ኮሚሽኑ ለአዲስ አበባ ትራፊክ ፓሊስ አመራርና አባላት በተለያየ ዙር ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና ማጠናቀቁን አስታወቀ
****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 12/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአዲስ አበባ ከተማ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ለከተማው ትራፊክ ፓሊስ አመራርና አባላት በሙያዊ ሥነምግባር፣ በብልሹ አሰራር ተጋላጭነት እና በሙስና መከላከል ዙሪያ በተለያየ ዙር ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ማጠናቀቁን አስታወቀ።
በስልጠና ማጠቃለያ የተገኙት የኮሚሽኑ ም/ኮሚሽነር መቅደስ ተስፋዬ በተለያዩ ዙር በከተማችን የሚገኙ ሁሉንም የትራፊክ ፓሊስ አመራርና አባላት በስልጠናው እንዲሳተፉ ማድረግ መቻሉን ገልፀዋል።
ስልጠናው የተሻለ አቅም የሚፈጥርና ህብረተሰባችሁን ሥነምግባር በተላበሰ መልኩ እንድታገለግሉ የሚረዳ እንደሆነ አስባለሁ ብለዋል።
ም/ኮሚሽነሯ አያይዘውም ተቋማችን በቀጣይ ከአዲስ አበባ ፓሊስ ትራፊክ መምሪያ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በስልጠናው የተሳተፉ አባላት በተግባር ስራዎቻቸው ላይ ተጨባጭ ለውጦችን አምጥቷል ወይስ አላመጣም የሚለው ዳሰሳ የሚደረግበት መሆኑንም አስታውቀዋል።
የአዲስ አበባ ትራፊክ ፓሊስ መምሪያ የቀጠና 4 ኃላፊ የሆኑት ኮማንደር ትዕግስት ኃይሉ በበኩላቸው ኮሚሽኑ በተለያየ ዙር ለአባላቶቻችን የሥራ ላይ ሥነምግባርና ብልሹ አሰራርን መከላከል ላይ ስልጠና መስጠት በመቻሉ ምስጋና አቅርበው አባሎቻችን በቀጣይ ወደ መደበኛ ስራዎቻችን ስንመለስ ከስልጠናውን ያገኘነውን እውቀትና ተሞክሮ ተግባራዊ ማድረግ ይጠበቃል ብለዋል።
የኮሚሽኑ የሥነምግባር ስልጠና ዳ/ዳይሬክተር አቶ ጀንበሩ ኢርኮ ስልጠናውን በሰጡበት ወቅት እንደገለፁት የትራፊክ ፖሊስ አባላት ሙያዊ ሥነምግባር ተላብሰው፤ ከብልሹ አሰራር ፀድተው ተግባራትን ማከናወናቸው በሰው ህይወት እና በንብረት ላይ የሚደርስ አደጋ እንዲቀንስ አይነተኛ ሚና ይጫወታል ብለዋል፡፡
አክለውም አባላቱ በሙያ ሥነምግባር መታነፃቸው የሙያውን ቅቡልነት ከፍ በማድረግ አዎንታዊ ፋይዳው የጎላ መሆኑን በመድረኩ ማመላከታቸውን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
ሰልጣኝ የትራፊክ ፓሊሶች በበኩላቸው የተሰጠው ስልጠና ለስራቸው የተሻለ አቅም የፈጠረላቸው መሆኑን ገልፀው፥ በቀጣይ በስራዎቻችን ላይ የሚስተዋሉ ትናንሽ ክፍተቶችን በማረም ተግባር ላይ ለማዋል እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 12/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአዲስ አበባ ከተማ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ለከተማው ትራፊክ ፓሊስ አመራርና አባላት በሙያዊ ሥነምግባር፣ በብልሹ አሰራር ተጋላጭነት እና በሙስና መከላከል ዙሪያ በተለያየ ዙር ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ማጠናቀቁን አስታወቀ።
በስልጠና ማጠቃለያ የተገኙት የኮሚሽኑ ም/ኮሚሽነር መቅደስ ተስፋዬ በተለያዩ ዙር በከተማችን የሚገኙ ሁሉንም የትራፊክ ፓሊስ አመራርና አባላት በስልጠናው እንዲሳተፉ ማድረግ መቻሉን ገልፀዋል።
ስልጠናው የተሻለ አቅም የሚፈጥርና ህብረተሰባችሁን ሥነምግባር በተላበሰ መልኩ እንድታገለግሉ የሚረዳ እንደሆነ አስባለሁ ብለዋል።
ም/ኮሚሽነሯ አያይዘውም ተቋማችን በቀጣይ ከአዲስ አበባ ፓሊስ ትራፊክ መምሪያ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በስልጠናው የተሳተፉ አባላት በተግባር ስራዎቻቸው ላይ ተጨባጭ ለውጦችን አምጥቷል ወይስ አላመጣም የሚለው ዳሰሳ የሚደረግበት መሆኑንም አስታውቀዋል።
