Event Addis/ሁነት አዲስ
7.19K subscribers
4.81K photos
5 videos
3 files
3.61K links
https://eventaddis.com

ለአስተያየትና ማስታወቂያ: @Tmanaye
Download Telegram
ከዛሬ ጀምሮ የ12ኛው የበጎ ሰው ሽልማት የእጩዎች ጥቆማ መስጠት ይችላል ተብሏል።

ላለፉት 11 ዓመታት በተለያዩ ዘርፎች ሽልማትና እውቅና ሲሰጥ የቆየው የበጎ ሰው የሽልማት ድርጅት ዘንድሮ ለ12ኛ ዙር ሽልማት እጩዎችን ለመቀበል የጊዜ ሰሌዳውን ይፋ አድርጓል፡፡

በዚህም ከዛሬ ግንቦት 14  እስከ ሰኔ 14/2016ዓ.ም ድረስ የእጩዎች ጥቆማ እንደሚከናወን ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቋል።

የበጎ ሰው ሽልማት እውቅና ከሚሰጣቸው ዘርፎች መካከል መምህርነት፣ መንግስታዊ ኃላፊነትን በአግባቡ የተወጡ አካላት፣ ሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ በጎ አድራጎት፣ ኪነጥበብ፣ ሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን እንዲሁም ሌሎች ዘርፎች ተካተውበታል።

ከዚህ ባለፈ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ሆነው በባህር ማዶ የሚኖሩ ለሀገር በጎ ተግባር ላበረከቱ ግለሰቦችም ይሰጣል ተብሏል ።

በተገለፀው አንድ ወር ጊዜ ውስጥ ህዝቡ ለሽልማቶቹ ብቁ ናቸው የሚላቸውን አካላት በስልክ ቁጥር 0977232323  መምረጥ ይችላል ።ከዚህ ባለፈ በፖስታ ቁጥር 150035 ላይ መልዕክት  መላክ ይቻላል ተብሏል ።

ዘገባው የኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ነው

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የሐሙሰ መረጃዎች ደርሰዋል(የቻናሉ ስፔሻል )

እነሆ ተወዳጇ እና ተናፋቂዋ ሐሙስ ደረሰች

የሳምንቱ ኪናዊ መረጃዎች ቀጥለው ይቀርባሉ:-

ተከታዩን ሊንክ
https://rb.gy/0qui84 በመነካት ብቻ የቻናሉን ስፔሻል የሐሙስ መረጃዎችን በድረገጻችን በጥሩ አቀራረብ ማንበብ ትችላላችሁ።

ማሳሰቢያ: የኤቨንት አዲስ ድረገጽ መረጃዎችን በእርሶዎ ሚዲያ ሲጠቀሙ እባክዎ በተገቢው መንገድ ምንጭ ይጠቀሱ።

የEventAddis/ሁነት አዲስ ማህበራዊ ገፆቻችን:

Telegram:https://t.me/EventAddis1

Website: https://eventaddis.com

Facebook:https://facebook.com/groups/2009372275938661/

Facebook Page:https://www.facebook.com/profile.php?id=100083170462851&mibextid=ZbWKwL
የሳምንቱን የሙዚቃ ሰሞነኛ መረጃዎች ( በአጭሩ )

📍የድምጻዊ አንተነህ ምናሉ "አይዞን" የተሰኘ ነጠላ ሙዚቃ ነገ አርብ በተለያዩ ዓለምአቀፍ የሙዚቃ ማሰራጫ መተግበሪያዎች በኩል ለአድማጮች ይደርሳል። የሙዚቃው ግጥም የሳሙኤል ሽፈራው ሲሆን ዜማውን ደግሞ ራሱ አንተነህ ምናሉ ሰርቶታል።  ድምጻዊ አንተነህ ምናሉ ከዚህ ቀደም "ዱንያ" እና "አንለይ" የተሰኙ ሙዚቃዎችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን ለአድማጮች አድርሷል።

