ሥነምግባር የታነፀ ሠራዊት ተልዕኮውን በድል እንደሚወጣ ተገለፀ
************************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 8/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በጦላይ የከፍተኛ ባለሌላ ማዕረግተኛ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት አመራሮችና ሠራዊት አባላት የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ስልጠና ተሰጥቷል።
በትምህርቱም በማሰልጠኛ ትምህርት ቤቱ ውስጥ እየሰለጠኑ ያሉ ሰልጣኝ ምልምል ወታደሮች፣ የ27ኛ ዙር መጋቢ ሃምሳ አለቃ ሰልጣኞች፣ አሰልጣኞችና የስታፍ ክፍል አባላቶች የተሳተፉ ሲሆን፣ በሥነምግባር የታነፀ ሠራዊት ተልዕኮውን በድል መወጣት እንደሚችልም ተገልጿል።
በትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ የሥነምግባር ክትትል ቡድን መሪ ሌተናል ኮሎኔል ሰፊነሽ ቢረዳ ውትድርና የህይወት መስዋዕትነት የሚከፈልበት፣ ሀገርንና ህግን የሚጠበቅበት ውድና እጅግ የተከበረ የሙያ ዘርፍ በመሆኑ መሰረቱ ሥነምግባር ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ውትድርና እጅግ የተከበረ ሙያ በመሆኑ ለሙያው የሚመጥን ሥነምግባር ያስፈልገዋል ያሉት ሌተናል ኮሎኔል ሰፊነሽ፣ መከላከያ ሰራዊታችን በጥሩ ሥነምግባርና ሙያዊ ዲሲፕሊን ሀገርንና ህዝብን ማገልገል ስለሚጠበቅበት ትምህርቱን መስጠት አስፈላጊ ነው ብለዋል።
ትምህርቱን የሰጡት ሻምበል አብዮት መንገሻ እንደ ተቋም በሥነምግባር የታነፀ መከላከያ ሠራዊት ለመገንባት ዓላማ ተደርጎ እየተሰራ መሆኑን አስታውሰው፣ ሁሉም የመከላከያ ሠራዊት አባላት መልካም ሥነምግባርንና ጥሩ ባህሪን በመላበስ የሚሰጠውን ማንኛውንም ግዳጅ በጀግንነት በታማኝነትና በሙያዊ ዲሲፕሊን ማከናወን ይጠበቅበታል ሲሉ ገልፀዋል።
በተመሳሳይ ሙስናን በመከላከል የዜግነት ግዴታዬን እወጣለሁ በሚል መሪ ሀሳብ ለመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ በአምቦ ዙሪያ ፕሮጀክት ሳይት ላይ ላሉ የተቋሙ የሠራዊት አባላትና ሲቪል ሰራተኞች የሥነ-ምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
************************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 8/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በጦላይ የከፍተኛ ባለሌላ ማዕረግተኛ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት አመራሮችና ሠራዊት አባላት የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ስልጠና ተሰጥቷል።
በትምህርቱም በማሰልጠኛ ትምህርት ቤቱ ውስጥ እየሰለጠኑ ያሉ ሰልጣኝ ምልምል ወታደሮች፣ የ27ኛ ዙር መጋቢ ሃምሳ አለቃ ሰልጣኞች፣ አሰልጣኞችና የስታፍ ክፍል አባላቶች የተሳተፉ ሲሆን፣ በሥነምግባር የታነፀ ሠራዊት ተልዕኮውን በድል መወጣት እንደሚችልም ተገልጿል።
በትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ የሥነምግባር ክትትል ቡድን መሪ ሌተናል ኮሎኔል ሰፊነሽ ቢረዳ ውትድርና የህይወት መስዋዕትነት የሚከፈልበት፣ ሀገርንና ህግን የሚጠበቅበት ውድና እጅግ የተከበረ የሙያ ዘርፍ በመሆኑ መሰረቱ ሥነምግባር ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ውትድርና እጅግ የተከበረ ሙያ በመሆኑ ለሙያው የሚመጥን ሥነምግባር ያስፈልገዋል ያሉት ሌተናል ኮሎኔል ሰፊነሽ፣ መከላከያ ሰራዊታችን በጥሩ ሥነምግባርና ሙያዊ ዲሲፕሊን ሀገርንና ህዝብን ማገልገል ስለሚጠበቅበት ትምህርቱን መስጠት አስፈላጊ ነው ብለዋል።
ትምህርቱን የሰጡት ሻምበል አብዮት መንገሻ እንደ ተቋም በሥነምግባር የታነፀ መከላከያ ሠራዊት ለመገንባት ዓላማ ተደርጎ እየተሰራ መሆኑን አስታውሰው፣ ሁሉም የመከላከያ ሠራዊት አባላት መልካም ሥነምግባርንና ጥሩ ባህሪን በመላበስ የሚሰጠውን ማንኛውንም ግዳጅ በጀግንነት በታማኝነትና በሙያዊ ዲሲፕሊን ማከናወን ይጠበቅበታል ሲሉ ገልፀዋል።
በተመሳሳይ ሙስናን በመከላከል የዜግነት ግዴታዬን እወጣለሁ በሚል መሪ ሀሳብ ለመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ በአምቦ ዙሪያ ፕሮጀክት ሳይት ላይ ላሉ የተቋሙ የሠራዊት አባላትና ሲቪል ሰራተኞች የሥነ-ምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
የንብረት ማስመለስ አዋጁ አስፈላጊነት እና ይዞ የመጣዉ አዲስ ነገር (ክፍል አንድ)
***************
1. የንብረት ማስመለስ ምንነት
የንብረት ማስመለስ ማለት በህገወጥ ድርጊት ምክንያት የተገኘን/የተመዘበረ ሃብትን/ንብረትን መመርመር፣ መለየት፣ ማገድ፣ መያዝ እንዲሁም መውረስና ማስተዳደርን የሚያካትት የህግ ሂደት ነው፡፡
