የትውልድን ሥነምግባር ለመገንባትና ሙስናን ለመከላከል ቅንጅታዊ አሰራርን መፍጠር አስፈላጊ መሆኑ ተገለፀ
************************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 10/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአማራ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ደሴ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለዴሞክራሲ ተቋማትና ለአጋር አካላት ባለሙያዎች በኮምቦልቻ ከተማ ስልጠና መስጠቱን ገልጿል፡፡
የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሀብታሙ ሞገስ ስልጠናው ቀጣይ በምናካሂደው የትውልድ ሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ስራዎች ላይ በቅንጅት የምንሰራበትን የጋራ ማድረግ ላይ ታሳቢ ያደረገ ነው ብለዋል፡፡
የሞራል እሴት በመገንባት የአገልግሎት አሰጣጥን ማሻሻልና ብልሹ አሠራርን መከላከል እንዲሁም የሙስና ወንጀል ድንጋጌዎች በሚሉ ርዕሰ ጉዳይ ዙሪያ የቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል የስልጠና ባለሙያ በሆኑት አቶ አብዱ መሀመድና አቶ ሀብታሙ አሰፋ ስልጠናው ተሰጥቷል።
የስልጠናው አላማ የሞራል ግንባታን በተቋማት ተግባራዊ በማድረግ የአመለካከት ለውጥ ለማምጣትና ሙስናን ለመከላከል መሆኑ ተገልጿል።
ተሳታፊዎች በበኩላቸው ሰው አስተሳሰቡ ካልተቀየረ በቀር በቅጣት ስለማይማር ሰውን ለመግራትና ሙስናን ለመከላከል በሞራል እሴት ግንባታ ላይ መስራት ትልቅ ውጤት ያመጣል ብለዋል፡፡
በሙስና ወንጀል ዙሪያ የሚሰሩ አቃቢ ህግና ፖሊሶች የሚሰሩት በተለመደው አግባብ እንጂ ኮሚሽኑ ትኩርት ሰጥቶ ወጥ የሆነ ግንዛቤ ስላልተፈጠረላቸው በአሰራሩ ላይ ችግር እየገጠመ መሆኑም ተነስቷል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም በኃይማኖት ተቋማትና እድሮች ላይ ሰፊ የሆነ ሙስና እና የህዝብ ቅሬታ ባለበት ሁኔታ ኮሚሽኑ ጣልቃ ገብቶ አለመስራቱ ችግሩ እየተባባሰ መሆኑ መግለፃቸውን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
************************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 10/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአማራ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ደሴ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለዴሞክራሲ ተቋማትና ለአጋር አካላት ባለሙያዎች በኮምቦልቻ ከተማ ስልጠና መስጠቱን ገልጿል፡፡
የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሀብታሙ ሞገስ ስልጠናው ቀጣይ በምናካሂደው የትውልድ ሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ስራዎች ላይ በቅንጅት የምንሰራበትን የጋራ ማድረግ ላይ ታሳቢ ያደረገ ነው ብለዋል፡፡
የሞራል እሴት በመገንባት የአገልግሎት አሰጣጥን ማሻሻልና ብልሹ አሠራርን መከላከል እንዲሁም የሙስና ወንጀል ድንጋጌዎች በሚሉ ርዕሰ ጉዳይ ዙሪያ የቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል የስልጠና ባለሙያ በሆኑት አቶ አብዱ መሀመድና አቶ ሀብታሙ አሰፋ ስልጠናው ተሰጥቷል።
የስልጠናው አላማ የሞራል ግንባታን በተቋማት ተግባራዊ በማድረግ የአመለካከት ለውጥ ለማምጣትና ሙስናን ለመከላከል መሆኑ ተገልጿል።
ተሳታፊዎች በበኩላቸው ሰው አስተሳሰቡ ካልተቀየረ በቀር በቅጣት ስለማይማር ሰውን ለመግራትና ሙስናን ለመከላከል በሞራል እሴት ግንባታ ላይ መስራት ትልቅ ውጤት ያመጣል ብለዋል፡፡
በሙስና ወንጀል ዙሪያ የሚሰሩ አቃቢ ህግና ፖሊሶች የሚሰሩት በተለመደው አግባብ እንጂ ኮሚሽኑ ትኩርት ሰጥቶ ወጥ የሆነ ግንዛቤ ስላልተፈጠረላቸው በአሰራሩ ላይ ችግር እየገጠመ መሆኑም ተነስቷል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም በኃይማኖት ተቋማትና እድሮች ላይ ሰፊ የሆነ ሙስና እና የህዝብ ቅሬታ ባለበት ሁኔታ ኮሚሽኑ ጣልቃ ገብቶ አለመስራቱ ችግሩ እየተባባሰ መሆኑ መግለፃቸውን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ተቋማዊ አቅምን በማጠናከር ዘላቂ የሆነ የመልካም አስተዳድር ችግሮችን ለመፍታት ከወዲሁ በትጋት መስራት ይጠበቃል - አቶ ፍቅሬ አማን
******
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 10/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የመልካም አስተዳድር ችግሮችን ማዕከል ያደረገ የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ውይይት ተካሄዷል።
በመድረኩ የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን የፓርቲያችን ብልጽግና ቀይ መስመር የሆኑትን ሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን አምርሮ መታገልን ወቅቱ ይጠይቃል ብለዋል።
የህዝብ ፍላጎቶት፣ ስሜትና ጥያቄዎችን በተገቢው ለመረዳት የሚያግዙ ስልቶችን በመጠቀም የልማትና የመልካም አስተዳድር ጥያቄዎችን ለማሳለጥ መትጋት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
