Federal Ethics And Anti- Corruption Commission
9.89K subscribers
10.4K photos
245 videos
32 files
3.04K links
Download Telegram
ሁለቱ ኮሚሽኖች በጋራ በሚሰሩባቸው ጉዳዮች ላይ የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ

****

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 12/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከክልሉ ብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ሥነምግባር ኮሚሽን ጋር በአመራርና በአባላት ውስጥ ሥነምግባር ለማስረጽና ሙስናን በጋራ ለመከላከል የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።

የመግባቢያ ስምምነቱን የብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ሥነምግባር ኮሚሽን ሰብሳቢ እና የኢፌድሪ የመከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ማርታ ሉዊጂ፣ የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ማሞ ቴጋ፣ የክልሉ ኢንስፔክሽንና ሥነምግባር ኮሚሽን ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብዱልዋሪስ ጀማል በተገኙበት ተፈርሟል።

ስምምነቱ በዘመናዊ መንገድ ጥናቶችን በማጥናት የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ እንዲሁም ቀልጣፋና ፍትሃዊ ከሙስና የጸዳ አገልግሎት ለህብረተሰቡ ለማድረስ መሰረት የሚጥል መሆኑ ተገልጿል።

እንዲሁም የፓርቲው አመራሮችና አባላት የተሰጣቸውን ኃላፊነትና ተልዕኮ በብቃት እንዲወጡ፣ በሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ላይ የተሻለ አቅም እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ተመላክቷል።

በፓርቲው አመራሮችና አባላት መካከል በሥነምግባር፣ በአቅም ግንባታ፣ በሙስና መከላከል እና በሌሎች ጉዳዮች ላይ መረጃዎችን ለመለዋወጥና ጥናቶችን ለማድረግ የመግባቢያ ስምምነቱ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው መገለፁን ከክልሉ የብልፅግና ፓርቲ የማህበራዊ ትስስር ገፅ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

#NCRS ሞባይል መተግበሪያ

#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details

#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
በኦሮሚያ ክልል በሙስና የተገኘ ሀብትን ከማስመለስ አንጻር ውጤታማ ስራ ተከናውኗል

****

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 12/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በኦሮሚያ ክልል በሙስና የተገኘ ሀብት በማስመለስ እና የወንጀሉ ተሳታፊዎችን ተጠያቂ ከማድረግ አንጻር ውጤታማ ስራ መከናወኑን የክልሉ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ገለፀ።

የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ኃላፊ አቶ ጉዮ ዋሪዮ፥ በክልሉ በሙስና የተገኘ ሀብትን ከማስመለስና ወንጀለኞችን ተጠያቂ ከማድረግ አንጻር በተከናወኑ ስራዎች ላይ ያተኮረ መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም፥ በክልሉ በበጀት ዓመቱ ያለፉት ወራት የተመዘበረ የመንግስት፣ የልማት ድርጅቶች እና የህዝብ ሀብት ለማስመለስ በኩል ከፍተኛ ጥረት ሲደረግ ቆይቷል።

በዚህም ባለፉት 9 ወራት 1 ሺህ 197 የሙስና ወንጀል ምርመራ መደረጉን ተናግረው፥ ምርመራ ከተደረገባቸው መዝገቦች ውስጥም 1 ሺህ 163 መዝገቦች ውሳኔ ማግኘታቸውን ገልጸዋል።

ውሳኔ በተሰጠባቸው የተለያዩ መዝገብ ተከሳሾችም ከአንድ አመት እስከ እድሜ ልክ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ የተደረገ ሲሆን፥ በገንዘብም ከ2 ሺህ እስከ 100 ሺህ ብር የሚደርስ ቅጣት እንደተጣላባቸው ተናግረዋል።

የሙስና ወንጀሎቹ በዋናነት ከመሬት አስተዳደር፣ ከማዕድን ፍለጋና ማውጣት ስራዎች እንዲሁም ከመንግስት ግዥና ክፍያ ጋር በተያያዙ ጉዳዮች የተፈፀሙ ናቸው ብለዋል።

የሙስና ወንጀል ውጤት እንደሆኑ የተጠረጠሩ በርካታ ንብረቶች ታግደው ምርመራ ሲደረግባቸው መቆየቱን ጠቅሰው፥ በሙስና ወንጀል የተገኘውን ሀብት ከማስመለስ አንጻርም 1 ቢሊዮን 157 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ሃብት ተመላሽ መደረጉን አቶ ጉዮ ዋረዮ አስታወቋል።

ከዚህም ባለፈ ከ1 ቢሊዮን 2 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመቱ ንብረቶች ታግደው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑንም አስረድተዋል።

የሙስና ወንጀል ለመከላከል በሚደረገው ስራ የህዝብ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፥ ህብረተሰቡ ጥቆማ በመስጠት እንዲያግዝ መጠየቃቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

#NCRS ሞባይል መተግበሪያ

#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details

#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319