የአምስት አመቱ የጁንታው ታጋች ህጻን
👉ከጁንታው ታጋቾች ውስጥ መንታ ልጆችን የተገላገለች እናት ለማመን የሚከብድ ስቃይ አሳልፋለች፤
👉በቀን የሚሰጠው አንዲት ዳቦ እና ጥቂት ውሃ ብቻ ነበር፤
**************************
( ኢ ፕ ድ)
ቢንያም ጌታቸው ገና አፉን በቅጡ ያልፈታ ህጻን ነው። አባቱ ምክትል መቶ አለቃ ጌታቸው ቦሮዳ የሰሜን እዝ ሰራዊት አባል ነው፡፡ መቶ አለቃ ጌታቸው ልጁን መስከረም 17 ቀን ወደሚኖርበት የመከላከያ ካምፕ አመጣው። የአባት ሃሳብ የነበረው የልጁን አይን አሳክሞ እረፍት እንዲያገኝ ነበር። ይህ የአባት ሃሳብ ግን ሳይሆን ቀረ፤ ያልታሰበው የጁንታው ጥቃት በሰራዊቱ ላይ ተፈጸመ።
የጁንታው ታጣቂዎች ሰራዊቱ ላይ ጥቃት ፈጽመው በርካቶችን ሲያፍኑ ህጻን ቢንያምም ከአባቱ ጋር ታገተ፡፡ በእገታው ወቅት ጁንታው የሚያቀርበው ምግብ ለህጻን ቢኒያም ተጨማሪ ፈተና ነበር፡፡ በቀን የሚሰጣቸው አንድ ዳቦ እና ጥቂት ውሃ ህጻኑን በምግብ እጥረት ሠውነቱ እንዲጎዳ አድርጎታል፡፡
የታገቱ የመከላከያ ሠራዊት መኮንኖች እና አዛዦች ከቢኒያም አባት ጋር እየተጋገዙ በእግራቸው ቢኒያምን በትከሻ ተሸክመው በረሃውን ያለ በቂ ምግብና ውሃ ለቀናት እንዲጓዙ ተፈርዶባቸዋል። የጁንታው አባላት በወቅቱ በተሽከርካሪያቸው ውስጥ ሆነው አቧራውን ታጋቾች ላይ እያቦነኑ ሲጓዙ ምክትል መቶ አለቃ ጌታቸው ቦሮዳ ልጁን አስቀምጦት ከታጋቾቹ ጋር አብሮ እንዲሄድ ይጠይቁታል።
የተሽከርካሪ ጋቢና ውስጥ አድርገው እዚሁ ይደር አሉት። ይህንን ሃሳብ ያልተቀበለው አባትም የበኩር ልጁን አንጠልጥሎ የድካም ጉዞውን ገፋበት። ህጻን ቢንያም ገና በለጋ እድሜው ከጦርነት አውድማ መሃል ገብቶ የተኩስ ድምጹንም ሆነ የፈንጂ አይነቶችንም ፊት ለፊት መጋፈጡ አይቀሬ ሆነ። የጁንታው ታጣቂዎች ሲታኮሡ የአየር ሃይል ድሮኖች እና ሄሊኮፐተሮች በሰማይ ሆነው እርምጃ ሲወስዱም ተመልክቷል።
ህጻን ቢንያም በዚህ እድሜው አሻንጉሊት ይዞ መጫወት እና ከእድሜ እኩዮቹ ጋር መቦረቅ ቢሆንም ፍላጎቱ በጁንታው እኩይ አላማ ግን ከአባቱ ጋር ታግቶ መራር ቀናትን ለማሳለፍ ተገዷል። ምን እየተፈጠረ እንዳለ እንኳን በውል የማያውቀው ህጻን በአቧራው እና በፀሐዩ የቀሉ አይኖቹን እያሸ ከታገቱ የመከላከያ መኮንኖች ጋር ችግሩ ተጋፍጧል፡፡
በወዲያኛው ማዶ ደግሞ ሌላም ግፍ አለ። አንዲት እናት መንታ ልጆችን ተገላግላ ልጆቿን ይዛ ለማመን የሚከብድ ስቃይ ስታሳልፍ ነበር። ለሀጻናቱ እንኳን ያልራሩት የጁንታው አባላት ወላጆቹን እንኳን ከእገታው ነጥለው ወደሰላማዊ ቦታ ለመላክ ቅንጣት ታክል ርህራሄንእንዳላሣዩ መቶ አለቃ ጌታቸው ይናገራል፡፡
በጁንታው የታገቱ የሰራዊት መኮንኖች ህጻን ቢንያምን እና አባቱን እያበረታቱ ዳገት ቁልቁለቱን፣ ወንዝ ጢሻውን እያቋረጡ አዴት ከተባለ ስፍራ ደረሱ። በወቅቱ የነበረው ሁኔታ መቶ አለቃ ጌታቸው እንዲህ ያስታውሳል፤ “ ህጻኑ ሄሊኮፕተሯን ግዳጅ ስትፈጽም አይቶ ‘አባዬ ምንድነው? አለኝ፡፡ ዶክተር ዐብይ ልኮልን ነው፣ ከዚህ ልትወስደን ነው አልኩት፡፡ ኦፕሬሽኑ ሲጀመር ልጄን ይዤ ከለላ ያዝኩ” ይላል፡፡
በመጨረሻም የመከላከያ ሰራዊት እና የአየር ሃይል በተቀናጀ እና ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ የጁንታው አባላት ላይ በወሰዱት እርምጃ የጁንታው ታጣቂዎች በየቦታው ተበታተኑ። አዴት ላይ ለቀናት የታገቱት ህጻን ቢንያም እና አባቱን ጨምሮ ከአንድ ሺህ በላይ መኮንኖች በጀግናው የመከላከያ ሠራዊታችን ነጻ ወጡ።
"በአፈናው ወቅት ሰራዊቱ ለህጻን ልጄ ያደረገው ድጋፍ እና እንክብካቤ ትልቅ ነው" የሚለው ምክትል መቶ አለቃ ጌተቸው፤ "የሀገር አደራ አለብኝና ልጄን አስተምሬ ለቁም ነገር ለማብቃት የማላደርገው ጥረት የለም" ሲል ተናግሯል።
ሁኔታውን አልፎ ሲያወሩት ቀልድ ይመስላል የሚለው ምክትል መቶ አለቃ ጌታቸው፤ ሰራዊቱ ለወሰደው ወገን የማዳን የጥንቃቄ እርምጃ ከፍ ያለ ምስጋናውን አቅርቧል። ህጻን ቢንያምም "ዶክተር ዐብይን ነው የምወደው፤ የእኛ መከላከያ ነው ያዳነን" ሲል በስፍራው ለሚገኘው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘጋቢ በሚኮላተፍ አንደበቱ ነግሮታል፡፡
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው የህግ ማስከበር ዘመቻውን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ ወንጀለኛው ጁንታ ከታጋች የሰራዊቱ መኮንኖች ባሻገር ሴቶችና ህጻናትን አግቶ መያዙን ገልጸዋል፡፡ ለዚህም ታጋቾቹን ከጁንታው በመነጠል ተጨማሪ ጉዳት ሳይደርስ ኦፕሬሽኑን ለማካሄድ መንግስታቸው በትኩረት እየሰራ መሆኑን መግላጻቸው ይታወሳል፡፡
👉ከጁንታው ታጋቾች ውስጥ መንታ ልጆችን የተገላገለች እናት ለማመን የሚከብድ ስቃይ አሳልፋለች፤
👉በቀን የሚሰጠው አንዲት ዳቦ እና ጥቂት ውሃ ብቻ ነበር፤
**************************
( ኢ ፕ ድ)
ቢንያም ጌታቸው ገና አፉን በቅጡ ያልፈታ ህጻን ነው። አባቱ ምክትል መቶ አለቃ ጌታቸው ቦሮዳ የሰሜን እዝ ሰራዊት አባል ነው፡፡ መቶ አለቃ ጌታቸው ልጁን መስከረም 17 ቀን ወደሚኖርበት የመከላከያ ካምፕ አመጣው። የአባት ሃሳብ የነበረው የልጁን አይን አሳክሞ እረፍት እንዲያገኝ ነበር። ይህ የአባት ሃሳብ ግን ሳይሆን ቀረ፤ ያልታሰበው የጁንታው ጥቃት በሰራዊቱ ላይ ተፈጸመ።
የጁንታው ታጣቂዎች ሰራዊቱ ላይ ጥቃት ፈጽመው በርካቶችን ሲያፍኑ ህጻን ቢንያምም ከአባቱ ጋር ታገተ፡፡ በእገታው ወቅት ጁንታው የሚያቀርበው ምግብ ለህጻን ቢኒያም ተጨማሪ ፈተና ነበር፡፡ በቀን የሚሰጣቸው አንድ ዳቦ እና ጥቂት ውሃ ህጻኑን በምግብ እጥረት ሠውነቱ እንዲጎዳ አድርጎታል፡፡
የታገቱ የመከላከያ ሠራዊት መኮንኖች እና አዛዦች ከቢኒያም አባት ጋር እየተጋገዙ በእግራቸው ቢኒያምን በትከሻ ተሸክመው በረሃውን ያለ በቂ ምግብና ውሃ ለቀናት እንዲጓዙ ተፈርዶባቸዋል። የጁንታው አባላት በወቅቱ በተሽከርካሪያቸው ውስጥ ሆነው አቧራውን ታጋቾች ላይ እያቦነኑ ሲጓዙ ምክትል መቶ አለቃ ጌታቸው ቦሮዳ ልጁን አስቀምጦት ከታጋቾቹ ጋር አብሮ እንዲሄድ ይጠይቁታል።
የተሽከርካሪ ጋቢና ውስጥ አድርገው እዚሁ ይደር አሉት። ይህንን ሃሳብ ያልተቀበለው አባትም የበኩር ልጁን አንጠልጥሎ የድካም ጉዞውን ገፋበት። ህጻን ቢንያም ገና በለጋ እድሜው ከጦርነት አውድማ መሃል ገብቶ የተኩስ ድምጹንም ሆነ የፈንጂ አይነቶችንም ፊት ለፊት መጋፈጡ አይቀሬ ሆነ። የጁንታው ታጣቂዎች ሲታኮሡ የአየር ሃይል ድሮኖች እና ሄሊኮፐተሮች በሰማይ ሆነው እርምጃ ሲወስዱም ተመልክቷል።
ህጻን ቢንያም በዚህ እድሜው አሻንጉሊት ይዞ መጫወት እና ከእድሜ እኩዮቹ ጋር መቦረቅ ቢሆንም ፍላጎቱ በጁንታው እኩይ አላማ ግን ከአባቱ ጋር ታግቶ መራር ቀናትን ለማሳለፍ ተገዷል። ምን እየተፈጠረ እንዳለ እንኳን በውል የማያውቀው ህጻን በአቧራው እና በፀሐዩ የቀሉ አይኖቹን እያሸ ከታገቱ የመከላከያ መኮንኖች ጋር ችግሩ ተጋፍጧል፡፡
በወዲያኛው ማዶ ደግሞ ሌላም ግፍ አለ። አንዲት እናት መንታ ልጆችን ተገላግላ ልጆቿን ይዛ ለማመን የሚከብድ ስቃይ ስታሳልፍ ነበር። ለሀጻናቱ እንኳን ያልራሩት የጁንታው አባላት ወላጆቹን እንኳን ከእገታው ነጥለው ወደሰላማዊ ቦታ ለመላክ ቅንጣት ታክል ርህራሄንእንዳላሣዩ መቶ አለቃ ጌታቸው ይናገራል፡፡
በጁንታው የታገቱ የሰራዊት መኮንኖች ህጻን ቢንያምን እና አባቱን እያበረታቱ ዳገት ቁልቁለቱን፣ ወንዝ ጢሻውን እያቋረጡ አዴት ከተባለ ስፍራ ደረሱ። በወቅቱ የነበረው ሁኔታ መቶ አለቃ ጌታቸው እንዲህ ያስታውሳል፤ “ ህጻኑ ሄሊኮፕተሯን ግዳጅ ስትፈጽም አይቶ ‘አባዬ ምንድነው? አለኝ፡፡ ዶክተር ዐብይ ልኮልን ነው፣ ከዚህ ልትወስደን ነው አልኩት፡፡ ኦፕሬሽኑ ሲጀመር ልጄን ይዤ ከለላ ያዝኩ” ይላል፡፡
በመጨረሻም የመከላከያ ሰራዊት እና የአየር ሃይል በተቀናጀ እና ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ የጁንታው አባላት ላይ በወሰዱት እርምጃ የጁንታው ታጣቂዎች በየቦታው ተበታተኑ። አዴት ላይ ለቀናት የታገቱት ህጻን ቢንያም እና አባቱን ጨምሮ ከአንድ ሺህ በላይ መኮንኖች በጀግናው የመከላከያ ሠራዊታችን ነጻ ወጡ።
"በአፈናው ወቅት ሰራዊቱ ለህጻን ልጄ ያደረገው ድጋፍ እና እንክብካቤ ትልቅ ነው" የሚለው ምክትል መቶ አለቃ ጌተቸው፤ "የሀገር አደራ አለብኝና ልጄን አስተምሬ ለቁም ነገር ለማብቃት የማላደርገው ጥረት የለም" ሲል ተናግሯል።
ሁኔታውን አልፎ ሲያወሩት ቀልድ ይመስላል የሚለው ምክትል መቶ አለቃ ጌታቸው፤ ሰራዊቱ ለወሰደው ወገን የማዳን የጥንቃቄ እርምጃ ከፍ ያለ ምስጋናውን አቅርቧል። ህጻን ቢንያምም "ዶክተር ዐብይን ነው የምወደው፤ የእኛ መከላከያ ነው ያዳነን" ሲል በስፍራው ለሚገኘው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘጋቢ በሚኮላተፍ አንደበቱ ነግሮታል፡፡