2. የንብረት ማስመለስ አዋጁ አስፈላጊነት እና ይዞ የመጣዉ አዲስ ነገር፡- የንብረት ማስመለስ አዋጁ (አዋጅ ቁጥር 1364/2017) አስፈላጊነት እና ይዞ የመጣዉ አዲስ ነገር በተመለከተ ኢትዮጵያ የተመድ እና የማፑቶ ፀረ-ሙስና ስምምነቶችን ፈርማ ያጸደቀች አገር ናት፡፡
2.1. የንብረት ማስመለስ አዋጁ አስፈላጊነት
የተለያዩ የአለም ዓቀፍ ግዴታዎች ያለባት በመሆኑ እና የንብረት ማስመለስ ሕግጋት፣ ስምምነቶችና ልምዶች ጋር በተጣጣመ መልኩ መዘጋጀት የሚያስፈልግ በመሆኑ፣ በሀገራችን ኢትዮጵያ ማንኛውም ዓይነት የገንዘብ ወይም የንብረት ጥቅም የሚያስገኝ ወይም ጉዳት እንዲደርስ የሚያደርግ ወንጀል በመፈጸም የተገኘውን ጥቅም ወይም የደረሰውን ጉዳት የሚያካክስ የሀብት ማስመለስ ሥርዓት የሚደነግጉ እዚህም እዛም የተበታተኑ የነበሩ መሆኑ፣ የንብረት ማስመለስ ሕግ ላይ ተጠቃልለው የማይገኙ በመሆናቸው በአፈጻጸም እና በሀብት ማስተዳደር ሂደት ላይ የራሳቸው የሆነ ክፍተት ማስከተላቸው ተጠቃሽ ነው፡፡
እነዚህ የንብረት ማስመለስ ድንጋጌዎች ወደ አንድ የሕግ ማዕቀፍ በማምጣት እና ለሁሉም የወንጀል ዓይነቶች እንዲያገለግሉ በማድረግ ለመሰረታዊ የሕግና የአፈጻጸም ጥያቄዎች ወጥነት ያለውና በቂ መልስ የሚሰጥ ሕግ እንዲኖር ማድረግ አላማ በማድረግ የወጣ ነው፡፡
2.2. የንብረት ማስመለስ ህግ አላማ
የንብረት ማስመለስ ህግ ዋና አለማው የወንጀል ፍሬ የሆኑ ንብረቶችንና ገንዘቦችን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመያዝ፣ ለማገድ፣ ለመውረስ ወይም ለማስተዳደር የሚያስችል ግልጽና ዝርዝር የሕግ ማዕቀፍ በማበጀት ማንም ሰው ከሕገ-ወጥ ድርጊት ማናቸውንም አይነት የኢኮኖሚ ጥቅም እንዳያገኝ ለማድረግ እና የንብረት ማስመለስ ሕግ ወንጀልን በመከላከል ሂደት ያለውን ከፍተኛ ሚና ለማሳካት የሚያስችል የንብረት ማስመለስና ማስተዳደር ሥርዓት መዘርጋት ነው፡፡
3. የንብረት ማስመለስ የህግ መአቀፍ (አዋጅ) ዲያስፖራዎችን ኢላማ ያደረገ አለመሆኑ እና መደበኛ ባልሆነ መልኩ ገንዘብ በመላክ ንብረት ያፈሩትን ስጋት ላይ የማይጥል እንዲሁም ኢንቨስትመንትን የማይጎዳ መሆኑን እንደሚከተለው መጥቀስ ይቻላል፡፡
👉🏿 በመሰረቱ የትኛውም ህግ አንድን የማህበረሰብ ክፍል ኢላማ/ታርጌት/ አደርጎ በሆነ መልኩ ሊወጣ አይችልም፡፡ የህግ መርህም አይደለም፡፡ በመሆኑም ህጉ ትኩረት አድርጎ የተነሳው የተወሰነ የህብረተሰብ ክፍል የለም፡፡ ህግ ሁሌም ትኩረት የሚያደርገው ህገወጥ ተግባሩ ላይ እንጂ ግለሰብ፣ ድርጅት ወይም የተወሰነን ማህበረሰብ አይደለም፡፡
👉🏿 ይህ ህግ የሚመለከተው በህገወጥ መንገድ ከግለሰቦች፣ ከህዝብ እና ከመንግስት ላይ በወንጀል ድርጊት ምክንያት ንብረትና ሀብት ያፈሩ ሰዎችን ነው፡፡ እነዚህን ሰዎች በህገ-ወጥ መንገድ ያገኙትን ንብረት ልትጠቀሙበት አይገባም ማለት ደግሞ በየትኛውም መመዘኛ ትክክለኛ እና ህጋዊ አካሄድ ነው፡፡
ከዚህ ውጪ ግን ቁጥጥር የማይደረግበት የገንዘብ ፍሰት መኖር፣ ዜጎች ከላባቸው ይልቅ በወንጀል ድርጊት የሚከብሩበትን የሚያበረታታ፣ ሀገር በተቃራኒው የዜጎችን ፍትሀዊ የሀብት ተጠቃሚነት ከማጥፋቱም በላይ በዚህ መልክ የሚገኙ ንብረቶች ምንም አይነት ክትትልና ቁጥጥር ስለማይደረግባቸው ተመልሶ ለተለያየ አይነት የወንጀል መፈፀሚያነት ሊውሉ እንደሚችሉ መረዳት ያስፈልጋል፡፡
ስለዚህ በሀገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱም ሆነ ከሀገር ውጭ የሚሸሹ ሀብቶችን ለመቆጣጠር የሚያስችል ስራን በግልጽ ስርዓት መምራት፣ ደህንነቱ የተጠበቀ የፋይናንስ ፍሰትን የሚያረጋገጥ በመሆኑ ለኢንቨስትመንት ሳቢ እና አስተማማኝ አካባቢ የሚፈጥር ነው፤ በዚህም ህጋዊ ሆነው የሚንቀሳቀሱ ባለሃብቶችንና ዜጎችን ከህገ-ወጥ የሀብት ሰብሳቢዎች የሚጠብቅ ህግ ነው፡፡
👉🏿 አንድን ምንጩ ያልታወቀ ሀብት ይዟል የሚባልን ሰው በሚመረመርበት ወቅት ከውጭ ሀገር ተልኮለት የሰራውን ቤት ወይም ለኑሮ የሚያስፈልገውን ጥቂት ነገር ላይ ትኩረት ያደረገ ሳይሆን አጠቃላይ ግለሰቡ የመኖሪያ ቦታ፣ በተደጋጋሚ ግለሰቡ የሚገኝበት ቦታ፣ ግለሰቡ የሚይዛቸው ቅንጡ መኪናዎች፣ ጌጣጌጦች፣ የኑሮ ሁኔታ መደበኛ ያልሆነ የባንክ ተቀማጭና ግብይቶች (መሬት፣ ቤት ወይም የትኛውም ንብረት)፣ ከተለያዩ ተቋማት (ውጭ ሀገርም፣ ሀገር ውስጥም) እንዲሁም ከግለሰቦች የሚመጣ ሪፖርት ወይም ጥቆማ በአንድነት የሚታዩ ጉዳዮች ናቸው እንጂ በጥቂት ጉዳዮች (ማንኛውም ሰው ለኑሮ የሚያስፈልገውን መጠቀሚያ) ላይ ያነጣጠረ አይደለም፡፡
👉🏿 ምንጩ ያልታወቀ ንብረት ምርመራ በሚደረግበት ጊዜ የአንድን ግለሰብ/ድርጅት ምንጩ የማይታወቀውን ንብረቱን ብቻ ሳይሆን ህጋዊ የገቢ ምንጩ ምን እንደሆነ በጥንቃቄ የሚታይ ስለሆነ ምንጩ ያልታወቀ ሀብት አፍርቷል ብሎ ለመጠርጠር የአንድን ግለሰብ ሙሉ ፋይናንሻል ፕሮፋይል መስራት በተለይም በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት መለየት አስፈላጊ በመሆኑ በሂደቱ ከፍተኛ የሆነውን የገንዘብ እንቅስቃሴውን በማየት የሚወሰን እንጂ አንድ/ጥቂት የሆነን የገንዘብ እንቅስቃሴን ብቻ በማየት የሚወሰን አይደለም፡፡
