና በኮሚሽኑ በሁሉም ዘርፎች ላይ የተደረገው የሱፐርቪዥን ሪፖርትና ግብረ-መልስ ቀርቦ ግምገማ ተካሄዶበታል።
በሌላ መድረክም በተቋማት በአዲስ ለተመደቡ የሥነምግባር መከታተያ ክፍል ዳሬክተሮች እና ባለሙያዎች የሥራ ማስጀመሪያ ስልጠና፣ ብሔራዊ የሙስና መቀበያ መተግበሪያ ላይ እንዲሁም በዲጂታል የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ ሥርዓት (EARS) ላይ ስልጠና ተሰጥቷል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
********
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 13/2017 ዓ.ም አዳማ) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በዘርፎች የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወር የሥራ አፈፃፀም እና በኮሚሽኑ በሁሉም ዘርፎች ላይ በተደረገ የሱፐርቪዥን ሪፖርትና ግብረ-መልስ ላይ የግምገማ መድረክ አካሄዷል።
በመድረኩ የተገኙት በኮሚሽኑ የሙስና መከላከል ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ክቡር አቶ እሸቴ አስፋው በ26 ዘርፎች ላይ የተጀመሩ የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ስራዎችን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።
ሙስና እና ብልሹ አሠራርን ለመከላከል በተቋማት ላይ ያሉ የውስጥ ኦዲት፣ ህግ አገልግሎት፣ ተቋማዊ ለውጥ እና የሥነምግባር መከታተያ ክፍል ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተቀናጅተው መስራት እንዳለባቸው ገልፀዋል።
በቀጣይም ለህብረተሰቡ እሮሮ የሆኑ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚስተዋሉ ብልሹ አሠራሮችን መከላከል ላይ በማተኮር እንሰራለን ብለዋል።
የኮሚሽኑ የሥነምግባር ግንባታ ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ክቡር አቶ ፍቃዱ ሰቦቃ በበኩላቸው የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች ከተቋማት አመራሮች ጋር ያላችሁን ግንኙነት፣ ቅንጅትና ትብብር በማጠናከር የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ሥራዎችን ውጤታማ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በቀጣይ የሱፐርቪዥን ሥራን አንዱ ዘርፍ ሌላውን የሚያይበት አሠራርን በመከተል እርስ በርዕስ ልምድ የምትለዋወጡበትና አቅም የምትገነባቡበት ይሆናል ብለዋል።
የተጀመረውን ዘርፍ ተኮር የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ሥልጠናውን አጠናክረን በማስቀጠል ሁሉንም ዘርፎች ተደራሽ እንደሚሆን ተናግረዋል።
በመድረኩ የዘርፎች የ6 ወር የሥራ አፈፃፀም እና በኮሚሽኑ በሁሉም ዘርፎች ላይ የተደረገው የሱፐርቪዥን ሪፖርትና ግብረ-መልስ ቀርቦ ግምገማ ተካሄዶበታል።
በሌላ መድረክም በተቋማት በአዲስ ለተመደቡ የሥነምግባር መከታተያ ክፍል ዳሬክተሮች እና ባለሙያዎች የሥራ ማስጀመሪያ ስልጠና፣ ብሔራዊ የሙስና መቀበያ መተግበሪያ ላይ እንዲሁም በዲጂታል የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ ሥርዓት (EARS) ላይ ስልጠና ተሰጥቷል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ወድቆ ያገኘውን 26 ሺህ ብር የመለሰው የኮሚሽኑ ባለሙያ ምስጋና ተቸረው