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው የህግ ማስከበር ዘመቻውን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ ወንጀለኛው ጁንታ ከታጋች የሰራዊቱ መኮንኖች ባሻገር ሴቶችና ህጻናትን አግቶ መያዙን ገልጸዋል፡፡ ለዚህም ታጋቾቹን ከጁንታው በመነጠል ተጨማሪ ጉዳት ሳይደርስ ኦፕሬሽኑን ለማካሄድ መንግስታቸው በትኩረት እየሰራ መሆኑን መግላጻቸው ይታወሳል፡፡
በመቐለ ከተማ ጁንታው ቀብሮት የነበረ 13 የነዳጅ ታንከር ተገኘ
******************
(ኢ.ፕ.ድ)
በመቐለ ከተማ ልዩ ስሙ ገብርኤል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ጁንታው ለጦርነት ዓላማ ሊያውለው በድብቅ ቀብሮት የነበረ 13 የነዳጅ ታንከር ተገኘ።
በታንከሩም ከ200 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ መገኘቱ ታውቋል።
በመከላከያ ሰራዊት የ25ኛ ፈንቅል ክፍለ ጦር 2ኛ ብርጌድ 1ኛ ሻለቃ ምክትል ኦፕሬሽናል አዛዥ ሻምበል ዮሐንስ ማቲዎስ እንዳስታወቁት፣ ጁንታው ለጦርነት ዓላማ አስቦ በድብቅ ቀብሮት የነበረው 13 የነዳጅ ታንከር በመከላከያ ሰራዊቱ አሰሳ በቁጥጥር ውሏል፡፡
ጁንታው የትግራይ ህዝብ በነዳጅ እጥረት እንዲቸገር በማድረግ ዘርፎ ለራሱ እኩይ አላማ ቀብሮት ቆይቷል ብለዋል።
ሆኖም ጥቅመኛው ሃይል የደበቀው ታንከር እንዲገኝ የአካባቢው ማህበረሰብ ከፍተኛ አስተዋፆ አድርጓል ብለዋል።
በአከባቢው ተቀብሮ ለነዳጅ ማጠራቀሚያ ሊውል የነበረ ተጨማሪ ዘጠኝ ታንከር መገኘቱንም ሻምበል ዮሐንስ ገልጸዋል፡፡
የህወሃት ጁንታ ለራሱ ጥቅም ብቻ የቆመ የህዝብ ጠላት መሆኑን የሚያረጋግጡ የተለያዩ ተጨባጭ ማስረጃዎች እየተገኙ ስለመሆኑም አብራርተዋል።
በመቐለ በተደረገው አሰሳ ለህገ ወጥ ተግባር ሊውሉ የነበሩ ቁሳቁሶች መያዛቸውን እንደገለጹ ኢዜአ ዘግቧል፡፡
******************
(ኢ.ፕ.ድ)
በመቐለ ከተማ ልዩ ስሙ ገብርኤል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ጁንታው ለጦርነት ዓላማ ሊያውለው በድብቅ ቀብሮት የነበረ 13 የነዳጅ ታንከር ተገኘ።
በታንከሩም ከ200 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ መገኘቱ ታውቋል።
በመከላከያ ሰራዊት የ25ኛ ፈንቅል ክፍለ ጦር 2ኛ ብርጌድ 1ኛ ሻለቃ ምክትል ኦፕሬሽናል አዛዥ ሻምበል ዮሐንስ ማቲዎስ እንዳስታወቁት፣ ጁንታው ለጦርነት ዓላማ አስቦ በድብቅ ቀብሮት የነበረው 13 የነዳጅ ታንከር በመከላከያ ሰራዊቱ አሰሳ በቁጥጥር ውሏል፡፡
ጁንታው የትግራይ ህዝብ በነዳጅ እጥረት እንዲቸገር በማድረግ ዘርፎ ለራሱ እኩይ አላማ ቀብሮት ቆይቷል ብለዋል።
ሆኖም ጥቅመኛው ሃይል የደበቀው ታንከር እንዲገኝ የአካባቢው ማህበረሰብ ከፍተኛ አስተዋፆ አድርጓል ብለዋል።
በአከባቢው ተቀብሮ ለነዳጅ ማጠራቀሚያ ሊውል የነበረ ተጨማሪ ዘጠኝ ታንከር መገኘቱንም ሻምበል ዮሐንስ ገልጸዋል፡፡
የህወሃት ጁንታ ለራሱ ጥቅም ብቻ የቆመ የህዝብ ጠላት መሆኑን የሚያረጋግጡ የተለያዩ ተጨባጭ ማስረጃዎች እየተገኙ ስለመሆኑም አብራርተዋል።
በመቐለ በተደረገው አሰሳ ለህገ ወጥ ተግባር ሊውሉ የነበሩ ቁሳቁሶች መያዛቸውን እንደገለጹ ኢዜአ ዘግቧል፡፡
ለቀጣይ አራት ወራት የሚቆይ የወጣቶች የአረንጓዴ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ ስራ በአዲስ አበባ ተጀመረ
****************************
(ኢ ፕ ድ)
በአዲስ አበባ ከተማ ለቀጣይ አራት ወራት የሚቆይ የወጣቶች የአረንጓዴ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ ስራን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ አስጀምረዋል።
በመርሐግብሩ ማስጀመሪያ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ እንደገለፁት አዲስ አበባ ከተማ የቱሪስት መዳረሻ እንድትሆን እና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን ለማሳደግ ውብ፣ጽዱ እና ለኑሮ ምቹ መሆን ይኖርበታል ብለዋል ።
በቀጣይ አራት ወራት በሚቆየው የወጣቶች የአረንጓዴ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ የበጎፍቃድ አገልግሎት ከ28ሺህ በላይ ሴቶች እና ወጣቶች በሣምንት ሁለት ቀናት እንደሚሳተፉ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ተናግረዋል ።
አዲስ አበባ ከተማ የአፍሪካ መዲናነቷን ፣የቱሪዝም እና የዲፕሎማቲክ ማዕከልነቷን ለማስጠበቅ በሚደረገው ጥረት ሁሉም ነዋሪዎች ጽዳቷን በመጠበቅ ድርሻቸውን እንዲወጡ ምክትል ከንቲባዋ ጥሪ አቅርበዋል ።
በአዲስ አበባ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ እና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን አስተባባሪነት በሁሉም ክፍለ ከተሞች ሴቶች፣ ወጣቶች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በችግኝ እንክብካቤ በአረንጓዴ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ ስራ የሚከናወን መሆኑን የአዲስ አበባ ፕሬስ ሰክሬታሪያት ገልጿል፡፡
****************************
(ኢ ፕ ድ)
በአዲስ አበባ ከተማ ለቀጣይ አራት ወራት የሚቆይ የወጣቶች የአረንጓዴ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ ስራን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ አስጀምረዋል።
በመርሐግብሩ ማስጀመሪያ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ እንደገለፁት አዲስ አበባ ከተማ የቱሪስት መዳረሻ እንድትሆን እና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን ለማሳደግ ውብ፣ጽዱ እና ለኑሮ ምቹ መሆን ይኖርበታል ብለዋል ።
በቀጣይ አራት ወራት በሚቆየው የወጣቶች የአረንጓዴ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ የበጎፍቃድ አገልግሎት ከ28ሺህ በላይ ሴቶች እና ወጣቶች በሣምንት ሁለት ቀናት እንደሚሳተፉ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ተናግረዋል ።
አዲስ አበባ ከተማ የአፍሪካ መዲናነቷን ፣የቱሪዝም እና የዲፕሎማቲክ ማዕከልነቷን ለማስጠበቅ በሚደረገው ጥረት ሁሉም ነዋሪዎች ጽዳቷን በመጠበቅ ድርሻቸውን እንዲወጡ ምክትል ከንቲባዋ ጥሪ አቅርበዋል ።
በአዲስ አበባ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ እና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን አስተባባሪነት በሁሉም ክፍለ ከተሞች ሴቶች፣ ወጣቶች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በችግኝ እንክብካቤ በአረንጓዴ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ ስራ የሚከናወን መሆኑን የአዲስ አበባ ፕሬስ ሰክሬታሪያት ገልጿል፡፡
“አሁን ያለችው ትግራይ 95 በመቶ ህግና ሥርዓት የተተገበረባት ናት ”
-አቶ ሊላይ ኃይለማርያም፣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ከፍተኛ አመራር
************************
(ኢ ፕ ድ)
አሁን ላይ ያለችው ትግራይ የአምባገነኑ ጁንታ እንቅስቃሴ እምብዛም የማይታይባት 95 በመቶ ህግና ሥርዓት የተተገበረባት መሆኗን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ ሊላይ ኃይለማርያም ተናገሩ።
የህወሓት ጁንታ ከአሁን በኋላ እንደማይመለስና ለመጨረሻ ጊዜ ወደ ገሀነም መውረዱን በመገንዘብም ደጋፊዎችና አባሎቻቸው ወደ ህዝባቸው ተመልሰው ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲመሰርቱና በጋራ አገር ግንባታ ውስጥ እንዲሳተፉም ጥሪ አቅርበዋል።
አቶ ሊላይ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ አሁን ትግራይ በአጠቃላይ 95 በመቶ ህግና ሥርዓት የተተገበረባት ሆናለች። የአምባገነኑ ጁንታ እንቅስቃሴ የሚታይበት ሁኔታ ብዙም የለም። አውሮፕላንን ጨምሮ ትራንስፖርት ከጫፍ እስከ ጫፍ ይንቀሳቀሳል።
መብራት እስከ አዲግራት እየሠራ ሲሆን፤ በዚህ ሳምንት ዓደዋና አክሱም ይገባል። አብዛኛው ከተሞችም መብራት ያገኛሉ። የውሃና የኔትዎርክ አገልግሎትም እየተዳረሱ ነው። በሚቀጥለው ሳምንትም የባንክ አገልግሎት በሰፊው ይጀመራል።
መቀሌም በጥሩ እንቅስቃሴ ውስጥ ነው ያለችው። ወደ ቀደመ መልኳ ተቀይራለች።
የመንግሥት ተቋማት አገልግሎት እንዲሰጡ ከማድረግ አንጻር መቶ በመቶ እንዲከፈቱ ተደርገዋል። በሰለማዊ መንገድ የሚንቀሳቀሰው ሁሉም ሰው ወደ ሥራ ገበታው ገብቷል።