4. ምንጩ ያልታወቀ ንብረት ኃላፊነት የመብት መጠበቂያ መንገድ የተቀመጡለት መሆኑን መመልከት ይቻላል፡፡ ምንጩ ያልታወቀ ንብረት ኃላፊነትን በተመለከተ የመብት መጠበቂያ መንገድ የተቀመጡለት ስለመሆኑ በአወጁ በግልፅ የተደነገገ ነው፡፡ ከእነዚህም መካከል የሚከተሉት ተጠቃሾች ናቸው፡፡
4.1. የመብት መጠበቂያ፡- ጉዳዩ ፍርድ ቤት ከመሄዱ በፊት ተጠርጣሪው ስለንብረቱ ህጋዊ ምንጭ ለዐቃቤ ህግ/ለሀብት መርማሪ የማስረዳት መብት የሚሰጥ መሆኑ እና ነፃና ገለልተኛ የፍርድ ቤት ውሳኔ ሰጪነት የሚካተት መሆኑ እንዲሁም ከዚህ በተጨማሪ የንብረቱን ምንጭ እንዲያስረዳ የተጠየቀው ሠው የንብረት ምንጩን ለማስረዳት በራሱ ላይ የወንጀል ኃላፊነት የሚያመጣበት ማስረጃ ቢሰጥም በወንጀል ችሎት ላይ ማስረጃ ሆኖ እንዳይቀርብ በማድረግ የመብት ጥበቃን ያደርጋል፡፡
በተጨማሪም የታወቀ መረጃን አጠቃቀም እና ለሶስተኛ ወገን ይህን መረጃ ስለማሳወቅ የሚመለከት ገደብ መኖሩ፣ የቅን ልቦና ገዢዎችን መብት ያከበረ መሆኑ እና ዝቅተኛው የንብረት ዋጋ ግምት መነሻ (10,000,000) የልዩነት ዋጋ (ጠቅላላ ሀብት ሳይሆን) ተደርጎ መቀመጡ ይጠቀሳሉ፡፡
4.2. ተቋማዊ ጥበቃ፡- ገለልተኛ የሆነ ቁጥጥር እና በዳኝኘት አካል ወይም በዳኛ የሚወሰን ጉዳይ ነው፡፡
4.3 ተግባራዊ ጥበቃዎች፡- ፍትሃዊ ሂደት እና ሥነ-ስርዓት በተለይም ምርመራ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅና ያለው በጊዜ የተገደበ፣ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ መሆን ይገባዋል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
***************
1. የንብረት ማስመለስ ምንነት
የንብረት ማስመለስ ማለት በህገወጥ ድርጊት ምክንያት የተገኘን/የተመዘበረ ሃብትን/ንብረትን መመርመር፣ መለየት፣ ማገድ፣ መያዝ እንዲሁም መውረስና ማስተዳደርን የሚያካትት የህግ ሂደት ነው፡፡
2. የንብረት ማስመለስ አዋጁ አስፈላጊነት እና ይዞ የመጣዉ አዲስ ነገር፡- የንብረት ማስመለስ አዋጁ (አዋጅ ቁጥር 1364/2017) አስፈላጊነት እና ይዞ የመጣዉ አዲስ ነገር በተመለከተ ኢትዮጵያ የተመድ እና የማፑቶ ፀረ-ሙስና ስምምነቶችን ፈርማ ያጸደቀች አገር ናት፡፡
2.1. የንብረት ማስመለስ አዋጁ አስፈላጊነት
የተለያዩ የአለም ዓቀፍ ግዴታዎች ያለባት በመሆኑ እና የንብረት ማስመለስ ሕግጋት፣ ስምምነቶችና ልምዶች ጋር በተጣጣመ መልኩ መዘጋጀት የሚያስፈልግ በመሆኑ፣ በሀገራችን ኢትዮጵያ ማንኛውም ዓይነት የገንዘብ ወይም የንብረት ጥቅም የሚያስገኝ ወይም ጉዳት እንዲደርስ የሚያደርግ ወንጀል በመፈጸም የተገኘውን ጥቅም ወይም የደረሰውን ጉዳት የሚያካክስ የሀብት ማስመለስ ሥርዓት የሚደነግጉ እዚህም እዛም የተበታተኑ የነበሩ መሆኑ፣ የንብረት ማስመለስ ሕግ ላይ ተጠቃልለው የማይገኙ በመሆናቸው በአፈጻጸም እና በሀብት ማስተዳደር ሂደት ላይ የራሳቸው የሆነ ክፍተት ማስከተላቸው ተጠቃሽ ነው፡፡
እነዚህ የንብረት ማስመለስ ድንጋጌዎች ወደ አንድ የሕግ ማዕቀፍ በማምጣት እና ለሁሉም የወንጀል ዓይነቶች እንዲያገለግሉ በማድረግ ለመሰረታዊ የሕግና የአፈጻጸም ጥያቄዎች ወጥነት ያለውና በቂ መልስ የሚሰጥ ሕግ እንዲኖር ማድረግ አላማ በማድረግ የወጣ ነው፡፡
2.2. የንብረት ማስመለስ ህግ አላማ
የንብረት ማስመለስ ህግ ዋና አለማው የወንጀል ፍሬ የሆኑ ንብረቶችንና ገንዘቦችን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመያዝ፣ ለማገድ፣ ለመውረስ ወይም ለማስተዳደር የሚያስችል ግልጽና ዝርዝር የሕግ ማዕቀፍ በማበጀት ማንም ሰው ከሕገ-ወጥ ድርጊት ማናቸውንም አይነት የኢኮኖሚ ጥቅም እንዳያገኝ ለማድረግ እና የንብረት ማስመለስ ሕግ ወንጀልን በመከላከል ሂደት ያለውን ከፍተኛ ሚና ለማሳካት የሚያስችል የንብረት ማስመለስና ማስተዳደር ሥርዓት መዘርጋት ነው፡፡
3. የንብረት ማስመለስ የህግ መአቀፍ (አዋጅ) ዲያስፖራዎችን ኢላማ ያደረገ አለመሆኑ እና መደበኛ ባልሆነ መልኩ ገንዘብ በመላክ ንብረት ያፈሩትን ስጋት ላይ የማይጥል እንዲሁም ኢንቨስትመንትን የማይጎዳ መሆኑን እንደሚከተለው መጥቀስ ይቻላል፡፡
👉🏿 በመሰረቱ የትኛውም ህግ አንድን የማህበረሰብ ክፍል ኢላማ/ታርጌት/ አደርጎ በሆነ መልኩ ሊወጣ አይችልም፡፡ የህግ መርህም አይደለም፡፡ በመሆኑም ህጉ ትኩረት አድርጎ የተነሳው የተወሰነ የህብረተሰብ ክፍል የለም፡፡ ህግ ሁሌም ትኩረት የሚያደርገው ህገወጥ ተግባሩ ላይ እንጂ ግለሰብ፣ ድርጅት ወይም የተወሰነን ማህበረሰብ አይደለም፡፡
👉🏿 ይህ ህግ የሚመለከተው በህገወጥ መንገድ ከግለሰቦች፣ ከህዝብ እና ከመንግስት ላይ በወንጀል ድርጊት ምክንያት ንብረትና ሀብት ያፈሩ ሰዎችን ነው፡፡ እነዚህን ሰዎች በህገ-ወጥ መንገድ ያገኙትን ንብረት ልትጠቀሙበት አይገባም ማለት ደግሞ በየትኛውም መመዘኛ ትክክለኛ እና ህጋዊ አካሄድ ነው፡፡