********
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 13/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የቤንሻንጉል ጉሙዝ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የስልጠና ባለሙያ አቶ አወቀ ገ/መስቀል ከሶስት ጓደኞቹ ጋር መንገድ ላይ ሲንቀሳቀስ ወድቆ ያገኘውን 26,000 ( ሃያ ስድስት ሺህ) ብር ለባለቤቱ በመመለሱ ምስጋና ተችሮታል።
አቶ አወቀ 26 ሺህ ብሩን ከሶስት የሥራ ባልደረቦቹ ጋር በመንገድ ሲንቀሳቀስ ቀድሞ በማየትና በማንሳት ለጓደኞቹ ብር እንዳገኘ ይናገራል፥ ጓደኞቹ ግን አላመኑም፤ ነገር ግን በሚያምነው ኃይማኖት ሲምልላቸው ለማመን ተገደዋል።
የተገኘውም ብር ተቆጥሮ መጠኑ ታወቀ፥ የብሩ ባለቤትም አድራሻ ተገኘና ተደውሎ ቦታው ድረስ በመምጣት 26 ሺህ ብር እንደጠፋበት ተናገረ፤ ብሩ በላቡ ያፈራው መሆኑ በመረጋገጡ በምስክር ፊት ገንዘቡ ሊሰጠው ችሏል፡፡ በምላሹም ምስጋናቸውን ለአቶ አወቀ ችረዋል፡፡
አቶ አወቀ በየመድረኩ የሚያስተምሩትን የሥነምግባር ስልጠና እና የብልሹ አሰራር አፀያፊነት በተግባር በማሳየታቸው ለሌሎች ያስተምራል በሚል ኮሚሽኑ በማህበራዊ ትስስር ገፁ መረጃውን አጋርቷል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
********
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 13/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የቤንሻንጉል ጉሙዝ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የስልጠና ባለሙያ አቶ አወቀ ገ/መስቀል ከሶስት ጓደኞቹ ጋር መንገድ ላይ ሲንቀሳቀስ ወድቆ ያገኘውን 26,000 ( ሃያ ስድስት ሺህ) ብር ለባለቤቱ በመመለሱ ምስጋና ተችሮታል።
አቶ አወቀ 26 ሺህ ብሩን ከሶስት የሥራ ባልደረቦቹ ጋር በመንገድ ሲንቀሳቀስ ቀድሞ በማየትና በማንሳት ለጓደኞቹ ብር እንዳገኘ ይናገራል፥ ጓደኞቹ ግን አላመኑም፤ ነገር ግን በሚያምነው ኃይማኖት ሲምልላቸው ለማመን ተገደዋል።
የተገኘውም ብር ተቆጥሮ መጠኑ ታወቀ፥ የብሩ ባለቤትም አድራሻ ተገኘና ተደውሎ ቦታው ድረስ በመምጣት 26 ሺህ ብር እንደጠፋበት ተናገረ፤ ብሩ በላቡ ያፈራው መሆኑ በመረጋገጡ በምስክር ፊት ገንዘቡ ሊሰጠው ችሏል፡፡ በምላሹም ምስጋናቸውን ለአቶ አወቀ ችረዋል፡፡
አቶ አወቀ በየመድረኩ የሚያስተምሩትን የሥነምግባር ስልጠና እና የብልሹ አሰራር አፀያፊነት በተግባር በማሳየታቸው ለሌሎች ያስተምራል በሚል ኮሚሽኑ በማህበራዊ ትስስር ገፁ መረጃውን አጋርቷል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
አሜሪካ በቀድሞ የአርጀንቲና ፕሬዝዳንት “ከፍተኛ የሙስና ወንጀል” ውንጀላ ተከትሎ የጉዞ እገዳ መጣሏን ገለፀች
********
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 14/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የቀድሞ የአርጀንቲና ፕሬዝዳንት ክሪስቲና ፈርናንዴዝ በቢሮ ውስጥ በነበሩበት ጊዜ "በከፍተኛ ሙስና" ውስጥ ተሳትፋለች በሚል ክስ ምክኒያት ወደ ዩናይትድ ስቴትስ እንዳይገቡ ከልክሏቸዋል።
የአርጀንቲና የቀድሞ ፕሬዚዳንት የሆኑት ክሪስቲና ኤሊሳቤት ፈርናንዴዝ ዴ ኪርችነር ('CFK') እና የአርጀንቲና የቀድሞ የፕላን ሚኒስትር ጁሊዮ ሚጌል ዴ ቪዶ ('ዴ ቪዶ') እንዲሁም ቤተሰቦቻቸውን ጭምር የጉዞ እገዳ የተጣለባቸው መሆኑ ተመላክቷል።