ጥሪውን ተቀብለው ወደ ሥራ ያልገቡ ሠራተኞች ላይ በአገሪቷ ህግ መሠረት ዕርምጃ ይወሰዳል። ይሄ ደግሞ የተሾሙት ካቢኔዎች ኃላፊነት ነው። ትጥቅን የማስፈታት እንቅስቃሴውም በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል። ታጥቆ የነበረው ትጥቅ በየቦታው እየተፈታ ነው።
https://www.press.et/Ama/?p=37618
-አቶ ሊላይ ኃይለማርያም፣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ከፍተኛ አመራር
************************
(ኢ ፕ ድ)
አሁን ላይ ያለችው ትግራይ የአምባገነኑ ጁንታ እንቅስቃሴ እምብዛም የማይታይባት 95 በመቶ ህግና ሥርዓት የተተገበረባት መሆኗን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ ሊላይ ኃይለማርያም ተናገሩ።
የህወሓት ጁንታ ከአሁን በኋላ እንደማይመለስና ለመጨረሻ ጊዜ ወደ ገሀነም መውረዱን በመገንዘብም ደጋፊዎችና አባሎቻቸው ወደ ህዝባቸው ተመልሰው ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲመሰርቱና በጋራ አገር ግንባታ ውስጥ እንዲሳተፉም ጥሪ አቅርበዋል።
አቶ ሊላይ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ አሁን ትግራይ በአጠቃላይ 95 በመቶ ህግና ሥርዓት የተተገበረባት ሆናለች። የአምባገነኑ ጁንታ እንቅስቃሴ የሚታይበት ሁኔታ ብዙም የለም። አውሮፕላንን ጨምሮ ትራንስፖርት ከጫፍ እስከ ጫፍ ይንቀሳቀሳል።
መብራት እስከ አዲግራት እየሠራ ሲሆን፤ በዚህ ሳምንት ዓደዋና አክሱም ይገባል። አብዛኛው ከተሞችም መብራት ያገኛሉ። የውሃና የኔትዎርክ አገልግሎትም እየተዳረሱ ነው። በሚቀጥለው ሳምንትም የባንክ አገልግሎት በሰፊው ይጀመራል።
መቀሌም በጥሩ እንቅስቃሴ ውስጥ ነው ያለችው። ወደ ቀደመ መልኳ ተቀይራለች።
የመንግሥት ተቋማት አገልግሎት እንዲሰጡ ከማድረግ አንጻር መቶ በመቶ እንዲከፈቱ ተደርገዋል። በሰለማዊ መንገድ የሚንቀሳቀሰው ሁሉም ሰው ወደ ሥራ ገበታው ገብቷል።
ጥሪውን ተቀብለው ወደ ሥራ ያልገቡ ሠራተኞች ላይ በአገሪቷ ህግ መሠረት ዕርምጃ ይወሰዳል። ይሄ ደግሞ የተሾሙት ካቢኔዎች ኃላፊነት ነው። ትጥቅን የማስፈታት እንቅስቃሴውም በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል። ታጥቆ የነበረው ትጥቅ በየቦታው እየተፈታ ነው።
https://www.press.et/Ama/?p=37618
www.press.et
“አሁን ያለችው ትግራይ 95 በመቶ ህግና ሥርዓት የተተገበረባት ናት ” -አቶ ሊላይ ኃይለማርያም፣ የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት ከፍተኛ አስተዳደር | የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት
የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የቆየዉን መደበኛ ስብሰባ አጠናቀቀ
*****^^***********
(ኢ.ፕ.ድ)
የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ከታህሳስ 8 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የቆየዉን መደበኛ ስብሰባ አጠናቋል፡፡
ኮሚቴዉ በሰላም፣ በልማት፣ በዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታና መጪዉን አገራዊ ምርጫ በተመለከቱ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት ተወያይቶ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል፡፡
በዋናነት ባለፉት ሁለት አመታት ተኩል በአገራችን የታየዉ ለዉጥ በርካታ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፈተናዎችን ተጋፍጦ የአገራችንን ብልጽግና እዉን ለማደረግ ሰፊ እድል የፈጠረና አገራችንን ከብተና አደጋ ያዳነ መሆኑ በዉይይቱ ከስምምነት ተደርሷል፡፡
በተለይም ብልጽግና ዉሁድ ህብረ ብሄራዊ አገራዊ ፓርቲ ሆኖ መደራጀቱ አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ለመገንባት ከፍተኛ እድል ከመፍጠሩም በላይ ከአገሪቱ ፖለቲካዊ ተሳትፎ ተገለዉ የዳር ተመልካች የነበሩ በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለማቀፍና ለማሳተፍ የቻለ የመጪዉ ትዉልድ ፓርቲ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡
በአገራዊ ለዉጡ የተገኙ ድሎችን ጠብቆ በማስቀጠል ወደ ሁለንተናዊ ብልጽግና ማሳደግ እንደሚያስፈልግ የተገለጸ ሲሆን ለዚህም የፓርቲዉን መርሆዎች፣ እሴቶችና አሰራሮችን በጥብቅ ዲሲፕሊን ተግባራዊ ማድረግና ጠንካራ ተቋማዊ ባህል መገንባት አስፈላጊ መሆኑ ከስምምነት ተደርሷል፡፡
ኮሚቴዉ በሁለቱ ቀናት መደበኛ ስብሰባዉ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ የሚከተሉትን አቅጣጫዎች አስቀምጧል፡፡
1. አገራችንን ለመበታተን በከፍተኛ ሁኔታ ሲዘጋጅ ቆይቶ ፍጹም አረመኔያዊ በሆነ መልኩ በአገር መከላከያ ሰራዊታችን ላይ ጥቃት መሰንዘሩ ይታወቃል፡፡ ይህ ስግብግብ ጁንታ በአጭር ጊዜ እንዲፈርስና አገራችን ከዚህ ከሃዲ ሃይል ነጻ እንድትወጣ ጀግናዉ መከላከያ ሰራዊታችን፣ የአማራና አፋር ክልሎች ልዩ ሃይልና ሚሊሻ እንዲሁም በተለያየ ደረጃ ድጋፍ ላደረጉ መላዉ የሀገራችን ህዝቦች ታላቅ ምስጋና እናቀርባለን፡፡ ጀግንነት ልምዳችን ስለሆነ በዚህ ድል ሳንኩራራ ይህንን አገራዊ የአንድነት ስሜትና ቁርጠኝነት በሌሎች የልማት ዘርፎችም በመድገም የአገራችንን ብልጽግና ለማረጋገጥ ርብርብ እንዲደረግ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
2. የወንጀለኛዉን ከሃዲ ጁንታ አባላት ከተደበቁበት አድኖ ለፍርድ ለማቅረብ ከሚደረገዉ ርብርብ ጎን ለጎን በህግ ማስከበር እርምጃው ሂደት ውስጥ የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቀዬያቸዉ ተመልሰዉ እንዲቋቋሙና እብሪተኛው ጁንታ ያፈራረሳቸዉ የህዝብ መሰረተ ልማቶች በፍጥነት ተጠግነዉ ለአገልግሎት እንዲውሉ ለማድረግ የተጀመረዉ ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡ በትግራይ ክልል የህዝብ አገልግሎቶችን ለማስጀመር፣ የእለት ደራሽ ሰብዓዊ አገልግሎቶችን በፍጥነት ለማድረስና ህብረተሰቡ ወደ መደበኛ የእለት ተእለት ህይወቱ እንዲመለስ በሚደረገዉ ርብርብ ዉስጥ የፓርቲዉ አመራሮች፣ አባላት፣ ደጋፊዎችና መላዉ የአገራችን ህዝቦች የቻሉትን አስተዋጽዖ ሁሉ እንዲያደርጉ ኮሚቴዉ ጥሪ ያቀርባል፡፡
3. በኢትዮጵያ የሀገረ መንግስትና ብሄረ መንግስት ግንባታ ሂደት የተለያዩ የፖለቲካ ሃይል አሰላለፎች የሚታዩበት ነዉ፡፡ በአገራችን የሚታየዉን ዉስብስብ ብዝሃነት የሚያስተናግድ አገራዊ አንድነት ከመገንባት አንጻር በወንድማማችነት እሴት ላይ የተመሰረተ ህብረብሄራዊ አንድነትን የሚያረጋግጥ የፌዴራል ስርዓት ግንባታ እዉን እንዲሆን የፓርቲያችን አመራሮችና አባላት በቁርጠኝነት እንዲታገሉ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
4. በተለያዩ አካባቢዎች ህዝቦች የሚያነሷቸዉ የማንነት ጥያቄዎች ተገቢነት ያላቸዉ ፍትሃዊ የህዝብ ጥያቄዎች መሆናቸዉን ኮሚቴዉ ያምናል፡፡ እነዚህ ጥያቄዎች ነባራዊ ሁኔታዉን መሰረት በማድረግ የህዝቦችን ወንድማማችነትና አብሮነት እንዲሁም የህዝቡን ነጻ ፍላጎት ከግምት ባስገባ መልኩ ህጋዊ አሰራርን ተከትሎ ምላሸ እንዲሰጣቸዉ ኮሚቴዉ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
5. በተለያዩ የአገራችን አካባቢዎች በንጹሃን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ማንነትን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች በአፋጣኝ እንዲቆሙ ተገቢዉ እርምጃ ሁሉ እንዲወሰድ ኮሚቴዉ ከስምምነት ደርሷል፡፡ እነዚህን እኩይ ተግባራት የሚፈጽሙ የጥፋት ሀይሎች በቁጥጥር ሥር ለማዋልና እርምጃ ለመዉሰድ በሚደረገዉ ርብርብ በየደረጃዉ የሚገኙ የብልጽግና አመራሮች በከፍተኛ ጽናትና ቁርጠኝነት እንዲሰሩ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
6. የአገራችንን ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች ለመፍታት በሚደረጉ ጥረቶች በየትኛዉም ቦታ የሚገኙ የብልጽግና አመራሮችና አባላት ከሚለያዩ ጥቃቅን ጉዳዮች ወጥተዉ ከፍ ያለ አገራዊ እይታ በመያዝ ኢትዮጵያንና የሁሉንም ዜጎቿን ሁለንተናዊ ብልጽግና እዉን በሚያደርግ መልኩ እንዲደጋገፉ፣እንዲረዳዱ፣በአብሮነትና በትብብር መንፈስ መስራት እንደሚገባቸዉ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