አመራሩ የአስተሳሰብ እና የተግባር አንድነት በማጎልበት በመልካም አስተዳድር ጉዳዮች ላይ የሚስተዋለውን ችግር በመቅረፍ ፈጣንና ጥራት ያለው የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት ይጠበቃል ብለዋል።
እያጋጠሙ ያሉትን ብልሹ አሰራሮችን የተደራጀ ብርቱ ትግል እንደሚደረግና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆኑን የገለጹት ኃላፊው፥ 7/24 ሰዓት በመስራት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተናበበ መልኩ መስራት እንደሚገባ ጠቅሰዋል።
የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ አበራ እንዳሉት አመራሩ አገልጋይ ተኮር እሳቤን በመላበስ ለህዝብ የገባነውን ቃል በፍትሃዊነትና በታማኝነት ማገልገል መቻል አለብን ብለዋል።
ሌብነትና ብልሹ አሰራር ለጠንካራ ፓርቲ፣ መንግስትና ሀገር ግንባታ እንቅፋት በመሆናቸው ችግሩን በማጤን፣ በመመርመርና በጥልቀት በማየት ከምንጩ ለማድረቅ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ እንደሆነ አብራርተዋል።
በመድረኩ የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳድር ሳንካ በሆኑትና በመንግስት ተቋማት የሚታዩ የአገልግሎት አሰጣጥ፣ በፍትህ ስርዓት የሚስተዋሉ ጉድለቶች፣ ሌብነትና ብልሹ አሰራሮች እንዲሁም በሌሎች ጉዳዮች ላይ ቀጣይ ከችግሮች መሻገር በሚያስችል መልኩ ዝርዝር ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።
የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው መድረኩ በቀጣይ ግልጸኝነትና ተጠያቂነትን የተላበሰ የአሰራር ስርዓትን በመከተል የህዝቡን የመልካም አስተዳድርና ብልሹ አሰራሮችን ለመቅረፍ ብሎም በተናበበ መልኩ ለመስራት እንደሚያስችል መግለፃቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
******
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 10/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የመልካም አስተዳድር ችግሮችን ማዕከል ያደረገ የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ውይይት ተካሄዷል።
በመድረኩ የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን የፓርቲያችን ብልጽግና ቀይ መስመር የሆኑትን ሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን አምርሮ መታገልን ወቅቱ ይጠይቃል ብለዋል።
የህዝብ ፍላጎቶት፣ ስሜትና ጥያቄዎችን በተገቢው ለመረዳት የሚያግዙ ስልቶችን በመጠቀም የልማትና የመልካም አስተዳድር ጥያቄዎችን ለማሳለጥ መትጋት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
አመራሩ የአስተሳሰብ እና የተግባር አንድነት በማጎልበት በመልካም አስተዳድር ጉዳዮች ላይ የሚስተዋለውን ችግር በመቅረፍ ፈጣንና ጥራት ያለው የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት ይጠበቃል ብለዋል።
እያጋጠሙ ያሉትን ብልሹ አሰራሮችን የተደራጀ ብርቱ ትግል እንደሚደረግና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆኑን የገለጹት ኃላፊው፥ 7/24 ሰዓት በመስራት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተናበበ መልኩ መስራት እንደሚገባ ጠቅሰዋል።
የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ አበራ እንዳሉት አመራሩ አገልጋይ ተኮር እሳቤን በመላበስ ለህዝብ የገባነውን ቃል በፍትሃዊነትና በታማኝነት ማገልገል መቻል አለብን ብለዋል።
ሌብነትና ብልሹ አሰራር ለጠንካራ ፓርቲ፣ መንግስትና ሀገር ግንባታ እንቅፋት በመሆናቸው ችግሩን በማጤን፣ በመመርመርና በጥልቀት በማየት ከምንጩ ለማድረቅ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ እንደሆነ አብራርተዋል።
በመድረኩ የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳድር ሳንካ በሆኑትና በመንግስት ተቋማት የሚታዩ የአገልግሎት አሰጣጥ፣ በፍትህ ስርዓት የሚስተዋሉ ጉድለቶች፣ ሌብነትና ብልሹ አሰራሮች እንዲሁም በሌሎች ጉዳዮች ላይ ቀጣይ ከችግሮች መሻገር በሚያስችል መልኩ ዝርዝር ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።
የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው መድረኩ በቀጣይ ግልጸኝነትና ተጠያቂነትን የተላበሰ የአሰራር ስርዓትን በመከተል የህዝቡን የመልካም አስተዳድርና ብልሹ አሰራሮችን ለመቅረፍ ብሎም በተናበበ መልኩ ለመስራት እንደሚያስችል መግለፃቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል
*********************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 11/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል፡፡
የምክር ቤቱ አባላት ሙስና እና ብልሹ አሠራርን በሚመለከት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ካነሷቸው ጥያቄዎች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፡፡
👉 ሙስና እና ብልሹ አሠራር እያደረሰ ያለውን ሀገራዊ ጉዳት ለመቀነስ ምን እየተሠራ ነው?