ከዚህ ውጪ ግን ቁጥጥር የማይደረግበት የገንዘብ ፍሰት መኖር፣ ዜጎች ከላባቸው ይልቅ በወንጀል ድርጊት የሚከብሩበትን የሚያበረታታ፣ ሀገር በተቃራኒው የዜጎችን ፍትሀዊ የሀብት ተጠቃሚነት ከማጥፋቱም በላይ በዚህ መልክ የሚገኙ ንብረቶች ምንም አይነት ክትትልና ቁጥጥር ስለማይደረግባቸው ተመልሶ ለተለያየ አይነት የወንጀል መፈፀሚያነት ሊውሉ እንደሚችሉ መረዳት ያስፈልጋል፡፡
ስለዚህ በሀገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱም ሆነ ከሀገር ውጭ የሚሸሹ ሀብቶችን ለመቆጣጠር የሚያስችል ስራን በግልጽ ስርዓት መምራት፣ ደህንነቱ የተጠበቀ የፋይናንስ ፍሰትን የሚያረጋገጥ በመሆኑ ለኢንቨስትመንት ሳቢ እና አስተማማኝ አካባቢ የሚፈጥር ነው፤ በዚህም ህጋዊ ሆነው የሚንቀሳቀሱ ባለሃብቶችንና ዜጎችን ከህገ-ወጥ የሀብት ሰብሳቢዎች የሚጠብቅ ህግ ነው፡፡
👉🏿 አንድን ምንጩ ያልታወቀ ሀብት ይዟል የሚባልን ሰው በሚመረመርበት ወቅት ከውጭ ሀገር ተልኮለት የሰራውን ቤት ወይም ለኑሮ የሚያስፈልገውን ጥቂት ነገር ላይ ትኩረት ያደረገ ሳይሆን አጠቃላይ ግለሰቡ የመኖሪያ ቦታ፣ በተደጋጋሚ ግለሰቡ የሚገኝበት ቦታ፣ ግለሰቡ የሚይዛቸው ቅንጡ መኪናዎች፣ ጌጣጌጦች፣ የኑሮ ሁኔታ መደበኛ ያልሆነ የባንክ ተቀማጭና ግብይቶች (መሬት፣ ቤት ወይም የትኛውም ንብረት)፣ ከተለያዩ ተቋማት (ውጭ ሀገርም፣ ሀገር ውስጥም) እንዲሁም ከግለሰቦች የሚመጣ ሪፖርት ወይም ጥቆማ በአንድነት የሚታዩ ጉዳዮች ናቸው እንጂ በጥቂት ጉዳዮች (ማንኛውም ሰው ለኑሮ የሚያስፈልገውን መጠቀሚያ) ላይ ያነጣጠረ አይደለም፡፡
👉🏿 ምንጩ ያልታወቀ ንብረት ምርመራ በሚደረግበት ጊዜ የአንድን ግለሰብ/ድርጅት ምንጩ የማይታወቀውን ንብረቱን ብቻ ሳይሆን ህጋዊ የገቢ ምንጩ ምን እንደሆነ በጥንቃቄ የሚታይ ስለሆነ ምንጩ ያልታወቀ ሀብት አፍርቷል ብሎ ለመጠርጠር የአንድን ግለሰብ ሙሉ ፋይናንሻል ፕሮፋይል መስራት በተለይም በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት መለየት አስፈላጊ በመሆኑ በሂደቱ ከፍተኛ የሆነውን የገንዘብ እንቅስቃሴውን በማየት የሚወሰን እንጂ አንድ/ጥቂት የሆነን የገንዘብ እንቅስቃሴን ብቻ በማየት የሚወሰን አይደለም፡፡
4. ምንጩ ያልታወቀ ንብረት ኃላፊነት የመብት መጠበቂያ መንገድ የተቀመጡለት መሆኑን መመልከት ይቻላል፡፡ ምንጩ ያልታወቀ ንብረት ኃላፊነትን በተመለከተ የመብት መጠበቂያ መንገድ የተቀመጡለት ስለመሆኑ በአወጁ በግልፅ የተደነገገ ነው፡፡ ከእነዚህም መካከል የሚከተሉት ተጠቃሾች ናቸው፡፡
4.1. የመብት መጠበቂያ፡- ጉዳዩ ፍርድ ቤት ከመሄዱ በፊት ተጠርጣሪው ስለንብረቱ ህጋዊ ምንጭ ለዐቃቤ ህግ/ለሀብት መርማሪ የማስረዳት መብት የሚሰጥ መሆኑ እና ነፃና ገለልተኛ የፍርድ ቤት ውሳኔ ሰጪነት የሚካተት መሆኑ እንዲሁም ከዚህ በተጨማሪ የንብረቱን ምንጭ እንዲያስረዳ የተጠየቀው ሠው የንብረት ምንጩን ለማስረዳት በራሱ ላይ የወንጀል ኃላፊነት የሚያመጣበት ማስረጃ ቢሰጥም በወንጀል ችሎት ላይ ማስረጃ ሆኖ እንዳይቀርብ በማድረግ የመብት ጥበቃን ያደርጋል፡፡
በተጨማሪም የታወቀ መረጃን አጠቃቀም እና ለሶስተኛ ወገን ይህን መረጃ ስለማሳወቅ የሚመለከት ገደብ መኖሩ፣ የቅን ልቦና ገዢዎችን መብት ያከበረ መሆኑ እና ዝቅተኛው የንብረት ዋጋ ግምት መነሻ (10,000,000) የልዩነት ዋጋ (ጠቅላላ ሀብት ሳይሆን) ተደርጎ መቀመጡ ይጠቀሳሉ፡፡
4.2. ተቋማዊ ጥበቃ፡- ገለልተኛ የሆነ ቁጥጥር እና በዳኝኘት አካል ወይም በዳኛ የሚወሰን ጉዳይ ነው፡፡
4.3 ተግባራዊ ጥበቃዎች፡- ፍትሃዊ ሂደት እና ሥነ-ስርዓት በተለይም ምርመራ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅና ያለው በጊዜ የተገደበ፣ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ መሆን ይገባዋል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
"የተቋማት መልካም ተሞክሮ ቅኝት"
*******
የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በተቋማት ሙስና እና ብልሹ አሠራርን ለመከላከል ሰፊ ተግባራትን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ ከዚህም ባሻገር በአገርዓቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የሙስና ትግል ያለኅብረተሰብ ተሳትፎ ከግብ ማድረስ ስለማይቻል ትግሉን በቴክኖሎጂ ለመደገፍ የብሔራዊ ሙስና መጠቆሚያ ዲጂታል መተግበሪያ ስርዓት /National Corruption Reporting System – NCRS/ በመዘርጋት ዜጎች በየተቋማቱ አገልግሎት ለማግኘት ሄደው የሙስና ተግባር ሲያጋጥማቸው ያለምንም ሥጋት በስልካቸው ጥቆማ የሚሰጡበት ሥርዓት ዘርግቶ መረጃዎችን እየተቀበለ ይገኛል፡፡