7. በ2013 ዓ.ም የሚካሄደዉ ምርጫ አገራችን ወደ እዉነተኛ የዲሞክራሲ ስርዓት ለምታደርገዉ ሽግግር ያለዉ ትርጉም እጅግ ከፍተኛ መሆኑ ይታመናል፡፡ የሚካሄደዉ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ነጻና በሂደቱም ሆነ በዉጤቱ በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት ያለዉ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የብልጽግና አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች በከፍተኛ ቁርጠኝነት እንዲሰሩ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
8. ብልጽግና ፓርቲ በመጪዉ ምርጫ ጠንካራ ተወዳዳሪ ሆኖ በዉጤታማነት እንዲያጠናቅቅ በፓርቲዉ ማኒፌስቶ ላይ በጥልቀት ተወያይቶ አጽድቆታል፡፡ መላዉ የፓርቲዉ አመራሮችና አባላት የጸደቀዉን ማኒፌስቶ መሰረት በማድረግ አስፈላጊዉን ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
9. በአገራችን በህጋዊ መንገድ ተመዝግበዉ በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ወደ እዉነተኛ የዲሞክራሲ ስርዓት ለመሸጋገር የተወሰዱ የአገራዊ ለዉጥ እርምጃዎችን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም መጪዉ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ነጻና በሂደቱም ሆነ በዉጤቱ በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት ያለዉ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸዉን አስተዋጽዖ እንዲያደርጉ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
10. መላዉ የአገሪቱ ህዝቦች ባለፉት ሁለት ተኩል አመታት በኢትዮጵያ የታዩ ለዉጦችና የተገኙ ድሎች ተጠናክረዉ እንዲቀጥሉ፣መጪዉ አገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ነጻና ተቀባይነት ያለዉ ሆኖ እንዲጠናቀቅና የዜጎች ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ብልጽግና የተረጋገጠባት ጠንካራ አገር ለመገንባት በሚደረገዉ ርብርብ ዉስጥ የሚጠበቅባቸዉን አስተዋጽዖ ሁሉ እንዲያደርጉ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
ብልጽግና ፓርቲ
ታህሳስ 10 ቀን 2012 ዓ.ም
*****^^***********
(ኢ.ፕ.ድ)
የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ከታህሳስ 8 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የቆየዉን መደበኛ ስብሰባ አጠናቋል፡፡
ኮሚቴዉ በሰላም፣ በልማት፣ በዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታና መጪዉን አገራዊ ምርጫ በተመለከቱ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት ተወያይቶ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል፡፡
በዋናነት ባለፉት ሁለት አመታት ተኩል በአገራችን የታየዉ ለዉጥ በርካታ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፈተናዎችን ተጋፍጦ የአገራችንን ብልጽግና እዉን ለማደረግ ሰፊ እድል የፈጠረና አገራችንን ከብተና አደጋ ያዳነ መሆኑ በዉይይቱ ከስምምነት ተደርሷል፡፡
በተለይም ብልጽግና ዉሁድ ህብረ ብሄራዊ አገራዊ ፓርቲ ሆኖ መደራጀቱ አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ለመገንባት ከፍተኛ እድል ከመፍጠሩም በላይ ከአገሪቱ ፖለቲካዊ ተሳትፎ ተገለዉ የዳር ተመልካች የነበሩ በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለማቀፍና ለማሳተፍ የቻለ የመጪዉ ትዉልድ ፓርቲ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡
በአገራዊ ለዉጡ የተገኙ ድሎችን ጠብቆ በማስቀጠል ወደ ሁለንተናዊ ብልጽግና ማሳደግ እንደሚያስፈልግ የተገለጸ ሲሆን ለዚህም የፓርቲዉን መርሆዎች፣ እሴቶችና አሰራሮችን በጥብቅ ዲሲፕሊን ተግባራዊ ማድረግና ጠንካራ ተቋማዊ ባህል መገንባት አስፈላጊ መሆኑ ከስምምነት ተደርሷል፡፡
ኮሚቴዉ በሁለቱ ቀናት መደበኛ ስብሰባዉ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ የሚከተሉትን አቅጣጫዎች አስቀምጧል፡፡
1. አገራችንን ለመበታተን በከፍተኛ ሁኔታ ሲዘጋጅ ቆይቶ ፍጹም አረመኔያዊ በሆነ መልኩ በአገር መከላከያ ሰራዊታችን ላይ ጥቃት መሰንዘሩ ይታወቃል፡፡ ይህ ስግብግብ ጁንታ በአጭር ጊዜ እንዲፈርስና አገራችን ከዚህ ከሃዲ ሃይል ነጻ እንድትወጣ ጀግናዉ መከላከያ ሰራዊታችን፣ የአማራና አፋር ክልሎች ልዩ ሃይልና ሚሊሻ እንዲሁም በተለያየ ደረጃ ድጋፍ ላደረጉ መላዉ የሀገራችን ህዝቦች ታላቅ ምስጋና እናቀርባለን፡፡ ጀግንነት ልምዳችን ስለሆነ በዚህ ድል ሳንኩራራ ይህንን አገራዊ የአንድነት ስሜትና ቁርጠኝነት በሌሎች የልማት ዘርፎችም በመድገም የአገራችንን ብልጽግና ለማረጋገጥ ርብርብ እንዲደረግ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
2. የወንጀለኛዉን ከሃዲ ጁንታ አባላት ከተደበቁበት አድኖ ለፍርድ ለማቅረብ ከሚደረገዉ ርብርብ ጎን ለጎን በህግ ማስከበር እርምጃው ሂደት ውስጥ የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቀዬያቸዉ ተመልሰዉ እንዲቋቋሙና እብሪተኛው ጁንታ ያፈራረሳቸዉ የህዝብ መሰረተ ልማቶች በፍጥነት ተጠግነዉ ለአገልግሎት እንዲውሉ ለማድረግ የተጀመረዉ ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡ በትግራይ ክልል የህዝብ አገልግሎቶችን ለማስጀመር፣ የእለት ደራሽ ሰብዓዊ አገልግሎቶችን በፍጥነት ለማድረስና ህብረተሰቡ ወደ መደበኛ የእለት ተእለት ህይወቱ እንዲመለስ በሚደረገዉ ርብርብ ዉስጥ የፓርቲዉ አመራሮች፣ አባላት፣ ደጋፊዎችና መላዉ የአገራችን ህዝቦች የቻሉትን አስተዋጽዖ ሁሉ እንዲያደርጉ ኮሚቴዉ ጥሪ ያቀርባል፡፡
3. በኢትዮጵያ የሀገረ መንግስትና ብሄረ መንግስት ግንባታ ሂደት የተለያዩ የፖለቲካ ሃይል አሰላለፎች የሚታዩበት ነዉ፡፡ በአገራችን የሚታየዉን ዉስብስብ ብዝሃነት የሚያስተናግድ አገራዊ አንድነት ከመገንባት አንጻር በወንድማማችነት እሴት ላይ የተመሰረተ ህብረብሄራዊ አንድነትን የሚያረጋግጥ የፌዴራል ስርዓት ግንባታ እዉን እንዲሆን የፓርቲያችን አመራሮችና አባላት በቁርጠኝነት እንዲታገሉ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
4. በተለያዩ አካባቢዎች ህዝቦች የሚያነሷቸዉ የማንነት ጥያቄዎች ተገቢነት ያላቸዉ ፍትሃዊ የህዝብ ጥያቄዎች መሆናቸዉን ኮሚቴዉ ያምናል፡፡ እነዚህ ጥያቄዎች ነባራዊ ሁኔታዉን መሰረት በማድረግ የህዝቦችን ወንድማማችነትና አብሮነት እንዲሁም የህዝቡን ነጻ ፍላጎት ከግምት ባስገባ መልኩ ህጋዊ አሰራርን ተከትሎ ምላሸ እንዲሰጣቸዉ ኮሚቴዉ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
5. በተለያዩ የአገራችን አካባቢዎች በንጹሃን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ማንነትን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች በአፋጣኝ እንዲቆሙ ተገቢዉ እርምጃ ሁሉ እንዲወሰድ ኮሚቴዉ ከስምምነት ደርሷል፡፡ እነዚህን እኩይ ተግባራት የሚፈጽሙ የጥፋት ሀይሎች በቁጥጥር ሥር ለማዋልና እርምጃ ለመዉሰድ በሚደረገዉ ርብርብ በየደረጃዉ የሚገኙ የብልጽግና አመራሮች በከፍተኛ ጽናትና ቁርጠኝነት እንዲሰሩ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
6. የአገራችንን ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች ለመፍታት በሚደረጉ ጥረቶች በየትኛዉም ቦታ የሚገኙ የብልጽግና አመራሮችና አባላት ከሚለያዩ ጥቃቅን ጉዳዮች ወጥተዉ ከፍ ያለ አገራዊ እይታ በመያዝ ኢትዮጵያንና የሁሉንም ዜጎቿን ሁለንተናዊ ብልጽግና እዉን በሚያደርግ መልኩ እንዲደጋገፉ፣እንዲረዳዱ፣በአብሮነትና በትብብር መንፈስ መስራት እንደሚገባቸዉ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
