ኢትዮጵያ ለጀመረችውና መድረስ ለምታስበው የለውጥ ጉዞ እንቅፋት የሆነውን ሙስና በጋራ ልንታገለው ይገባል - ወ/ሮ አየለች እሸቴ
****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 6/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በትምህርት ዘርፍ ባጠናው የሙስና ተጋላጭነት ሥጋት ጥናት ዙሪያ ከሚኒስቴር መስሪያቤቱ እና ተጠሪ ተቋማት አመራሮች ጋር ውይይት አካሄዷል።
በመድረኩ የተገኙት በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ኢትዮጵያ ለጀመረችውና መድረስ ለምታስበው የለውጥ ጉዞ እንቅፋት የሆነውን ሙስና በጋራ መታገል ያስፈልጋል።
በተለይ የትምህርት ዘርፉ ትውልዱን በመልካም ሥነምግባር የመቅረፅና ሙስናን የመከላከል ኃላፊነት አለበት ብለዋል።
ሚኒስትር ዴታዋ አክለውም ዘርፉ ትውልድን በሥነምግባር ከመገንባት አኳያ የአንበሳውን ድርሻ የሚወጣ ተቋም መሆኑን ጠቁመው፥ ለዚህም ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ የግብረገብነት ትምህርት እየተሰጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
አመራሩ በጥናቱ የተለዩ የብልሹ አሠራር አዝማሚያዎችን የእቅድ አካል በማድረግ ቀዳዳዎችን መድፈን እንደሚገባ ገልፀው፥ ችግሩን ለመቅረፍም ከኮሚሽኑ ጋር በትብብርና ቅንጅት እንሰራለን ብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው በትምህርት ዘርፍ የሚስተዋሉ ሙስና እና ብልሹ አሠራሮችን ለመከላከል በቴክኖሎጂ የተደገፈ ሥርዓት ማበጀት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
ሙስና እንደ ሀገር የልማት ግቦችን ለማሳካት ግንባር ቀደም ማነቆ በመሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መስራት ይገባል ብለዋል።
የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የሙስና መከላከል ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ክቡር አቶ እሸቴ አስፋው ዘርፍ ተኮር የሙስና መከላከል ጥናት ተቋማት ያሉባቸውን ክፍተቶች በማሳየት በየደረጃው ያለው አመራር ችግሩን በማወቅ ትኩረት አድርጎ እንዲሰራና ሙስና ከመፈፀሙ በፊት ለመከላከል ያግዛል ብለዋል።
ምክትል ኮሚሽነሩ አክለውም ሙስና እና ብልሹ አሰራርን መከላከል የሚቻለው መብቱን በገንዘብ የማይገዛ ማህበረሰብ ስንፈጥር ነው፥ ለዚህም የትምህርት ዘርፍ ትውልዱን በሥነምግባር ማነፅ ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።
በቀጣይም በትምህርት ዘርፍ የሀብት ማሳወቅና ማስመዝገብ እንደሚሰራ ጠቁመው፥ አመራሩም ለውጤታማነቱ በግንባር ቀደምትነት አርዓያ በመሆን የማስመዝገብ ሥራውን በኃላፊነት መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል።
የኮሚሽኑ የሙስና መከላከል ጥናት መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ገዛኸኝ ጋሻው በትምህርት ዘርፍ የሙስና ተጋላጭነት ጥናትና የአመራሩ ሚና በሚል ርዕስ የተዘጋጀውን የጥናት ሪፖርት አቅርበው ተሳታፊዎች ሀሳብና አስተያየት በማንሳት ውይይት ተደርጎበታል።
በውይይቱ ላይ የትምህርት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታዎችና አመራሮች እንዲሁም የተጠሪ ተቋማት አመራሮች፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዝዳንቶችና አመራሮች እንዲሁም የኮሚሽኑ የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 6/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በትምህርት ዘርፍ ባጠናው የሙስና ተጋላጭነት ሥጋት ጥናት ዙሪያ ከሚኒስቴር መስሪያቤቱ እና ተጠሪ ተቋማት አመራሮች ጋር ውይይት አካሄዷል።
በመድረኩ የተገኙት በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ኢትዮጵያ ለጀመረችውና መድረስ ለምታስበው የለውጥ ጉዞ እንቅፋት የሆነውን ሙስና በጋራ መታገል ያስፈልጋል።
