የቴሌብር አገልግሎት በ2017 የመጀመሪያው መንፈቅ ዓመት 5 ሚሊዮን ደንበኞች በማፍራት አጠቃላይ የአገልግሎት ተጠቃሚዎችን ቁጥር 51.5 ሚሊዮን በላይ በማድረስ የዕቅዱን 99.8% አሳክቷል፡፡
በግማሽ ዓመቱ በቴሌብር 1.03 ትሪሊዮን ብር የኤሌክትሮኒክ ገንዘብ ዝውውር የተከናወነ ሲሆን፣ እስካሁን ድረስ በአጠቃላይ 3.58 ትሪሊየን የኤሌክትሮኒክ ገንዘብ በኢኮኖሚው ውስጥ ማንቀሳቀስ ተችሏል፡፡
ይህም የገንዘብ ዝውውርን ቀላል እና ቀልጣፋ በማድረግ አካታችና ተደራሽ የዲጂታል ኢኮኖሚ ለመገንባት በማስቻል ላይ ነው፡፡
የቴሌብር አገልግሎት በዓለም አቀፉ የጥራት ደረጃ ማረጋገጫ ተቋም የ ISO 27001:2022 እና የ PCI DSS V4.0.1 የደኅንነት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀቶች ያገኘ ሲሆን ይህም የቴሌብር ፋይናንሻል እና ክፍያ አገልግሎቶቻችን አስተማማኝ እና ዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃዎችን ያሟሉ መሆናቸውን የሚያሳይ ነው፡፡
የቴሌብር አገልግሎት ለማኅበረሰባችን ሁለንተናዊ ለውጥና መሻሻል ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ከመሆኑ ባሻገር ትርጉም ያለው ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ የፋይናንስ አገልግሎችን ማለትም የሞባይል አነስተኛ ብድር፣ የቁጠባ አገልግሎትና ተያያዥ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶችን እያቀረበ ይገኛል፡፡
ውድ የቴሌብር ደንበኞቻችን፣ አጋሮቻችን እና የኩባንያችን ቤተሰቦች በስኬታችን ጉዞ አብሮነታችሁ ስላልተለየን ከልብ እናመሰግናለን!
ለሙሉ ሪፖርቱ https://bit.ly/40RlnYV ይጫኑ
#telebirr #Ethiotelecom #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
በግማሽ ዓመቱ በቴሌብር 1.03 ትሪሊዮን ብር የኤሌክትሮኒክ ገንዘብ ዝውውር የተከናወነ ሲሆን፣ እስካሁን ድረስ በአጠቃላይ 3.58 ትሪሊየን የኤሌክትሮኒክ ገንዘብ በኢኮኖሚው ውስጥ ማንቀሳቀስ ተችሏል፡፡
ይህም የገንዘብ ዝውውርን ቀላል እና ቀልጣፋ በማድረግ አካታችና ተደራሽ የዲጂታል ኢኮኖሚ ለመገንባት በማስቻል ላይ ነው፡፡
የቴሌብር አገልግሎት በዓለም አቀፉ የጥራት ደረጃ ማረጋገጫ ተቋም የ ISO 27001:2022 እና የ PCI DSS V4.0.1 የደኅንነት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀቶች ያገኘ ሲሆን ይህም የቴሌብር ፋይናንሻል እና ክፍያ አገልግሎቶቻችን አስተማማኝ እና ዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃዎችን ያሟሉ መሆናቸውን የሚያሳይ ነው፡፡
የቴሌብር አገልግሎት ለማኅበረሰባችን ሁለንተናዊ ለውጥና መሻሻል ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ከመሆኑ ባሻገር ትርጉም ያለው ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ የፋይናንስ አገልግሎችን ማለትም የሞባይል አነስተኛ ብድር፣ የቁጠባ አገልግሎትና ተያያዥ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶችን እያቀረበ ይገኛል፡፡
ውድ የቴሌብር ደንበኞቻችን፣ አጋሮቻችን እና የኩባንያችን ቤተሰቦች በስኬታችን ጉዞ አብሮነታችሁ ስላልተለየን ከልብ እናመሰግናለን!