7. በ2013 ዓ.ም የሚካሄደዉ ምርጫ አገራችን ወደ እዉነተኛ የዲሞክራሲ ስርዓት ለምታደርገዉ ሽግግር ያለዉ ትርጉም እጅግ ከፍተኛ መሆኑ ይታመናል፡፡ የሚካሄደዉ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ነጻና በሂደቱም ሆነ በዉጤቱ በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት ያለዉ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የብልጽግና አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች በከፍተኛ ቁርጠኝነት እንዲሰሩ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
8. ብልጽግና ፓርቲ በመጪዉ ምርጫ ጠንካራ ተወዳዳሪ ሆኖ በዉጤታማነት እንዲያጠናቅቅ በፓርቲዉ ማኒፌስቶ ላይ በጥልቀት ተወያይቶ አጽድቆታል፡፡ መላዉ የፓርቲዉ አመራሮችና አባላት የጸደቀዉን ማኒፌስቶ መሰረት በማድረግ አስፈላጊዉን ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
9. በአገራችን በህጋዊ መንገድ ተመዝግበዉ በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ወደ እዉነተኛ የዲሞክራሲ ስርዓት ለመሸጋገር የተወሰዱ የአገራዊ ለዉጥ እርምጃዎችን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም መጪዉ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ነጻና በሂደቱም ሆነ በዉጤቱ በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት ያለዉ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸዉን አስተዋጽዖ እንዲያደርጉ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
10. መላዉ የአገሪቱ ህዝቦች ባለፉት ሁለት ተኩል አመታት በኢትዮጵያ የታዩ ለዉጦችና የተገኙ ድሎች ተጠናክረዉ እንዲቀጥሉ፣መጪዉ አገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ነጻና ተቀባይነት ያለዉ ሆኖ እንዲጠናቀቅና የዜጎች ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ብልጽግና የተረጋገጠባት ጠንካራ አገር ለመገንባት በሚደረገዉ ርብርብ ዉስጥ የሚጠበቅባቸዉን አስተዋጽዖ ሁሉ እንዲያደርጉ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
ብልጽግና ፓርቲ
ታህሳስ 10 ቀን 2012 ዓ.ም
የህወሓት አመራሮች በስብሰባዎች ላይ ባለስልጣናትን ያሰልሉ ነበር- አምባሳደር ኩማ ደመቅሳ
--------------------------------------------------
(ኢ ፕ ድ)
የህወሓት አመራሮች በስብሰባዎች ጭምር ሰላይ በማስቀመጥ ባለስልጣናትን ያሰልሉ እንደነበር አምባሳደር ኩማ ደመቅሳ ተናገሩ፡፡
የህወሓት አመራሮች በማዕከላዊ ስበሰባዎች ጭምር ሰላይ ያስቀምጡ ነበር ያሉት አምባሳደር ኩማ፣ ጉንጭ አልፋና ተጠያቂነት የሌላቸው ስብሰባዎች ይበዙ እንደነበር እና ኦህዴድ በተገመገሙ አመራሮች እርምጃ ሲወስድ ጣልቃ በመግባት ይረብሹ እንደነበርም አስታውሰዋል፡፡
የህወሓት ዘራፊ ቡድን የቁልቁለት ጉዞን የጀመረው በ1993 ዓ.ም መሆኑንም አምባሳደር ኩማ ከዋልታ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስታውሰዋል፡፡
በ1983 ዓ.ም ወደ ስልጣን የመጣው ኢህአዴግ በህወሓት መሪነት ሶስት መሰረታዊ አላማዎችን አንግቦ መንገዱን ጀመሯል የሚሉት አምባሳደሩ፣ በሀገሪቱ ሰላምና መረጋጋት እንዲሁም ዴሞክራሲና ልማት ማረጋገጥ የቤት ስራው መሆኑን አስቀምጦ ሀገር መምራት ቢጀምርም ግልጽ የሆነ የርዕዮትዓለም ሳይኖረው ለአስር ዓመታት በጭፍን ሲጓዝ ነበር ብለዋል፡፡
ከ10 አመታት በኋላ በ1993 ዓ.ም ሰነዶች ተዘጋጅተው ለውይይት እንደቀረቡ ገልጸው፣ የውይይት ሃሳቡና ኢህአዴግ የሚመራበት ሰነድ በህወሓት ቡድኖች መሃል የልዩነት መስመር ማበጀቱን ጠቁመዋል፡፡
ዴሞክራሲን በሰነድ ከማስፈር ውጪ በተግባር የማያውቀው ህወሓት በሀገሪቱ ዴሞክራሲ እንዳይኖር አድርጓል ብለዋል፡፡ ይህ ደግሞ ውድቀቱን አፋጥኖታል፤ ሌሎችም ፓርቲዎችም ከህወሓት ውደቀት ሊማሩ ይገባል ብለዋል፡፡
--------------------------------------------------
(ኢ ፕ ድ)
የህወሓት አመራሮች በስብሰባዎች ጭምር ሰላይ በማስቀመጥ ባለስልጣናትን ያሰልሉ እንደነበር አምባሳደር ኩማ ደመቅሳ ተናገሩ፡፡
የህወሓት አመራሮች በማዕከላዊ ስበሰባዎች ጭምር ሰላይ ያስቀምጡ ነበር ያሉት አምባሳደር ኩማ፣ ጉንጭ አልፋና ተጠያቂነት የሌላቸው ስብሰባዎች ይበዙ እንደነበር እና ኦህዴድ በተገመገሙ አመራሮች እርምጃ ሲወስድ ጣልቃ በመግባት ይረብሹ እንደነበርም አስታውሰዋል፡፡
የህወሓት ዘራፊ ቡድን የቁልቁለት ጉዞን የጀመረው በ1993 ዓ.ም መሆኑንም አምባሳደር ኩማ ከዋልታ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስታውሰዋል፡፡
በ1983 ዓ.ም ወደ ስልጣን የመጣው ኢህአዴግ በህወሓት መሪነት ሶስት መሰረታዊ አላማዎችን አንግቦ መንገዱን ጀመሯል የሚሉት አምባሳደሩ፣ በሀገሪቱ ሰላምና መረጋጋት እንዲሁም ዴሞክራሲና ልማት ማረጋገጥ የቤት ስራው መሆኑን አስቀምጦ ሀገር መምራት ቢጀምርም ግልጽ የሆነ የርዕዮትዓለም ሳይኖረው ለአስር ዓመታት በጭፍን ሲጓዝ ነበር ብለዋል፡፡
ከ10 አመታት በኋላ በ1993 ዓ.ም ሰነዶች ተዘጋጅተው ለውይይት እንደቀረቡ ገልጸው፣ የውይይት ሃሳቡና ኢህአዴግ የሚመራበት ሰነድ በህወሓት ቡድኖች መሃል የልዩነት መስመር ማበጀቱን ጠቁመዋል፡፡
ዴሞክራሲን በሰነድ ከማስፈር ውጪ በተግባር የማያውቀው ህወሓት በሀገሪቱ ዴሞክራሲ እንዳይኖር አድርጓል ብለዋል፡፡ ይህ ደግሞ ውድቀቱን አፋጥኖታል፤ ሌሎችም ፓርቲዎችም ከህወሓት ውደቀት ሊማሩ ይገባል ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ሦስት ሳተላይቶችን ታመጥቃለች
*********************
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ለተለያየ አገልግሎቶች የሚውሉ ሦስት ሳተላይቶችን እንደምታመጥቅ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዲሳ ይልማ እንደገለፁት፤ በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ውስጥ ለተለያዩ አግልግሎቶች የሚውሉ ሦስት ሳተላይቶችን ለማምጠቅ ታቅዷል። በአሥር ዓመቱ ከሚመጥቁት ሳተላይቶች ውስጥ አንደኛው የኮሚዩንኬሽን እና ብሮድካስት ሲሆን፤ የተቀሩት ሁለቱ የመሬት ምልከታ ሳተላይቶች ናቸው።
እንደ ዋና ዳይሬክተሩ ገለፃ፤ የኮሚዩንኬሽን እና ብሮድካስት ሳተላይት የሚባለው በብሮድካስት ሚዲያዎች ለኢንተርኔት፣ ለስክልና ለኮሚዩንኬሽን አገልግሎት የሚውል ነው። በአሁኑ ሰዓት ሀገራችን እነዚህን አገልግሎቶች ከውጭ በመከራየት በሚሊዮን ዶላር የሚገመት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ታወጣለች።
ለአብነትም፣ ከብሮድካስቲንግ በዓመት እስከ አሥር ሚሊዮን ዶላር ወጪ ይደረጋል። ለቴሌ ኮሚዩንኬሽን ደግሞ በርካታ ሚሊዮን ዶላሮች ወጭ ይሆናሉ። ስለዚህ ሳተላይት የመገንባት እቅዱን በተግባር በማረጋገጥ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወጪን መቀነስ ተገቢ ነው።
https://www.press.et/Ama/?p=37690
*********************
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ለተለያየ አገልግሎቶች የሚውሉ ሦስት ሳተላይቶችን እንደምታመጥቅ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዲሳ ይልማ እንደገለፁት፤ በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ውስጥ ለተለያዩ አግልግሎቶች የሚውሉ ሦስት ሳተላይቶችን ለማምጠቅ ታቅዷል። በአሥር ዓመቱ ከሚመጥቁት ሳተላይቶች ውስጥ አንደኛው የኮሚዩንኬሽን እና ብሮድካስት ሲሆን፤ የተቀሩት ሁለቱ የመሬት ምልከታ ሳተላይቶች ናቸው።
እንደ ዋና ዳይሬክተሩ ገለፃ፤ የኮሚዩንኬሽን እና ብሮድካስት ሳተላይት የሚባለው በብሮድካስት ሚዲያዎች ለኢንተርኔት፣ ለስክልና ለኮሚዩንኬሽን አገልግሎት የሚውል ነው። በአሁኑ ሰዓት ሀገራችን እነዚህን አገልግሎቶች ከውጭ በመከራየት በሚሊዮን ዶላር የሚገመት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ታወጣለች።
ለአብነትም፣ ከብሮድካስቲንግ በዓመት እስከ አሥር ሚሊዮን ዶላር ወጪ ይደረጋል። ለቴሌ ኮሚዩንኬሽን ደግሞ በርካታ ሚሊዮን ዶላሮች ወጭ ይሆናሉ። ስለዚህ ሳተላይት የመገንባት እቅዱን በተግባር በማረጋገጥ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወጪን መቀነስ ተገቢ ነው።
https://www.press.et/Ama/?p=37690
www.press.et
ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ሦስት ሳተላይቶችን ታመጥቃለች | የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት
