ኩባንያችን ከጅማ ከተማ አስተዳደር ጋር በከተማዋ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ የሚያደርግ የስማርት ሲቲ “ስማርት ጅማ” ፕሮጀክትን ለመተግበር የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ስምምነት አደረገ።
ፕሮጀክቱ ከተማዋን በሁለገብ ዲጂታል ሶሉሽኖች ለማዘመን ያለመ ሲሆን፣ የክላውድ መሰረተ ልማትን፣ የጥሪ ማዕከልን፣ ጠንካራ የመረጃ ማዕከልን፣ እጅግ ከፍተኛ ፍጥነትና ጥራት ያለው ኢንተርኔትን፣ የላቀ የሲሲቲቪ ደህንነት ካሜራ ሲስተምን፣ የኦፕቲካል ፋይበር እንዲሁም ሌሎች የዲጂታል መሰረተ ልማቶችን ያካትታል።
ስምምነቱ የማዘጋጃ ቤት አገልግሎቶችን ጨምሮ በትምህርት፣ በጤና፣ በግብርና፣ በትራንስፖርት፣ ግብር የመሳሰሉ አገልግሎቶችን ለማዘመን ከፍተኛ ሚና የሚጫወት ከመሆኑም ባሻገር እጅግ ቀልጣፋ አገልግሎት አሰጣጥን ዕውን በማድረግ የዜጎችን የዕለት ተዕለት ህይወት ቀላል ያደርጋል።
ጅማ ለቱሪዝም ቀዳሚ መዳረሻነት፣ ለኮንፈረንስ፣ ለኢንዱስትሪ እና ለተለያዩ ኢንቨስትመንቶች ተመራጭ እንድትሆን የሚያስችላትን አቅም በማጎልበት ተወዳዳሪነቷን የሚያሳድግ ሲሆን፣ ይህም የንግድ እንቅስቃሴን በማነቃቃት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ያሳድጋል።
የስማርት ሲቲ ፕሮጀክት በአዲስ አበባ (ሲቲኔት)፣ አዳማ፣ ሸገር ሲቲ፣ ሐረር፣ ደሴ፣ ኮምቦልቻ እና ባህር ዳር የመጀመሪያውን ምዕራፍ በስኬት የተገበርን ሲሆን በጅግጅጋ ከተማ በትግበራ ሂደት እንዲሁም ከሌሎች ከተሞች አስተዳደሮች ጋር በውይይት ላይ እንገኛለን።
#Jimma #SmartCity #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #SmartAfrica #Ethiotelecom #telebirr #RealizingDigitalEthiopia
ፕሮጀክቱ ከተማዋን በሁለገብ ዲጂታል ሶሉሽኖች ለማዘመን ያለመ ሲሆን፣ የክላውድ መሰረተ ልማትን፣ የጥሪ ማዕከልን፣ ጠንካራ የመረጃ ማዕከልን፣ እጅግ ከፍተኛ ፍጥነትና ጥራት ያለው ኢንተርኔትን፣ የላቀ የሲሲቲቪ ደህንነት ካሜራ ሲስተምን፣ የኦፕቲካል ፋይበር እንዲሁም ሌሎች የዲጂታል መሰረተ ልማቶችን ያካትታል።
ስምምነቱ የማዘጋጃ ቤት አገልግሎቶችን ጨምሮ በትምህርት፣ በጤና፣ በግብርና፣ በትራንስፖርት፣ ግብር የመሳሰሉ አገልግሎቶችን ለማዘመን ከፍተኛ ሚና የሚጫወት ከመሆኑም ባሻገር እጅግ ቀልጣፋ አገልግሎት አሰጣጥን ዕውን በማድረግ የዜጎችን የዕለት ተዕለት ህይወት ቀላል ያደርጋል።
ጅማ ለቱሪዝም ቀዳሚ መዳረሻነት፣ ለኮንፈረንስ፣ ለኢንዱስትሪ እና ለተለያዩ ኢንቨስትመንቶች ተመራጭ እንድትሆን የሚያስችላትን አቅም በማጎልበት ተወዳዳሪነቷን የሚያሳድግ ሲሆን፣ ይህም የንግድ እንቅስቃሴን በማነቃቃት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ያሳድጋል።
የስማርት ሲቲ ፕሮጀክት በአዲስ አበባ (ሲቲኔት)፣ አዳማ፣ ሸገር ሲቲ፣ ሐረር፣ ደሴ፣ ኮምቦልቻ እና ባህር ዳር የመጀመሪያውን ምዕራፍ በስኬት የተገበርን ሲሆን በጅግጅጋ ከተማ በትግበራ ሂደት እንዲሁም ከሌሎች ከተሞች አስተዳደሮች ጋር በውይይት ላይ እንገኛለን።
#Jimma #SmartCity #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #SmartAfrica #Ethiotelecom #telebirr #RealizingDigitalEthiopia
👍19❤3🥰2👏2
ኢትዮ ቴሌኮም የ5ጂ ኔትወርክ ማስፋፊያ አጠናክሮ በመቀጠል በዛሬው ዕለት በደሴና በኮምቦልቻ ከተሞች አገልግሎቱን በይፋ አስጀምሯል፡፡
ይህ ኩባንያችን የሀገራችንን ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ለማፋጠን የሚያደርገው ሀገራዊ ጥረት አካል ሲሆን፣ የላቀ ፍጥነት ያለው ኢንተርኔት በማዳረስ ለአዳዲስ ፈጠራዎችና ኢኮኖሚያዊ የዕድገት ዕድሎች በር ለመክፈት ያስችላል።