📍የድምጻዊት ለምለም ኃ/ሚካኤል "ይለያል "የተሰኘ የሙዚቃ ቪዲዮ ነገ አርብ ግንቦት 16 2016 ዓ.ም በናሆም ሪከርድስ በኩል ይለቀቃል። የሙዚቃው ግጥም የወንድሰን ይሁብ ሲሆን ዜማው በብስራት ሱራፌል ተሰርቷል። የሙዚቃ ቪዲዮው ዳይሬክተር ወንድሰን ይሁብ ነው። ለምለም ኃ/ሚካኤል ባሳለፍነው ሳምንት "ማያዬ" የተሰኘ አልበም ለአድማጮች ማድረሷ ይታወሳል።

📍"አዲስ ጃዝ" የጃዝ ፌስቲቫል ከግንቦት 16 እስከ 18 ቀን 2016 ዓ.ም ይካሄዳል።ዝግጅቱ የሚካሄድበት ስፍራ አፍሪካን ጃዝ ቪሌጅ ሲሆን  አፍሪጎ ባንድ ከዩጋንዳ፣ ድምጻዊ ሴልሞር ቱኩድዚ ከዚምባብዌ፣ ማቲው ቴምቦ ከዛምቢያ በዕለቱ የሙዚቃ ስራቸውን ያቀርባሉ ተብሏል።ከኢትዮጵያ ደግሞ ዳዊት ይፍሩ ፣ግርማ በየነ፣ ጆርጋ መስፍን፣ ያሆ ባህላዊ የሙዚቃ ባንድ፣ መሐሪ ብራዘርስና ዮሃና ሳህሌ በፌስቲቫሉ ስራቸውን እንደሚያቀርቡ ተነግሯል።በዚህ ፌስቲቫል የሙዚቀኛ ጆርጋ መስፍን "ከሁሉም የላቀው ደግ" አልበም ይመረቃል።

📍"ብርሃን ኮንሰርት" የፊታችን ቅዳሜ ይካሄዳል። ገቢው ለሰበታ መርሐ የዓይነስውራን ት/ቤት እንዲውል  የተዘጋጀው "ብርሃን ኮንሰርት " የፊታችን ቅዳሜ ግንቦት 17 2016 ዓ.ም በግዮን ሆቴል እንደሚካሄድ ተገልጿል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የፐርፐዝ ብላክ " Invest in Poverty  Intiative" የተሰኘ አዲስ ዘመቻ የማስጀመሪያ መርሃግብር ተካሄደ

ፐርፐዝ ብላክ በዛሬዉ ዕለት ሰዎች በየወሩ 100 እና ከዚያህ በላይ ብር የሚቆጥቡበት"Invest in Poverty  Intiative" የተሰኘ ዘመቻ  አስጀምሯል።

ፐርፐዝ ብላክ በዚህ ዘመቻ ተጠቃሚዎች በየወሩ ከአነስተኛ እስከ ከፍተኛ ገንዘብን በመቆጠብ ከፍ ያለ ትርፍ የሚያገኙበት አሰራር እንደሆነ አስታውቋል።

ተቋሙ በዚሁ መርሐግብር ላይ እንዳሳወቀዉ በአሁኑ ወቅት ካፒታሉ 2.4 ቢሊዮን ብር መድረሱን ነው። የፐርፐዝ ብላክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሰሃ እሸቱ(ዶ/ር) ሰዎች የሚያስቀምጡት ገንዘብ በዝግ ሂሳብ የሚቀመጥና ባሻቸዉ ጊዜ ወጪ የሚያደርጉበት መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህ አዲስ አሰራር መሰረት ተቋሙ በቀጣዮቹ አምስት አመታት 100 ቢሊዮን ዶላር ለማሰባሰብ ማቀዱንም ይፋ አድርገዋል።

ቆጣቢዎች በተለመፈዉ የባንክ ቁጠባ ከሚያገኙት 7 በመቶ ወለድ በተሻለ በዚህ የቁጠባ ስርዓት 10 በመቶ ወለድ ተከፋይ እንደሚሆኑ ተገልጿል።

ከሕብረት ባንክ 19 በመቶ ወለድን ለተቋሙ የሚያቀርብ ሲሆን በጋራ ይሰራል ባሉት ስራም ፐርፐዝ ብላክ 9 በመቶ ድርሻ እንደሚያገኝ ጠቅሰዋል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የ"አኮፋዳ" ፕሮጀክት አካል የሆነው የፋይናንስ መረጃ ቋት ዛሬ በተካሄደ ሥነሥርዓት ይፋ ተደረገ

