FastMereja.com
50.9K subscribers
5.92K photos
291 videos
5 files
1.42K links
Download Telegram
❀1👎1
ዚተሰራው ለቀጣዩ ሥኬት ማሳያ ምልክት ነው🙏

በጌጠኛው ቀት ዚሚካሔደውን ልማት እያገዝን ሚድኀት እግዚአብሔርን አጋዥ አድርገን ታላቅ ሥራ መሥራት ቜለናል፡፡ በማዕኹላዊ ጎንደር  ሀገሹ ስብኚት ምስራቅ በለሳ ወሚዳ ቀተ ክህነት ስር ዹሚገኘውን እና ታላቅ ዚበሚኚት ስፍራ ዹሆነው ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኀል አንድነት ገዳም ዹሚገኙ ገዳማውያንን ለማገዝና ቅዱሱን ስፍራ በልማት ራሱን ቜሎ ለሌሎቜ ዹሚተርፍ ለማድሚግ ስንሰራ ቆይተናል፡፡ 

ዹውሃ ጠብታ ቀስ በቀስ ድንጋይን እንደሚበሳው ሁሉ በስፍራው ያለውን ቜግር ለመፍታት በዚወቅቱ ያደሚጋቜሁት ልገሳ ለኑሮ እጅግ አስ቞ጋሪ በነበሹው ስፍራ ለውጥ ማምጣት ኹጀመሹ ሰነባበተ፡፡ ወደ ገዳሙ ዚሚወስደውና ለእንቅስቃሎ እጅግ አስ቞ጋሪ ዹነበሹው መንገድ ዹ8 ኪሎ ሜትር ዚጥርጊያ መንገድ ተሰርቶለት ለእንቅስቃሎ አመቺ በመደሚጉፀ ማንኛውም ሰው ገዳሙ ድሚስ በመሄድ መሣለም፣ ዚስፍራውን በሚኚት ማግኘትና ገዳማዊያኑን መጎብኘት ዚሚያስቜል ሁኔታ ተፈጥሯል፣ ወደ ገዳሙ ኚደሚሱ በኋላም ተራራ ተቊርቡሮ ዚተሰራውንና በአስ቞ጋሪ ስፍራ ዹነበሹውን እንቅስቃሎ ዹለወጠው ምቹ ዹ170 ሜትር ደሹጃ ዚተሰራለት ዚአርማታ ዚውስጥ ለውስጥ መንገድ ያገኛሉ፡፡ ይህ መንገድ ኚመሰራቱ በፊት ገዳማዊያኑ ለእንቅስቃሎ እጅግ ይ቞ገሩ ነበር።

ገዳማውያን እናቶቜ በቅዱሱ ስፍራ ለመንፈሳዊ ሕይወታ቞ው በሚመቜ መልኩ በዓት ወይም ቀት እና መጞዳጃ ቀቶቜ ተሟልተውለት ተሰርቶ ተጠናቋል፡፡ ኹኹተማ እጅግ ዚራቀው ስፍራ በሌሊት ለእንቅስቃሎ ምቹ ያልነበሚ በቀንም ኚሚሰሩ ዚልማት ስራዎቜ በኃይል እጥሚት ዹሚቾገር ዹነበሹ ሲሆን አሁን ዚሶላር መብራት ተሟልቶ ዚመብራት ተጠቃሚ ለማድሚግ ተቜሏል።

ገዳማዊያኑ በተደጋጋሚ ዚሚያጋጥማ቞ውን ዚምግብ አቅርቊት ቜግር እና ዹአቅም ውስንነት በዘላቂነት ለመቅሹፍ ኹሚደሹገው ጥሚት በተጚማሪም ዹተገኘውንም ቢሆን በገዳማዊው ስርዓት አዘጋጅቶ ለመመገብ ዚሚያስቜል ቀተ-እግዚአብሔር ወይም ማዕድ ቀት ተሰርተውፀ ዚሚያስፈልጉ ቁሳቁሶቜም ሙሉ በሙሉ ተሟልተውለታል።

በቅድስት ቀተ ክርስቲያናቜን ስርዓት መሠሚት ምንኩስና ዚጞሎትና በሥራ ዚመትጋት ሕይወት ነው፡፡ ገዳማውያኑ ዚእደ-ጥበባት ውጀቶቜን ዚሚያመርቱበት ሌድ ግንባታ በማኚናወን፣ ለስራው ዚሚያስፈልጉ መሳሪያዎቜ እና ዚጥሬ እቃ ግብዓቶቜ በማሟላት ዹሾማ ስራ ሙያ እንዲሰለጥኑ በማድሚግ ወደ ስራ ኚተገባ ውሎ አድሯል፡፡ ዚሻማ እና ዹጧፍ መስሪያ ማሜን ግዢም ተኚናውኗል።

ኚሚመለኚታ቞ው  አካላት ጋር በመነጋገር ዚገዳሙ ይዞታ ህጋዊ ዚይዞታ ማሚጋገጫ ሰነድ ያልነበሚው በመሆኑ ዚገዳሙ ህጋዊ ይዞታው እንዲሚጋገጥለት ዹተደሹገ ሲሆን በቆዹው ተፈጥሯዊ አካባቢን ዹመጠበቅና ዚማልማት ዚቀተ ክርስቲያን ልማድ በተደጋጋሚ በድርቅ ዹሚጠቃውን አካባቢው ዚተሻለ ለማድሚግ ዚአካባቢ ጥበቃ ስራዎቜ እዚተኚናወኑ ነው። ገዳማዊያኑ እዚሰሩ ቀጣይነት ያለው ገቢ እንዲያመነጩ ለማድሚግ ዚሞቀጣ ሞቀጊቜና ዚንዋያተ ቅዱሳት መሞጫ ሱቅ በገዳሙ አቅራቢያ ባለ ሀሙሲት ኹተማ አንዲሁም  በአዲስ አበባ መካኒሳ አቩ አካባቢ ተኚፍቶ ወደ ስራ ኚተገባ ሰነባብቷል።


እስካሁን ባደሚጋቜሁት ድጋፍ ይህን ያህል ድንቅ ሥራ መስራትና ገዳማውያኑ ለካ ሕዝበ ክርስቲያኑ ኚጎናቜን ነው እንዲሉ ያደሚገ ስኬት ማምጣት ተቜሏልና ዹሊቀ መላእክት ዚቅዱስ ሚካኀል በሚኚትና ሚድኀት አይለያቜሁ ይሏቜኋል፡፡

