ሁለንተናዊ ተቋማዊ አቅም በማቀናጀትና በመረባረብ ሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን መታገል እንደሚገባ ተገለጸ
************************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 8/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ሥነምግባር ኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት እና የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን መካከል ብልሹ አሰራርንና ሙስናን ለመታገል በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
የክልሉ ሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሙሉሰው ዘውዴ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፤ የመደመር ሳንካ የሆኑት ሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን በጽኑ አቋም በመታገል ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ መረባረብ ይገባል።
የስምምነት ሰነዱ ቅንጅታዊ አሰራሮችን በማሳለጥ ውጤታማ የሆነ የሙስና እና ብልሹ አሰራሮች ላይ ማዕከል አድርጎ በጥብቅ ዲስፕሊን እና በተጠናከረ መልኩ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።
ለፀረ-ሙስና ትግሉ የሚያግዙ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን መስጠት፣ ጥናት ላይ ተመስርቶ ሙስናን መከላከል እና መረጃዎችን መለዋወጥ እንዲሁም የትውልድ ሥነምግባር ግንባታው ላይ በጋራ ተቀናጅቶ መስራት የኮሚሽኖች የስምምነት አንኳር ጉዳዮች እንደሆነ ኮሚሽነር ሙሉሰው ዘውዴ ገልጸዋል።
በመግባቢያ ሰነዱ የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ታደሰ አይበራ እንደገለጹት፤ በየደረጃው ያለው አመራር፣ ባለሙያና ህብረተሰቡ በሙስና እና ብልሹ አሰራሮች ላይ የተቀናጀ ትግል በማድረግ የተጀመረውን ሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ መረባረብ ይገባል።
ሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን ተቋማት ሁለንተናዊ አቅም በማቀናጀት በመረባረብ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣትና የህብረተሰቡን እርካታ ማሳደግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በተቀናጀና በተደራጀ ሁኔታ ሙስና እና ብልሹ አሰራር በመከላከል የሀገራችንን እና የክልሉን ሁለንተናዊ ብልጽግና እንዲረጋገጥ ሁሉም አመራርና ባለሙያዎች በቁርጠኝነት መስራት እንዳለባቸው ጠቅሰዋል።
በመንግስት እና ህዝብ መካከል ሆኖ በህገ ወጥ ተግባር ላይ የተሰማራውን ኃይል በተቀናጀ መንገድ ተጨባጭነት ያለው የሙስና መከላከል በመስራት እንዲነጠል ማድረግ ይኖርብናል ብለዋል።
ሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል በየደረጃው በተደረጉ የተቀናጁ ጥረቶች በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡ መሆኑን ገልጸው፣ ይህን የተቀናጀ ጥረት የመንግስትና ህዝባዊ ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ በቁርጠኝነት መታገል እንደሚገባ አመላክተዋል።
የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ኢንስፔክሽንና ሥነምግባር ኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳንኤል ያዙ እንደገለጹት፤ በፀረ-ሙስና ትግል ላይ በጋራ አቋም ከሰራን ፓርቲው ያስቀመጣቸውን ግቦች ለማሳካት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል።
ሙስና እና ሌብነት የብልጽግና ፓርቲ ቀይ መስመር በመሆኑ እነዚህን ብልሹ አሰራሮችን ከምንጩ ለማድረቅ አመራሩና ባለሙያው በጽኑ አቋም መታገል እንደሚገባ ጠቅሰዋል።
በየደረጃዉ የሚገኙ አባላትና አመራር በፕሮግራም፣ በመተዳደሪያ ደንብ እና በዲስፒሊን መመሪያ የተቀመጡ የፀረ-ሙስና ትግል አቅጣጫዎች ማወቅ ብቻ ሳይሆን በሀገሪቱ የፀረ-ሙስና ህጎችና አሰራሮች ግንዛቤ ኖሯቸዉ ተልዕኳቸዉን በብቃትና በቁርጠኝነት መወጣት ይጠበቃል ብለዋል።
የክልሉ ኢንስፔክሽንና ሥነምግባር ኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሰብሳቢ ወ/ሮ ራሄል ለዊ በበኩላቸው ጠንካራ ኮሚሽንና ፓርቲ ለመገንባት የፀረ-ሙስና ትግሉ ህዝባዊ መሰረት እንዲኖረው በቁርጠኝነት መስራት አለብን ብለዋል።
ሌብነትን የሚጸየፍ ትውልድ ለመፍጠር አመራሩ የመሪነት ሚናውን መወጣት እንዳለበት መግለፃቸውን የደ.ሬቴ.ድ ዘግቧል።