ለሙሉ ሪፖርቱ https://bit.ly/40RlnYV ይጫኑ
#telebirr #Ethiotelecom #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
👍23❤5🥰1
በጀት ዓመቱ የመጀመሪያ አጋማሽ ኩባንያችን በማህበራዊ ኃላፊነት ረገድ በድምሩ ከ287.17 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አድርጓል።
ድጋፉ ለትምህርት፣ ለጤና፣ ለሰብአዊ ድጋፍ፣ ለአካባቢ ጥበቃ፣ ለአረንጓዴ ልማትና ማስዋብ እንዲሁም ለሀገራዊ ፕሮጀክቶች የተደረገ ሲሆን፣ በዓይነት 131.3 ሚሊዮን ብር፣ በገንዘብ ደግሞ ከ155.9 ሚሊዮን ብር በላይ ነው።
የኩባንያችን ሰራተኞች፣ አጋር አካላት እና የአካባቢ ማህበረሰብ ክፍሎችን በአረንጓዴ ልማት ሥራዎች በንቃት በማሳተፍ፣ በበጀት አመቱ አጋማሽ በ105 ቦታዎች ከ446,000 በላይ ችግኞችን ለመትከል ተችሏል፡፡
የኩባንያችን ሰራተኞች ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ ከማድረግ ባሻገር፣ ደም በመለገስ እና የተለያዩ አይነት የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶችን በመስጠት በማህበራዊ ኃላፊነት አርአያ የሚሆን ተግባር አከናውነዋል።
ለተጨማሪ https://bit.ly/40RlnYV ይጫኑ
#CSR #Ethiotelecom #telebirr #GSMA #ITU #WorldBank #OECD #G6countries #HOPR #HoF
ድጋፉ ለትምህርት፣ ለጤና፣ ለሰብአዊ ድጋፍ፣ ለአካባቢ ጥበቃ፣ ለአረንጓዴ ልማትና ማስዋብ እንዲሁም ለሀገራዊ ፕሮጀክቶች የተደረገ ሲሆን፣ በዓይነት 131.3 ሚሊዮን ብር፣ በገንዘብ ደግሞ ከ155.9 ሚሊዮን ብር በላይ ነው።
የኩባንያችን ሰራተኞች፣ አጋር አካላት እና የአካባቢ ማህበረሰብ ክፍሎችን በአረንጓዴ ልማት ሥራዎች በንቃት በማሳተፍ፣ በበጀት አመቱ አጋማሽ በ105 ቦታዎች ከ446,000 በላይ ችግኞችን ለመትከል ተችሏል፡፡
የኩባንያችን ሰራተኞች ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ ከማድረግ ባሻገር፣ ደም በመለገስ እና የተለያዩ አይነት የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶችን በመስጠት በማህበራዊ ኃላፊነት አርአያ የሚሆን ተግባር አከናውነዋል።
ለተጨማሪ https://bit.ly/40RlnYV ይጫኑ
#CSR #Ethiotelecom #telebirr #GSMA #ITU #WorldBank #OECD #G6countries #HOPR #HoF
👏11👍6❤1🥰1
ውድ ቤተሰቦቻችን መልካም ቀን! መልካም የሥራ ሳምንት ይሁንላችሁ!
#MondayMotivation
#Ethiotelecomfamily
#Ethiotelecom #telebirr #RealizingDigitalEthiopia
#MondayMotivation
#Ethiotelecomfamily
#Ethiotelecom #telebirr #RealizingDigitalEthiopia
👍11❤2🥰1
ኢትዮ ቴሌኮም በጅማ ከተማ የ5ጂ ኔትወርክ አገልግሎት አስጀመረ፤ የዲጂታል ኢትዮጵያን ጉዞ በማፋጠን ላይ!