በዘመናት ውስጥ አባቶቻቜን ጀምሹው ያልጚሚሱት አንዳቜም ነገር ዚለም፡፡ እኛም መነሻቜን ይህ ዚአባቶቻቜን ትጋትና ቆራጥነት ነውና በሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኀል አንድነት ገዳም ዹጀመርነውን ልማት እስኚጥግ ማድሚስ ይገባናል፡፡ ዹማይዛነፍ አላማቜን ገዳሙን ራሱን ኚማስቻል አልፎ ለሌሎቜ ዹሚተርፍ ማድሚግ ነውና ድጋፋቜንን አጠናክሹን እንቀጥል፡፡ ዚደሚስንባ቞ው ሥኬቶቜ ቀጣዮቹን ሚድኀተ እግዚአብሔርን አጋዥ አድርገን ኚማሳካት ዚሚያግደን እደሌለ ማሳያ ና቞ው፡፡

በቀጣይ ዚተጀመሩ ሥራዎቜ ኚመቌውም ጊዜ በላይ ትልቅ ርብርብ ዹሚጠይቁ ና቞ው፡፡ ዚስዕለት ሰሚው ዚታላቁ አለቃ ዚቅዱስ ሚካኀል ህንጻ ቀተክርስቲያን እዚተሰራ ነው፡፡  ገዳማውያን አባቶቜ ኹዚህ ቀደም በነበሹው አስ቞ጋሪ ሁኔታ ኹመኖር ገና አልተላቀቁም፡፡ ይህን ቜግር ለመቅሹፍም ዚአባቶቜ በዓት በፍጥነት ሰርተን ለማጠናቀቅ ሌት ኹቀን እዚሰራን ነው፡፡

ቅድስት ቀተ ክርስቲያን በዘመናት ያጋጠሟትን ቜግሮቜ ያለፈቜው በዓለማዊውም በመንፈሳዊውም  ዕውቀት በመጠቁ ሊቃውንቶቜ ነው ፣ አሁንም በሁለት እንደተሳለ ሰይፍ ፍጹም በተሰማሩበት ሁሉ ስኬትን ዹሚጎናጾፉ አገልጋዮቜን ለማፍራት በገዳሙ አቅራቢያ በሚገኝ ሀሙሲት ኹተማ 30 ሺህ ካሬ ሜትር ቊታ ኚመንግስት በሊዝ በመውሰድ ዚአብነት ት/ቀትና አለማዊ ት/ቀት እዚገነቡ ነው፡፡

ቅድስት ቀተክርስቲያን ምዕመናን ዚሚጠቀሙበትን ልማት መስራት አንዱና ትልቁ መገለጫዋ ሲሆን ኚገዳሙ ማህበሚሰብ በተጚማሪ ለህብሚተሰቡ አግልግሎት ዚሚሰጥ ዚመጀመሪያ ደሹጃ ጀና ጣቢያ ግንባታም እዚተሳለጠ ነው፡፡ በአጠቃላይ ሚድኀተ እግዚአብሔርን አምነን፣ በትጋት ዚሚያሰራና ዚሚሰራ ባለበት ሁሉ እጃቜሁን ዚምትዘሚጉትን እናንተን ለጋሶቹን ምዕመናን ይዘን ዚሰራነው ሥራ ቀጣዮቹንም አብሚን ጥግ እንደምናደርሳ቞ው ማሳያ ነው፡፡

ላደሚጋቜሁትም ሁሉ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኀል በእጥፍ ይተካላቜሁ፡፡

ድጋፍ ለማድሚግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኀል አንድነት  ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

ለበለጠ መሹጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
❀14👎1
ለትንሳዔ በዓል ዹሚሆን ዹ650 ብር ስጋና ሰፊ ዚሞቀጥ አቅርቊት መዘጋጀቱ ተገለጾ

​#FastMereja I ዚአዲስ አበባ ኹተማ ንግድ ቢሮ ዚትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድሚግ በኹተማዋ ዚሞቀጊቜ እጥሚት እንዳይኚሰትና ገበያው እንዲሚጋጋ ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታወቀ። ቢሮው በተለይ ዚሥጋ ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅሚብ በአንድ ኪሎ 650 ብር እንዲሞጥ መወሰኑን ይፋ አድርጓል።

​ዚቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ ሀቢባ ሲራጅ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፣ ዚነዳጅ እጥሚት በምርት ስርጭት ላይ ተፅዕኖ እንዳያሳድር ካለፈው ወር ጀምሮ ኚክልሎቜ ጋር ዹተቀናጀ ዚምርት ማሰባሰብ ሥራ ተኚናውኗል። ለዚህም በኹተማዋ 6 ዋና ዋና ማዕኚላት፣ 246 ዚሰንበት ገበያዎቜ እና ኹ2 ሺህ በላይ ዚኅብሚት ሥራ ማህበራት ሱቆቜ በቂ ምርት እንዲያቀርቡ ተዘጋጅተዋል።

​በበዓሉ ወቅት ዹዋጋ ንሚትና ዚንግድ ማጭበርበርን ለመኹላኹል ቢሮው ቁጥጥር ዚሚያደርግ ግብሚ ኃይል ያሰማራ ሲሆንፀ ያለአግባብ ዋጋ በሚጚምሩና በሚዛን በሚያጭበሚብሩ ነጋዎዎቜ ላይ ጥብቅ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ አስጠንቅቋል።
❀8
በአለታ ወንዶ ዚንግድ ባንክ አገልግሎት መቆራሚጥ በንግዱ ማህበሚሰብ ላይ ኹፍተኛ እሮሮ ቀሰቀሰ

#FastMereja I በአለታ ወንዶ ኹተማ ዹሚገኘው ዚኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በዹቀኑ በሚያጋጥሙ ዚ”ሲስተም” እና ዚ”መብራት” መቆራሚጊቜ ሳቢያ ደንበኞቜ ለአላስፈላጊ እንግልትና ለኢኮኖሚ ኪሳራ እዚተዳሚጉ መሆኑ ተገለጞ።

በሲዳማ ክልል ዚንግድ እንቅስቃሎ ማዕኹልና ዚቡና ምርት መውጫ በሆነቜው አለታ ወንዶ፣ ዚኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አገልግሎት አሰጣጥ ኹኹተማዋ ዚንግድ ፍሰት ጋር አለመመጣጠኑ ተገልጋዮቜን እያስመሚሚ ይገኛል። ባንኩ “መብራት ዹለም” እና “ኔትወርክ ተቋርጧል” በሚሉ ምክንያቶቜ ስራ ዚሚያቆምባ቞ው ሰዓታት መብዛታ቞ው፣ በኹተማዋ ያለውን ዚገንዘብ ዝውውር ሜባ እያደሚገው መሆኑን ኚስፍራው ዹደሹሰን መሹጃ ያመለክታል።