በተለይ የትምህርት ዘርፉ ትውልዱን በመልካም ሥነምግባር የመቅረፅና ሙስናን የመከላከል ኃላፊነት አለበት ብለዋል።
ሚኒስትር ዴታዋ አክለውም ዘርፉ ትውልድን በሥነምግባር ከመገንባት አኳያ የአንበሳውን ድርሻ የሚወጣ ተቋም መሆኑን ጠቁመው፥ ለዚህም ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ የግብረገብነት ትምህርት እየተሰጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
አመራሩ በጥናቱ የተለዩ የብልሹ አሠራር አዝማሚያዎችን የእቅድ አካል በማድረግ ቀዳዳዎችን መድፈን እንደሚገባ ገልፀው፥ ችግሩን ለመቅረፍም ከኮሚሽኑ ጋር በትብብርና ቅንጅት እንሰራለን ብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው በትምህርት ዘርፍ የሚስተዋሉ ሙስና እና ብልሹ አሠራሮችን ለመከላከል በቴክኖሎጂ የተደገፈ ሥርዓት ማበጀት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
ሙስና እንደ ሀገር የልማት ግቦችን ለማሳካት ግንባር ቀደም ማነቆ በመሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መስራት ይገባል ብለዋል።
የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የሙስና መከላከል ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ክቡር አቶ እሸቴ አስፋው ዘርፍ ተኮር የሙስና መከላከል ጥናት ተቋማት ያሉባቸውን ክፍተቶች በማሳየት በየደረጃው ያለው አመራር ችግሩን በማወቅ ትኩረት አድርጎ እንዲሰራና ሙስና ከመፈፀሙ በፊት ለመከላከል ያግዛል ብለዋል።
ምክትል ኮሚሽነሩ አክለውም ሙስና እና ብልሹ አሰራርን መከላከል የሚቻለው መብቱን በገንዘብ የማይገዛ ማህበረሰብ ስንፈጥር ነው፥ ለዚህም የትምህርት ዘርፍ ትውልዱን በሥነምግባር ማነፅ ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።
በቀጣይም በትምህርት ዘርፍ የሀብት ማሳወቅና ማስመዝገብ እንደሚሰራ ጠቁመው፥ አመራሩም ለውጤታማነቱ በግንባር ቀደምትነት አርዓያ በመሆን የማስመዝገብ ሥራውን በኃላፊነት መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል።
የኮሚሽኑ የሙስና መከላከል ጥናት መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ገዛኸኝ ጋሻው በትምህርት ዘርፍ የሙስና ተጋላጭነት ጥናትና የአመራሩ ሚና በሚል ርዕስ የተዘጋጀውን የጥናት ሪፖርት አቅርበው ተሳታፊዎች ሀሳብና አስተያየት በማንሳት ውይይት ተደርጎበታል።
በውይይቱ ላይ የትምህርት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታዎችና አመራሮች እንዲሁም የተጠሪ ተቋማት አመራሮች፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዝዳንቶችና አመራሮች እንዲሁም የኮሚሽኑ የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
የተቋማትን አሠራር ግልፀኝነትና ተጠያቂነት በማስፈን ለሀገር ልማትና ብልፅግና ፀር የሆነውን የሙስና ወንጀል ለመከላከል በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ተገለፀ
****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 7/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የጋምቤላ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ለማጃንግ ዞን እና ለጎደሬ ወረዳ አመራር፣ ለግዥና ፋይናንስ እና ለፍትህ ዘርፍ አመራሮች እንዲሁም ለሥነምግባር መኮነኖች በስ ሥራ ላይ ሥነምግባር፣ ግዥና ሙስና በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።
በስልጠናው የተገኙት የማጃንግ ብሔረሰብ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ትህትና ቢኒያም ሙስና ቀይ መስመር መሆኑ አንደ ፓርቲና መንግስት አቅጣጫ የተቀመጠበት በመሆኑ አመራሩ ተጠያቂነት እንደማይቀር በማመን ከሙስና እና ኢ-ሥነምግባራዊነት ራሱን እንዲያርቅና እጁን ከመሰብሰቡ ባሻገር ትክክልኛ ሀብቱን እንዲያስመዘግብ አሳስበዋል።
