የኮሚሽናችን አሠራር በማዘመንና ከእጅ ንክኪ ነፃ በማድረግ ለሙስና እና ብልሹ አሠራር ተጋላጭ እንዳይሆን የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - አቶ አዘዘው ጫኔ
************************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 8/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ለጉምሩክ ኮሚሽን ሠራተኞች ሙስና በመከላከል የዜግነት ግዴታዬን እወጣለሁ በሚል መሪ ሀሳብ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል፡፡
በስልጠናው የተገኙት የጉምሩክ ኮሚሽን የህግ ማስከበር ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር አቶ አዘዘው ጫኔ ስልጠናው ከተቋማችን አመራርና ሠራተኛች ባሻገር ለባለድርሻ አካላት ጠቃሚ በመሆኑ በተከታታይነት የምንሰጥ ይሆናል ብለዋል፡፡
ኮሚሽኑ በባህሪው ለሙስና እና ብልሹ አሠራር ተጋላጭ በመሆኑ አመራሩና ሠራተኛው በሥነምግባሩ አርዓያ እንዲሆንና ብልሹ አሠራርን አምርሮ እንዲታገል የሥነምግባር ግንባታ ስልጠናዎችን እየሰጠን እንገኛለን ብለዋል፡፡
ተቋማችን ሥነምግባርን ከመገንባትና ሙስናን ከመከላከል አንፃር ከቁልፍ ባለድርሻ አካላት ጋርም ትኩረት በመስጠት እተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የኮሚሽናችን አሠራር በማዘመንና ከእጅ ንክኪ ነፃ በማድረግ ለሙስና እና ብልሹ አሠራር ተጋላጭ እንዳይሆን የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልዋል፡፡
ለሁለት ቀናት የስልጠና ቆይታችሁ ፍፁም ሠላማዊ በሆነ መልኩ ስልጠናውን መከታተል አልባችሁ ብለዋል፡፡
የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ክቡር አቶ ፍቃዱ ሰቦቃ በበኩላቸው ስልጠናው በዘርፉ የሙስና እና ብልሹ አሠራር ተጋላጭትን ጥናት ላይ በተለዩ ችግሮች መነሻነት የሚሰጥ ነው ብለዋል፡፡
ተቋሙ ለሙስና እና ብልሹ አሠራር ተጋላጭነቱ ከፍተኛ መሆኑን በመገንዘብ አመራሩና ሠራተኛው በኮሚሽኑ ላይ የሚስተዋሉ ሙስና እና ብልሹ አሠራሮችን በጥናት በመለየት ቀዳዳዎችን መድፈን እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
የኮሚሽኑ አመራርና ሠራተኛ በአገርዓቀፍ ደረጃ ኮንትሮባንድ እንዳይበራከት የራሱን አስተዋፅኦ መወጣት አለበት፤ በተለይ ከመድሃኒት ጋር የሚስተዋሉ የኮንትሮባንድ ብልሹ አሠራሮች በዜጎች ህይዎት ላይ የሚደርሰውን ችግር በመረዳት በጋራ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
ከዚህ ባሻገር የራሳቸውን ኔትወርክ በመዘርጋት ሙስና እና ብልሹ አሰራር በሚሰሩ ግለሰቦች ላይ ክትትል በማድረግ የማያዳገም የዕርምት እርምጃ መውሰድ እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡
ስልጠናው በዶ/ር አወቀ አሸናፊ እና በዶ/ር የሱፍ ኢብራሒም እየተሰጠ ሲሆን፤ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚቀጥል ይሆናል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
************************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 8/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ለጉምሩክ ኮሚሽን ሠራተኞች ሙስና በመከላከል የዜግነት ግዴታዬን እወጣለሁ በሚል መሪ ሀሳብ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል፡፡
በስልጠናው የተገኙት የጉምሩክ ኮሚሽን የህግ ማስከበር ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር አቶ አዘዘው ጫኔ ስልጠናው ከተቋማችን አመራርና ሠራተኛች ባሻገር ለባለድርሻ አካላት ጠቃሚ በመሆኑ በተከታታይነት የምንሰጥ ይሆናል ብለዋል፡፡
ኮሚሽኑ በባህሪው ለሙስና እና ብልሹ አሠራር ተጋላጭ በመሆኑ አመራሩና ሠራተኛው በሥነምግባሩ አርዓያ እንዲሆንና ብልሹ አሠራርን አምርሮ እንዲታገል የሥነምግባር ግንባታ ስልጠናዎችን እየሰጠን እንገኛለን ብለዋል፡፡