በኢትዮጵያ ቀዳሚው የቴሌኮም እና ዲጂታል አገልግሎቶች አቅራቢ የሆነው ኢትዮ ቴሌኮም በሀገር አቀፍ ደረጃ የአምስተኛው ትውልድ (5ጂ) ኔትወርክ ማስፋፊያ አጠናክሮ በመቀጠል በዛሬው ዕለት በጅማ ከተማ አገልግሎቱን በይፋ አስጀምሯል፡፡
ኩባንያችን የ5ጂ አገልግሎትን በአዲስ አበባ እ.ኤ.አ በ2022 ካስጀመረበት ጊዜ አንስቶ፣ እስካሁን ድረስ፣ ጅማን ጨምሮ በ12 ከተሞች ማለትም በአዲስ አበባ፣ በአዳማ፣ በጅግጅጋ፣ በድሬዳዋ፣ በሐረር፣ በባህር ዳር፣ በሐዋሳ፣ በወላይታ ሶዶ፣ በሆሳዕና፣ በአርባ ምንጭ እና በቢሾፍቱ አገልግሎቱን ዕውን አድርጓል።
ቴክኖሎጂው የኔትወርክ አቅም ከመጨመር ባሻገር አዳዲስ የዲጂታል እና የፋይናንስ አገልግሎቶች፣ ለኦንላይን ትምህርት፣ ለጀማሪ የንግድ ተቋማት (startups)፣ የስራ እድል ፈጠራ፣ የዲጂታል ክፍተትን ለማጥበብ፣ የስማርት ስልክ አቅርቦት ለማሳደግ እና የዲጂታል ሊትሬሲን ለመጨመር አስቻይ ሁኔታ ይፈጥራል።
የ5ጂ ቴክኖሎጂ የድርጅት ደንበኞችን የዕለት ተዕለት አሰራርን ከማዘመን በተጨማሪ፣ ቁልፍ በሆኑ ዘርፎች ላይ ማለትም ጤናን፣ ግብርናን፣ ትምህርትን፣ ማኑፋክቸሪንግን እና ማዕድንን፣ ትራንስፖርትን፣ ቱሪዝምን፣ መዝናኛን በስማርት ቴኮኖሎጂ በማዘመን ረገድ ቁልፍ ሚና ይጫወታል፡፡
ለተጨማሪ፡- https://bit.ly/42Z0ygF
አዲስ ፍጥነት፣ አዲስ ምቾት፣ አዲስ አኗኗር!
በኢትዮጵያ ቀዳሚው የቴሌኮም እና ዲጂታል አገልግሎቶች አቅራቢ የሆነው ኢትዮ ቴሌኮም በሀገር አቀፍ ደረጃ የአምስተኛው ትውልድ (5ጂ) ኔትወርክ ማስፋፊያ አጠናክሮ በመቀጠል በዛሬው ዕለት በጅማ ከተማ አገልግሎቱን በይፋ አስጀምሯል፡፡
ኩባንያችን የ5ጂ አገልግሎትን በአዲስ አበባ እ.ኤ.አ በ2022 ካስጀመረበት ጊዜ አንስቶ፣ እስካሁን ድረስ፣ ጅማን ጨምሮ በ12 ከተሞች ማለትም በአዲስ አበባ፣ በአዳማ፣ በጅግጅጋ፣ በድሬዳዋ፣ በሐረር፣ በባህር ዳር፣ በሐዋሳ፣ በወላይታ ሶዶ፣ በሆሳዕና፣ በአርባ ምንጭ እና በቢሾፍቱ አገልግሎቱን ዕውን አድርጓል።
ቴክኖሎጂው የኔትወርክ አቅም ከመጨመር ባሻገር አዳዲስ የዲጂታል እና የፋይናንስ አገልግሎቶች፣ ለኦንላይን ትምህርት፣ ለጀማሪ የንግድ ተቋማት (startups)፣ የስራ እድል ፈጠራ፣ የዲጂታል ክፍተትን ለማጥበብ፣ የስማርት ስልክ አቅርቦት ለማሳደግ እና የዲጂታል ሊትሬሲን ለመጨመር አስቻይ ሁኔታ ይፈጥራል።
የ5ጂ ቴክኖሎጂ የድርጅት ደንበኞችን የዕለት ተዕለት አሰራርን ከማዘመን በተጨማሪ፣ ቁልፍ በሆኑ ዘርፎች ላይ ማለትም ጤናን፣ ግብርናን፣ ትምህርትን፣ ማኑፋክቸሪንግን እና ማዕድንን፣ ትራንስፖርትን፣ ቱሪዝምን፣ መዝናኛን በስማርት ቴኮኖሎጂ በማዘመን ረገድ ቁልፍ ሚና ይጫወታል፡፡
ለተጨማሪ፡- https://bit.ly/42Z0ygF
አዲስ ፍጥነት፣ አዲስ ምቾት፣ አዲስ አኗኗር!
👍18❤1🥰1👏1