Federal Ethics And Anti- Corruption Commission
9.9K subscribers
10.4K photos
244 videos
32 files
3.04K links
Download Telegram
ያለንን ውስን ሀብት በአግባቡና ከሙስና በጸዳ መልኩ መጠቀም ይገባል - አቶ ተስፋዬ ወርቁ

************************

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 5/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) "ሙስናን በመከላከል የዜግነት ግዴታዬን እወጣለሁ" በሚል መሪ ሀሳብ ለጤና ዘርፍ ሠራተኞች የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ስልጠና ለ3ኛ ዙር እየተሰጠ ይገኛል፡፡

በስልጠናው የተገኙት የጤና መድህን ዋና ዳሬክተር አቶ ተስፋዬ ወርቁ ያለንን ውስን ሀብት በአግባቡና ከሙስና በጸዳ መልኩ መጠቀም እንደሚገባ ተናግረዋል።

በጤና ሚኒስቴር የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሻምበል ነጋሲ በበኩላቸው ሙስና ብዙ ትርጉም ያለው እና መጠነ ሰፊ ጉዳት የሚያደርስ በመሆኑ በጋራ ልንታገለው ይገባል ብለዋል።

ስልጠናው በረዳት ፕሮፌሰር አብዱልሀኪም አባሜጫ እየተሰጠ ሲሆን፣ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

#NCRS ሞባይል መተግበሪያ

#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details

#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ለፋይናንስ ዘርፍ ሠራተኞች ሙስናን በመከላከል የዜግነት ግዴታዬን እወጣለሁ በሚል መሪ ሀሳብ ስልጠና እየተሰጠ ነው

************************

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 5/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) "ሙስናን በመከላከል የዜግነት ግዴታዬን እወጣለሁ" በሚል መሪ ሀሳብ ለፋይናንስ ዘርፍ ሠራተኞች የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል፡፡

በመክፈቻ ንግግር ስልጠናውን ያስጀመሩት የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሀና በርሄ ሁሉም ሠራተኛ ሙስናን በመከላከል የዜግነት ግዴታውን መወጣት እንዳለበት ተናግረዋል።

ስልጠናው በኮሚሽኑ የሥልጠና ጥራትና ተገቢነት ዴስክ ኃላፊ በአቶ የኋላሸት ደሳለኝ እየተሰጠ ሲሆን፣ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

#NCRS ሞባይል መተግበሪያ

#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details

#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
የትምህርት ዘርፉ አመራሮች በሥነምግባራችን አርዓያ መሆን ከቻልን ሀገር እናሻግራለን - ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ

************************

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 5/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ሥነምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት በሚል መሪ ሀሳብ ለትምህርት ዘርፍ አመራሮች የሥነምግባርና ሙስና መከላከል ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል፡፡

በስልጠናው የተገኙት በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ትምህርት የትውልድ ሥነምግባርን ለመቅረፅ ቁልፍ መሳሪያ ነው ብለዋል፡፡

ግብረ-ገብነትን በካሪኩለም በማካተት ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ በትምህርት እንዲሰጥ እየተደረገ መሆኑን ገልፀው፤ ይህም ሀገሩን የሚወድና በሥነምግባሩ የታነፀ ትውልድ ለማፍራት አይነተኛ መሳሪያ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በትምህርት ዘርፉ የጀመርናቸውን የቴክኖሎጂ ሥርዓቶች አጠናክረን በማስቀጠል ሀሰተኛ የትምህርት መረጃንና ኩረጃን ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች መኖራቸውን ጠቁመዋል፡፡

አመራሩ በዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ሙስና እና ብልሹ አሠራሮችን በጥናት በመለየት ቀዳዳዎችን መድፈን እንደሚገባ ገልፀው፤ ችግሩን የእቅዳችን አንድ አካል በማድረግ መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡

የትምህርት ዘርፉ አመራሮች በሥነምግባራችን አርዓያ መሆን ከቻልን ሀገር እናሻግራለን ያሉት ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ፣ በሥነምግባር አርዓያ በመሆንና ተቋማችንን አውቀን ከመራን ሙስና እና ብልሹ አሠራርን ለመቀነስ አያቅተንም ብለዋል፡፡

የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ክቡር አቶ ፍቃዱ ሰቦቃ በበኩላቸው ስልጠናው በትምህርት ዘርፍ ያለውን የሙስና ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያስችል መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ትምህርት ለአንድ አገር እድገት የመሠረት ድጋይ መሆኑን ገልፀው፤ ለዚህም የትምህርት ዘርፉ ትውልድን በማነፅና ዜጋን በመቅረፅ ረገድ ግንባር ቀደም ነው ብለዋል፡፡

ሙስና እና ብልሹ አሰራር የአስተሳሰብ መበላሸት እና የማህበራዊ እሴቶች መሸርሸር ውጤት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አመራሩ ከተማሪዎች ምግብ አቅርቦት፣ የትምህርት ቁሳቁስ ግዥ፣ ከቴክኖሎጂና የምርምር አቅርቦት እና ከፕሮጀክቶች እርክክብ እንዲሁም የሙያ ብቃት እድሳትና ስረዛ ጋር የሚስተዋሉትን ብልሹ አሠራሮች የመከላከል ኃላፊነት መወጣት አለበት ብለዋል፡፡