ተቋማችን ሥነምግባርን ከመገንባትና ሙስናን ከመከላከል አንፃር ከቁልፍ ባለድርሻ አካላት ጋርም ትኩረት በመስጠት እተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የኮሚሽናችን አሠራር በማዘመንና ከእጅ ንክኪ ነፃ በማድረግ ለሙስና እና ብልሹ አሠራር ተጋላጭ እንዳይሆን የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልዋል፡፡
ለሁለት ቀናት የስልጠና ቆይታችሁ ፍፁም ሠላማዊ በሆነ መልኩ ስልጠናውን መከታተል አልባችሁ ብለዋል፡፡
የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ክቡር አቶ ፍቃዱ ሰቦቃ በበኩላቸው ስልጠናው በዘርፉ የሙስና እና ብልሹ አሠራር ተጋላጭትን ጥናት ላይ በተለዩ ችግሮች መነሻነት የሚሰጥ ነው ብለዋል፡፡
ተቋሙ ለሙስና እና ብልሹ አሠራር ተጋላጭነቱ ከፍተኛ መሆኑን በመገንዘብ አመራሩና ሠራተኛው በኮሚሽኑ ላይ የሚስተዋሉ ሙስና እና ብልሹ አሠራሮችን በጥናት በመለየት ቀዳዳዎችን መድፈን እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
የኮሚሽኑ አመራርና ሠራተኛ በአገርዓቀፍ ደረጃ ኮንትሮባንድ እንዳይበራከት የራሱን አስተዋፅኦ መወጣት አለበት፤ በተለይ ከመድሃኒት ጋር የሚስተዋሉ የኮንትሮባንድ ብልሹ አሠራሮች በዜጎች ህይዎት ላይ የሚደርሰውን ችግር በመረዳት በጋራ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
ከዚህ ባሻገር የራሳቸውን ኔትወርክ በመዘርጋት ሙስና እና ብልሹ አሰራር በሚሰሩ ግለሰቦች ላይ ክትትል በማድረግ የማያዳገም የዕርምት እርምጃ መውሰድ እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡
ስልጠናው በዶ/ር አወቀ አሸናፊ እና በዶ/ር የሱፍ ኢብራሒም እየተሰጠ ሲሆን፤ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚቀጥል ይሆናል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ሁለንተናዊ ተቋማዊ አቅም በማቀናጀትና በመረባረብ ሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን መታገል እንደሚገባ ተገለጸ
************************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 8/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ሥነምግባር ኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት እና የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን መካከል ብልሹ አሰራርንና ሙስናን ለመታገል በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
የክልሉ ሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሙሉሰው ዘውዴ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፤ የመደመር ሳንካ የሆኑት ሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን በጽኑ አቋም በመታገል ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ መረባረብ ይገባል።
የስምምነት ሰነዱ ቅንጅታዊ አሰራሮችን በማሳለጥ ውጤታማ የሆነ የሙስና እና ብልሹ አሰራሮች ላይ ማዕከል አድርጎ በጥብቅ ዲስፕሊን እና በተጠናከረ መልኩ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።
ለፀረ-ሙስና ትግሉ የሚያግዙ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን መስጠት፣ ጥናት ላይ ተመስርቶ ሙስናን መከላከል እና መረጃዎችን መለዋወጥ እንዲሁም የትውልድ ሥነምግባር ግንባታው ላይ በጋራ ተቀናጅቶ መስራት የኮሚሽኖች የስምምነት አንኳር ጉዳዮች እንደሆነ ኮሚሽነር ሙሉሰው ዘውዴ ገልጸዋል።
በመግባቢያ ሰነዱ የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ታደሰ አይበራ እንደገለጹት፤ በየደረጃው ያለው አመራር፣ ባለሙያና ህብረተሰቡ በሙስና እና ብልሹ አሰራሮች ላይ የተቀናጀ ትግል በማድረግ የተጀመረውን ሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ መረባረብ ይገባል።
ሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን ተቋማት ሁለንተናዊ አቅም በማቀናጀት በመረባረብ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣትና የህብረተሰቡን እርካታ ማሳደግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በተቀናጀና በተደራጀ ሁኔታ ሙስና እና ብልሹ አሰራር በመከላከል የሀገራችንን እና የክልሉን ሁለንተናዊ ብልጽግና እንዲረጋገጥ ሁሉም አመራርና ባለሙያዎች በቁርጠኝነት መስራት እንዳለባቸው ጠቅሰዋል።
በመንግስት እና ህዝብ መካከል ሆኖ በህገ ወጥ ተግባር ላይ የተሰማራውን ኃይል በተቀናጀ መንገድ ተጨባጭነት ያለው የሙስና መከላከል በመስራት እንዲነጠል ማድረግ ይኖርብናል ብለዋል።
ሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል በየደረጃው በተደረጉ የተቀናጁ ጥረቶች በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡ መሆኑን ገልጸው፣ ይህን የተቀናጀ ጥረት የመንግስትና ህዝባዊ ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ በቁርጠኝነት መታገል እንደሚገባ አመላክተዋል።
የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ኢንስፔክሽንና ሥነምግባር ኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳንኤል ያዙ እንደገለጹት፤ በፀረ-ሙስና ትግል ላይ በጋራ አቋም ከሰራን ፓርቲው ያስቀመጣቸውን ግቦች ለማሳካት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል።
ሙስና እና ሌብነት የብልጽግና ፓርቲ ቀይ መስመር በመሆኑ እነዚህን ብልሹ አሰራሮችን ከምንጩ ለማድረቅ አመራሩና ባለሙያው በጽኑ አቋም መታገል እንደሚገባ ጠቅሰዋል።
በየደረጃዉ የሚገኙ አባላትና አመራር በፕሮግራም፣ በመተዳደሪያ ደንብ እና በዲስፒሊን መመሪያ የተቀመጡ የፀረ-ሙስና ትግል አቅጣጫዎች ማወቅ ብቻ ሳይሆን በሀገሪቱ የፀረ-ሙስና ህጎችና አሰራሮች ግንዛቤ ኖሯቸዉ ተልዕኳቸዉን በብቃትና በቁርጠኝነት መወጣት ይጠበቃል ብለዋል።
የክልሉ ኢንስፔክሽንና ሥነምግባር ኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሰብሳቢ ወ/ሮ ራሄል ለዊ በበኩላቸው ጠንካራ ኮሚሽንና ፓርቲ ለመገንባት የፀረ-ሙስና ትግሉ ህዝባዊ መሰረት እንዲኖረው በቁርጠኝነት መስራት አለብን ብለዋል።
ሌብነትን የሚጸየፍ ትውልድ ለመፍጠር አመራሩ የመሪነት ሚናውን መወጣት እንዳለበት መግለፃቸውን የደ.ሬቴ.ድ ዘግቧል።
በመግባቢያ የስምምነት ሰነዱ ላይ የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነሮች፣ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ሥነምግባር ኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመራሮች፣ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመራሮች፣ የክልሉ የህብረት ኮሚሽን ኮሚቴ አባላት፣ የዞን የኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመራሮች ተገኝተዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
************************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 8/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ሥነምግባር ኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት እና የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን መካከል ብልሹ አሰራርንና ሙስናን ለመታገል በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
የክልሉ ሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሙሉሰው ዘውዴ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፤ የመደመር ሳንካ የሆኑት ሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን በጽኑ አቋም በመታገል ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ መረባረብ ይገባል።