ከኮሚሽኑ ባሻገር ተቋማት የሙስና ወንጀሎችን በተለያዩ አማራጮች ከህብረተሰቡ እየተቀበሉና መፍትሄ እየሰጡ ነው፡፡ ለአብነት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሙስና ወንጀል መቀበያ ስርዓት https://eeuethics.et/ በመዘረጋት ጥቆማዎችን በመቀበል ለመረጃዎች መፍትሄ እየሰጠ መሆኑ በመልካም ተሞክሮ የሚወሰድ ነው፡፡
ሌሎችም ተቋማትም በተመሳሳይ የራሳቸውን የሙስና ወንጀል መቀበያ ስርዓት በመዘርጋት ስራዎችን እየተገበሩ ከሆነ መልካም ተሞክሮ ስለሚሆን በኮሚሽኑ የማህበራዊ ሚዲያ መልዕክት መቀበያ ላይ እንዲያስቀምጡልን ጥሪ እናስተላልፋለን፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
*******
የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በተቋማት ሙስና እና ብልሹ አሠራርን ለመከላከል ሰፊ ተግባራትን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ ከዚህም ባሻገር በአገርዓቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የሙስና ትግል ያለኅብረተሰብ ተሳትፎ ከግብ ማድረስ ስለማይቻል ትግሉን በቴክኖሎጂ ለመደገፍ የብሔራዊ ሙስና መጠቆሚያ ዲጂታል መተግበሪያ ስርዓት /National Corruption Reporting System – NCRS/ በመዘርጋት ዜጎች በየተቋማቱ አገልግሎት ለማግኘት ሄደው የሙስና ተግባር ሲያጋጥማቸው ያለምንም ሥጋት በስልካቸው ጥቆማ የሚሰጡበት ሥርዓት ዘርግቶ መረጃዎችን እየተቀበለ ይገኛል፡፡
ከኮሚሽኑ ባሻገር ተቋማት የሙስና ወንጀሎችን በተለያዩ አማራጮች ከህብረተሰቡ እየተቀበሉና መፍትሄ እየሰጡ ነው፡፡ ለአብነት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሙስና ወንጀል መቀበያ ስርዓት https://eeuethics.et/ በመዘረጋት ጥቆማዎችን በመቀበል ለመረጃዎች መፍትሄ እየሰጠ መሆኑ በመልካም ተሞክሮ የሚወሰድ ነው፡፡
ሌሎችም ተቋማትም በተመሳሳይ የራሳቸውን የሙስና ወንጀል መቀበያ ስርዓት በመዘርጋት ስራዎችን እየተገበሩ ከሆነ መልካም ተሞክሮ ስለሚሆን በኮሚሽኑ የማህበራዊ ሚዲያ መልዕክት መቀበያ ላይ እንዲያስቀምጡልን ጥሪ እናስተላልፋለን፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ዜጎች መልካም ሥነምግባርን እንዲላበሱ ማስተማር ከመገናኛ ብዙኃን ይጠበቃል
************************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 9/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአማራ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የሚዲያ ተቋማት ከሥነምግባር ግንባታ እና ሙስና መከላከል አንጻር ያላቸውን ሚና የተመለከተ ውይይት አድርጓል።
በውይይቱ ላይ የሚዲያ ተቋማት ባለሙያዎች እና የዘርፉ መሪዎች ተሳትፈዋል።
በመድረኩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የአማራ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኀላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ.ር) "ሙስና እንደ ሀገር የያዝነውን ሁሉን አቀፍ ለውጥ ወደ ኋላ የሚጎትት ብልሹ ተግባር መኾኑን በመገንዘብ በጋራ መታገል ይገባል" ብለዋል።
ሌብነት የሀገርን እድገት እና የሕዝብን ጥቅም ወደ ኋላ ለመጎትት በጥቂት አጥፊ እጆች የሚፈጸም የሥነምግባር ብልሽት ስለመኾኑም ተናግረዋል። ይህንን ተግባር በማረም በኩል የመገናኛ ብዙኃን ሚና ከፍተኛ ስለመኾኑም ጠቁመዋል።
አሚኮን ጨምሮ ሁሉም የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እና ባለሙያዎች የሕዝብ አገልግሎት ተቋማትን አሠራር መፈተሽ እና ማጋለጥ እንዳለባቸውም አሳስበዋል።
በተለይም ጠንካራ የምርመራ ጋዜጠኝነት ሥራን መሥራት እንደሚገባ ተናግረዋል።
የመንግሥት መሪዎች ሥልጣን እና ተጠያቂነትን ጎን ለጎን የያዙ ናቸው፣ ኀላፊነታቸውን እንዴት እየተወጡ እንደኾነ ለሕዝብ ማሳወቅ እና ያጎደሉት ነገር ሲኖርም ለተጠያቂነት አጋልጦ መስጠት ይገባል ብለዋል።
በሥነምግባራቸው፣ በሀገር ወዳድነታቸው እና በታማኝነታቸው ታዋቂ እና ሞዴል የኾኑ ሰዎችን ተሞክሮ በሚዲያ በማቅረብ መጭውን ትውልድ በምግባር ማነጽ እንደሚገባም አሳስበዋል።
በውይይቱ ላይ የተገኙት የአሚኮ ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ሙሉቀን ሰጥየ በበኩላቸው ሙስናን በጋራ ቆሞ ከመከላከል አኳያ በርካታ ክፍተቶች መኖራቸውን ጠቁመዋል።
የአፈር ማዳበሪያን እንደ አብነት ያነሱት አቶ ሙሉቀን፣ ይህንን የሕዝብ ህልውና የኾነ ሀብት መስረቅ "ከእናት ጡት እንደመስረቅ" መቁጠር እንዴት አቃተን ሲሉ ጠይቀዋል።
የብልሹ አሠራር እና የሌብነትን ተግባር በጋራ በመቆም መታገል ለነገ የማይባል ሥራ መኾኑንም አንስተዋል።
አሚኮ በሁሉም ሚዲየሞቹ በመጠቀም በሥነምግባር የታነጸ ትውልድ የመፍጠር ኀላፊነቱን እንደሚወጣም ገልጸዋል።