በኢትዮጵያ ለሚገኘው የፋይናንስ ዘርፍ አጠቃላይ መረጃ ፣ ምልከታና ልዩ ልዩ ግብዓቶችን ያለምንም ክፍያ የሚያቀርብ ፈጠራ የታከለበት ፕላትፎርም ይፋ ተደረጓል።

ኢትዮጵያ ውስጥ በተቀናጀ ሚዲያ፣ መረጃ አቅርቦትና ትንተና እንዲሁም ማማከር ከተሰማሩ ተጠቃሽ ድርጅቶች አንዱ የሆነው ሸጋ፣ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት  የኢትዮጵያ ፕላትፎርም መከፈቱን በዛሬው ዕለት ይፋ ያደርገው።

በኢትዮጵያ የፋይናንስ ተካታችነትን በከፍተኛ ሁኔታ ለማሻሻል የሚያስችል አገልግሎት ማዕከል እንደሆነም ተገልጿል።

ይህ መረጃ ትንታኔና ምልከታን ይዞ ለየት ባለ መልኩ የመጣው ፕላትፎርም የፋይናንስ ተቋማትን፣ ውሳኔ ሰጪዎችን፣ የዘርፉ ባለ ድርሻዎችን እንዲሁም ተጠቃሚዎችን ሁሉ አቅም በማሳደግ፣ የኢትዮጵያን ዲጂታል ፋይናንስ ዘርፍን ለመደገፍ ያለመ  ተብሏል።

ፕላትፎርሙ በሸጋ የበለፀገ ሲሆን፣ የሦስት ዓመት "አኮፋዳ" የተሰኘ ፕሮጀክት አካል ነው፡፡

የፕሮጀክቱ ዓላማ የባለ ድርሻ አካላትን ዕውቀት በማዳበር፣ ለአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች የሚሆኑ አገልግሎቶችን መደገፍ፣ እንዲሁም በዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶች ላይ ሰዎች ያላቸውን መተማመን በመገንባት የፋይናንስ ተካታችነትን ለማሻሻል ያለመ ነው፡፡

የፕላትፎርሙ ማብሰሪያ ሥነ ሥርዐት ዛሬ በሃያት ሬጀንሲ ሆቴል የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የአገር ውስጥና ዓለም አቀፍ የዘርፉ ባለሙያዎች እንዲሁም ልዩ ልዩ ባለ ድርሻ አካላት በተገኙበት ተከናውኗል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የኢትዮጵያ አባቶች ቀን ተከበረ

የኢትዮጵያ አባቶች ቀን "ክብር ለአባትነት" በሚል ዛሬ ግንቦት 15 ቀን 2016 ዓ.ም ለ16ኛ ጊዜ ተከብሮ ውሏል።

ላለፉት አመታት በኢትዮጵያ የአባቶች ቀንን ግንቦት 15 ላይ ሲያከብር የቆየው የኢትዮጵያ አባቶች ቀን በጎ አድራጎት ድርጅት ዘንድሮ ለ16ኛ ጊዜ "ክብር ለአባትነት" በሚል ዕለቱን በዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ በልዩ ልዩ ሁነቶች አክብሮ ውሏል።

ከዚህ ቀደም በነበሩት ዓመታት ከቤተሰብ እስከ ሃገር በመልካም አባትነትና አበርክቶ የሚነሱ አባቶችን፤ የኢትዮጵያ አባቶች የክብር መገለጫ የሆነውን ጋቢ በመደረብ፣ ዝቅ ብሎ እግር በማጠብ፣ የዕውቅና ምስክር ወረቀት በመስጠትና ታሪካቸውን በመሰነድ ሲያመሰግን እና ሲያከብር ቆይቷል።

በዘንድሮው ዓመት የኢትዮጵያ አባቶች ቀንም ልጆች ለአባታቸው ያላቸውን ፍቅርና ክብር እንዲገልፁ ብሎም አባቴ የተለየ ታሪክ አለው የሚሉ ታሪካቸውን እንዲያጋሩ በማድረግ ለሁለት አባቶች ልዩ ዕውቅና እና የምስጋና ሰርተፊኬት ተበርክቶላቸዋል፤ የክብር ጋቢ የማልበስና እግር የማጠብ ስነ ስርዓትም ተከናውኗል።

