Federal Ethics And Anti- Corruption Commission
9.89K subscribers
10.4K photos
245 videos
32 files
3.04K links
Download Telegram
ባንካችን አዲስ እንደመሆኑ መጠን የብልሹ አሠራር ችግሮች ከመከሰታቸው በፊት በእንጭጩ ሊቀጩ ይገባል - አቶ ታደሰ ሐጥያ

********

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 13/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ‘‘ሥነምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት’’ በሚል መሪ ሀሳብ ለሲዳማ ባንክ አመራሮች ለሁለት ቀናት የሥነምግባር ግንባታ እና ሙስና መከላከል ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

በሥልጠናው የተገኙት የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ታደሰ ሐጥያ ሙስና በአገራችን ሁለንተናዊ እድገት ላይ ፀር ነው። ባንኮች ላይ ሲፈጸም ደግሞ ልንታገለው ይገባል፥ ጸያፍም ተግባር ነው ብለዋል።

አቶ ታደሰ ሐጥያ አክለውም ባንካችን አዲስ እንደመሆኑ መጠን የብልሹ አሠራር ችግሮች ከመከሰታቸው በፊት በእንጭጩ ሊቀጩ ይገባል ብለዋል።

በባንኩ ላይ የሚከሰቱ ሙስና እና የሙስና መከላከያ ስልቶች ላይ ትኩረት ያደረግው ስልጠና በዶ/ር ምረተዓብ አብርሃም ተሰጥቷል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

#NCRS ሞባይል መተግበሪያ

#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details

#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319