ከሀሰተኛ ትምህርት አሰጣጥና ኩረጃ እንዲሁም ለተማሪዎች ያለአግባብ ውጤት ከመስጠት አኳያ ችግሮችን በመለየት መፍታት እንደሚያስፈልግም አሳስበዋል፡፡

ስልጠናው በፕሮፌሰር አለማየሁ ተ/ማሪያም እና በዶ/ር አቢ ለማ እየተሰጠ ሲሆን፣ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

#NCRS ሞባይል መተግበሪያ

#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details

#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ሰነድን አስመስሎ ጊዜዉ ያለፈበትን የጸረ-ወባ ኬሚካል ሲሰበስቡ በነበሩ ተከሳሾች ላይ የጥፋተኝነትና የቅጣት ዉሳኔ ተላለፈ

******

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 5/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የፍትህ ቢሮ ዐቃቤ ህግ መንግስታዊ ሰነድን አስመስሎ ጊዜው ያለፈበትን የፀረ-ወባ ኬሚካል ሲሰበስቡ በነበሩ ተከሳሾች ላይ በመሰረተዉ የወንጀል ክስ የጥፋተኝነትና የቅጣት ዉሳኔ መሰጠቱን አስታውቋል።

ውሳኔ የተሰጠው ለክልሉ ፍትሕ ቢሮ እና ለክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን በደረሰዉ የወንጀል ጥቆማ መነሻ በተጠርጣሪዎች 1ኛ ምንአሉ አበበ፣ 2ኛ ሰይፉ ጋሊ እና 3ኛ ተመስገን መና በተባሉ ግለሰቦች ላይ የወንጀል ምርመራ በማጣራት የክልሉ ዐቃቤ ህግም የደረሰዉን የምርመራ መዝገብ በመቀበል ከላይ በተጠቀሱ ተካሳሾች ላይ በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመሰረተዉ ክስ መሆኑ ተገልጿል።

ክሱ የተመሠረተው ሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣዉን አዋጅ ቁጥር 881/2007 በመተላለፍ በሀሰተኛ ሰነድ መገልገል የሙስና ወንጀል እና የፀረ-ተባይ ምዝገባና ቁጥጥር አዋጅ ቁጥር 674/2002 በመተላለፍ በፈጸሙት ወንጀል ነው።

ተከሳሾች ጊዜዉ ያለፈበትን የፀረ-ወባ ኬሚካል እንዲሰበስቡ ከፌዴራል ጤና ሚኒስቴር የተጻፈ መንግስታዊ ሰነድ በማስመሰል ለክልሉ ጤና ቢሮ ይዞ በመቅረብ ቢሮዉንም ህጋዊ ሰነድ ይዘዉ የቀረቡ በማስመሰልና በማሳሳት የድጋፍ ደብዳቤ በክልሉ ለሚገኙ ስድስድቱም ዞኖች ጊዜዉ ያለፈበትን የፀረ-ወባ ኬሚካል እንዲሰበስቡ የሚል ደብዳቤ ካጻፉ በኃላ ከኮንታ ዞን 76 ኩንታል እና 33 ኬረጢት የፀረ-ወባ ኬሚካል ጭነዉ መዉሰዳቸው በክሱ ተዘርዝሯል።

በተጨማሪም ከሸካ ዞን ቴፒ ከተማ የፀረ-ወባ ኬሚካል ለመዉሰድ ኮድ አ.አ-3 -B- 57075 በሆነዉ አይሱዙ መኪና በመጫን ሂደት ላይ እያሉ ከፌዴራል ጤና ተቋማት ተጻፉ የተባሉ ደብዳቤዎች ሀሰተኛ በመሆናቸው የክልሉ ዐቃቤ ህግ ክስ መመስረቱ ተገልጿል።

ክሱ በሰዉና በሰነድ ማስረጃ በማስደገፍ በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት መቅረቡንና ፍርድ ቤቱም የግራ ቀኙን ክርክር ሰምቶ ተከሳሾች በዐቃቤ ህግ በኩል የቀረበባቸዉን የወንጀል ድርጊት ማስተባበል ባለመቻላቸዉ በቀን 04/07/2017 ዓ.ም በዋለዉ ችሎት የጥፋተኝነት ውሳኔ መሰጠቱን የክልሉ ፍትህ ቢሮ ገልጿል።

በዚሁ መሠረት በ1ኛ እና በ2ኛ ተከሳሾች ላይ 5 ዓመት ከ6 ወር ጽኑ እስራት እና በብር 10,000 እንዲቀጡ እንዲሁም 3ኛ ተከሳሽ በ 2 ዓመት ጽኑ እስራትና በብር 3,000 የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ በማስወሰንና ለወንጀል ድርጊት ማስፈጸሚ የተገለገሉበት ኮድ አአ-3 –B- 57075 የሆነዉ የአይሱዙ የጭነት መኪና ዉርስ እንዲሆን መወሰኑን የክልሉ ፍትህ ቢሮ አሳውቋል።

በመሆኑም መሠል ህገ ወጥ እንቅስቃሴዎች ሲመለከቱ ህብረተሰቡ በዜጐች ላይ የጤና ጉዳትና በሀገር ላይ ኪሳራ ከመድረሱ በፊት ህጎወጦችን ለህግ አካላት በመጠቆም ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ቢሮው ጥሪ ማስተላለፋን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

#NCRS ሞባይል መተግበሪያ

#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details

#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319