የስምምነት ሰነዱ ቅንጅታዊ አሰራሮችን በማሳለጥ ውጤታማ የሆነ የሙስና እና ብልሹ አሰራሮች ላይ ማዕከል አድርጎ በጥብቅ ዲስፕሊን እና በተጠናከረ መልኩ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።
ለፀረ-ሙስና ትግሉ የሚያግዙ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን መስጠት፣ ጥናት ላይ ተመስርቶ ሙስናን መከላከል እና መረጃዎችን መለዋወጥ እንዲሁም የትውልድ ሥነምግባር ግንባታው ላይ በጋራ ተቀናጅቶ መስራት የኮሚሽኖች የስምምነት አንኳር ጉዳዮች እንደሆነ ኮሚሽነር ሙሉሰው ዘውዴ ገልጸዋል።
በመግባቢያ ሰነዱ የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ታደሰ አይበራ እንደገለጹት፤ በየደረጃው ያለው አመራር፣ ባለሙያና ህብረተሰቡ በሙስና እና ብልሹ አሰራሮች ላይ የተቀናጀ ትግል በማድረግ የተጀመረውን ሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ መረባረብ ይገባል።
ሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን ተቋማት ሁለንተናዊ አቅም በማቀናጀት በመረባረብ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣትና የህብረተሰቡን እርካታ ማሳደግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በተቀናጀና በተደራጀ ሁኔታ ሙስና እና ብልሹ አሰራር በመከላከል የሀገራችንን እና የክልሉን ሁለንተናዊ ብልጽግና እንዲረጋገጥ ሁሉም አመራርና ባለሙያዎች በቁርጠኝነት መስራት እንዳለባቸው ጠቅሰዋል።
በመንግስት እና ህዝብ መካከል ሆኖ በህገ ወጥ ተግባር ላይ የተሰማራውን ኃይል በተቀናጀ መንገድ ተጨባጭነት ያለው የሙስና መከላከል በመስራት እንዲነጠል ማድረግ ይኖርብናል ብለዋል።
ሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል በየደረጃው በተደረጉ የተቀናጁ ጥረቶች በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡ መሆኑን ገልጸው፣ ይህን የተቀናጀ ጥረት የመንግስትና ህዝባዊ ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ በቁርጠኝነት መታገል እንደሚገባ አመላክተዋል።
የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ኢንስፔክሽንና ሥነምግባር ኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳንኤል ያዙ እንደገለጹት፤ በፀረ-ሙስና ትግል ላይ በጋራ አቋም ከሰራን ፓርቲው ያስቀመጣቸውን ግቦች ለማሳካት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል።
ሙስና እና ሌብነት የብልጽግና ፓርቲ ቀይ መስመር በመሆኑ እነዚህን ብልሹ አሰራሮችን ከምንጩ ለማድረቅ አመራሩና ባለሙያው በጽኑ አቋም መታገል እንደሚገባ ጠቅሰዋል።
በየደረጃዉ የሚገኙ አባላትና አመራር በፕሮግራም፣ በመተዳደሪያ ደንብ እና በዲስፒሊን መመሪያ የተቀመጡ የፀረ-ሙስና ትግል አቅጣጫዎች ማወቅ ብቻ ሳይሆን በሀገሪቱ የፀረ-ሙስና ህጎችና አሰራሮች ግንዛቤ ኖሯቸዉ ተልዕኳቸዉን በብቃትና በቁርጠኝነት መወጣት ይጠበቃል ብለዋል።
የክልሉ ኢንስፔክሽንና ሥነምግባር ኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሰብሳቢ ወ/ሮ ራሄል ለዊ በበኩላቸው ጠንካራ ኮሚሽንና ፓርቲ ለመገንባት የፀረ-ሙስና ትግሉ ህዝባዊ መሰረት እንዲኖረው በቁርጠኝነት መስራት አለብን ብለዋል።
ሌብነትን የሚጸየፍ ትውልድ ለመፍጠር አመራሩ የመሪነት ሚናውን መወጣት እንዳለበት መግለፃቸውን የደ.ሬቴ.ድ ዘግቧል።
በመግባቢያ የስምምነት ሰነዱ ላይ የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነሮች፣ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ሥነምግባር ኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመራሮች፣ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመራሮች፣ የክልሉ የህብረት ኮሚሽን ኮሚቴ አባላት፣ የዞን የኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመራሮች ተገኝተዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319