ለ30 አመታት አዲስ አበባ በሚገኘው የጣሊያን ኤምባሲ ተጠልለው የነበሩት የደርግ ባለስልጣናት የሞት ፍርድ ወደ እድሜ ልክ እስራት ተሻሻለላቸው
******************
(ኢ.ፕ.ድ)
ላለፉት 30 አመታት አዲስ አበባ በሚገኘው የጣሊያን ኤምባሲ ተጠልለው የነበሩት የደርግ ባለስልጣናት የሞት ፍርድ ወደ እድሜ ልክ እስራት እንደተሻሻለላቸው የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
በኤምባሲው ተጠልለው የነበሩት የደርግ ባለስልጣናት ሌተናል ኮለኔል ብርሃኑ ባየህና ሌተናል ጄነራል አዲስ ተድላ ሲሆኑ፤ በሁለቱም ላይ ተላልፎ የነበረው የሞት ፍርድ ወደ እድሜ ልክ እስራት እንደተሻሻለላቸው ነው ጽ/ቤቱ የገለጸው፡፡
ማሻሻያውንም ፕሬዝደንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ በፊርማቸው ማጽደቃቸው ተገልጿል፡፡
******************
(ኢ.ፕ.ድ)
ላለፉት 30 አመታት አዲስ አበባ በሚገኘው የጣሊያን ኤምባሲ ተጠልለው የነበሩት የደርግ ባለስልጣናት የሞት ፍርድ ወደ እድሜ ልክ እስራት እንደተሻሻለላቸው የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
በኤምባሲው ተጠልለው የነበሩት የደርግ ባለስልጣናት ሌተናል ኮለኔል ብርሃኑ ባየህና ሌተናል ጄነራል አዲስ ተድላ ሲሆኑ፤ በሁለቱም ላይ ተላልፎ የነበረው የሞት ፍርድ ወደ እድሜ ልክ እስራት እንደተሻሻለላቸው ነው ጽ/ቤቱ የገለጸው፡፡
ማሻሻያውንም ፕሬዝደንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ በፊርማቸው ማጽደቃቸው ተገልጿል፡፡
ኦነግ ሸኔን በመደምሰሱ ሂደት የህዝቡ ድጋፍ ትልቅ ድርሻ እንደነበረው ተገለጸ
***********************
(ኢ ፕ ድ)
በሰላም ለመታገል ወደ አገር ውስጥ ከገባ በኋላ ወደ ትጥቅ ትግል የተመለሰው ኦነግ ሸኔን በመደምሰስ ሂደት ህዝቡ ከጸጥታ አካሉ ጎን ሆኖ በአሰሳ እያገዘ፤ በሰላማዊ ሰልፍም ቡድኑን እያወገዘ መሆኑ ተገለጸ።
ከመስከረም 2013 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን በተወሰደው እርምጃ 846 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ሲደመሰሱ፤ ከ3ሺህ 700 በላይ ተጠርጣሪዎች በህግ ቁጥጥር ስር ሆነው ጉዳያቸው እየተጣራ መሆኑንም የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ መርዳሳ ተናግረዋል።
ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ የኦነግ ሸኔ ቡድን ኃይሉን ለማጠናከር በክልሉ ጠረፋማ አካባቢዎች ተደብቆ የጥፋት ኃይሎችን በመመልመል ሲያሰለጥን፤ እንዲሁም በህወሓት ጁንታ ኃይል የሎጀስቲክ ድጋፍ ተደርጎላቸው በትግራይ ክልል ጭምር በመሄድ ስልጠና ሲወስድ ነበር።
አሁን ላይ ግን ጁንታው በመደምሰሱ የቡድኑ ኃይል እየተዳከመ ከመሆኑ በተጨማሪ፤ ባለፉት ሦስት ወራት የክልሉ መንግሥት ህዝቡን በጎኑ በማሰለፍ በወሰደው እርምጃ 413 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች እጅ ባለመስጠታቸው ሲገደሉ፤ እጅ የሰጡና የተያዙ ደግሞ 433 ናቸው። በዚህም በጥቅሉ 846 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ተደምስሰዋል።
የኦነግ ሸኔ ቡድን እጅግ ጨካኝ ከመሆኑ የተነሳ ስልቱን በመቀያየር አንዳንድ አካባቢዎች እንደ ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ በብሔር ላይ ያነጣጠሩ ጥቃት ይፈጽማል፤ በምስራቅ ኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች ደግሞ ሀይማኖታዊ መልክ ያለው ጥቃት በመፈጸም አገርን ለማተራመስ ይጥራል። በዚህ መልኩ እስካሁን መንግሥት ሹመኞችና በንጹኃን ዜጎች ላይ በወሰዳቸው እርምጃዎችም ከ500 በላይ ንጹኃን ህይወታቸውን አጥተዋል።
አሁን ግን አንዳንድ እንደ ቄለም ወለጋ ያሉ አካባቢዎች ህዝቡ ወጥቶ አሰሳ እያደረገ፣ በሠላማዊ ሰልፍም እያወገዘ በመሆኑ እንደ ከዚህ በፊቱ ጉልበቱን አጠናክሮ የጥፋት ስራውን መፈጸም አይችልም። እንደከዚህ በፊቱም መንገድ ዝጉ እንዲ አድርጉ የሚሉ ትዕዛዞችን ህዝቡ እየተቀበለ አይደለም። የክልሉ ጸጥታ አካላትም ቡድኑ የሚንቀሳቀስበት አካባቢን ተቆጣጥረው እንዳሉ፤ እና ህዝቡም የጀመረውን ድጋፍ አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባው ነው ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ የተናገሩት።
https://www.press.et/Ama/?p=37765
***********************
(ኢ ፕ ድ)
በሰላም ለመታገል ወደ አገር ውስጥ ከገባ በኋላ ወደ ትጥቅ ትግል የተመለሰው ኦነግ ሸኔን በመደምሰስ ሂደት ህዝቡ ከጸጥታ አካሉ ጎን ሆኖ በአሰሳ እያገዘ፤ በሰላማዊ ሰልፍም ቡድኑን እያወገዘ መሆኑ ተገለጸ።
ከመስከረም 2013 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን በተወሰደው እርምጃ 846 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ሲደመሰሱ፤ ከ3ሺህ 700 በላይ ተጠርጣሪዎች በህግ ቁጥጥር ስር ሆነው ጉዳያቸው እየተጣራ መሆኑንም የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ መርዳሳ ተናግረዋል።
ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ የኦነግ ሸኔ ቡድን ኃይሉን ለማጠናከር በክልሉ ጠረፋማ አካባቢዎች ተደብቆ የጥፋት ኃይሎችን በመመልመል ሲያሰለጥን፤ እንዲሁም በህወሓት ጁንታ ኃይል የሎጀስቲክ ድጋፍ ተደርጎላቸው በትግራይ ክልል ጭምር በመሄድ ስልጠና ሲወስድ ነበር።
አሁን ላይ ግን ጁንታው በመደምሰሱ የቡድኑ ኃይል እየተዳከመ ከመሆኑ በተጨማሪ፤ ባለፉት ሦስት ወራት የክልሉ መንግሥት ህዝቡን በጎኑ በማሰለፍ በወሰደው እርምጃ 413 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች እጅ ባለመስጠታቸው ሲገደሉ፤ እጅ የሰጡና የተያዙ ደግሞ 433 ናቸው። በዚህም በጥቅሉ 846 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ተደምስሰዋል።
የኦነግ ሸኔ ቡድን እጅግ ጨካኝ ከመሆኑ የተነሳ ስልቱን በመቀያየር አንዳንድ አካባቢዎች እንደ ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ በብሔር ላይ ያነጣጠሩ ጥቃት ይፈጽማል፤ በምስራቅ ኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች ደግሞ ሀይማኖታዊ መልክ ያለው ጥቃት በመፈጸም አገርን ለማተራመስ ይጥራል። በዚህ መልኩ እስካሁን መንግሥት ሹመኞችና በንጹኃን ዜጎች ላይ በወሰዳቸው እርምጃዎችም ከ500 በላይ ንጹኃን ህይወታቸውን አጥተዋል።
አሁን ግን አንዳንድ እንደ ቄለም ወለጋ ያሉ አካባቢዎች ህዝቡ ወጥቶ አሰሳ እያደረገ፣ በሠላማዊ ሰልፍም እያወገዘ በመሆኑ እንደ ከዚህ በፊቱ ጉልበቱን አጠናክሮ የጥፋት ስራውን መፈጸም አይችልም። እንደከዚህ በፊቱም መንገድ ዝጉ እንዲ አድርጉ የሚሉ ትዕዛዞችን ህዝቡ እየተቀበለ አይደለም። የክልሉ ጸጥታ አካላትም ቡድኑ የሚንቀሳቀስበት አካባቢን ተቆጣጥረው እንዳሉ፤ እና ህዝቡም የጀመረውን ድጋፍ አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባው ነው ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ የተናገሩት።
https://www.press.et/Ama/?p=37765
የኢትዮጵያ መንግሥት በትግራይ ክልል የፈጸመው የህግ ማስከበር ሥራ የአገሪቱን አንድነትና መረጋጋት ለማረጋገጥ የወሰደው እርምጃ ነው ሲሉ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ተናገሩ
*************************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ መንግሥት በትግራይ የወሰደው የህግ ማስከበር እርምጃ የአገሪቱን አንድነትና መረጋጋት ለማረጋገጥ የወሰደው ነው ሲሉ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ተናገሩ።
ሙሳ ፋኪ ማሐማት ይህንን የተናገሩት ትናንት ጂቡቲ ውስጥ በተካሄደው የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) 38ኛ አስቸኳይ ስብሰባ ላይ ነው።
የሕብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር ጨምረውም የኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት የወሰደው እርምጃ "የአገሪቱን ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት ለማስከበር" መሆኑን ጠቅሰው፣ ይህም ሁሉም አገራት የሚጠበቅባቸው ሕጋዊ ኃላፊነት መሆኑንም አመልክተዋል።