ይህ የኢትዮጵያ አባቶች ቀን ኢትዮጵያውያን በራሳችን ወግና እሴት ብሎም የመከባበር ባህል መሰረት ኢትዮጵያዊ ቀለም ባለው መልኩ "ክብር ለአባትነት" በሚል ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ በየዓመቱ ግንቦት 15 በሃገር አቀፍ ደረጃ መከበር የጀመረ ሲሆን ዕለቱ የተመረጠበትም ምክንያት የጣልያን ወረሪ ኃይልን አድዋ ላይ መክተው ያሸነፉት አባቶቻችን በድል አድራጊነት ወደመናገሻ ከተማቸው የተመለሱበት በመሆኑ ብዙሃኑ አባቶች ከቤተሰብ ባሻገር ለሃገር መፅናት ላደረጉት ተግባር ምስጋና ለመስጠት በማሰብ ነው፡፡

በቀጣይ በተለያዩ ክልል ከተሞችም መከበሩን የሚቀጥል ይሆናል ተብሏል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
አዘጋጅ ዳግማዊ አመለወርቅ ፈይሳ ታሰረ

የ"እብድት በህብረት" የአንድ ሰው ቴአትር አዘጋጅ ዳግማዊ አመለወርቅ ፈይሳ እንደታሠረ ከቅርብ ምንጮች ኤቨንት አዲስ ድረገጽ ሰምቷል።

የቴአትሩ አዘጋጅ ዳግማዊ አመለወርቅ ፈይሳ በፖሊስ" ትፈልጋለህ" ተብሎ እንደተወሰደ እና በሶስተኛ ፖሊስ ጣቢያ በእስር ላይ እንደሚገኝ ተሰምቷል።

ከወራት በፊትም "እብድት በህብረት" ቴአትርን ለማሳየት ወደ እስራኤል ሀገር ለመጓዝ በዝግጅት ላይ የነበረውን አርቲስት አማኑኤል ሀብታሙን ከአዲስ አበባ ኤርፖርት "ትፈልጋለህ" በሚል እንደወሰዱት እና እስካሁንም በእስር ላይ እንደሚገኝ ይታወሳል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የሳምንቱ የኪነጥበብ ዝግጅቶች ጥቆማ

📍"ግጥም ሲጥም "ለሁሉም ክፍት የሆነ የኪነጥበብ  መድረክ ነገ አርብ ግንቦት 16 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ ገርጂ በሚገኘው ደስክ አዲስ ውስጥ ይካሄዳል ተብሏል።

📍"ሆሄ ተስፋ የኪነጥበብ መድረክ" የፊታችን እሁድ ግንቦት 18 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ መገናኛ ዋኣች ሕንፃ ላይ በሚገኘው "ጣዕም ባህላዊ ምግብ ቤት" ውስጥ ይካሄዳል ተብሏል።

የEventAddis/ሁነት አዲስ ማህበራዊ ገፆቻችን:

Telegram:https://t.me/EventAddis1

Website: https://eventaddis.com

Facebook:https://facebook.com/groups/2009372275938661/
የሳምንቱን የሥነጽሑፍ ውይይቶች በአጭሩ

📍በዛጎል መጻሕፍት ባንክ የሚዘጋጀው "ነገረ መጻሕፍት" የመጽሐፍ ውይይት የፊታችን ቅዳሜ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ይካሄዳል። በዚህ ሳምንት በገጣሚ እና ደራሲ ታገል ሰይፉ "ዝንቡላ እና ካሮት"በተሰኘው መጽሐፉ ላይ  ውይይት ይካሄዳል።የዕለቱ አወያይ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ ነው። ይህ መርሐግብር ቅዳሜ ግንቦት 17 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 እስከ 10:30 ይካሄዳል።

📍በዘርዓያዕቆብ የፍልስፍና ት/ቤት በየሳምንቱ የሚዘጋጀው የሀሳብ ውይይት በዚህም ሳምንት "አዲስ አፍላጦናዊነት በቅዱስ ኦገስቲን ኑዛዜ" የተሰኘ ርዕስ መርጧል ይህም ውይይት  ቅዳሜ ግንቦት 17 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ 5 ኪሎ በሚገኘው አፄ ናኦድ ት/ቤት ግቢ ውስጥ ይካሄዳል።"አዲስ አፍላጦናዊነት በቅዱስ ኦገስቲን ኑዛዜ"በሚል ርዕስ በዘካርያስ ደበበ መነሻ ሀሳብ ይቀርባል ተብሏል።