ኪርችነር እና ዴ ቪዶ "የሕዝብ ሥራ ኮንትራቶችን የሚያካትቱ በርካታ የጉቦ ስልቶችን በማደራጀት እና በገንዘብ ጥቅም በማግኘት ቦታቸውን አላግባብ በመጠቀም ከአርጀንቲና መንግስት በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር ተዘርፏል" ሲሉ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ አርብ ዕለት በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል።
የተለያዩ ፍርድ ቤቶች ጥንዶቹን በሙስና ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው የፈረደባቸው መሆኑንም ጠቁመዋል።
"ዩናይትድ ስቴትስ የህዝብን ስልጣን ለግል ጥቅማቸው ለሚጠቀሙ ግለሰቦችን ተጠያቂነትን ማራመዷን ትቀጥላለች" ሲል ሩቢዮ ተናግሯል። "እነዚህ ውሳኔዎች ከፍተኛ የመንግስት እርከኖችን ጨምሮ ዓለምአቀፍ ሙስናን ለመከላከል ያለንን ቁርጠኝነት ያረጋግጣሉ" ብለዋል።
በኖቬምበር ላይ የአርጀንቲና ፍርድ ቤት በፈርናንዴዝ ላይ የስድስት አመት እስራት እና የእድሜ ልክ እገዳን ማፅናቱ አስታውሶ ኤንቢሲ ኒውስ ዘግቧል።
የቀድሞዋ ፕሬዝዳንት በስልጣን ዘመናቸው በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ በህዝብ ስራ ፕሮጀክቶች በመመዝበር በ2022 በሶስት ዳኞች ተከሰው ተፈርዶባቸዋል። ይግባኝ ቢጠይቁም ከፍተኛው ፍርድ ቤት የመጀመሪያውን ብይን ማፅናቱ ተገልጿል።
ፈርናንዴዝ ሁሉንም ክሶች ውድቅ በማድረግ እስር ቤት የወጡ ሲሆን፥ በደቡብ አሜሪካ አገር ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ዋና የፖለቲካ መሪ መሆናቸው ተመላክቷል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
********
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 14/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የቀድሞ የአርጀንቲና ፕሬዝዳንት ክሪስቲና ፈርናንዴዝ በቢሮ ውስጥ በነበሩበት ጊዜ "በከፍተኛ ሙስና" ውስጥ ተሳትፋለች በሚል ክስ ምክኒያት ወደ ዩናይትድ ስቴትስ እንዳይገቡ ከልክሏቸዋል።
የአርጀንቲና የቀድሞ ፕሬዚዳንት የሆኑት ክሪስቲና ኤሊሳቤት ፈርናንዴዝ ዴ ኪርችነር ('CFK') እና የአርጀንቲና የቀድሞ የፕላን ሚኒስትር ጁሊዮ ሚጌል ዴ ቪዶ ('ዴ ቪዶ') እንዲሁም ቤተሰቦቻቸውን ጭምር የጉዞ እገዳ የተጣለባቸው መሆኑ ተመላክቷል።
ኪርችነር እና ዴ ቪዶ "የሕዝብ ሥራ ኮንትራቶችን የሚያካትቱ በርካታ የጉቦ ስልቶችን በማደራጀት እና በገንዘብ ጥቅም በማግኘት ቦታቸውን አላግባብ በመጠቀም ከአርጀንቲና መንግስት በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር ተዘርፏል" ሲሉ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ አርብ ዕለት በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል።
የተለያዩ ፍርድ ቤቶች ጥንዶቹን በሙስና ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው የፈረደባቸው መሆኑንም ጠቁመዋል።
"ዩናይትድ ስቴትስ የህዝብን ስልጣን ለግል ጥቅማቸው ለሚጠቀሙ ግለሰቦችን ተጠያቂነትን ማራመዷን ትቀጥላለች" ሲል ሩቢዮ ተናግሯል። "እነዚህ ውሳኔዎች ከፍተኛ የመንግስት እርከኖችን ጨምሮ ዓለምአቀፍ ሙስናን ለመከላከል ያለንን ቁርጠኝነት ያረጋግጣሉ" ብለዋል።
በኖቬምበር ላይ የአርጀንቲና ፍርድ ቤት በፈርናንዴዝ ላይ የስድስት አመት እስራት እና የእድሜ ልክ እገዳን ማፅናቱ አስታውሶ ኤንቢሲ ኒውስ ዘግቧል።
