ሙስናን መዋጋት የሚችል የተቋም ሠራተኛን በማፍራት የተጣለብንን ሀገራዊ ተልዕኮዎች ማሳካት ይጠበቅብናል - ኮ/ል ስለሺ ነገራ
********
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 6/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) "ሙስናን በመከላከል የዜግነት ግዴታዬን እወጣለሁ" በሚል መሪ ሀሳብ በመከላከያ ዘርፍ ለመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ለየሆሚቾ አሙኒሽን ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ አመራርና ሠራተኞች ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል የሚወሰዱ መከላከያ ስልቶች ላይ ያተኮረ የሁለት ቀናት ሥልጠና በአምቦ ከተማ ተሰጥቷል፡፡
በመክፈቻ ንግግር ስልጠናውን ያስጀመሩት የሆሚቾ አሙኒሽን ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ዋና ስራ አስኪያጅ ኮ/ል ስለሺ ነገራ ሙስናን መዋጋት የሚችል የተቋም ሠራተኛን በማፍራት የተጣለብንን ሀገራዊ ተልዕኮዎች ማሳካት ይጠበቅብናል ብለዋል።
ስልጠናውን የሰጡት ሻ/ቃ ኤፍሬም ተሸመ በበኩላቸው የሙስና ወንጀል ዓይነቶችን ጠንቅቆ በማወቅ ራስን ብሎም ሃገርን ከሙስና ስጋት መጠበቅ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
በመጨረሻም የስልጠናው ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ”ሙስና የሀገርን እድገት የሚያቀጭጭ የዜጎችን የማደግ ዕድል የሚገታ አደገኛ ወንጀል በመሆኑ ሁሉም ዜጋ የመታገል ኃላፊነት አለበት ብለዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
********
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 6/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) "ሙስናን በመከላከል የዜግነት ግዴታዬን እወጣለሁ" በሚል መሪ ሀሳብ በመከላከያ ዘርፍ ለመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ለየሆሚቾ አሙኒሽን ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ አመራርና ሠራተኞች ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል የሚወሰዱ መከላከያ ስልቶች ላይ ያተኮረ የሁለት ቀናት ሥልጠና በአምቦ ከተማ ተሰጥቷል፡፡
በመክፈቻ ንግግር ስልጠናውን ያስጀመሩት የሆሚቾ አሙኒሽን ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ዋና ስራ አስኪያጅ ኮ/ል ስለሺ ነገራ ሙስናን መዋጋት የሚችል የተቋም ሠራተኛን በማፍራት የተጣለብንን ሀገራዊ ተልዕኮዎች ማሳካት ይጠበቅብናል ብለዋል።
ስልጠናውን የሰጡት ሻ/ቃ ኤፍሬም ተሸመ በበኩላቸው የሙስና ወንጀል ዓይነቶችን ጠንቅቆ በማወቅ ራስን ብሎም ሃገርን ከሙስና ስጋት መጠበቅ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
በመጨረሻም የስልጠናው ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ”ሙስና የሀገርን እድገት የሚያቀጭጭ የዜጎችን የማደግ ዕድል የሚገታ አደገኛ ወንጀል በመሆኑ ሁሉም ዜጋ የመታገል ኃላፊነት አለበት ብለዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ኢትዮጵያ ለጀመረችውና መድረስ ለምታስበው የለውጥ ጉዞ እንቅፋት የሆነውን ሙስና በጋራ ልንታገለው ይገባል - ወ/ሮ አየለች እሸቴ
****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 6/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በትምህርት ዘርፍ ባጠናው የሙስና ተጋላጭነት ሥጋት ጥናት ዙሪያ ከሚኒስቴር መስሪያቤቱ እና ተጠሪ ተቋማት አመራሮች ጋር ውይይት አካሄዷል።
በመድረኩ የተገኙት በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ኢትዮጵያ ለጀመረችውና መድረስ ለምታስበው የለውጥ ጉዞ እንቅፋት የሆነውን ሙስና በጋራ መታገል ያስፈልጋል።
በተለይ የትምህርት ዘርፉ ትውልዱን በመልካም ሥነምግባር የመቅረፅና ሙስናን የመከላከል ኃላፊነት አለበት ብለዋል።
ሚኒስትር ዴታዋ አክለውም ዘርፉ ትውልድን በሥነምግባር ከመገንባት አኳያ የአንበሳውን ድርሻ የሚወጣ ተቋም መሆኑን ጠቁመው፥ ለዚህም ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ የግብረገብነት ትምህርት እየተሰጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
አመራሩ በጥናቱ የተለዩ የብልሹ አሠራር አዝማሚያዎችን የእቅድ አካል በማድረግ ቀዳዳዎችን መድፈን እንደሚገባ ገልፀው፥ ችግሩን ለመቅረፍም ከኮሚሽኑ ጋር በትብብርና ቅንጅት እንሰራለን ብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው በትምህርት ዘርፍ የሚስተዋሉ ሙስና እና ብልሹ አሠራሮችን ለመከላከል በቴክኖሎጂ የተደገፈ ሥርዓት ማበጀት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
ሙስና እንደ ሀገር የልማት ግቦችን ለማሳካት ግንባር ቀደም ማነቆ በመሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መስራት ይገባል ብለዋል።
የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የሙስና መከላከል ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ክቡር አቶ እሸቴ አስፋው ዘርፍ ተኮር የሙስና መከላከል ጥናት ተቋማት ያሉባቸውን ክፍተቶች በማሳየት በየደረጃው ያለው አመራር ችግሩን በማወቅ ትኩረት አድርጎ እንዲሰራና ሙስና ከመፈፀሙ በፊት ለመከላከል ያግዛል ብለዋል።
ምክትል ኮሚሽነሩ አክለውም ሙስና እና ብልሹ አሰራርን መከላከል የሚቻለው መብቱን በገንዘብ የማይገዛ ማህበረሰብ ስንፈጥር ነው፥ ለዚህም የትምህርት ዘርፍ ትውልዱን በሥነምግባር ማነፅ ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።
በቀጣይም በትምህርት ዘርፍ የሀብት ማሳወቅና ማስመዝገብ እንደሚሰራ ጠቁመው፥ አመራሩም ለውጤታማነቱ በግንባር ቀደምትነት አርዓያ በመሆን የማስመዝገብ ሥራውን በኃላፊነት መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል።
የኮሚሽኑ የሙስና መከላከል ጥናት መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ገዛኸኝ ጋሻው በትምህርት ዘርፍ የሙስና ተጋላጭነት ጥናትና የአመራሩ ሚና በሚል ርዕስ የተዘጋጀውን የጥናት ሪፖርት አቅርበው ተሳታፊዎች ሀሳብና አስተያየት በማንሳት ውይይት ተደርጎበታል።
በውይይቱ ላይ የትምህርት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታዎችና አመራሮች እንዲሁም የተጠሪ ተቋማት አመራሮች፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዝዳንቶችና አመራሮች እንዲሁም የኮሚሽኑ የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 6/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በትምህርት ዘርፍ ባጠናው የሙስና ተጋላጭነት ሥጋት ጥናት ዙሪያ ከሚኒስቴር መስሪያቤቱ እና ተጠሪ ተቋማት አመራሮች ጋር ውይይት አካሄዷል።
በመድረኩ የተገኙት በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ኢትዮጵያ ለጀመረችውና መድረስ ለምታስበው የለውጥ ጉዞ እንቅፋት የሆነውን ሙስና በጋራ መታገል ያስፈልጋል።
በተለይ የትምህርት ዘርፉ ትውልዱን በመልካም ሥነምግባር የመቅረፅና ሙስናን የመከላከል ኃላፊነት አለበት ብለዋል።
ሚኒስትር ዴታዋ አክለውም ዘርፉ ትውልድን በሥነምግባር ከመገንባት አኳያ የአንበሳውን ድርሻ የሚወጣ ተቋም መሆኑን ጠቁመው፥ ለዚህም ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ የግብረገብነት ትምህርት እየተሰጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
አመራሩ በጥናቱ የተለዩ የብልሹ አሠራር አዝማሚያዎችን የእቅድ አካል በማድረግ ቀዳዳዎችን መድፈን እንደሚገባ ገልፀው፥ ችግሩን ለመቅረፍም ከኮሚሽኑ ጋር በትብብርና ቅንጅት እንሰራለን ብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው በትምህርት ዘርፍ የሚስተዋሉ ሙስና እና ብልሹ አሠራሮችን ለመከላከል በቴክኖሎጂ የተደገፈ ሥርዓት ማበጀት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
ሙስና እንደ ሀገር የልማት ግቦችን ለማሳካት ግንባር ቀደም ማነቆ በመሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መስራት ይገባል ብለዋል።
የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የሙስና መከላከል ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ክቡር አቶ እሸቴ አስፋው ዘርፍ ተኮር የሙስና መከላከል ጥናት ተቋማት ያሉባቸውን ክፍተቶች በማሳየት በየደረጃው ያለው አመራር ችግሩን በማወቅ ትኩረት አድርጎ እንዲሰራና ሙስና ከመፈፀሙ በፊት ለመከላከል ያግዛል ብለዋል።
ምክትል ኮሚሽነሩ አክለውም ሙስና እና ብልሹ አሰራርን መከላከል የሚቻለው መብቱን በገንዘብ የማይገዛ ማህበረሰብ ስንፈጥር ነው፥ ለዚህም የትምህርት ዘርፍ ትውልዱን በሥነምግባር ማነፅ ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።
በቀጣይም በትምህርት ዘርፍ የሀብት ማሳወቅና ማስመዝገብ እንደሚሰራ ጠቁመው፥ አመራሩም ለውጤታማነቱ በግንባር ቀደምትነት አርዓያ በመሆን የማስመዝገብ ሥራውን በኃላፊነት መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል።
የኮሚሽኑ የሙስና መከላከል ጥናት መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ገዛኸኝ ጋሻው በትምህርት ዘርፍ የሙስና ተጋላጭነት ጥናትና የአመራሩ ሚና በሚል ርዕስ የተዘጋጀውን የጥናት ሪፖርት አቅርበው ተሳታፊዎች ሀሳብና አስተያየት በማንሳት ውይይት ተደርጎበታል።
በውይይቱ ላይ የትምህርት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታዎችና አመራሮች እንዲሁም የተጠሪ ተቋማት አመራሮች፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዝዳንቶችና አመራሮች እንዲሁም የኮሚሽኑ የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319