አሚኮ በምርመራ ጋዜጠኝነት እና የተለያዩ ፕሮግራሞቹን በመጠቀም ብልሹ አሠራሮችን የማጋለጥ ሥራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።
የአማራ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ማሩ ቸኮል ሙስና እና ብልሹ አሠራርን ከመቅረፍ አንጻር የመገናኛ ብዙኃን ተጽዕኖ ከፍተኛ ነው ብለዋል።
በተለይም ሌብነትን እና ብልሹ አሠራርን የሚጠየፍ ትውልድ ከመገንባት አኳያ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች በትጋት ሊሠሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።
መገናኛ ብዙኃን መልካም እሴቶችን እና ባሕርያትን ማራመድ፣ ሥነምግባር የጎደላቸውን ድርጊቶች እና አመለካከቶች ደግሞ እንዳይስፋፋ መታገል አለባቸው ነው ያሉት።
የትምህርት ተቋማት፣ የሃይማኖት ተቋማት፣ የሲቪል ማኅበረሰብ እና የመሳሰሉት ተቋማት መልካም ሥነምግባርን ለተተኪው ትውልድ ለማስረጽ የሚያደርጉትን አስተምህሮ በሚዲያ ሥራ ማገዝ እንደሚገባም ምክትል ኮሚሽነሩ አስገንዝበዋል።
አቶ ማሩ እንዳሉት የተቋማትን ተግባራት፣ በጀት እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶችን በመከታተል እና ለሕዝብ ሪፖርት በማቅረብ የሕዝብ ሀብት በአግባቡ ጥቅም ላይ ስለመዋሉ መከታተልም ከመገናኛ ብዙኃን ይጠበቃል።
መልካም ሥነምግባር ለሀገር እድገት ያለውን ፋይዳ ገልጦ ማሳየት እና ዜጎች መልካም ሥነምግባርን እንዲላበሱ መምከር እና ማስተማርም ከመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ይጠበቃል ብለዋል።
ሙስናን በማጋለጥ ወንጀለኞችን ተጠያቂ ሊያደርግ የሚችል የምርመራ ጋዜጠኝነት ሥራ መከናወን እንዳለበትም ምክትል ኮሚሽነሩ አሳስበዋል።
የውይይቱ ተሳታፊ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችም ሙስናን የሚጠየፍ ትውልድ በመፍጠሩ ረገድ የበኩላቸውን ሚና እንደሚጫወቱ ማረጋገጣቸውን አሚኮ ዘግቧል።
ሙስና እና ብልሹ አሠራርን ለመታገል በሚከናወኑ የሚዲያ ሥራዎች ላይ የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን አስፈላጊውን ትብብር ማድረግ እንዳለበትም ባለሙያዎች ገልጸዋል።
ተጨባጭ ጥፋት በተገኘባቸው ሰዎች ላይም የተጠያቂነት አሠራርን ማስፈን እንደሚገባ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች አሳስበዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
************************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 9/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአማራ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የሚዲያ ተቋማት ከሥነምግባር ግንባታ እና ሙስና መከላከል አንጻር ያላቸውን ሚና የተመለከተ ውይይት አድርጓል።
በውይይቱ ላይ የሚዲያ ተቋማት ባለሙያዎች እና የዘርፉ መሪዎች ተሳትፈዋል።
በመድረኩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የአማራ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኀላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ.ር) "ሙስና እንደ ሀገር የያዝነውን ሁሉን አቀፍ ለውጥ ወደ ኋላ የሚጎትት ብልሹ ተግባር መኾኑን በመገንዘብ በጋራ መታገል ይገባል" ብለዋል።
ሌብነት የሀገርን እድገት እና የሕዝብን ጥቅም ወደ ኋላ ለመጎትት በጥቂት አጥፊ እጆች የሚፈጸም የሥነምግባር ብልሽት ስለመኾኑም ተናግረዋል። ይህንን ተግባር በማረም በኩል የመገናኛ ብዙኃን ሚና ከፍተኛ ስለመኾኑም ጠቁመዋል።
አሚኮን ጨምሮ ሁሉም የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እና ባለሙያዎች የሕዝብ አገልግሎት ተቋማትን አሠራር መፈተሽ እና ማጋለጥ እንዳለባቸውም አሳስበዋል።
በተለይም ጠንካራ የምርመራ ጋዜጠኝነት ሥራን መሥራት እንደሚገባ ተናግረዋል።
የመንግሥት መሪዎች ሥልጣን እና ተጠያቂነትን ጎን ለጎን የያዙ ናቸው፣ ኀላፊነታቸውን እንዴት እየተወጡ እንደኾነ ለሕዝብ ማሳወቅ እና ያጎደሉት ነገር ሲኖርም ለተጠያቂነት አጋልጦ መስጠት ይገባል ብለዋል።
በሥነምግባራቸው፣ በሀገር ወዳድነታቸው እና በታማኝነታቸው ታዋቂ እና ሞዴል የኾኑ ሰዎችን ተሞክሮ በሚዲያ በማቅረብ መጭውን ትውልድ በምግባር ማነጽ እንደሚገባም አሳስበዋል።
በውይይቱ ላይ የተገኙት የአሚኮ ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ሙሉቀን ሰጥየ በበኩላቸው ሙስናን በጋራ ቆሞ ከመከላከል አኳያ በርካታ ክፍተቶች መኖራቸውን ጠቁመዋል።