የቀድሞዋ ፕሬዝዳንት በስልጣን ዘመናቸው በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ በህዝብ ስራ ፕሮጀክቶች በመመዝበር በ2022 በሶስት ዳኞች ተከሰው ተፈርዶባቸዋል። ይግባኝ ቢጠይቁም ከፍተኛው ፍርድ ቤት የመጀመሪያውን ብይን ማፅናቱ ተገልጿል።
ፈርናንዴዝ ሁሉንም ክሶች ውድቅ በማድረግ እስር ቤት የወጡ ሲሆን፥ በደቡብ አሜሪካ አገር ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ዋና የፖለቲካ መሪ መሆናቸው ተመላክቷል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
በአፈር ማዳበሪያ አቅርቦትና ሥርጭት ዙሪያ በሕገወጥ ነጋዴዎች እና ደላሎች የነበሩ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ በተሰራው ሥራ ከፍተኛ ለውጥ መጥቷል - ሚኒስቴሩ
****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 14/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት እና ሥርጭት ዙሪያ በሕገወጥ ነጋዴዎች፣ ደላሎች እና በማዳበሪያ ግዥ ሥርዓት ዙሪያ የነበሩ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ በተሰራው ሥራ ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን የግብርና ሚኒስቴር የኢንቨስትመንትና ግብዓት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ሶፍያ ካሳ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦትና ስርጭትን ከተለምዶ (ከወረቀት) አሠራር ወደ ዲጂታል ማሸጋገር ወቅታዊና የመንግስት የትኩረት አቅጣጫ መሆኑንና ይህንን ሥራ የሚያግዝ ሶፍትዌር እየበለጸገ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
እየለማ የሚገኘው ሶፍትዌር የአርሶ አደሩ የማዳበሪያ ፍላጎት በመሬቱ ልክና በሰብል ዓይነት መሆኑን ከማረጋገጥ ባሻገር በስርጭት ወቅት የሚያጋጥሙ ችግሮችንና ብልሹ አሠራሮችን ለመቅረፍ ትልቅ ፋይዳ እንዳለውም አንስተዋል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልም በተሳካ ሁኔታ ሙከራ እየተደረገ እንደሚኝ መናገራቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል።
በመድረኩ በቀረበው የመወያያ ሰነድ መነሻነት ተሳታፊዎች ሀሳብና አስተያየት ያቀረቡ ሲሆን፥ በሚኒስቴሩ አመራሮች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶበታል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 14/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት እና ሥርጭት ዙሪያ በሕገወጥ ነጋዴዎች፣ ደላሎች እና በማዳበሪያ ግዥ ሥርዓት ዙሪያ የነበሩ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ በተሰራው ሥራ ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን የግብርና ሚኒስቴር የኢንቨስትመንትና ግብዓት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ሶፍያ ካሳ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦትና ስርጭትን ከተለምዶ (ከወረቀት) አሠራር ወደ ዲጂታል ማሸጋገር ወቅታዊና የመንግስት የትኩረት አቅጣጫ መሆኑንና ይህንን ሥራ የሚያግዝ ሶፍትዌር እየበለጸገ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