ጉዳዩን አስመልክቶ ያነጋገርና቞ው ዚንግዱ ማህበሚሰብ አባላት እንደገለጹት፣ ባንኩ እንደ አማራጭ ሊጠቀማቾው ዚሚገቡ ዚጄነሬተርና ዚሳተላይት ኢንተርኔት አገልግሎቶቜ አለመኖራ቞ው ለቜግሩ መባባስ ዋነኛ ምክንያት ነው። ይህ መጉላላት በደንበኞቜና በባንኩ መካኚል ያለውን ዚ”አገልግሎት ደሹጃ ውል” ዚሚጥስ ኹመሆኑም ባለፈ፣ በብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሰሚት ዚፋይናንስ ተቋማት ሊያሟሏ቞ው ዚሚገቡ ዝቅተኛ ዚአገልግሎት መስፈርቶቜን ያላሟላ መሆኑን ይጠቅሳሉ።
❀7😢3👍1
ዚኢራን አብዮታዊ ዘበ ዚደህንነት ሃላፊ መገደል ተሹጋገጠ

​#FastMereja I ዚኢራን አብዮታዊ ዘበ (IRGC) ዚደህንነት ቢሮ ሃላፊ ሜጀር ጄኔራል ማጂድ ካዎሚ በዛሬው ዕለት በተሰነዘሹ ዹአዹር ጥቃት መገደላቾውን ዚሀገሪቱ መንግስታዊ መገናኛ ብዙኃን አሚጋገጡ።

​በ቎ህራን በተፈጾመው በዚህ ጥቃት ጄኔራል ማጂድ ካዎሚ መገደላቾውን ዚአብዮታዊ ዘበኛው ይፋዊ መግለጫ ጠቅሶ “ታስኒም” ዹዜና ወኪል ዘግቧል። እንደ ዘገባው ኹሆነ ጥቃቱ ዹተፈጾመው ዛሬ ሰኞ ጎህ ሲቀድ ሲሆን፣ ለግድያው “ዚአሜሪካ እና እስራኀል ጥምሚት” ተጠያቂ መሆኑን ዚሀገሪቱ ባለስልጣናት ገልጞዋል።

​ሜጀር ጄኔራል ካዎሚ በፈሚንጆቹ ሰኔ 2025 ነበር ዚቀድሞውን ዚደህንነት ሃላፊ ሞሃመድ ካዜሚን በመተካት ለዚህ ኹፍተኛ ኃላፊነት ዚተሟሙት። ካዜሚም በተመሳሳይ መልኩ ባለፈው ዓመት በእስራኀል ዹአዹር ጥቃት መገደላቾው ይታወሳል።

​ጄኔራል ካዎሚ ኚአብዮታዊ ዘበኛው ዚደህንነት መዋቅር በተጚማሪ፣ በሀገሪቱ ዚመኚላኚያ ሚኒስ቎ር ውስጥ ዹመሹጃ ጥበቃ ድርጅትን በመምራት ለሹጅም ዓመታት ኹፍተኛ ወታደራዊ እና ዚደህንነት ልምድ ያካበቱ አንጋፋ መኮንን ነበሩ። ጥቃቱን ተኚትሎ እስካሁን ኚአሜሪካም ሆነ ኚእስራኀል ወገን ዹተሰጠ ይፋዊ ምላሜ ዚለም።
​ይህ ግድያ በክልሉ እዚተባባሰ ዚመጣውን ውጥሚት ወደ አዲስ ምዕራፍ ሊያሞጋግሚው እንደሚቜል ዚፖለቲካ ተንታኞቜ ስጋታ቞ውን እዚገለጹ ይገኛሉ።
❀2👏2
❀15
በበለስ አንጻር ኃጢአትን ሚገማት🙏

በትንቢተ ኢሳይያስ 53÷4-12 “ደዌያቜንን ተቀበለፀ ሕማማቜንንም ተሞኚመ፡፡ ኚዓመፀኞቜም ጋር ተቈጠሚ፡፡ እርሱ ግን ግፍን አላደሚገምፀ ተንኮልም በአፉ አልተገኘበትም፡፡” ተብሎ እንደ ተጻፈ፡፡ ሰሙነ ሕማማት፣ ሕማምና ሞት ዚማይገባው ጌታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ዚእኛን ሕማምና ሞት ለራሱ በማድሚግ ለእኛ ቀዛ መሆኑ ዚሚነገርበት ነው፡፡ ምእመናን ክርስቶስ ዹተቀበለው ዚእኛን ሕማም መኟኑን በመዘኚርፀ ኹማንኛውም ዚሥጋ ሥራ በመታቀብ ዋዛ ፈዛዛ ባለመነጋገር ሰሙነ ሕማማትን ልናኚብር ይገባል፡፡ ዹሰሙነ ሕማማት ሰኞ ዚበለስ ቀን ይባላል፡፡ ጌታቜን መድኀኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ በሆሣዕና ማግሥት ኚቢታንያ ወደ ኢዚሩሳሌም ሲገባ ሁለት ነገሮቜን አኚናውኗልፀ አንደኛ ኹቅጠል በስተቀር ፍሬ ያልተገኘባትን ዕፀ በለስ ሚግሟል፡፡ ሁለተኛ ወደ ቀተ መቅደስ ገብቶ ዚሚሞጡትንና ዚሚለውጡትን አስወጥቷል፡፡

ቅዱስ ማ቎ዎስ በወንጌሉ “በማግሥቱ ተራበ” ይላል፡፡ ነገር ግን በኢሳ. 46÷25 “እግዚአብሔር ለዘለዓለም አይራብምፀ አይጠማምፀ አይደክምም” ተብሎ ተጜፏል፡፡ ጌታቜንም በመዋዕለ ስጋዌው ሲያስተምር “ዚእኔስ መብል ዹላኹኝን ዚአባ቎ን ፈቃድ አደርግ ዘንድፀ ሥራውንም እንፈጜም ዘንድ ነውፀ” ሲል ተናግሯል፡፡ ታዲያ ጌታቜን ለምን ተራበ? ሰማያውያን መላእክት እንዳይራቡ አድርጎ ዚፈጠሚፀ እስራኀልን ገበሬ በማያርስበት፣ ዘር በሌለበት፣ ዝናብ በማይጥልበት ምድሚ በዳ ዚመገበፀ በአምስት አንጀራና በሁለት ዓሣ ኚአምስት ሺሕ ዚሚበልጡ ሰዎቜን ዹመገበ ጌታ “ተራበ” ተብሎ ሲነገር እጅግ ይደንቃል፡፡ በእርግጥ ኢዚሱስ ክርስቶስ ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው በመሆኑ አልተራበም አንልም፡፡ ዚጌታቜን ሚኃብ ዚድህነት፣ ዚማጣት አይደለም፡፡ ዚክርስቶስ ሚኃቡ ዚበለስ ፍሬ ሳይሆን ዚሃይማኖትና ዚመልካም ሥነ ምግባርን ፍሬ ሜቶ ማጣቱን ለማጠዹቅ ዹተነገሹ ነው።