እንደ ዞንም ሆነ እንደ ወረዳ ያለውን ዕምቅ የተፈጥሮ ሀብት፣ የመሬት አያያዝና ልማት እንዲሁም የመንግስት በጀት አጠቃቀም ከሙስና እና ብልሹ አሰራር የፀዳ ለማድረግና በፍትሃዊነት ለመጠቀም የአመራሩና ባለሙያው አቅም በማብቃት ያሉብንን የአሠራር ክፍተቶች ለመሙላት፣ መመሪያ እንዲተገበር ለማስቻል እንዲህ ያሉ ስልጠናዎች አስፈላጊ በመሆናቸው ቀጣይነት ሊኖራቸው ይገባል ብለዋል።
የክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የሙስና መከላከል ከፍተኛ ባለሙያ አቶ አዲሱ ታደሰ በበኩላቸው የስልጠናው ዋና ዓላማ በመንግሥት መ/ቤቶችም ሆነ በልማት ድርጅቶች የአሰራር ብልሽቶች ሊያስከትሉ የሚችሉ ክፍተቶች በመለየት የግንዛቤ መፍጠሪያ ሥራዎች በማጠናከር ሙስናንን አስቀድሞ መከላከል ትኩረት ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ሙስና እና ብልሹ አሰራሮች በመንግስትና በህዝብ ሀብት የሚፈፀሙ ወንጀሎች በመሆናቸው ሁሉም ዜጋ በቁርጠኝነት ሊታገላቸው እንደሚገባም አሳስበዋል ።
የኮሚሽኑ የሙስና ወንጀል መከላከል ዳይሬክተር ወ/ሮ መሠረት ሙሉቀን፥ ኮሚሽኑ ከሚያከናውናቸው ዋና ዋና ተግባራት አንዱ ህብረተሰቡንና ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል እንዲቻል ሥልጠናዎችን ማዘጋጀትና ትምህርት መሥጠት መሆኑን ገልፀው፥ ጠቃሜታው ጉልህ እንደሆነ አመላክተዋል።
ስለሆነም የተቋማትን አሰራር ግልፅና ተጠያቂነት ያለበት ለማድረግ የሥነምግባር መከታተያ ክፍል ባለሙያዎች እንዲሟሉ ማድረግ ይገባል ማለታቸውን ከኮሚሽኑ የማህበራዊ ትስስር ገፅ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ወ/ሮ መሠረት አክለውም ለዕድገትና ብልፅግና ተግዳሮት የሆነውን የሙስና ወንጀልን ለመከላከል የባለድርሻ አካላትንና የዜጎችን ንቁ ተሳትፎ የሚጠይቅ ሥራ በመሆኑ በትብብር እንድንሠራ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 7/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የጋምቤላ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ለማጃንግ ዞን እና ለጎደሬ ወረዳ አመራር፣ ለግዥና ፋይናንስ እና ለፍትህ ዘርፍ አመራሮች እንዲሁም ለሥነምግባር መኮነኖች በስ ሥራ ላይ ሥነምግባር፣ ግዥና ሙስና በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።
በስልጠናው የተገኙት የማጃንግ ብሔረሰብ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ትህትና ቢኒያም ሙስና ቀይ መስመር መሆኑ አንደ ፓርቲና መንግስት አቅጣጫ የተቀመጠበት በመሆኑ አመራሩ ተጠያቂነት እንደማይቀር በማመን ከሙስና እና ኢ-ሥነምግባራዊነት ራሱን እንዲያርቅና እጁን ከመሰብሰቡ ባሻገር ትክክልኛ ሀብቱን እንዲያስመዘግብ አሳስበዋል።
እንደ ዞንም ሆነ እንደ ወረዳ ያለውን ዕምቅ የተፈጥሮ ሀብት፣ የመሬት አያያዝና ልማት እንዲሁም የመንግስት በጀት አጠቃቀም ከሙስና እና ብልሹ አሰራር የፀዳ ለማድረግና በፍትሃዊነት ለመጠቀም የአመራሩና ባለሙያው አቅም በማብቃት ያሉብንን የአሠራር ክፍተቶች ለመሙላት፣ መመሪያ እንዲተገበር ለማስቻል እንዲህ ያሉ ስልጠናዎች አስፈላጊ በመሆናቸው ቀጣይነት ሊኖራቸው ይገባል ብለዋል።
የክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የሙስና መከላከል ከፍተኛ ባለሙያ አቶ አዲሱ ታደሰ በበኩላቸው የስልጠናው ዋና ዓላማ በመንግሥት መ/ቤቶችም ሆነ በልማት ድርጅቶች የአሰራር ብልሽቶች ሊያስከትሉ የሚችሉ ክፍተቶች በመለየት የግንዛቤ መፍጠሪያ ሥራዎች በማጠናከር ሙስናንን አስቀድሞ መከላከል ትኩረት ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ሙስና እና ብልሹ አሰራሮች በመንግስትና በህዝብ ሀብት የሚፈፀሙ ወንጀሎች በመሆናቸው ሁሉም ዜጋ በቁርጠኝነት ሊታገላቸው እንደሚገባም አሳስበዋል ።