እየለማ የሚገኘው ሶፍትዌር የአርሶ አደሩ የማዳበሪያ ፍላጎት በመሬቱ ልክና በሰብል ዓይነት መሆኑን ከማረጋገጥ ባሻገር በስርጭት ወቅት የሚያጋጥሙ ችግሮችንና ብልሹ አሠራሮችን ለመቅረፍ ትልቅ ፋይዳ እንዳለውም አንስተዋል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልም በተሳካ ሁኔታ ሙከራ እየተደረገ እንደሚኝ መናገራቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል።
በመድረኩ በቀረበው የመወያያ ሰነድ መነሻነት ተሳታፊዎች ሀሳብና አስተያየት ያቀረቡ ሲሆን፥ በሚኒስቴሩ አመራሮች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶበታል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
የትውልድን ሥነምግባር ማነፅ፣ የአገረ-መንግስት ግንባታ መሠረት ነው!
***************
በአገራችን የትውልድ ሥነምግባር በኃላፊነት እና በተጠያቂነት ከመገንባት አንጻር ወላጆች፣የቤተሰብ አባላት፣ ህብረተሰቡና የትምህርት ተቋማት እንዲሁም የኃይማኖት ተቋማትና ሚዲያ የሚኖራቸው ሚና የማይተካ ነው፡፡ ወላጆች እና የቤተሰብ አባላት፣ ትውልድን በሥነምግባር እና በሞራል እሴቶች በማነጽ፣ የአገራችን የፀረ-ሙስና ትግል ውጤታማ እንዲሆን ከፍተኛ ሚና መጫወት ይገባቸዋል። በተለይም የሥነምግባር ዝቅጠት ያጋጠመው የቤተሰብ አባል ሲያጋጥመው ተገቢው ክትትል እና ድጋፍ ካልተደረገ በቀር፣ አንድ የቤተሰብ አባል በሙስና እና ብልሹ አሰራር ችግሮች የመዘፈቅ አጋጣሚዎች ይሰፋሉ።
በተለይም፣ ቤተሰብ ውስጥ ምንጩ ያልታወቀ ሀብት የሚያንቀሳቅስ አባል ሲገኝ፣ በዝምታ የሚታለፍ ወይም በማሞካሸት መቀበል፣ የቤተሰብ አባላትን የሚያፈርስ የመሆን ዕድል ይኖረዋል። በመሆኑም በአገራችን ወላጅና ቤተሰብ-ተኮር የትውልድ ሥነምግባር ግንባታ እና ሙስና መከላከል ትኩረት ተሰጥቶ መሠራት ያለበት በመሆኑ፣ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተለይም የማህበራዊ ዘርፍ ተቋማት በተልዕኳቸው በተገቢው በማካተት መተግበር ይገባል።
ቤተሰብ ትውልድን በመልካም ሥነምግባር ለመገንባት ትልቅ ኃላፊነት ካላቸው ማህበራዊ ተቋማት መካከል አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ ልጆች ወደ ማህበረሰቡ የሚቀላቀሉት ከቤተሰብ የገነቡትን እሴት ይዘው ነው፡፡ ዛሬ በአደባባይ የሚያሸልሙም ሆነ የሚያስወግዙ ተግባሮች የአስተዳደግ ድምር ውጤቶች ናቸው፡፡ የዛሬዎቹ ህፃናት የነገዎቹ ሀገር ተረካቢዎች በሥነምግባራቸው እንዲመሰገኑ ወይም እንዲወገዙ የቤተሰብ ድርሻ ትልቁን ቦታ ይይዛል፡፡ ወቅቱ የመረጃ ዘመን እንደመሆኑ ልዩ ልዩ መረጃዎች በተለያዩ መንገዶች ሊገኙ ይችላሉ፡፡
መልካም ሥነምግባር የማግኛ ዋነኛ መንገድ ግን ቤተሰብ ነው፡፡ ስለዚህ ቤተሰብ በመልካም ሥነምግባር ለልጆች የቅርብ አርዓያ በመሆን፣ ልጆች ጥሩውን ከመጥፎው እንዲለዩ በመምከርና በማስተማር፣ በጥሩ እሴቶች ጎልብተው እንዲያድጉ በመርዳት በመልካም ሥነምግባር የተገነባ ትውልድ የመቅረጽ ኃላፊነትን መወጣት ይኖርበታል፡፡ ያን ጊዜ ለራሱና ለሀገሩ ታማኝ የሆነ ትውልድ ማፍራት ይቻላል፡፡
ሌላው ለትውልድ ሥነምግባር ግንባታ መሠረት ህብረተሰቡ ነው፡፡ በየትኛውም የሥራ መስክ የተሰማሩ ሰዎች ምንጫቸው ማህበረሰቡ ነው፡፡ በሥነምግባሩ ጠንካራ የሆነ ማህበረሰብ በሥነምግባር ጉድለት የሚከሰቱ ወንጀሎች ተጠቂ ወይም ሰለባ አይሆንም፡፡ ስለዚህ ህብረተሰቡ ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ መልካም ሥነምግባር እሴቶችን እያጎለበተ፣ በስግብግብነትና በሙስና የሚገኝ ብልጽግናን እያወገዘ በመልካም ሥነምግባር የተገነባ ትውልድ የመቅረፁን ኃላፊነት መወጣት አለበት፡፡