በለስስ ቀተ እስራኀል ናቾው እንዲል፡፡ ጌታቜን ዹፈለገውን ጜድቅ ኚእነርሱ ባለማግኘቱ ጉባኀ አይሁድን ሚግሟል፡፡ ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ “በበለስ አንጻር ኃጢአትን ሚገማት” ብሏል፡፡ እስራኀልም በአንድ ወገን ዚተጠበቀባ቞ውን ፍሬ ባለማፍራታ቞ው ተሚግመዋል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ “አሕዛብ በእግዚአብሔር ቞ርነት አበባ ሰበሰቡፀ በአይሁድ ዘንድ ግን እሟኹ ተሚፈ፡፡ ይኾውም ዚሃይማኖት ጉድለት ነውፀ” በማለት እስራኀል ኹፍቅር ይልቅ እርግማን እንዳገኛ቞ውፀ አሕዛብ ደግሞ ዹቃሉን ትምህርት ሰምተው ዚእጁን ተአምራት አይተው ያመኑበትን ዚእግዚአብሔር ዹጾጋ ልጁ ለመኟን መብቃታ቞ውን ይመሰክራል፡፡ እሟኜ ዚእርግማንፀ አበባ ዚእግዚአብሔር ጾጋ ልጅነት ምሳሌ ነው፡፡  ዛሬ ጌታቜን ወደ መቅደስ ሕይወታቜን ቢመጣ ምን ያገኝ ይሆን? ፍሬ ወይስ ቅጠል? በቅዱሳን ጞሎት በገዳማት በሚኚት እንታጠር፡፡ ገዳማውያንን እንደግፍ በዓታ቞ውን እናጜና።

ድጋፍ ለማድሚግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኀል አንድነት  ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

ለበለጠ መሹጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
❀12
ዓለም አቀፍ ዚሰዎቜ አዘዋዋሪ ይትባሚክ ዳዊት (ክብሮም) በቁጥጥር ስር ዋለ

​#FastMereja I ዚኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኹ3 ሺህ በላይ ዜጎቜን በሕገ-ወጥ መንገድ ያዘዋወሚውና በዓለም አቀፍ ደሹጃ ሲፈለግ ዹነበሹው አደገኛ ወንጀለኛ ይትባሚክ ዳዊት (ክብሮም) ኹ9 ግብሚ-አበሮቹ ጋር መያዙን አስታወቀ። ተጠርጣሪው በትግራይ ክልል ሜሬ ኹተማ ውስጥ በድብቅ ሲንቀሳቀስ በቁጥጥር ስር ዚዋለው፣ ፖሊስ ኹዓለም አቀፉ ዹ”ROCK” ተቋም ጋር ባደሚገው ዚጋራ ክትትልና ዹመሹጃ ልውውጥ ነው።

​ተጠርጣሪው ይትባሚክ ዳዊት በተለያዩ አገራት አድሀኖም፣ አህመድ፣ ሙኒር እና ክብሮም ዹሚሉ ስድስት ዚሀሰት ስሞቜንና ፓስፖርቶቜን በመጠቀም ለዓመታት ሲያመልጥ ቆይቷል። በምርመራው እንደተሚጋገጠው፣ ግለሰቡና ቡድኑ ኹ2010 ዓ.ም ጀምሮ ኚኢትዮጵያ፣ ኀርትራ፣ ሱዳንና ሶማሊያ ወጣቶቜን በመመልመል ሊቢያ ውስጥ በሚገኙ አምስት መጋዘኖቜ አግተው ኢ-ሰብአዊ ስቃይ ሲያደርሱባ቞ው ነበር።

​በዚህ ዹወንጀል ድርጊት ሳቢያፊ

​ኹ100 በላይ ሰዎቜ ለሞት ተዳርገዋል።

​ኹ50 በላይ ሎቶቜ ተደፍሚዋል።

​ኹ3 ቢሊዮን ብር በላይ በሕገ-ወጥ መንገድ ተንቀሳቅሷል።

​ፌደራል ፖሊስ ዘመናዊ ቮክኖሎጂን በመጠቀም በ9 አገራት ዹሚገኙ 16 ተጎጂዎቜን ጚምሮ ዹ100 ሰዎቜን ምስክርነት ተቀብሏል። ተጠርጣሪዎቹ በወንጀል ያፈሩት ሀብትና ዚባንክ ሂሳብ እንዲታገድ ዹተደሹገ ሲሆን፣ ዚፖሊስ ምርመራ ተጠናቆ መዝገቡ ለዓቃቀ ሕግ መላኩ ተሚጋግጧል።

​መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም
❀12
❀21👍1
ሰሙነ ሕማማት ማክሰኞ - ዚጥያቄና ዚትምህርት ቀን 🙏

ጌታቜን አምላካቜን መድኀኒታቜን ኢዚሱሱ ክርስቶስ በዕለተ ሰኞ ባደሚገው አንጜሖተ ቀተመቅደስ ምክንያት፣ ሥልጣንን ለሰው ልጅ ዹሰጠው ጌታቜን፣ ስለ ሥልጣኑ በጞሐፍት ፈሪሳውያን ተጠይቋልና ዕለተ ማክሰኞ ዚጥያቄ ቀን ይባላል፡፡ ጠያቂዎቹ ዚካህናት አለቆቜና ዚሕዝብ አለቆቜ ና቞ው፡፡ አንድም በዚህ ዕለት ጌታቜን በቀተ መቅደስ ሹጅም ትምህርት ስላስተማሚ ዕለቱ “ዚትምህርት ቀን” ይባላል፡፡ ክርስቲያን ዹሆነ ሁሉ ኚሥጋዊ ነገር ርቆ በዚህ ሰሞን ዚሃይማኖት ትምህርት ሲማር፣ ሲጠይቅ መሰንበት እንደሚገባው ይህ መጜሐፋዊ ሥርዓት ይነግሚናል፡፡ በዕለተ ሰኞ ዚነጋዎዎቜን ንብሚት መገልበጥና ማባሚሩን መነሻ በማድሚግ “በማን ሥልጣን እነዚህን ታደርጋለህ?” ሲሉ ጠይቀውታል፡፡ ጌታቜን ሲያደርጋ቞ው ዚነበሩት ተአምራት፣ ድንቅ ድንቅ ሥራዎቜና ትምህርቱ ህዝቡ እንዲኚተለው ስላደሚገ ዚካህናት አለቆቜ በቅናት ኚሮማ መንግሥት ባለ ሥልጣናት ጋር ሊያጋጩት ዚቀዚሱት ስልት ነው፡፡