በመግባቢያ የስምምነት ሰነዱ ላይ የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነሮች፣ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ሥነምግባር ኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመራሮች፣ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመራሮች፣ የክልሉ የህብረት ኮሚሽን ኮሚቴ አባላት፣ የዞን የኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመራሮች ተገኝተዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
************************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 8/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ሥነምግባር ኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት እና የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን መካከል ብልሹ አሰራርንና ሙስናን ለመታገል በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
የክልሉ ሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሙሉሰው ዘውዴ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፤ የመደመር ሳንካ የሆኑት ሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን በጽኑ አቋም በመታገል ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ መረባረብ ይገባል።
የስምምነት ሰነዱ ቅንጅታዊ አሰራሮችን በማሳለጥ ውጤታማ የሆነ የሙስና እና ብልሹ አሰራሮች ላይ ማዕከል አድርጎ በጥብቅ ዲስፕሊን እና በተጠናከረ መልኩ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።
ለፀረ-ሙስና ትግሉ የሚያግዙ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን መስጠት፣ ጥናት ላይ ተመስርቶ ሙስናን መከላከል እና መረጃዎችን መለዋወጥ እንዲሁም የትውልድ ሥነምግባር ግንባታው ላይ በጋራ ተቀናጅቶ መስራት የኮሚሽኖች የስምምነት አንኳር ጉዳዮች እንደሆነ ኮሚሽነር ሙሉሰው ዘውዴ ገልጸዋል።
በመግባቢያ ሰነዱ የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ታደሰ አይበራ እንደገለጹት፤ በየደረጃው ያለው አመራር፣ ባለሙያና ህብረተሰቡ በሙስና እና ብልሹ አሰራሮች ላይ የተቀናጀ ትግል በማድረግ የተጀመረውን ሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ መረባረብ ይገባል።
ሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን ተቋማት ሁለንተናዊ አቅም በማቀናጀት በመረባረብ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣትና የህብረተሰቡን እርካታ ማሳደግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በተቀናጀና በተደራጀ ሁኔታ ሙስና እና ብልሹ አሰራር በመከላከል የሀገራችንን እና የክልሉን ሁለንተናዊ ብልጽግና እንዲረጋገጥ ሁሉም አመራርና ባለሙያዎች በቁርጠኝነት መስራት እንዳለባቸው ጠቅሰዋል።
በመንግስት እና ህዝብ መካከል ሆኖ በህገ ወጥ ተግባር ላይ የተሰማራውን ኃይል በተቀናጀ መንገድ ተጨባጭነት ያለው የሙስና መከላከል በመስራት እንዲነጠል ማድረግ ይኖርብናል ብለዋል።
ሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል በየደረጃው በተደረጉ የተቀናጁ ጥረቶች በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡ መሆኑን ገልጸው፣ ይህን የተቀናጀ ጥረት የመንግስትና ህዝባዊ ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ በቁርጠኝነት መታገል እንደሚገባ አመላክተዋል።
የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ኢንስፔክሽንና ሥነምግባር ኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳንኤል ያዙ እንደገለጹት፤ በፀረ-ሙስና ትግል ላይ በጋራ አቋም ከሰራን ፓርቲው ያስቀመጣቸውን ግቦች ለማሳካት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል።
ሙስና እና ሌብነት የብልጽግና ፓርቲ ቀይ መስመር በመሆኑ እነዚህን ብልሹ አሰራሮችን ከምንጩ ለማድረቅ አመራሩና ባለሙያው በጽኑ አቋም መታገል እንደሚገባ ጠቅሰዋል።
በየደረጃዉ የሚገኙ አባላትና አመራር በፕሮግራም፣ በመተዳደሪያ ደንብ እና በዲስፒሊን መመሪያ የተቀመጡ የፀረ-ሙስና ትግል አቅጣጫዎች ማወቅ ብቻ ሳይሆን በሀገሪቱ የፀረ-ሙስና ህጎችና አሰራሮች ግንዛቤ ኖሯቸዉ ተልዕኳቸዉን በብቃትና በቁርጠኝነት መወጣት ይጠበቃል ብለዋል።
የክልሉ ኢንስፔክሽንና ሥነምግባር ኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሰብሳቢ ወ/ሮ ራሄል ለዊ በበኩላቸው ጠንካራ ኮሚሽንና ፓርቲ ለመገንባት የፀረ-ሙስና ትግሉ ህዝባዊ መሰረት እንዲኖረው በቁርጠኝነት መስራት አለብን ብለዋል።
ሌብነትን የሚጸየፍ ትውልድ ለመፍጠር አመራሩ የመሪነት ሚናውን መወጣት እንዳለበት መግለፃቸውን የደ.ሬቴ.ድ ዘግቧል።