በተጨማሪም ለትውልድ ሥነምግባር ግንባታ መሠረት የትምህርት ተቋማት ናቸው፡፡ ከቤተሰብና ከህብረተሰቡ ቀጥሎ ትውልዱን በመልካም ሥነምግባር ለመገንባት ትልቅ ኃላፊነት ያለባቸው የትምህርት ተቋማት ናቸው፡፡ መምህራን ከሚሰጡት የትምህርት እውቀት ባሻገር በሥነምግባራቸው አርዓያ ሊሆኑ ይገባል፡፡ ከተፃፈው ሥርዓተ ትምህርት ባሻገር መምህራን የሚያደርጉት ተግባርና እያንዳንዱ እንቅስቃሴ ሌላው በተማሪዎች የሚነበብ ድብቁ ሥርዓተ ትምህርት ነው፡፡
ስለዚህ ተማሪዎች የሚያነቡት ሁለቱንም ስርዓተ ትምህርቶች ነውና መምህራን በመልካም ሥነምግባር ጭምር አርዓያ ሊሆኑላቸው ይገባል፡፡ ዛሬ ለተማሪዎቹ አርዓያ መሆን ያልቻለ መምህር ነገ በተለያዩ ተቋማት ከሚሰሩ ተማሪዎቹ መልካም ሥነምግባርን ወይም ከብልሹ አሰራር የፀዳ አገልግሎትን መጠበቅ የለበትም፡፡ ከመምህሩ ሌላ በትምህርት ተቋማት ውስጥ በየደረጃው ያሉ የአስተዳደር ሠራተኞች በሚሰጡት መልካም አገልግሎት ለተማሪዎቻቸው አርዓያ ሊሆኑ ይገባል፡፡ ይህንን በማድረግም በመልካም ሥነምግባር የተገነባ ትውልድን የመገንባት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል፡፡
እንዲሁም ለትውልድ ሥነምግባር ግንባታ መሠረት የኃይማኖት ተቋማት ናቸው፡፡ የትውልድን ሥነምግባር በመቅረጽ ረገድ የኃይማኖት ተቋማት ትልቅ ኃላፊነት አለባቸው፡፡ ምዕመናን ወደሚያመልኩበት ተቋም የሚመጡት በፈቃዳቸው ነው፡፡ በእምነታቸው ውስጥ ያሉ እሴቶችንም ወደውና ፈቅደው ይጠብቋቸዋል፡፡ ይህ ትውልድን በመልካም ሥነምግባር ለመቅረጽ ትልቅ አጋጣሚ ነው፡፡ በመሆኑም እያንዳንዱ የእምነት ተቋም ምዕመኑን ስለመልካም ሥነምግባር በማስተማር፣ በእየተሰማራበት ቦታም የመልካም ሥነምግባር ፍሬዎችን እንዲያሳይ በማበረታታትና በመምከር በመልካም ሥነምግባር የተገነባ ዜጋን የመፍጠር ኃላፊነት አለባቸው፡፡
ለትውልድ ሥነምግባር ግንባታ መሠረት የአንበሳውን ሚና ከሚጫወቱት መካከል የሚዲያ ተቋማት ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ሚዲዎች የህብረተሰቡን ግንዛቤ ለማስጨበጥ ድርሻቸው የጎላ መሆኑና ወጣቱ ትውልድም በስፋት እየተጠቀመበት የሚገኝ ነው፡፡ በተለይም ማህበራዊ ሚዲያው ወጣቱ ትውልድ ላይ ትልቅ ተፅዕኖ እየፈጠረ ያለ የሚዲያ አንዱ አካል ነው፡፡ በመሆኑም ትውልድን በመልካም ሥነምግባር በመገንባት መልካም እሴቶችን የሚጠብቁ፣ በሀገሪቱ የልማት እንቅስቃሴ የበኩላቸውን ድርሻ የሚያበረክቱበትና በእድገቱም ተጠቃሚ እንዲሆኑ ትውልድን በመልካም ሥነምግባር እንዲታነፁ በማድረግ የሚዲያ ተቋማት ድርሻቸውን ሊወጡ ይገባል፡፡
ከነዚህ በተጨማሪ ለትውልድ ሥነምግባር ግንባታ መሠረት የመንግስትና የግል ተቋማት ተጠቃሽ ናቸው፡፡ የመንግስትም ሆኑ የግል ተቋማት ሠራተኞቻቸውን በመልካም ሥነምግባር የመገንባት ኃላፊነት አለባቸው፡፡ እቅዳቸውን ለማሳካት የተመደበላቸውን በጀትና ንብረት በአግባቡ ለመጠቀም በመልካም ሥነምግባር የተገነባ ሠራተኛ ያስፈልጋቸዋል፡፡ ስለዚህ የሥነምግባር ጉዳይን አጀንዳቸው አድርገው ከየእለት ተግባራቸው ጋር ሊያስተሳስሩት ይገባል፡፡ እሴቶቻችን ናቸው ብለው ያወጧቸው ቁምነገሮችም ከፅሁፍ አልፈው በእያንዳንዱ ሠራተኛ የዕለት ተዕለት የሥራ ውሎ ላይ ማንፀባረቅ አለባቸው፡፡
መልካም ሥነምግባር በቅጥር፣ በሠራተኛ ምልመላ፣ በእድገትና ዝውውር ላይ ትኩረት ተሰጥቶት ሊሰራ ይገባል፡፡ የሥራ ኃላፊዎችም ሠራተኞቻቸው መልካም ሥነምግባርን የሚያጎለብቱበት ስልጠናዎችን ከማመቻቸት ባሻገር ራሳቸው የመልካም ሥነምግባር አርዓያ ሆነው መገኘት ይጠበቅባቸዋል፡፡