የአፈር ማዳበሪያን እንደ አብነት ያነሱት አቶ ሙሉቀን፣ ይህንን የሕዝብ ህልውና የኾነ ሀብት መስረቅ "ከእናት ጡት እንደመስረቅ" መቁጠር እንዴት አቃተን ሲሉ ጠይቀዋል።
የብልሹ አሠራር እና የሌብነትን ተግባር በጋራ በመቆም መታገል ለነገ የማይባል ሥራ መኾኑንም አንስተዋል።
አሚኮ በሁሉም ሚዲየሞቹ በመጠቀም በሥነምግባር የታነጸ ትውልድ የመፍጠር ኀላፊነቱን እንደሚወጣም ገልጸዋል።
አሚኮ በምርመራ ጋዜጠኝነት እና የተለያዩ ፕሮግራሞቹን በመጠቀም ብልሹ አሠራሮችን የማጋለጥ ሥራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።
የአማራ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ማሩ ቸኮል ሙስና እና ብልሹ አሠራርን ከመቅረፍ አንጻር የመገናኛ ብዙኃን ተጽዕኖ ከፍተኛ ነው ብለዋል።
በተለይም ሌብነትን እና ብልሹ አሠራርን የሚጠየፍ ትውልድ ከመገንባት አኳያ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች በትጋት ሊሠሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።
መገናኛ ብዙኃን መልካም እሴቶችን እና ባሕርያትን ማራመድ፣ ሥነምግባር የጎደላቸውን ድርጊቶች እና አመለካከቶች ደግሞ እንዳይስፋፋ መታገል አለባቸው ነው ያሉት።
የትምህርት ተቋማት፣ የሃይማኖት ተቋማት፣ የሲቪል ማኅበረሰብ እና የመሳሰሉት ተቋማት መልካም ሥነምግባርን ለተተኪው ትውልድ ለማስረጽ የሚያደርጉትን አስተምህሮ በሚዲያ ሥራ ማገዝ እንደሚገባም ምክትል ኮሚሽነሩ አስገንዝበዋል።
አቶ ማሩ እንዳሉት የተቋማትን ተግባራት፣ በጀት እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶችን በመከታተል እና ለሕዝብ ሪፖርት በማቅረብ የሕዝብ ሀብት በአግባቡ ጥቅም ላይ ስለመዋሉ መከታተልም ከመገናኛ ብዙኃን ይጠበቃል።
መልካም ሥነምግባር ለሀገር እድገት ያለውን ፋይዳ ገልጦ ማሳየት እና ዜጎች መልካም ሥነምግባርን እንዲላበሱ መምከር እና ማስተማርም ከመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ይጠበቃል ብለዋል።
ሙስናን በማጋለጥ ወንጀለኞችን ተጠያቂ ሊያደርግ የሚችል የምርመራ ጋዜጠኝነት ሥራ መከናወን እንዳለበትም ምክትል ኮሚሽነሩ አሳስበዋል።
የውይይቱ ተሳታፊ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችም ሙስናን የሚጠየፍ ትውልድ በመፍጠሩ ረገድ የበኩላቸውን ሚና እንደሚጫወቱ ማረጋገጣቸውን አሚኮ ዘግቧል።
ሙስና እና ብልሹ አሠራርን ለመታገል በሚከናወኑ የሚዲያ ሥራዎች ላይ የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን አስፈላጊውን ትብብር ማድረግ እንዳለበትም ባለሙያዎች ገልጸዋል።
ተጨባጭ ጥፋት በተገኘባቸው ሰዎች ላይም የተጠያቂነት አሠራርን ማስፈን እንደሚገባ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች አሳስበዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
አገልግሎቱ በ22 አመራርና ሰራተኞች ላይ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያና የደሞዝ ቅጣት እርምጃ ወስጃለው አለ
********
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 9/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ተቋሙ በ2017 በጀት ዓመት ሰባት ወራት ውስጥ ብልሹ አስራርን ለማስወገድ ባከናወናቸው ተግባራት በ22 አመራርና ሰራተኞች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቋል፡፡
እርምጃው የተወሰደው ከደንበኞች የቀረቡ ጥቆማዎችን መሰረት በማድረግ እና አስፈላጊው ማጣሪያ ተደርጎ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮሚኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ መላኩ ታዬ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል፡፡
እርምጃ ከተወሰደባቸው አመራር እና ሰራተኞች መካከል 3ቱ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ እና 19ኙ የደመወዝ ቅጣት የተቀጡ መሆናቸውን ስራ አስፈፃሚው ገልፀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የብልሹ አሰራር እና የሙስና ጥቆማ መስጫ ዲጂታል የሞባይል መተግበሪያ ስራ ላይ ማዋሉ የሚታወስ ነው፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
********
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 9/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ተቋሙ በ2017 በጀት ዓመት ሰባት ወራት ውስጥ ብልሹ አስራርን ለማስወገድ ባከናወናቸው ተግባራት በ22 አመራርና ሰራተኞች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቋል፡፡