📍የብራና ጁፒተር የንባብ ቡድን የፊታችን ቅዳሜ ግንቦት 17 2016 ዓ.ም በዶ/ር መላኩ አዳል "ለሉሲ ሀገር ሰዎች" መጽሐፍ ላይ ውይይት ያካሄዳል። ይህ ውይይት ከ9:45 እስከ 12:00 ካዛንቺስ በሚገኘው ጁፒተር ሆቴል ውስጥ ይካሄዳል።

📍 "አውደ ፋጎስ" 37ኛው ዙር የሀሳብ ውይይት የፊታችን እሁድ ግንቦት 18 2016 ዓ.ም በወመዘክር አዳራሽ ይካሄዳል።በዚህኛው ዙር "አደባባያችን እንደገና ሲብሰለሰል"በሚል ርዕሰ ጉዳይ በሚዲያ እና ኮምኒኬሽን ባለሞያዋ ነዋል አቡበከር መነሻ ሀሳብ ይቀርባል።ውይይቱ ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ይካሄዳል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
"የሁለት ጌቶች አሽከር" ተውኔት ዛሬ ይሰናበታል

በካርሎ ጎልዶኒ "The servant of two Masters" በሚል የተጻፈውና ወደ አማርኛ"የሁለት ጌቶች አሽከር" በሚል ርዕስ በተስፋዬ ገ/ማርያም የተተረጎመ ተውኔት ዛሬ ግንቦት 16 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 11:30 ጀምሮ ከመድረክ ይሰናበታል።

በተውኔቱ ላይ ሚኪ ተስፋዬ ፣ እታፈራው መብራቱ ፣ሔኖክ ዘርዓብሩክ ፣ሳምራዊት ከበደ፣እንዳለ ብርሃኑና ሌሎችም ተሳትፈዋል።

ተውኔቱ ከጥቅምት 9 2016 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ሲመደረክ እንደቆየ ይታወሳል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የሙዚቀኛ ጆርጋ መስፍን አልበም ዛሬ ይለቀቃል

የሙዚቀኛ ጆርጋ መስፍን ቀደም ሲል ‘ደጋጎቹ‘ በሚል ርዕስ ለአድማጮች ያደረሰውና በድጋሜ ተሰርቶ "ከሁሉ የላቀው ደግ" የሚል ስያሜ የተሰጠው የኢትዮ ጃዝ አልበም ዛሬ ግንቦት 16 2016 ዓ.ም በሙዚቃዊ ዩቲዩብ ቻናል እና በዓለምአቀፍ የሙዚቃ ማሰራጫ መተግበሪያዎች በኩል ይለቀቃል።

የጆርጋ መስፍን"ከሁሉ የላቀው ደግ" አልበም ከዛሬ ግንቦት 16 2016 ዓ.ም ጀምሮ በሚካሄደው "አዲስ ጃዝ ፌስቲቫል" ላይ በመክፈቻው ዕለት በአፍሪካ ጃዝ ቪሌጅ ይመረቃል ተብሏል።

በዛሬው ዝግጅት ላይ የሙዚቃ ሸክላው ለሽያጭ የሚቀረብ ሲሆን ሙዚቀኛውም የሙዚቃ ስራውን እንደሚያቀርብ ተገልጿል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
"ብርሃን ኮንሰርት" ላልተወሰነ ጊዜ ተራዘመ

ገቢው ለሰበታ መርሐ የዓይነስውራን ት/ቤት እንዲውል የተዘጋጀውና ነገ ግንቦት 17 2016 ዓ.ም አመሻሽ ላይ በግዮን ሆቴል እንደሚካሄድ ሲገለፅ የቆየው"ብርሃን ኮንሰርት" ላልተወሰነ ጊዜ እንደተራዘመ ከቅርብ ምንጮች ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።

በዚህ የገቢ ማሰባሰቢያ ኮንሰርት ላይ ድምጻዊያኑ አብዱ ኪያር ፣ ቀመር የሱፍ ፣ ይርዳው ጤና ፣ባልከው አለሙ፣ ኃይማኖት ግርማና ሌሎችም የሙዚቃ ስራዎችን እንደሚያቀረቡ ሲገለጽ ቆይቷል።