በደሴ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት፣ ደቡብ ወሎ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት፣ የኢትዮ ቴሌኮም ሰሜን ምስራቅ ሪጅን ጽ/ቤት፣ ወሎ ዩኒቨርሲቲ ዋና ካምፓስ፣ ሉሲ ሆቴልና ደሴ ሙዚየም አካባቢዎችን ይሸፍናል፡፡
በኮምቦልቻ ደግሞ ኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት፣ ኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅና ወሎ ዩኒቨርሲቲ ኮምቦልቻ ካምፓስ አካባቢዎችን ይሸፍናል፡፡
አገልግሎቱ አዳዲስ የዲጂታል እና የፋይናንስ አገልግሎቶች፣ ለኦንላይን ትምህርት፣ ለጀማሪ የንግድ ተቋማት ፣ የስራ እድል ፈጠራ፣ የዲጂታል ክፍተትን ለማጥበብ፣ የስማርት ስልክ አቅርቦት ለማሳደግና ዲጂታል ክህሎትን ለመጨመር ያስችላል።
5ጂ የግል እና የመንግስት ተቋማትን አሰራር ያዘምናል፤ እንደ ጤና፣ ግብርና፣ ትምህርት፣ ማኑፋክቸሪንግን፣ ማዕድን፣ ትራንስፖርት እና ቱሪዝምን የመሳሰሉ ቁልፍ ዘርፎችን በማዘመን ረገድ ጉልህ ሚና ይጫወታል፡፡
በአዲስ አበባ በ2022 እ.ኤ.አ ያስጀመርነው 5ጂ ደሴ እና ኮምቦልቻን ጨምሮ በ14 ከተሞች ማለትም በአዲስ አበባ፣ በአዳማ፣ በጅግጅጋ፣ በድሬዳዋ፣ በሐረር፣ በባህር ዳር፣ በሐዋሳ፣ በወላይታ ሶዶ፣ በሆሳዕና፣ በአርባ ምንጭ፣ ቢሾፍቱና ጅማ አገልግሎት ላይ ውሏል።
ለተጨማሪ፡- https://bit.ly/3F2QyJe
ይህ ኩባንያችን የሀገራችንን ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ለማፋጠን የሚያደርገው ሀገራዊ ጥረት አካል ሲሆን፣ የላቀ ፍጥነት ያለው ኢንተርኔት በማዳረስ ለአዳዲስ ፈጠራዎችና ኢኮኖሚያዊ የዕድገት ዕድሎች በር ለመክፈት ያስችላል።
በደሴ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት፣ ደቡብ ወሎ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት፣ የኢትዮ ቴሌኮም ሰሜን ምስራቅ ሪጅን ጽ/ቤት፣ ወሎ ዩኒቨርሲቲ ዋና ካምፓስ፣ ሉሲ ሆቴልና ደሴ ሙዚየም አካባቢዎችን ይሸፍናል፡፡
በኮምቦልቻ ደግሞ ኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት፣ ኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅና ወሎ ዩኒቨርሲቲ ኮምቦልቻ ካምፓስ አካባቢዎችን ይሸፍናል፡፡
አገልግሎቱ አዳዲስ የዲጂታል እና የፋይናንስ አገልግሎቶች፣ ለኦንላይን ትምህርት፣ ለጀማሪ የንግድ ተቋማት ፣ የስራ እድል ፈጠራ፣ የዲጂታል ክፍተትን ለማጥበብ፣ የስማርት ስልክ አቅርቦት ለማሳደግና ዲጂታል ክህሎትን ለመጨመር ያስችላል።
5ጂ የግል እና የመንግስት ተቋማትን አሰራር ያዘምናል፤ እንደ ጤና፣ ግብርና፣ ትምህርት፣ ማኑፋክቸሪንግን፣ ማዕድን፣ ትራንስፖርት እና ቱሪዝምን የመሳሰሉ ቁልፍ ዘርፎችን በማዘመን ረገድ ጉልህ ሚና ይጫወታል፡፡
በአዲስ አበባ በ2022 እ.ኤ.አ ያስጀመርነው 5ጂ ደሴ እና ኮምቦልቻን ጨምሮ በ14 ከተሞች ማለትም በአዲስ አበባ፣ በአዳማ፣ በጅግጅጋ፣ በድሬዳዋ፣ በሐረር፣ በባህር ዳር፣ በሐዋሳ፣ በወላይታ ሶዶ፣ በሆሳዕና፣ በአርባ ምንጭ፣ ቢሾፍቱና ጅማ አገልግሎት ላይ ውሏል።
ለተጨማሪ፡- https://bit.ly/3F2QyJe
👏12👍8🥰1
ውድ ቤተሰቦቻችን መልካም ቀን! ስኬታማ የሥራ ሳምንት ይሁንላችሁ!
#MondayMotivation
#Ethiotelecomfamily
#Ethiotelecom #telebirr #RealizingDigitalEthiopia
የቪቫ ኢንጌጅ ቻናላችንን ለመቀላቀል: https://bit.ly/3NoMbcx
#MondayMotivation
#Ethiotelecomfamily
#Ethiotelecom #telebirr #RealizingDigitalEthiopia
የቪቫ ኢንጌጅ ቻናላችንን ለመቀላቀል: https://bit.ly/3NoMbcx
👍13🥰1