በአጠቃላይ በትውልድ ሥነምግባር እና ሞራል እሴት ግንባታ ተገቢውን ሚና ከመወጣት አንፃር ሁሉም አካላት ትኩረት ማድረግ አስፈላጊ ነው። በሥነምግባር የታነፀ ትውልድ፣ ሙስና እና ብልሹ አሠራርን ከመጠየፍ ባሻገር ይታገላል፣ ለአገር-መንግስት ግንባታም የላቀ ሚና መጫወት ይችላል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
***************
በአገራችን የትውልድ ሥነምግባር በኃላፊነት እና በተጠያቂነት ከመገንባት አንጻር ወላጆች፣የቤተሰብ አባላት፣ ህብረተሰቡና የትምህርት ተቋማት እንዲሁም የኃይማኖት ተቋማትና ሚዲያ የሚኖራቸው ሚና የማይተካ ነው፡፡ ወላጆች እና የቤተሰብ አባላት፣ ትውልድን በሥነምግባር እና በሞራል እሴቶች በማነጽ፣ የአገራችን የፀረ-ሙስና ትግል ውጤታማ እንዲሆን ከፍተኛ ሚና መጫወት ይገባቸዋል። በተለይም የሥነምግባር ዝቅጠት ያጋጠመው የቤተሰብ አባል ሲያጋጥመው ተገቢው ክትትል እና ድጋፍ ካልተደረገ በቀር፣ አንድ የቤተሰብ አባል በሙስና እና ብልሹ አሰራር ችግሮች የመዘፈቅ አጋጣሚዎች ይሰፋሉ።
በተለይም፣ ቤተሰብ ውስጥ ምንጩ ያልታወቀ ሀብት የሚያንቀሳቅስ አባል ሲገኝ፣ በዝምታ የሚታለፍ ወይም በማሞካሸት መቀበል፣ የቤተሰብ አባላትን የሚያፈርስ የመሆን ዕድል ይኖረዋል። በመሆኑም በአገራችን ወላጅና ቤተሰብ-ተኮር የትውልድ ሥነምግባር ግንባታ እና ሙስና መከላከል ትኩረት ተሰጥቶ መሠራት ያለበት በመሆኑ፣ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተለይም የማህበራዊ ዘርፍ ተቋማት በተልዕኳቸው በተገቢው በማካተት መተግበር ይገባል።
ቤተሰብ ትውልድን በመልካም ሥነምግባር ለመገንባት ትልቅ ኃላፊነት ካላቸው ማህበራዊ ተቋማት መካከል አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ ልጆች ወደ ማህበረሰቡ የሚቀላቀሉት ከቤተሰብ የገነቡትን እሴት ይዘው ነው፡፡ ዛሬ በአደባባይ የሚያሸልሙም ሆነ የሚያስወግዙ ተግባሮች የአስተዳደግ ድምር ውጤቶች ናቸው፡፡ የዛሬዎቹ ህፃናት የነገዎቹ ሀገር ተረካቢዎች በሥነምግባራቸው እንዲመሰገኑ ወይም እንዲወገዙ የቤተሰብ ድርሻ ትልቁን ቦታ ይይዛል፡፡ ወቅቱ የመረጃ ዘመን እንደመሆኑ ልዩ ልዩ መረጃዎች በተለያዩ መንገዶች ሊገኙ ይችላሉ፡፡
መልካም ሥነምግባር የማግኛ ዋነኛ መንገድ ግን ቤተሰብ ነው፡፡ ስለዚህ ቤተሰብ በመልካም ሥነምግባር ለልጆች የቅርብ አርዓያ በመሆን፣ ልጆች ጥሩውን ከመጥፎው እንዲለዩ በመምከርና በማስተማር፣ በጥሩ እሴቶች ጎልብተው እንዲያድጉ በመርዳት በመልካም ሥነምግባር የተገነባ ትውልድ የመቅረጽ ኃላፊነትን መወጣት ይኖርበታል፡፡ ያን ጊዜ ለራሱና ለሀገሩ ታማኝ የሆነ ትውልድ ማፍራት ይቻላል፡፡
ሌላው ለትውልድ ሥነምግባር ግንባታ መሠረት ህብረተሰቡ ነው፡፡ በየትኛውም የሥራ መስክ የተሰማሩ ሰዎች ምንጫቸው ማህበረሰቡ ነው፡፡ በሥነምግባሩ ጠንካራ የሆነ ማህበረሰብ በሥነምግባር ጉድለት የሚከሰቱ ወንጀሎች ተጠቂ ወይም ሰለባ አይሆንም፡፡ ስለዚህ ህብረተሰቡ ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ መልካም ሥነምግባር እሴቶችን እያጎለበተ፣ በስግብግብነትና በሙስና የሚገኝ ብልጽግናን እያወገዘ በመልካም ሥነምግባር የተገነባ ትውልድ የመቅረፁን ኃላፊነት መወጣት አለበት፡፡
በተጨማሪም ለትውልድ ሥነምግባር ግንባታ መሠረት የትምህርት ተቋማት ናቸው፡፡ ከቤተሰብና ከህብረተሰቡ ቀጥሎ ትውልዱን በመልካም ሥነምግባር ለመገንባት ትልቅ ኃላፊነት ያለባቸው የትምህርት ተቋማት ናቸው፡፡ መምህራን ከሚሰጡት የትምህርት እውቀት ባሻገር በሥነምግባራቸው አርዓያ ሊሆኑ ይገባል፡፡ ከተፃፈው ሥርዓተ ትምህርት ባሻገር መምህራን የሚያደርጉት ተግባርና እያንዳንዱ እንቅስቃሴ ሌላው በተማሪዎች የሚነበብ ድብቁ ሥርዓተ ትምህርት ነው፡፡