ነጋዮን ማባሚርና መደብን ማስለቀቅ መንግሥታዊ ሥራ ነውና ጌታቜን በራሎ ሥልጣን ነው ቢላ቞ው ጾሹ መንግሥት ነው በማለት ለሮማ መንግሥት ያሳጡት ነበር፡፡ ጌታቜን ግን ለጥያቄያ቞ው ቀጥተኛ ምላሜ ኚመስጠት ይልቅ “ዚዮሐንስ ጥምቀት ኚዚት ነው? ኹሰማይ ነው ወይስ ኚምድር?” በማለት በጥያቄ መልሶላ቞ዋል፡፡ እነርሱም “ኹሰማይ ነው” ቢሉት “ለምን አላመናቜሁበትም?” እንዳይላ቞ው ሰጉ፡፡ “ኹሰው ነው” ቢሉት ደግሞ ሕዝቡ ዮሐንስን እንደ መምህር ይፈሩት፣ እንደ አባት ያኚብሩት ነበርና እንዳይጣሏ቞ው ፈሩፀ እናም “ኚወዎት እንደሆነ አናውቅም” ዹሚል ዚተንኮል ምላሜ ሰጡት፡፡ እርሱም “እኔም በማን ሥልጣን እነዚህን እንደማደርግ አልነግራቜሁም” አላ቞ው፡፡ በልቡና቞ው ዚሚያደርጋ቞ውን ተግባራት ሁሉ በራሱ ሥልጣን እንደሚያደርግ ቢያውቁም በክፋትና በጥርጥሬ ስለተሞሉ ነበር ዚጠዚቁት፡፡

በማ቎ዎስ ወንጌል 21÷28፣ 25÷46፣ በማርቆስ ወንጌል 12÷12፣ 13÷37ፀ በሉቃስ ወንጌል 20÷9፣ 21÷38፣ ዹሚገኙ ዚመጜሐፍ ቅዱስ ክፍሎቜ ስለማክሰኞ ዕለት ዚሚነገሩ ትምህርቶቜን ይዘዋል፡፡ ዳግመኛም በዚህ ዕለት በቀተ መቅደስ ሹጅም ትምህርት ስላስተማሚ ዚትምህርት ቀን ይባላል፡፡ ይኾውም ኚሃይማኖት ዚራቁትን፣ ኹፍቅሹ እግዚአብሔር ዚተለዩትን አስተምሮ ማቅሚብ፣ መክሮ መመለስ እንደሚገባን ሲገልጜልን ነው፡፡ ክርስቲያን ዹሆነ ሁሉ ኚሥጋዊ ነገር ርቆ፣ ኹዋዛ ፈዛዛ ተጠብቆ ዚጌታቜንን ውለታ፣ ሕማሙን፣ ግሚፋትና ስቅለቱን፣ ሞቱንና መኚራውን እያሰበ በስግደት ይህን ሳምንት ሊያሳልፈው ይገባል፡፡ ገዳማውያን ይህን ፍቅሩን እያሰቡ በጟምና በጞሎት ይኖራሉፀ ገዳማ቞ውን እንደግፍ በዓታ቞ውን እናጜና፡፡
  
ድጋፍ ለማድሚግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኀል አንድነት  ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

ለበለጠ መሹጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
❀27👍1
ዚተሰራው ለቀጣዩ ሥኬት ማሳያ ምልክት ነው🙏

በጌጠኛው ቀት ዚሚካሔደውን ልማት እያገዝን ሚድኀት እግዚአብሔርን አጋዥ አድርገን ታላቅ ሥራ መሥራት ቜለናል፡፡ በማዕኹላዊ ጎንደር  ሀገሹ ስብኚት ምስራቅ በለሳ ወሚዳ ቀተ ክህነት ስር ዹሚገኘውን እና ታላቅ ዚበሚኚት ስፍራ ዹሆነው ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኀል አንድነት ገዳም ዹሚገኙ ገዳማውያንን ለማገዝና ቅዱሱን ስፍራ በልማት ራሱን ቜሎ ለሌሎቜ ዹሚተርፍ ለማድሚግ ስንሰራ ቆይተናል፡፡ 

ዹውሃ ጠብታ ቀስ በቀስ ድንጋይን እንደሚበሳው ሁሉ በስፍራው ያለውን ቜግር ለመፍታት በዚወቅቱ ያደሚጋቜሁት ልገሳ ለኑሮ እጅግ አስ቞ጋሪ በነበሹው ስፍራ ለውጥ ማምጣት ኹጀመሹ ሰነባበተ፡፡ ወደ ገዳሙ ዚሚወስደውና ለእንቅስቃሎ እጅግ አስ቞ጋሪ ዹነበሹው መንገድ ዹ8 ኪሎ ሜትር ዚጥርጊያ መንገድ ተሰርቶለት ለእንቅስቃሎ አመቺ በመደሚጉፀ ማንኛውም ሰው ገዳሙ ድሚስ በመሄድ መሣለም፣ ዚስፍራውን በሚኚት ማግኘትና ገዳማዊያኑን መጎብኘት ዚሚያስቜል ሁኔታ ተፈጥሯል፣ ወደ ገዳሙ ኚደሚሱ በኋላም ተራራ ተቊርቡሮ ዚተሰራውንና በአስ቞ጋሪ ስፍራ ዹነበሹውን እንቅስቃሎ ዹለወጠው ምቹ ዹ170 ሜትር ደሹጃ ዚተሰራለት ዚአርማታ ዚውስጥ ለውስጥ መንገድ ያገኛሉ፡፡ ይህ መንገድ ኚመሰራቱ በፊት ገዳማዊያኑ ለእንቅስቃሎ እጅግ ይ቞ገሩ ነበር።

ገዳማውያን እናቶቜ በቅዱሱ ስፍራ ለመንፈሳዊ ሕይወታ቞ው በሚመቜ መልኩ በዓት ወይም ቀት እና መጞዳጃ ቀቶቜ ተሟልተውለት ተሰርቶ ተጠናቋል፡፡ ኹኹተማ እጅግ ዚራቀው ስፍራ በሌሊት ለእንቅስቃሎ ምቹ ያልነበሚ በቀንም ኚሚሰሩ ዚልማት ስራዎቜ በኃይል እጥሚት ዹሚቾገር ዹነበሹ ሲሆን አሁን ዚሶላር መብራት ተሟልቶ ዚመብራት ተጠቃሚ ለማድሚግ ተቜሏል።