እርምጃው የተወሰደው ከደንበኞች የቀረቡ ጥቆማዎችን መሰረት በማድረግ እና አስፈላጊው ማጣሪያ ተደርጎ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮሚኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ መላኩ ታዬ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል፡፡
እርምጃ ከተወሰደባቸው አመራር እና ሰራተኞች መካከል 3ቱ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ እና 19ኙ የደመወዝ ቅጣት የተቀጡ መሆናቸውን ስራ አስፈፃሚው ገልፀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የብልሹ አሰራር እና የሙስና ጥቆማ መስጫ ዲጂታል የሞባይል መተግበሪያ ስራ ላይ ማዋሉ የሚታወስ ነው፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ሙያዊ ሥነምግባርን በመላበስ ራስን ከብልሹ አሰራር መጠበቅ እንደሚገባ ተገለፀ
****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 9/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአዲስ አበባ ከተማ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ለአዲስ ከተማ፣ ለልደታ እና አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተሞች ትራፊክ ፖሊስ ዲቪዥን አመራርና አባላት በሙያዊ ሥነምግባር፣ በብልሹ አሰራር ተጋላጭነት እና በሙስና መከላከል ዙሪያ ስልጠና እየሰጠ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡
የከተማው የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር መቅደስ ተስፋዬ ስልጠናው ከዚህ ቀደም በተለያዩ ክፍለ ከተማ ለሚገኙ ትራፊክ ፖሊስ አመራሮችና አባላት መሰጠቱን ገልፀው፥ ሙያዊ ሥነምግባር በመላበስ ራስን ከብልሹ አሰራር መጠበቅ አንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
ሙስናን መከላከል ግለሰባዊ ሳይሆን ሀገራዊ ጉዳይ ነው ያሉት ም/ኮሚሽነሯ፥ ይህን ተግባር ውጤታማ ለማድረግ ዋነኛ ባለድርሻ አካል በመሆን ኃላፊነታችንን መወጣት አለብን ብለዋል።
የኮሚሽኑ የሥነምግባር ግንባታ ስልጠና ዳ/ዳይሬክተር አቶ ጀንበሩ ኢርኮ ስልጠናውን በሰጡበት ወቅት እንደገለፁት የትራፊክ ፖሊስ አባላት ሙያዊ ሥነምግባርን ተላብሰውና ከብልሹ አሰራር በፀዳ መልኩ ተግባራትን ማከናወናቸው በሰው ህይወትና ንብረት ላይ የሚደርስ አደጋ እንዲቀንስ አይነተኛ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል፡፡
ዳይሬክተሩ አክለውም አባላቱ በሙያ ሥነምግባር መታነፃቸው የሙያውን ቅቡልነት ከፍ በማድረግ አወንታዊ ፋይዳው የጎላ መሆኑን መግለፃቸውን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 9/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአዲስ አበባ ከተማ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ለአዲስ ከተማ፣ ለልደታ እና አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተሞች ትራፊክ ፖሊስ ዲቪዥን አመራርና አባላት በሙያዊ ሥነምግባር፣ በብልሹ አሰራር ተጋላጭነት እና በሙስና መከላከል ዙሪያ ስልጠና እየሰጠ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡
የከተማው የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር መቅደስ ተስፋዬ ስልጠናው ከዚህ ቀደም በተለያዩ ክፍለ ከተማ ለሚገኙ ትራፊክ ፖሊስ አመራሮችና አባላት መሰጠቱን ገልፀው፥ ሙያዊ ሥነምግባር በመላበስ ራስን ከብልሹ አሰራር መጠበቅ አንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
ሙስናን መከላከል ግለሰባዊ ሳይሆን ሀገራዊ ጉዳይ ነው ያሉት ም/ኮሚሽነሯ፥ ይህን ተግባር ውጤታማ ለማድረግ ዋነኛ ባለድርሻ አካል በመሆን ኃላፊነታችንን መወጣት አለብን ብለዋል።
የኮሚሽኑ የሥነምግባር ግንባታ ስልጠና ዳ/ዳይሬክተር አቶ ጀንበሩ ኢርኮ ስልጠናውን በሰጡበት ወቅት እንደገለፁት የትራፊክ ፖሊስ አባላት ሙያዊ ሥነምግባርን ተላብሰውና ከብልሹ አሰራር በፀዳ መልኩ ተግባራትን ማከናወናቸው በሰው ህይወትና ንብረት ላይ የሚደርስ አደጋ እንዲቀንስ አይነተኛ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል፡፡
ዳይሬክተሩ አክለውም አባላቱ በሙያ ሥነምግባር መታነፃቸው የሙያውን ቅቡልነት ከፍ በማድረግ አወንታዊ ፋይዳው የጎላ መሆኑን መግለፃቸውን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319