ስለዚህ ተማሪዎች የሚያነቡት ሁለቱንም ስርዓተ ትምህርቶች ነውና መምህራን በመልካም ሥነምግባር ጭምር አርዓያ ሊሆኑላቸው ይገባል፡፡ ዛሬ ለተማሪዎቹ አርዓያ መሆን ያልቻለ መምህር ነገ በተለያዩ ተቋማት ከሚሰሩ ተማሪዎቹ መልካም ሥነምግባርን ወይም ከብልሹ አሰራር የፀዳ አገልግሎትን መጠበቅ የለበትም፡፡ ከመምህሩ ሌላ በትምህርት ተቋማት ውስጥ በየደረጃው ያሉ የአስተዳደር ሠራተኞች በሚሰጡት መልካም አገልግሎት ለተማሪዎቻቸው አርዓያ ሊሆኑ ይገባል፡፡ ይህንን በማድረግም በመልካም ሥነምግባር የተገነባ ትውልድን የመገንባት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል፡፡
እንዲሁም ለትውልድ ሥነምግባር ግንባታ መሠረት የኃይማኖት ተቋማት ናቸው፡፡ የትውልድን ሥነምግባር በመቅረጽ ረገድ የኃይማኖት ተቋማት ትልቅ ኃላፊነት አለባቸው፡፡ ምዕመናን ወደሚያመልኩበት ተቋም የሚመጡት በፈቃዳቸው ነው፡፡ በእምነታቸው ውስጥ ያሉ እሴቶችንም ወደውና ፈቅደው ይጠብቋቸዋል፡፡ ይህ ትውልድን በመልካም ሥነምግባር ለመቅረጽ ትልቅ አጋጣሚ ነው፡፡ በመሆኑም እያንዳንዱ የእምነት ተቋም ምዕመኑን ስለመልካም ሥነምግባር በማስተማር፣ በእየተሰማራበት ቦታም የመልካም ሥነምግባር ፍሬዎችን እንዲያሳይ በማበረታታትና በመምከር በመልካም ሥነምግባር የተገነባ ዜጋን የመፍጠር ኃላፊነት አለባቸው፡፡
ለትውልድ ሥነምግባር ግንባታ መሠረት የአንበሳውን ሚና ከሚጫወቱት መካከል የሚዲያ ተቋማት ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ሚዲዎች የህብረተሰቡን ግንዛቤ ለማስጨበጥ ድርሻቸው የጎላ መሆኑና ወጣቱ ትውልድም በስፋት እየተጠቀመበት የሚገኝ ነው፡፡ በተለይም ማህበራዊ ሚዲያው ወጣቱ ትውልድ ላይ ትልቅ ተፅዕኖ እየፈጠረ ያለ የሚዲያ አንዱ አካል ነው፡፡ በመሆኑም ትውልድን በመልካም ሥነምግባር በመገንባት መልካም እሴቶችን የሚጠብቁ፣ በሀገሪቱ የልማት እንቅስቃሴ የበኩላቸውን ድርሻ የሚያበረክቱበትና በእድገቱም ተጠቃሚ እንዲሆኑ ትውልድን በመልካም ሥነምግባር እንዲታነፁ በማድረግ የሚዲያ ተቋማት ድርሻቸውን ሊወጡ ይገባል፡፡
ከነዚህ በተጨማሪ ለትውልድ ሥነምግባር ግንባታ መሠረት የመንግስትና የግል ተቋማት ተጠቃሽ ናቸው፡፡ የመንግስትም ሆኑ የግል ተቋማት ሠራተኞቻቸውን በመልካም ሥነምግባር የመገንባት ኃላፊነት አለባቸው፡፡ እቅዳቸውን ለማሳካት የተመደበላቸውን በጀትና ንብረት በአግባቡ ለመጠቀም በመልካም ሥነምግባር የተገነባ ሠራተኛ ያስፈልጋቸዋል፡፡ ስለዚህ የሥነምግባር ጉዳይን አጀንዳቸው አድርገው ከየእለት ተግባራቸው ጋር ሊያስተሳስሩት ይገባል፡፡ እሴቶቻችን ናቸው ብለው ያወጧቸው ቁምነገሮችም ከፅሁፍ አልፈው በእያንዳንዱ ሠራተኛ የዕለት ተዕለት የሥራ ውሎ ላይ ማንፀባረቅ አለባቸው፡፡
መልካም ሥነምግባር በቅጥር፣ በሠራተኛ ምልመላ፣ በእድገትና ዝውውር ላይ ትኩረት ተሰጥቶት ሊሰራ ይገባል፡፡ የሥራ ኃላፊዎችም ሠራተኞቻቸው መልካም ሥነምግባርን የሚያጎለብቱበት ስልጠናዎችን ከማመቻቸት ባሻገር ራሳቸው የመልካም ሥነምግባር አርዓያ ሆነው መገኘት ይጠበቅባቸዋል፡፡
በአጠቃላይ በትውልድ ሥነምግባር እና ሞራል እሴት ግንባታ ተገቢውን ሚና ከመወጣት አንፃር ሁሉም አካላት ትኩረት ማድረግ አስፈላጊ ነው። በሥነምግባር የታነፀ ትውልድ፣ ሙስና እና ብልሹ አሠራርን ከመጠየፍ ባሻገር ይታገላል፣ ለአገር-መንግስት ግንባታም የላቀ ሚና መጫወት ይችላል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319