ገዳማዊያኑ በተደጋጋሚ ዚሚያጋጥማ቞ውን ዚምግብ አቅርቊት ቜግር እና ዹአቅም ውስንነት በዘላቂነት ለመቅሹፍ ኹሚደሹገው ጥሚት በተጚማሪም ዹተገኘውንም ቢሆን በገዳማዊው ስርዓት አዘጋጅቶ ለመመገብ ዚሚያስቜል ቀተ-እግዚአብሔር ወይም ማዕድ ቀት ተሰርተውፀ ዚሚያስፈልጉ ቁሳቁሶቜም ሙሉ በሙሉ ተሟልተውለታል።

በቅድስት ቀተ ክርስቲያናቜን ስርዓት መሠሚት ምንኩስና ዚጞሎትና በሥራ ዚመትጋት ሕይወት ነው፡፡ ገዳማውያኑ ዚእደ-ጥበባት ውጀቶቜን ዚሚያመርቱበት ሌድ ግንባታ በማኚናወን፣ ለስራው ዚሚያስፈልጉ መሳሪያዎቜ እና ዚጥሬ እቃ ግብዓቶቜ በማሟላት ዹሾማ ስራ ሙያ እንዲሰለጥኑ በማድሚግ ወደ ስራ ኚተገባ ውሎ አድሯል፡፡ ዚሻማ እና ዹጧፍ መስሪያ ማሜን ግዢም ተኚናውኗል።

ኚሚመለኚታ቞ው  አካላት ጋር በመነጋገር ዚገዳሙ ይዞታ ህጋዊ ዚይዞታ ማሚጋገጫ ሰነድ ያልነበሚው በመሆኑ ዚገዳሙ ህጋዊ ይዞታው እንዲሚጋገጥለት ዹተደሹገ ሲሆን በቆዹው ተፈጥሯዊ አካባቢን ዹመጠበቅና ዚማልማት ዚቀተ ክርስቲያን ልማድ በተደጋጋሚ በድርቅ ዹሚጠቃውን አካባቢው ዚተሻለ ለማድሚግ ዚአካባቢ ጥበቃ ስራዎቜ እዚተኚናወኑ ነው። ገዳማዊያኑ እዚሰሩ ቀጣይነት ያለው ገቢ እንዲያመነጩ ለማድሚግ ዚሞቀጣ ሞቀጊቜና ዚንዋያተ ቅዱሳት መሞጫ ሱቅ በገዳሙ አቅራቢያ ባለ ሀሙሲት ኹተማ አንዲሁም  በአዲስ አበባ መካኒሳ አቩ አካባቢ ተኚፍቶ ወደ ስራ ኚተገባ ሰነባብቷል።


እስካሁን ባደሚጋቜሁት ድጋፍ ይህን ያህል ድንቅ ሥራ መስራትና ገዳማውያኑ ለካ ሕዝበ ክርስቲያኑ ኚጎናቜን ነው እንዲሉ ያደሚገ ስኬት ማምጣት ተቜሏልና ዹሊቀ መላእክት ዚቅዱስ ሚካኀል በሚኚትና ሚድኀት አይለያቜሁ ይሏቜኋል፡፡

በዘመናት ውስጥ አባቶቻቜን ጀምሹው ያልጚሚሱት አንዳቜም ነገር ዚለም፡፡ እኛም መነሻቜን ይህ ዚአባቶቻቜን ትጋትና ቆራጥነት ነውና በሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኀል አንድነት ገዳም ዹጀመርነውን ልማት እስኚጥግ ማድሚስ ይገባናል፡፡ ዹማይዛነፍ አላማቜን ገዳሙን ራሱን ኚማስቻል አልፎ ለሌሎቜ ዹሚተርፍ ማድሚግ ነውና ድጋፋቜንን አጠናክሹን እንቀጥል፡፡ ዚደሚስንባ቞ው ሥኬቶቜ ቀጣዮቹን ሚድኀተ እግዚአብሔርን አጋዥ አድርገን ኚማሳካት ዚሚያግደን እደሌለ ማሳያ ና቞ው፡፡

በቀጣይ ዚተጀመሩ ሥራዎቜ ኚመቌውም ጊዜ በላይ ትልቅ ርብርብ ዹሚጠይቁ ና቞ው፡፡ ዚስዕለት ሰሚው ዚታላቁ አለቃ ዚቅዱስ ሚካኀል ህንጻ ቀተክርስቲያን እዚተሰራ ነው፡፡  ገዳማውያን አባቶቜ ኹዚህ ቀደም በነበሹው አስ቞ጋሪ ሁኔታ ኹመኖር ገና አልተላቀቁም፡፡ ይህን ቜግር ለመቅሹፍም ዚአባቶቜ በዓት በፍጥነት ሰርተን ለማጠናቀቅ ሌት ኹቀን እዚሰራን ነው፡፡

ቅድስት ቀተ ክርስቲያን በዘመናት ያጋጠሟትን ቜግሮቜ ያለፈቜው በዓለማዊውም በመንፈሳዊውም  ዕውቀት በመጠቁ ሊቃውንቶቜ ነው ፣ አሁንም በሁለት እንደተሳለ ሰይፍ ፍጹም በተሰማሩበት ሁሉ ስኬትን ዹሚጎናጾፉ አገልጋዮቜን ለማፍራት በገዳሙ አቅራቢያ በሚገኝ ሀሙሲት ኹተማ 30 ሺህ ካሬ ሜትር ቊታ ኚመንግስት በሊዝ በመውሰድ ዚአብነት ት/ቀትና አለማዊ ት/ቀት እዚገነቡ ነው፡፡

ቅድስት ቀተክርስቲያን ምዕመናን ዚሚጠቀሙበትን ልማት መስራት አንዱና ትልቁ መገለጫዋ ሲሆን ኚገዳሙ ማህበሚሰብ በተጚማሪ ለህብሚተሰቡ አግልግሎት ዚሚሰጥ ዚመጀመሪያ ደሹጃ ጀና ጣቢያ ግንባታም እዚተሳለጠ ነው፡፡ በአጠቃላይ ሚድኀተ እግዚአብሔርን አምነን፣ በትጋት ዚሚያሰራና ዚሚሰራ ባለበት ሁሉ እጃቜሁን ዚምትዘሚጉትን እናንተን ለጋሶቹን ምዕመናን ይዘን ዚሰራነው ሥራ ቀጣዮቹንም አብሚን ጥግ እንደምናደርሳ቞ው ማሳያ ነው፡፡

ላደሚጋቜሁትም ሁሉ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኀል በእጥፍ ይተካላቜሁ፡፡

ድጋፍ ለማድሚግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኀል አንድነት  ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

ለበለጠ መሹጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
❀17👍1👏1
አዲስ አበባን ዚአህጉሪቱ ዚሥነ-ፈጠራ ማዕኹል ዚሚያደርገው ታላቁ ፌስቲቫል ይፋ ሆነ!