ሙሳ ፋኪ እንዳሉት በዚህ በትግራይ ክልል ውስጥ የተከሰተውን ቀውስ ተከትሎ ከፍተኛ መጠን ያለው መፈናቀል መከሰቱን ገልጸው፤ በዚህ ረገድ ኢጋድ ለስደተኞችና ለተፈናቀሉ ሰዎች የተለየ ትኩረት በመስጠት ኢትዮጵያ ከምታደርገው የሰብአዊ ድጋፍ ጥረት ከጎኗ እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።
ኮሚሽነሩ ፋኪ ማሐማት ከዚህ በፊት፣ የፌደራል መንግሥቱና የትግራይ ክልል ወደ ድርድር እንዲመጡና ሰላማዊ መፍትሄ እንዲፈልጉ ጥሪ ማቅረባቸው ይታወሳል ሲል የዘገበው ቢቢሲ ነው።
ለአንድ ቀን በተካሄደው በዚህ ጉባኤ ላይ የተሳተፉት የኢጋድ አባል አገራት ከአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበር በተጨማሪ ለኢትዮጵያ መንግሥት ድጋፋቸውን መግለጻቸው ይታወቃል።
*************************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ መንግሥት በትግራይ የወሰደው የህግ ማስከበር እርምጃ የአገሪቱን አንድነትና መረጋጋት ለማረጋገጥ የወሰደው ነው ሲሉ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ተናገሩ።
ሙሳ ፋኪ ማሐማት ይህንን የተናገሩት ትናንት ጂቡቲ ውስጥ በተካሄደው የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) 38ኛ አስቸኳይ ስብሰባ ላይ ነው።
የሕብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር ጨምረውም የኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት የወሰደው እርምጃ "የአገሪቱን ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት ለማስከበር" መሆኑን ጠቅሰው፣ ይህም ሁሉም አገራት የሚጠበቅባቸው ሕጋዊ ኃላፊነት መሆኑንም አመልክተዋል።
ሙሳ ፋኪ እንዳሉት በዚህ በትግራይ ክልል ውስጥ የተከሰተውን ቀውስ ተከትሎ ከፍተኛ መጠን ያለው መፈናቀል መከሰቱን ገልጸው፤ በዚህ ረገድ ኢጋድ ለስደተኞችና ለተፈናቀሉ ሰዎች የተለየ ትኩረት በመስጠት ኢትዮጵያ ከምታደርገው የሰብአዊ ድጋፍ ጥረት ከጎኗ እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።
ኮሚሽነሩ ፋኪ ማሐማት ከዚህ በፊት፣ የፌደራል መንግሥቱና የትግራይ ክልል ወደ ድርድር እንዲመጡና ሰላማዊ መፍትሄ እንዲፈልጉ ጥሪ ማቅረባቸው ይታወሳል ሲል የዘገበው ቢቢሲ ነው።
ለአንድ ቀን በተካሄደው በዚህ ጉባኤ ላይ የተሳተፉት የኢጋድ አባል አገራት ከአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበር በተጨማሪ ለኢትዮጵያ መንግሥት ድጋፋቸውን መግለጻቸው ይታወቃል።
ሰራዊቱ ለተቀዳጀው ድል ቴክኖሎጂ አስተዋጾ ማድረጉንና ለቴክኖሎጂው መተግበር ደግሞ የአንበሳውን ድርሻ የሚይዙት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መሆናቸውን ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ አስታወቁ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የሀገር መከላከያ ሰራዊት ለተቀዳጀው ድል የቴክኖሎጂ አስተዋጾ የጎላ መሆኑንና ለቴክኖሎጂው መተግበር ደግሞ ትልቁን የአንበሳ ድርሻ የሚይዙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ መሆናቸውን የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ አስታወቁ።
ኤታማዦር ሹሙ ጀነራል ብርሀኑ ጁላ ዛሬ እንደተናገሩት፤ ሰራዊቱ ለተቀዳጀው ድል የታጠቀው ቴክኖሎጂ ልዩነት ፈጥሯል። ለዚህ ቴክኖሎጂ መተግበርና ሰራዊቱ እንዲታጠቅ በማድረጉ በኩል ደግሞ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ አስተዋጾ ትልቁን የአንበሳ ድርሻ ይይዛል።
“ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቴክኖሎጂ ሰው ነው፤ ኢትዮጵያንም ዓለምንም በደንብ የሚያውቅ ነው፤ ወደ ጠቅላይ ሚኒስትርነት መንበር ሲመጣ ቁጥር አንድ የሪፎርም ስራ ያደረገው ሰራዊቱን የቴክኖሎጂ ባለቤት ማድረግ ነበር” ያሉት ጄኔራል ብርሃኑ፤ ሰራዊቱ በቴክኖሎጂ የሚመራ፣ ዘመናዊ መሳሪያና ትጥቅ ሊኖረው ይገባል የሚል አቅጣጫ አስቀምጠው ያንን ተግባራዊ በማድረጋቸው የህግ የማስከበር ዘመቻው በአጭር ጊዜ ውስጥ ውጤታማ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ አድርጓል ነው ያሉት።
የጠቅላይ ሚኒስትሩን ሃሳብ ተቀብሎ ወደስራ የገባ እንዳለ ሁሉ በወቅቱ የሚያደናቅፍ ሰው እንዳልታጣ የጠቀሱት ጄኔራል ብርሃኑ፤ የማይናቅ ቁጥር ያለው የሰራዊቱ አካል ቴክኖሎጂውን ተቀብሎ በማስፈጸሙ በህግ ማስከበር ስራው በአጭር ጊዜ ውጤታማ ሆነናል ነው ያሉት።
“በጠቅላይ ሚኒስትሩ በኩል ከታቀደው የቴክኖሎጂ አቅም የመፍጠር አንጻር የሰራነው ትንሽ ነው፤ ገና ለመስራት ያቀድነው ይበልጣል፤ ትንሽም ሆኖ ግን የታጠቅነው ቴክኖሎጂ የውጊያውን አጠቃላይ ገጽታና ተፈጥሮ የቀየረ ነው” ሲሉም ነው ጄነራል ብርሃኑ ከኦቢኤን ጋር በነበራቸው ቆይታ ያብራሩት።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ይሄንን ያደረጉት የቴክኖሎጂ ሰው በመሆናቸው ነው ያሉት ጄኔራል ብርሃኑ፤ “ሰራዊቱን እጅግ የማዘመን ራዕይ ያለው መሪ ነው” ሲሉም ነው የገለጿቸው።
“አገር እገነባለሁ ብሎ ሃላፊነት የወሰደ ሰው ነው፤ አገሪቷን የተከበረች እንድትሆን የሚያስከብራት ሃይል በቂ ቴክኖሎጂ የታጠቀ መሆን አለበት" የሚል እምነት በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ዘንድ መኖሩን የጠቀሱት ጄኔራል ብርሃኑ፤ “ሁሉም የእኔ ነው የሚለው የመከላከያ ሰራዊት እንዲፈጠር እየሰራ ነው” ሲሉም አስታውቀዋል።
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የሀገር መከላከያ ሰራዊት ለተቀዳጀው ድል የቴክኖሎጂ አስተዋጾ የጎላ መሆኑንና ለቴክኖሎጂው መተግበር ደግሞ ትልቁን የአንበሳ ድርሻ የሚይዙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ መሆናቸውን የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ አስታወቁ።
ኤታማዦር ሹሙ ጀነራል ብርሀኑ ጁላ ዛሬ እንደተናገሩት፤ ሰራዊቱ ለተቀዳጀው ድል የታጠቀው ቴክኖሎጂ ልዩነት ፈጥሯል። ለዚህ ቴክኖሎጂ መተግበርና ሰራዊቱ እንዲታጠቅ በማድረጉ በኩል ደግሞ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ አስተዋጾ ትልቁን የአንበሳ ድርሻ ይይዛል።
“ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቴክኖሎጂ ሰው ነው፤ ኢትዮጵያንም ዓለምንም በደንብ የሚያውቅ ነው፤ ወደ ጠቅላይ ሚኒስትርነት መንበር ሲመጣ ቁጥር አንድ የሪፎርም ስራ ያደረገው ሰራዊቱን የቴክኖሎጂ ባለቤት ማድረግ ነበር” ያሉት ጄኔራል ብርሃኑ፤ ሰራዊቱ በቴክኖሎጂ የሚመራ፣ ዘመናዊ መሳሪያና ትጥቅ ሊኖረው ይገባል የሚል አቅጣጫ አስቀምጠው ያንን ተግባራዊ በማድረጋቸው የህግ የማስከበር ዘመቻው በአጭር ጊዜ ውስጥ ውጤታማ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ አድርጓል ነው ያሉት።
የጠቅላይ ሚኒስትሩን ሃሳብ ተቀብሎ ወደስራ የገባ እንዳለ ሁሉ በወቅቱ የሚያደናቅፍ ሰው እንዳልታጣ የጠቀሱት ጄኔራል ብርሃኑ፤ የማይናቅ ቁጥር ያለው የሰራዊቱ አካል ቴክኖሎጂውን ተቀብሎ በማስፈጸሙ በህግ ማስከበር ስራው በአጭር ጊዜ ውጤታማ ሆነናል ነው ያሉት።
“በጠቅላይ ሚኒስትሩ በኩል ከታቀደው የቴክኖሎጂ አቅም የመፍጠር አንጻር የሰራነው ትንሽ ነው፤ ገና ለመስራት ያቀድነው ይበልጣል፤ ትንሽም ሆኖ ግን የታጠቅነው ቴክኖሎጂ የውጊያውን አጠቃላይ ገጽታና ተፈጥሮ የቀየረ ነው” ሲሉም ነው ጄነራል ብርሃኑ ከኦቢኤን ጋር በነበራቸው ቆይታ ያብራሩት።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ይሄንን ያደረጉት የቴክኖሎጂ ሰው በመሆናቸው ነው ያሉት ጄኔራል ብርሃኑ፤ “ሰራዊቱን እጅግ የማዘመን ራዕይ ያለው መሪ ነው” ሲሉም ነው የገለጿቸው።
“አገር እገነባለሁ ብሎ ሃላፊነት የወሰደ ሰው ነው፤ አገሪቷን የተከበረች እንድትሆን የሚያስከብራት ሃይል በቂ ቴክኖሎጂ የታጠቀ መሆን አለበት" የሚል እምነት በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ዘንድ መኖሩን የጠቀሱት ጄኔራል ብርሃኑ፤ “ሁሉም የእኔ ነው የሚለው የመከላከያ ሰራዊት እንዲፈጠር እየሰራ ነው” ሲሉም አስታውቀዋል።
በህግ ማስከበር ዘመቻው ግዳጃቸውን በጀግንነት ለፈጸሙ የሰራዊቱ አባላት እውቅና እንደሚሰጥ ተገለጸ
*****************
( ኢ ፕ ድ)