የኮሚሽኑ የሙስና ወንጀል መከላከል ዳይሬክተር ወ/ሮ መሠረት ሙሉቀን፥ ኮሚሽኑ ከሚያከናውናቸው ዋና ዋና ተግባራት አንዱ ህብረተሰቡንና ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል እንዲቻል ሥልጠናዎችን ማዘጋጀትና ትምህርት መሥጠት መሆኑን ገልፀው፥ ጠቃሜታው ጉልህ እንደሆነ አመላክተዋል።
ስለሆነም የተቋማትን አሰራር ግልፅና ተጠያቂነት ያለበት ለማድረግ የሥነምግባር መከታተያ ክፍል ባለሙያዎች እንዲሟሉ ማድረግ ይገባል ማለታቸውን ከኮሚሽኑ የማህበራዊ ትስስር ገፅ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ወ/ሮ መሠረት አክለውም ለዕድገትና ብልፅግና ተግዳሮት የሆነውን የሙስና ወንጀልን ለመከላከል የባለድርሻ አካላትንና የዜጎችን ንቁ ተሳትፎ የሚጠይቅ ሥራ በመሆኑ በትብብር እንድንሠራ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ኮሚሽኑ በሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ላይ ትኩረት ያደረገ የውይይት መድረክ እያካሄደ መሆኑን ገለፀ
************************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 8/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ላይ ትኩረት ያደረገ የውይይት መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ በማካሄድ ላይ ይገኛል።
ውይይቱ በሀገሪቱ የሚከሰቱ የሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል ያለመ መሆኑን ተመላክቷል።
በወቅቱ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሶፈንያስ ደስታ ሙስና ሀገርን የሚያወድም አደገኛ በሽታ ነዉ ብለዋል።
በሙስና የሚከሰቱ ችግሮች በጊዜ ካልተቀረፈ በሀገሪቱ የሚፈለገውን ልማት ማስመዝገብ እንደማይቻል ገልፀው፣ ለዚህም በትውልድ ላይ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
በትውልድ ላይ ሥነምግባር ማስተማር ይገባል ያሉት አቶ ሶፈንያስ፣ የክልሉ ኮሚሽንም ትውልድን በሥነምግባር ለማነጽ ትኩረት ሰጥቶት እየሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ለውይይቱ መነሻ የሚሆን በሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ላይ ትኩረት ያደረገ ሰነድ ቀርቦ ዉይይት የሚደረግ ይሆናል።
በመድረኩ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ እንደሆኑም ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
************************
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 8/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ላይ ትኩረት ያደረገ የውይይት መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ በማካሄድ ላይ ይገኛል።
ውይይቱ በሀገሪቱ የሚከሰቱ የሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል ያለመ መሆኑን ተመላክቷል።
በወቅቱ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሶፈንያስ ደስታ ሙስና ሀገርን የሚያወድም አደገኛ በሽታ ነዉ ብለዋል።
በሙስና የሚከሰቱ ችግሮች በጊዜ ካልተቀረፈ በሀገሪቱ የሚፈለገውን ልማት ማስመዝገብ እንደማይቻል ገልፀው፣ ለዚህም በትውልድ ላይ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
በትውልድ ላይ ሥነምግባር ማስተማር ይገባል ያሉት አቶ ሶፈንያስ፣ የክልሉ ኮሚሽንም ትውልድን በሥነምግባር ለማነጽ ትኩረት ሰጥቶት እየሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ለውይይቱ መነሻ የሚሆን በሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ላይ ትኩረት ያደረገ ሰነድ ቀርቦ ዉይይት የሚደረግ ይሆናል።
በመድረኩ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ እንደሆኑም ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319