በመግባቢያ የስምምነት ሰነዱ ላይ የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነሮች፣ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ሥነምግባር ኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመራሮች፣ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመራሮች፣ የክልሉ የህብረት ኮሚሽን ኮሚቴ አባላት፣ የዞን የኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመራሮች ተገኝተዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ሥነምግባር የታነፀ ሠራዊት ተልዕኮውን በድል እንደሚወጣ ተገለፀ
************************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 8/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በጦላይ የከፍተኛ ባለሌላ ማዕረግተኛ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት አመራሮችና ሠራዊት አባላት የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ስልጠና ተሰጥቷል።
በትምህርቱም በማሰልጠኛ ትምህርት ቤቱ ውስጥ እየሰለጠኑ ያሉ ሰልጣኝ ምልምል ወታደሮች፣ የ27ኛ ዙር መጋቢ ሃምሳ አለቃ ሰልጣኞች፣ አሰልጣኞችና የስታፍ ክፍል አባላቶች የተሳተፉ ሲሆን፣ በሥነምግባር የታነፀ ሠራዊት ተልዕኮውን በድል መወጣት እንደሚችልም ተገልጿል።
በትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ የሥነምግባር ክትትል ቡድን መሪ ሌተናል ኮሎኔል ሰፊነሽ ቢረዳ ውትድርና የህይወት መስዋዕትነት የሚከፈልበት፣ ሀገርንና ህግን የሚጠበቅበት ውድና እጅግ የተከበረ የሙያ ዘርፍ በመሆኑ መሰረቱ ሥነምግባር ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ውትድርና እጅግ የተከበረ ሙያ በመሆኑ ለሙያው የሚመጥን ሥነምግባር ያስፈልገዋል ያሉት ሌተናል ኮሎኔል ሰፊነሽ፣ መከላከያ ሰራዊታችን በጥሩ ሥነምግባርና ሙያዊ ዲሲፕሊን ሀገርንና ህዝብን ማገልገል ስለሚጠበቅበት ትምህርቱን መስጠት አስፈላጊ ነው ብለዋል።
ትምህርቱን የሰጡት ሻምበል አብዮት መንገሻ እንደ ተቋም በሥነምግባር የታነፀ መከላከያ ሠራዊት ለመገንባት ዓላማ ተደርጎ እየተሰራ መሆኑን አስታውሰው፣ ሁሉም የመከላከያ ሠራዊት አባላት መልካም ሥነምግባርንና ጥሩ ባህሪን በመላበስ የሚሰጠውን ማንኛውንም ግዳጅ በጀግንነት በታማኝነትና በሙያዊ ዲሲፕሊን ማከናወን ይጠበቅበታል ሲሉ ገልፀዋል።
በተመሳሳይ ሙስናን በመከላከል የዜግነት ግዴታዬን እወጣለሁ በሚል መሪ ሀሳብ ለመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ በአምቦ ዙሪያ ፕሮጀክት ሳይት ላይ ላሉ የተቋሙ የሠራዊት አባላትና ሲቪል ሰራተኞች የሥነ-ምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
************************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 8/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በጦላይ የከፍተኛ ባለሌላ ማዕረግተኛ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት አመራሮችና ሠራዊት አባላት የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ስልጠና ተሰጥቷል።
በትምህርቱም በማሰልጠኛ ትምህርት ቤቱ ውስጥ እየሰለጠኑ ያሉ ሰልጣኝ ምልምል ወታደሮች፣ የ27ኛ ዙር መጋቢ ሃምሳ አለቃ ሰልጣኞች፣ አሰልጣኞችና የስታፍ ክፍል አባላቶች የተሳተፉ ሲሆን፣ በሥነምግባር የታነፀ ሠራዊት ተልዕኮውን በድል መወጣት እንደሚችልም ተገልጿል።
በትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ የሥነምግባር ክትትል ቡድን መሪ ሌተናል ኮሎኔል ሰፊነሽ ቢረዳ ውትድርና የህይወት መስዋዕትነት የሚከፈልበት፣ ሀገርንና ህግን የሚጠበቅበት ውድና እጅግ የተከበረ የሙያ ዘርፍ በመሆኑ መሰረቱ ሥነምግባር ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ውትድርና እጅግ የተከበረ ሙያ በመሆኑ ለሙያው የሚመጥን ሥነምግባር ያስፈልገዋል ያሉት ሌተናል ኮሎኔል ሰፊነሽ፣ መከላከያ ሰራዊታችን በጥሩ ሥነምግባርና ሙያዊ ዲሲፕሊን ሀገርንና ህዝብን ማገልገል ስለሚጠበቅበት ትምህርቱን መስጠት አስፈላጊ ነው ብለዋል።
ትምህርቱን የሰጡት ሻምበል አብዮት መንገሻ እንደ ተቋም በሥነምግባር የታነፀ መከላከያ ሠራዊት ለመገንባት ዓላማ ተደርጎ እየተሰራ መሆኑን አስታውሰው፣ ሁሉም የመከላከያ ሠራዊት አባላት መልካም ሥነምግባርንና ጥሩ ባህሪን በመላበስ የሚሰጠውን ማንኛውንም ግዳጅ በጀግንነት በታማኝነትና በሙያዊ ዲሲፕሊን ማከናወን ይጠበቅበታል ሲሉ ገልፀዋል።
በተመሳሳይ ሙስናን በመከላከል የዜግነት ግዴታዬን እወጣለሁ በሚል መሪ ሀሳብ ለመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ በአምቦ ዙሪያ ፕሮጀክት ሳይት ላይ ላሉ የተቋሙ የሠራዊት አባላትና ሲቪል ሰራተኞች የሥነ-ምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319