#Fastmereja:”ዚሥነ-ፈጠራ ጥበባት ለለውጥ” በሚል መሪ ታላቁ ዚክራፍት አዲስ(CRAFT Addis 2026) ፌስቲቫል ኚሚያዝያ 22 እስኚ 24 ቀን 2018 ዓ.ም.ለሶስት ተኚታታይ ቀናት በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚዹም እንደሚካሄድ በዛሬዉ እለት በተሰጠ መግለጫ ተገለፀ።

በዘሌማን (Zeleman) ኮሚኒኬሜን አዘጋጅነት ኚአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሜን እና ፍሎዉለስ ኀቚንትስ ጋር በመተባበር ዹሚቀርበው ይህ መድሚክፀ ዚአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሜንን፣ ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድን እና ንጉሥ ማልትን በአጋርነት ያሳተፈ ሲሆን፣ ዓላማውም ዚአፍሪካን ዚሥነ-ፈጠራ ኢንዱስትሪ ወደ ተጚባጭ ዚኢኮኖሚ አቅም መቀዹር እንደሆነ ተገልጿል።

ዘሌማን በአፍሪካ ዚሥነ-ፈጠራ ዘርፍ ያለውን ዹ20 ዓመታት ልምድ በመጠቀም ያዘጋጀው ይህ ፌስቲቫል፣ ኹመደበኛ ትርኢቶቜ ባለፈ ዚገበያ ተደራሜነት እና ዚቢዝነስ ትስስር ላይ ትኩሚት እንደሚያሚግ ነዉ ዚተገለፀዉ።

ዹዘሌማን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዘላለም ወልደማርያም እንደገለጹት፣ “ዚክራፍት ዋነኛ ግብ ዚአፍሪካን ዚፈጠራ ምናብ ኚተሰጥኊ ወደ ተቋም፣ ኚሥነ-ፈጠራ ደግሞ ወደ ዘላቂ ብልጜግና ዚሚያሞጋግሩ ዚለውጥ መንገዶቜን መገንባት ነው” ብለዋል።

ፌስቲቫሉ ኹ10,000 በላይ ተሳታፊዎቜን በአካል፣ ኹ3 እስኚ 5 ሚሊዮን ዹሚሆኑ ሰዎቜን ደግሞ በዲጂታል አማራጮቜ ተደራሜ ያደርጋል ተብሎ ዹሚጠበቅ ሲሆን ይህም አዲስ አበባን በአህጉሪቱ እያደገ ዚመጣው ዚሥነ-ፈጠራ ማዕኹል ዚማድሚግ ራዕይን እንደሚያሳካ ነዉ ዚተገለፀዉ።

ዚዘንድሮው ፌስቲቫል ልዩ ትኩሚት ዹሚሰጠው ዚኢትዮ-ጃዝ አባት በሆኑት በክቡር ዶክተር ሙላቱ አስታጥቄ ለሚቀርበው ‘ዚክብርኮንሰርት’ (Legacy Concert) ሲሆን ዶክተር ሙላቱ 10 አባላት ያሉትና በዓለም አቀፍ ደሹጃ ዝነኛ ዹሆነውን ዹ’Steps Ahead’ ባንዳ቞ውን ኹለንደን በማምጣት ታሪካዊ ዹሙዚቃ ድግስ ዚሚያቀርቡ መሆኑም በመግለጫዉ ተገልጿል።

ለሊስት ተኚታታይ ቀናት በሚቆዹው በዚህ መርሃ-ግብር ላይ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (Al)፣ በኢንቚስትመንት እና በሥነ-ፈጠራ ኢኮኖሚ ዙሪያ ዹፓናል ውይይቶቜ፣
በፋሜን፣ በፊልም፣ በዲጂታል ጥበባት (AR/VR) እና በቪዲዮ ጚዋታዎቜ (Gaming) ላይ ያተኮሩ ማስተር ክላሶቜ ዚሚቀርቡበት እንዲሁም ፈጣሪዎቜን በቀጥታ ኚገዢዎቜ ጋር ዚሚያገናኝ “ዚክራፍት ገበያ” ኀግዚቢሜን እንደሚካሄድ ተገልጿል።

ፌስቲቫሉ ሲጠናቀቅ በአፍሪካ ዚፈጠራ ባለሙያዎቜ እና በዓለም አቀፍ ኩባንያዎቜ መካኚል ኹ100 በላይ ዚንግድ ስምምነቶቜ እንዲፈሚሙ ምቹ ሁኔታ ዚሚፈጥር ሲሆን በተጚማሪም ባለሙያዎቜ ሥራ቞ውን በዓለም አቀፍ ደሹጃ እንዲያቀርቡ ዚሚያስቜል ዚዲጂታል ዚሥራ ዕድል መድሚክ(Digital Freelance Platform) ይፋ እንደሚደሚግ ይጠበቃል።

ዝግጅቱ በመጚሚሻው ቀን ዚአዲስ አበባን ዚቱሪስት መዳሚሻዎቜ እና ዚፈጠራ ማዕኚላትን በሚያስጎበኝ ልዩ ዹኹተማ ጉብኝት ፍጻሜውን እንደሚያገኝ ተነግሯል።
❀3😢1
አዋሜ ባንክ ለፋሲካ በዓል ኹ5 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወገኖቜ ድጋፍ አደሹገ

#FastMereja I አዋሜ ባንክ ዹ2018 ዓ.ም ዚፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድሚግ “ክብራቜን ወገናቜን – ደስታቜን ማካፈላቜን” በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባና በተለያዩ ዚሀገሪቱ ኚተሞቜ ለሚገኙ ኹ5 ሺህ በላይ አሚጋውያንና አቅመ ደካማ ወገኖቜ ዚዓይነትና ዚገንዘብ ድጋፍ አደሚገ።

ባንኩ ዛሬ በአዲስ አበባ ቩሌ መድኃኒዓለም ካ቎ድራል ዚማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር አካሂዷል፣ በሀገር አቀፍ ደሹጃ ለተመሚጡ ለእነዚሁ ወገኖቜ ለእያንዳንዳ቞ው 5 ሊትር ዘይት፣ 25 ኪሎ ዱቄት እና ዚጥሬ ገንዘብ ድጋፍ እዚተደሚገ ይገኛል።