ኮንሰርቱ በምን ምክያንት እንደተራዘመ አዘጋጆቹ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጡበታል ተብሏል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በድምጻዊት ህሩት በቀል ላይ ያተኮረ "አንፀባራቂዋ ኮኮብ" የተሰኘ መጽሐፍ ቀጣይ ሳምንት ለንባብ ይበቃል

በዐብይ ፈቅይበሉ የተዘጋጅውና በድምጻዊት ሒሩት በቀለ ህይወት ዙሪያ የሚያጠነጥነው "አንፀባራቂዋ ኮኮብ" የተሰኘ መጽሐፍ የፊታችን ሰኞ ግንቦት 19 2016 ዓ.ም ከቀኑ በ9:00 ጀምሮ የአንደኛ ዓመት መታሰቢያዋ በኢሊሌ ኢንተርናሽናል ሆቴል በሚታሰብበት ቀን ለንባብ እንደሚበቃ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።

በዕለቱ የፌድራል ፖሊስ ማርሽ ባንድን ጨምሮ የፌዴራል ፖሊስ ኦኬስትራ እና የዳዊት ፅጌ ባንድ እንዲሁም የሒሩት በቀለን ስራዎች ከሚያቀነቅኑት ታዋቂ ድምፃዊያን ጋር በመሆን ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል።

መፅሐፉ ተፅፎ እስኪጠናቅ ድረስ 2.5 ሚልዮን ብር ወጪ እንደተደረገበት የመፅሐፉ ደራሲ ዐቢይ ፈቅይበሉ ገልጿል።

ከመጽሐፉም የሚገኘው ገቢ በስሟ ለሚቋቋመው በጎ አድራጎት ፋውንዴሽን ምስረታ የሚውል እንደሆነም ተገልጿል።

ግንቦት 4 2015 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት የተለየችው ዝነኛዋ የፖሊስ ኦኬስትራ የቀድሞ ድምፃዊት በኋላም ዘማሪት ሒሩት በቀለ በሙያዋ ለሀገሯ ያበረከተችውን ጉልህ አስተዋፅኦ ከግምት ውስጥ በማስገባት በዚህ መታሰቢያ ፕሮግራም ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የሀገራችን የኪነጥበብ ባለሞያዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦች እና የአርቲስቷ ወዳጅ ዘመዶች በተገኙበት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
ለሚዲያዎች መልዕክት ከኤቨንት አዲስ አዘጋጅ !

የመረጃ ምንጭን መጥቀስ/ክሬዲት መስጠት

ሚዲያችን Event Addis/ሁነት አዲስ የኩነት እና መዝናኛ መረጃዎች ምንጭ መሆን ከጀመረ የፊታችን ግንቦት 29 2016 ዓ.ም ሁለተኛ ዓመቱን ይይዛል።

በእነዚህ ሁለት ዓመታት ያለማቋረጥ በየዕለቱ የሥነጽሑፍ ፣ የኪነጥበብ ፣ የሥነጥበብ ፣ የእድ ጥበብ፣ የኩነት እና ሚዲያ መረጃዎችን ለተከታዮቹ በፍጥነት እና በጥራት ሲያቀረብ ቆይቷል።

አሁንም በኢትዮጵያ ለሚገኙ በርካታ የቴሌቪዥን ፣ ሬድዮ ፣ ጋዜጦች እና መጽሔቶች ፣ ማህበራዊ ትስስር ገፆች ሁነኛ የመዝናኛ መረጃዎች ምንጭ በመሆን እያገለገለ ይገኛል። በዚህም እጅግ ደስተኞች ነን። ከልብ እናመሰግናለን።

ነገር ግን በበርካታ የሬድዮ ፕሮግራሞች፣ በቴሌቪዥን ዜና ሰዓቶች ፣ጋዜጦች እና ማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ የኤቨንት አዲስ/ሁነት አዲስ መረጃዎችን "እንደወረዱ" የሚጠቀሙ ነገር የመረጃውን ባለቤት  "Event Addis/ሁነት አዲስ" ሚዲያን በተገቢው መንገድ የመረጃ ምንጩነቱን የማይጠቅሱ ፕሮግራሞች ገጥመውናል።በዚህም እጅግ እናዝናለን።