የአዲስ አበባ ትራፊክ ፓሊስ መምሪያ የቀጠና 4 ኃላፊ የሆኑት ኮማንደር ትዕግስት ኃይሉ በበኩላቸው ኮሚሽኑ በተለያየ ዙር ለአባላቶቻችን የሥራ ላይ ሥነምግባርና ብልሹ አሰራርን መከላከል ላይ ስልጠና መስጠት በመቻሉ ምስጋና አቅርበው አባሎቻችን በቀጣይ ወደ መደበኛ ስራዎቻችን ስንመለስ ከስልጠናውን ያገኘነውን እውቀትና ተሞክሮ ተግባራዊ ማድረግ ይጠበቃል ብለዋል።
የኮሚሽኑ የሥነምግባር ስልጠና ዳ/ዳይሬክተር አቶ ጀንበሩ ኢርኮ ስልጠናውን በሰጡበት ወቅት እንደገለፁት የትራፊክ ፖሊስ አባላት ሙያዊ ሥነምግባር ተላብሰው፤ ከብልሹ አሰራር ፀድተው ተግባራትን ማከናወናቸው በሰው ህይወት እና በንብረት ላይ የሚደርስ አደጋ እንዲቀንስ አይነተኛ ሚና ይጫወታል ብለዋል፡፡
አክለውም አባላቱ በሙያ ሥነምግባር መታነፃቸው የሙያውን ቅቡልነት ከፍ በማድረግ አዎንታዊ ፋይዳው የጎላ መሆኑን በመድረኩ ማመላከታቸውን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
ሰልጣኝ የትራፊክ ፓሊሶች በበኩላቸው የተሰጠው ስልጠና ለስራቸው የተሻለ አቅም የፈጠረላቸው መሆኑን ገልፀው፥ በቀጣይ በስራዎቻችን ላይ የሚስተዋሉ ትናንሽ ክፍተቶችን በማረም ተግባር ላይ ለማዋል እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ባንካችን አዲስ እንደመሆኑ መጠን የብልሹ አሠራር ችግሮች ከመከሰታቸው በፊት በእንጭጩ ሊቀጩ ይገባል - አቶ ታደሰ ሐጥያ
********
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 13/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ‘‘ሥነምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት’’ በሚል መሪ ሀሳብ ለሲዳማ ባንክ አመራሮች ለሁለት ቀናት የሥነምግባር ግንባታ እና ሙስና መከላከል ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
በሥልጠናው የተገኙት የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ታደሰ ሐጥያ ሙስና በአገራችን ሁለንተናዊ እድገት ላይ ፀር ነው። ባንኮች ላይ ሲፈጸም ደግሞ ልንታገለው ይገባል፥ ጸያፍም ተግባር ነው ብለዋል።
አቶ ታደሰ ሐጥያ አክለውም ባንካችን አዲስ እንደመሆኑ መጠን የብልሹ አሠራር ችግሮች ከመከሰታቸው በፊት በእንጭጩ ሊቀጩ ይገባል ብለዋል።
በባንኩ ላይ የሚከሰቱ ሙስና እና የሙስና መከላከያ ስልቶች ላይ ትኩረት ያደረግው ስልጠና በዶ/ር ምረተዓብ አብርሃም ተሰጥቷል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
********
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 13/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ‘‘ሥነምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት’’ በሚል መሪ ሀሳብ ለሲዳማ ባንክ አመራሮች ለሁለት ቀናት የሥነምግባር ግንባታ እና ሙስና መከላከል ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
በሥልጠናው የተገኙት የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ታደሰ ሐጥያ ሙስና በአገራችን ሁለንተናዊ እድገት ላይ ፀር ነው። ባንኮች ላይ ሲፈጸም ደግሞ ልንታገለው ይገባል፥ ጸያፍም ተግባር ነው ብለዋል።
አቶ ታደሰ ሐጥያ አክለውም ባንካችን አዲስ እንደመሆኑ መጠን የብልሹ አሠራር ችግሮች ከመከሰታቸው በፊት በእንጭጩ ሊቀጩ ይገባል ብለዋል።
በባንኩ ላይ የሚከሰቱ ሙስና እና የሙስና መከላከያ ስልቶች ላይ ትኩረት ያደረግው ስልጠና በዶ/ር ምረተዓብ አብርሃም ተሰጥቷል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319