👉 የፍትሕ ተደራሽነት እና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከመሰረቱ ለመፍታት መንግሥት በቀጣይ ምን ለመስራት አስቧል?
👉 በተለያዩ ዘርፎች የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን በዘላቂት ለመፍታት በቀጣይ የሚቀመጡ አቅጣጫዎች ላይ ማብራሪያ ቢሰጥ?
👉 መንግሥት በድጎማ የሚያቀርበው ነዳጅ በሕገ-ወጥ መንገድ እንዳይሸጥ ምን አይነት ጠንካራ እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው?
👉 የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴዎችን ለመቆጣጠር መንግሥት ምን እየሠራ ነው?
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከምክር ቤቱ አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እንደሚሰጡም ይጠበቃል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
*********************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 11/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል፡፡
የምክር ቤቱ አባላት ሙስና እና ብልሹ አሠራርን በሚመለከት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ካነሷቸው ጥያቄዎች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፡፡
👉 ሙስና እና ብልሹ አሠራር እያደረሰ ያለውን ሀገራዊ ጉዳት ለመቀነስ ምን እየተሠራ ነው?
👉 የፍትሕ ተደራሽነት እና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከመሰረቱ ለመፍታት መንግሥት በቀጣይ ምን ለመስራት አስቧል?
👉 በተለያዩ ዘርፎች የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን በዘላቂት ለመፍታት በቀጣይ የሚቀመጡ አቅጣጫዎች ላይ ማብራሪያ ቢሰጥ?
👉 መንግሥት በድጎማ የሚያቀርበው ነዳጅ በሕገ-ወጥ መንገድ እንዳይሸጥ ምን አይነት ጠንካራ እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው?
👉 የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴዎችን ለመቆጣጠር መንግሥት ምን እየሠራ ነው?
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከምክር ቤቱ አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እንደሚሰጡም ይጠበቃል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ሙስናን ለመከላከል የምክርቤት አባላት ድርሻ ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ
*********************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 11/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ሙስናን ለመከላከል የምክርቤት አባላት ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን የቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 07 ገልጿል፡፡
የቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 07 የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ክፍል በሙስና ፅንስ ሀሳብ ዙሪያ ለወረዳው የምክር ቤት አባላት ስልጠና ሰጥቷል፡፡
ስልጠናውን የሰጡት የወረዳው የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ክፍል ቡድን መሪ ወ/ሮ ሰናይት ግርማው ሙስና ሀገራችንን በከፍተኛ ደረጃ የሚጓዳ፣ የሀገር እድገት እና የዜጓችን የወደፊት እጣ ፍንታ ወደ ኋላ የሚያስቀር መሆኑን ተናግረዋል።
ወ/ሮ ሰናይት አክለውም ሙስናን ለመከላከል የምክርቤት አባላት ድርሻ ከፍተኛ ነው ብለዋል።
ከስልጠናው ተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ላይ ውይይት መደረጉን ከወረዳው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
*********************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 11/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ሙስናን ለመከላከል የምክርቤት አባላት ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን የቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 07 ገልጿል፡፡
የቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 07 የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ክፍል በሙስና ፅንስ ሀሳብ ዙሪያ ለወረዳው የምክር ቤት አባላት ስልጠና ሰጥቷል፡፡
ስልጠናውን የሰጡት የወረዳው የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ክፍል ቡድን መሪ ወ/ሮ ሰናይት ግርማው ሙስና ሀገራችንን በከፍተኛ ደረጃ የሚጓዳ፣ የሀገር እድገት እና የዜጓችን የወደፊት እጣ ፍንታ ወደ ኋላ የሚያስቀር መሆኑን ተናግረዋል።
ወ/ሮ ሰናይት አክለውም ሙስናን ለመከላከል የምክርቤት አባላት ድርሻ ከፍተኛ ነው ብለዋል።
ከስልጠናው ተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ላይ ውይይት መደረጉን ከወረዳው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319