በተደጋጋሚም የኤቨንት አዲስ/ሁነት አዲስ መረጃዎችን ምንም አይነት ምንጭ ሳይጠቅሱ( Credit ሳይሰጡ) የሚጠቀሙ የሬድዮ ፕሮግራሞችን ፣ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችን ፣ የጋዜጣ እና ማህበራዊ ትስስር ገፆችን ከነማስረጃው ለይትን ያስቀመጥን ስለሆነ በተገቢው መንገድ ምንጭ በመጠቀስ ለመረጃዎቻችን እውቅና እንዲሰጡ እናሳስባለን።

የሚዲያችንን መረጃዎች በተገቢው መንገድ ምንጭ ጠቅሰው ለሚጠቀሙ ሚዲያዎች ደግሞ አክብሮታችን የላቀ ነው እናመሰግናለን።

በተጨማሪም ብዙ ዋጋ ከፍሎ ያለምንም ዋጋ በነፃ መረጃዎችን እያቀረበ የሚገኘውን ቻናላችንን በማስተዋወቅ ብታግዙን እጅግ ደስተኞች ነን።

https://t.me/EventAddis1
የሳምንቱን የመጻህፍት መረጃዎች በአጭሩ

📍የገጣሚ መንበረማርያም ኃይሉ አዲስ መጽሐፍ በቅርቡ ለንባብ ይበቃል። መጽሐፉ "የጊዜ ሠሌዳ" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው ሲሆን የግጥም ስብስብ መጽሐፍ ነው። ገጣሚ መንበረማርያም ኃይሉ ከሁለት ዓመት በፊት  "የቃል ሠሌዳ" የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ ማብቃቷ ይታወሳል።

📍 የደራሲ ዓለማየሁ ደመቀ "ዮቶር 2" የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ በዚህ ሳምንት ለንባብ በቅቷል።በ207 ገፆች የተቀነበበው መጽሐፉ በ450 ብር የጀርባ ዋጋ ለአንባቢያን ቀርቧል።መጽሐፉ ጃፋር መጻሕፍት መደብርን ጨምሮ በተለያዩ መጻሕፍት መደብሮች ይገኛል።ከዚህ ቀደም በደራሲ አለማየሁ ደመቀ የተጻፈው "ዮቶር ኮባላይ ካህን" 15ተኛ ዕትም መጽሐፍ ከሰሞኑ በድጋሚ ለአንባቢያን መቅረቡ ይታወሳል።

📍የገጣሚ አይዳ ታደሰ "አልፅፍም" የተሰኘ የግጥም መጽሐፍ ከሰሞኑ ለንባብ በቅቷል።የግጥም መጽሐፉ በ140 ገፆች የተቀነበበ ሲሆን በ200 ብር የጀርባ ዋጋ ለአንባቢያን ቀርቧል በዓይናለም መጻሕፍት መደብር ውስጥም ይገኛል ተብሏል።መጽሐፉ “ሰቆቃ ወ አይዳ” እና “ምናብና ትዝብት” በተሰኙ ንዑሰ ርዕሶች ተከፍሎ የቀረበ የግጥም ስብስብ መጽሐፍ ነው።

📍የገጣሚ ሰሎሞን ሞገስ "ባሻ አሸብር በጀርመን" የግጥም መፅሃፍ ለሀገር ውስጥ አንባቢያን ቀረበ።ገጣሚ ሰሎሞን ሞገስ ከዚህ ቀደም እውነትን ስቀሏት እና ሌሎችንም የግጥም መድብሎች ለንባብ ያበቃ ሲሆን ይህኛው መጽሐፉ አምስተኛ ስራው ነው።

📍የመጋቢ ሐዲስ ዶ/ር ሮዳስ ታደሰ "37 አልፋ ገ3" የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ በሚቀጥለው ሳምንት ለአንባቢያን ይቀርባል ተብሏል።

📍የህይወት ተፈራ"ማማ በሰማይ" ፣ "ምንተዋብ" እና "ኀሠሣ" የተሰኙ ሶስት መጻሕፍት በድጋሚ ታትመው በዚህ ሳምንት ለአንባቢያን ቀረበዋል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1