ባንኩ ለማኅበራዊ ኃላፊነት ስራዎቜ ኹፍተኛ ትኩሚት እንደሚሰጥ ዹገለጾ ሲሆን፣ ባለፈው ዹ2024/25 ዚሒሳብ ዓመት ብቻ ለማኅበራዊ ኃላፊነት ተግባራት ኹ600 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት መድቊ ዚተለያዩ ስራዎቜን ማኹናወኑን ገልጿል። ይህም በትምህርት፣ በጀና፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ እና ዹአቅመ ደካሞቜን ቀት በመገንባት ሚገድ ኹፍተኛ አስተዋጜኊ ማድሚጉ ተጠቅሷል።

ባንኩ ካለፉት 31 ዓመታት ጀምሮ እንዲህ ያሉ ሰው-ተኮር ተግባራትን ሲያኚናውን መቆዚቱን አስታውሶ፣ ወደፊትም በተፈጥሮና በሰው ሰራሜ አደጋ ለተጎዱ ዚማኅበሚሰብ ክፍሎቜ ዚሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሚጋግጧል።
በተጚማሪም አዋሜ ባንክ በአሁኑ ወቅት በሀገር አቀፍ ደሹጃ ኹ1005 በላይ ቅርንጫፎቜ ያሉት ሲሆን፣ ኹ16 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ደንበኞቹ ዘመናዊ ዚባንክ አገልግሎት እዚሰጠ ይገኛል።
🙏6❀2
ሃሪ ማጓዹር በማንቜስተር ዩናይትድ ቀት ለመቆዚት አዲስ ውል ፈሹመ

​#FastMereja I ዚማንቜስተር ዩናይትድ ተኚላካዩ ሃሪ ማጓዹር በኊልድ ትራፎርድ ዚሚያቆይበትን አዲስ ዹውል ስምምነት በይፋ መፈሹሙ ተሚጋግጧል። ተጫዋቹ ኚክለቡ ጋር ያለውን ቆይታ ለማራዘም መስማማቱን ተኚትሎ፣ ዹቀይ ሰይጣኖቹ ዹኋላ ክፍል መጠናኹር ላይ ትልቅ ተስፋ ጥሏል።

​ማጓዹር ውሉን ማደሱ ኹተሹጋገጠ በኋላ በሰጠው መግለጫ፣ “ማንቜስተር ዩናይትድን መወኹል ዚመጚሚሻው ትልቅ ክብር ነው” ሲል ስሜቱን ገልጿል። ይህ ኃላፊነት እርሱንና ቀተሰቡን በዹቀኑ ኩራት እንዲሰማ቞ው እንደሚያደርግ ዹጠቀሰው ተኚላካዩ፣ በክለቡ ውስጥ ለዋና ዋና ዋንጫዎቜ ለመታገል ያለው ቁርጠኝነት ግልጜ መሆኑን አስሚድቷል።

​ተጫዋቹ አክሎም “ኚክለቡ ጋር ወደፊት ዚምናሳልፋ቞ው ምርጥ ጊዜያት ኚፊታቜን እንደሚጠብቁን ሙሉ እምነት አለኝ” ሲል ለደጋፊዎቹ ዚተስፋ መልእክት አስተላልፏል።

​ባለፉት ዚውድድር ዓመታት በተለያዩ ፈተናዎቜ ውስጥ ያለፈው ማጓዚር፣ በአዲሱ ውል መሠሚት በክለቡ ዚመኚላኚያ መስመር ውስጥ ያለውን ሚና አጠናክሮ ይቀጥላል ተብሎ ይጠበቃል። ይህ ስምምነት ክለቡ ነባር ተጫዋ቟ቹን በማቆዚት ዚቡድኑን ጥንካሬ ለማስጠበቅ ዚሚያደርገው ጥሚት አካል ተደርጎ ተወስዷል።
❀9👍2
ኊሮሚያ ባንክ ለ7 ግብሚ ሰናይ ድርጅቶቜ ዚገንዘብ ድጋፍ አደሹገ!

#Fastmereja: ኊሮሚያ ባንክ ዚዘንድሮን ዚፋሲካ በዓል ምክንያት በማድሚግ ለ7 ዚተለያዩ ሀገር በቀል ግብሚ ሰናይ ድርጅቶቜ ዹ5 ሚሊዮን ዚገንዘብ ድጋፍ አደሚገ።

በዚህ መርሃ ግብር ድጋፍ ዹተደሹገላቾዉ ድርጅቶቜ:
1. ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ዚልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኊ ኮሚሜን 1,000,000.00 ብር

2. አበበቜ ጎበና ዹበጎ አድራጎት ድርጅት 1,000,000.00 ብር

3. ዚኩላሊት ህመምተኞቜ እጥበት በጎ አድራጎት ድርጅት 1,000,000.00 ብር

4. ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዚምገባ ማዕኹል 500,000.00 ብር
5. ኊዳ አዳሪ ትምህርት ቀት 500,000.00 ብር

6. ተስፋ አዲስ፡ ዚህጻናት ዚካንሰር ህሙማን ማዕኹል 500,000.00 ብር

7. ሰበታ ዹአይነ ስዉራን ትምህርት ቀት 500,000.00 ብር ድጋፍ ተደርጓል።

ዚኊሮሚያ ባንክ ዋና ስራ አስፈጻሚ ኩቩ ተፈሪ መኰንን በድጋፍ መርሐ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክ፣ ባንኩ ዚሚመዳን ወር ምክንያት በማድሚግ ለተለያዩ ሀገር በቀል ድርጅቶቜ ተመሳሳይ ድጋፍ ማድሚጉን አስታዉሰዉ፣ በዛሬዉ ዕለትም አብይ ጟምን ምክንያት በማድሚግ ዚተለያዩ ማህበራዊ ቜግር ያለባ቞ዉን ዜጎቜ ዚሚሚዱ ግብሚ ሰናይ ድርጅቶቜን ዚገንዘብ ድጋፍ ማድሚጉን ገልጿል።

በመጚሚሻም ዚግብሚ ሰናይ ድርጅቶቹ ዚስራ ኃላፊዎቜ እና ተወካዮቜ ባንኩ ላደሹገላቾዉ ድጋፍ አመስግነዉ፣ ይህ ድጋፍ አኛ ለምንሰራዉ ሰብአዊ ስራ ትልቅ ስንቅ እና ማበሚታቻ ዹሚሆነን ነዉ ብለዋል፡፡
❀27👏2
❀19👍2