በትግራይ ክልል በተደረገው የህግ ማስከበር ዘመቻ ግዳጃቸውን በጀግንነት ለፈጸሙ የሰራዊቱ አባላት በየደረጃው እውቅና እንደሚሰጥ የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ። የክልል ልዩ ሃይሎች በየቦታው የነበራቸው አስተዋጽ ከፍተኛ መሆኑንም አስታውቀዋል።
ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ ትናንት ከኦቢኤን ጋር በነበራቸው ቆይታ ላይ እንዳስታወቁት፤ በዚህ የህግ ማስከበር ላይ የተሳተፉ የሰራዊቱ አባላት እንደየደረጃቸው የተለያዩ ሽልማቶችን የሚሸለሙ ይሆናል። ሜዳሊያ እና ማዕረግ የሚሸለሙ እንዲሁም ሌሎች የዕውቅና አሰጣጥ ሥነ ስርአቶችም የሚሰጡ ይሆናል።
“ጀግኖች ይሸለማሉ ታሪካቸውም ተፅፎ ለትውልድ ይቀመጣል” ያሉት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ፤ እነዚህ ጀግኖች የሀገር ቅርስ ስለሆኑ እነሱን ማስተዋወቅ፣ መጠበቅና ማበረታታት ተገቢ ነው ሲሉም አስታውቀዋል።
እንደ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ማብራሪያ፤ በዚህ የህግ ማስከበር ስራ ላይ የህዝቡ ተሳትፎ ከፍተኛ የነበረ ሲሆን፤ የአማራ ክልል፣ የኦሮሚያ ክልል፣ የአፋር፣ የሶማሌ እና ሌሎችም ክልሎች በተለያዩ መንገዶች ያደረጉት አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደነበር አብራርተዋል።
የቆሰሉ የሰራዊቱ አባላት በአብዛኛው በአማራ ክልል ሆስፒታሎች ሲታከሙ መቆየታቸውን የገለጹት ጄኔራል ብርሃኑ፤ በክልሉ ያሉ ሆስፒታሎችና የህክምና መስጫ ተቋማት ለሰራዊቱ ክፍት እንዲሆኑ በማድረግ አምቡላንስና የህክምና ባለሙያ መድበው ቁስለኞችን በሰፊው ማከማቸውንና ሪፈር የተባሉት ብቻ ወደማዕከል መምጣታቸውን አስታውቀዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=37843
*****************
( ኢ ፕ ድ)
በትግራይ ክልል በተደረገው የህግ ማስከበር ዘመቻ ግዳጃቸውን በጀግንነት ለፈጸሙ የሰራዊቱ አባላት በየደረጃው እውቅና እንደሚሰጥ የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ። የክልል ልዩ ሃይሎች በየቦታው የነበራቸው አስተዋጽ ከፍተኛ መሆኑንም አስታውቀዋል።
ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ ትናንት ከኦቢኤን ጋር በነበራቸው ቆይታ ላይ እንዳስታወቁት፤ በዚህ የህግ ማስከበር ላይ የተሳተፉ የሰራዊቱ አባላት እንደየደረጃቸው የተለያዩ ሽልማቶችን የሚሸለሙ ይሆናል። ሜዳሊያ እና ማዕረግ የሚሸለሙ እንዲሁም ሌሎች የዕውቅና አሰጣጥ ሥነ ስርአቶችም የሚሰጡ ይሆናል።
“ጀግኖች ይሸለማሉ ታሪካቸውም ተፅፎ ለትውልድ ይቀመጣል” ያሉት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ፤ እነዚህ ጀግኖች የሀገር ቅርስ ስለሆኑ እነሱን ማስተዋወቅ፣ መጠበቅና ማበረታታት ተገቢ ነው ሲሉም አስታውቀዋል።
እንደ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ማብራሪያ፤ በዚህ የህግ ማስከበር ስራ ላይ የህዝቡ ተሳትፎ ከፍተኛ የነበረ ሲሆን፤ የአማራ ክልል፣ የኦሮሚያ ክልል፣ የአፋር፣ የሶማሌ እና ሌሎችም ክልሎች በተለያዩ መንገዶች ያደረጉት አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደነበር አብራርተዋል።
የቆሰሉ የሰራዊቱ አባላት በአብዛኛው በአማራ ክልል ሆስፒታሎች ሲታከሙ መቆየታቸውን የገለጹት ጄኔራል ብርሃኑ፤ በክልሉ ያሉ ሆስፒታሎችና የህክምና መስጫ ተቋማት ለሰራዊቱ ክፍት እንዲሆኑ በማድረግ አምቡላንስና የህክምና ባለሙያ መድበው ቁስለኞችን በሰፊው ማከማቸውንና ሪፈር የተባሉት ብቻ ወደማዕከል መምጣታቸውን አስታውቀዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=37843
“መገንባት የምንፈልገው ዴሞክራሲ ጥቂቶች ብቻ የሚጫወቱበት ሜዳ ሳይሆን ብዙሃንን የሚያሳትፍ ሜዳ እንዲሆን ይፈለጋል”ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል የሰላም ሚኒስቴር
**********************
( ኢ ፕ ድ)
መገንባት የምንፈልገው ዴሞክራሲ ጥቂቶች ብቻ የሚጫወቱበት ሜዳ ሳይሆን ብዙሃንን የሚያሳትፍ ሜዳ እንዲሆን ስለሚፈለግ ለሁሉም የሆነች አገርን በመገንባት ሂደት ላይ ሁሉንም ለማሳተፍ የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የሰላም ሚኒስትሯ ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል ተናገሩ፡፡
ትናንት በይፋ የተጀመረውን የብሔራዊ የማህረበሰብ ተኮር የምክክር መድረክን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተሰጠውን መሰረታዊ ተልዕኮ ለመወጣት ከባለድርሻዎች ጋር በትኩረት እየሰራ ይገኛል።
እንደ አገር መገንባት የምንፈልገው ዴሞክራሲ ጥቂቶች ብቻ የሚጫወቱበት ሜዳ ሳይሆን ብዙሃንን የሚያሳትፍ ሜዳ እንዲሆን ስለሚፈለግም፤ ብዝሃነት ባለበት አገር ሁሉም ድምጾች እንዲደመጡ እድል መስጠት የሚያስችል ስራዎችን አቅዶ እየሰራ ይገኛል፡፡
የሰላም ሚኒስቴር ከተሰጡት መሰረታዊ ተልዕኮዎች መካከል አንዱ በአገሪቱ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን፣ የህግ የበላይነት እና የዳበረ ዴሞክራሲ እንዲገነባ፣ እናም ብሔራዊ መግባባት እንዲፈጠር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር መስራት መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትሯ፤ ይሄን መሰረት በማድረግም በሁለት እርከን የተከፈለ ብሔራዊ የምክክር መድረክ ለማዘጋጀት ባለፈው አንድ ዓመት ተኩል ጊዜ ሰፋፊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን ተናግረዋል፡፡
https://www.press.et/Ama/?p=37844
**********************
( ኢ ፕ ድ)
መገንባት የምንፈልገው ዴሞክራሲ ጥቂቶች ብቻ የሚጫወቱበት ሜዳ ሳይሆን ብዙሃንን የሚያሳትፍ ሜዳ እንዲሆን ስለሚፈለግ ለሁሉም የሆነች አገርን በመገንባት ሂደት ላይ ሁሉንም ለማሳተፍ የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የሰላም ሚኒስትሯ ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል ተናገሩ፡፡
ትናንት በይፋ የተጀመረውን የብሔራዊ የማህረበሰብ ተኮር የምክክር መድረክን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተሰጠውን መሰረታዊ ተልዕኮ ለመወጣት ከባለድርሻዎች ጋር በትኩረት እየሰራ ይገኛል።
እንደ አገር መገንባት የምንፈልገው ዴሞክራሲ ጥቂቶች ብቻ የሚጫወቱበት ሜዳ ሳይሆን ብዙሃንን የሚያሳትፍ ሜዳ እንዲሆን ስለሚፈለግም፤ ብዝሃነት ባለበት አገር ሁሉም ድምጾች እንዲደመጡ እድል መስጠት የሚያስችል ስራዎችን አቅዶ እየሰራ ይገኛል፡፡
የሰላም ሚኒስቴር ከተሰጡት መሰረታዊ ተልዕኮዎች መካከል አንዱ በአገሪቱ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን፣ የህግ የበላይነት እና የዳበረ ዴሞክራሲ እንዲገነባ፣ እናም ብሔራዊ መግባባት እንዲፈጠር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር መስራት መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትሯ፤ ይሄን መሰረት በማድረግም በሁለት እርከን የተከፈለ ብሔራዊ የምክክር መድረክ ለማዘጋጀት ባለፈው አንድ ዓመት ተኩል ጊዜ ሰፋፊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን ተናግረዋል፡፡
https://www.press.et/Ama/?p=37844
“በኃይል ወንበር እይዛለሁ ብሎ የሚመጣ ይጎዳል እንጂ አይጠቀምም ” ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ መንግስቴ
*******************
( ኢ ፕ ድ)
ጥሩ አላማ እና ህዝብ ይጠቅማል የሚል ሃሳብ ይዞ ከመቅረብ ያለፈ በሃይል ወንበር እይዛለሁ ብሎ የሚመጣ ማንኛውም ኃይል ከመጎዳት ያለፈ ምንም እንደማይጠቀም የህወሓት ጁንታ አፍኗቸው ከነበሩት መካከል አንዱ የሆኑት የሰሜን ዕዝ ምክትል ኦፕሬሽን አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ መንግስቴ ተናገሩ።መከላከያ ሰራዊቱም በሰላማዊ መንገድና በዴሞክራሲያዊ አካሄድ የሚመጣውን ብቻ ተቀብሎ ለመሄድ የሚሰራ እንደሆነም አስገንዝበዋል።
ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ እንደተናገሩት፤ የህወሓት ጁንታ ቡድን ለዓመታት የሀሰት ፕሮፖጋንዳ ላይ ተጠምዶ ከማሳለፉ ባሻገር በሃይል ወንበር ለመያዝ እንዲያመቸው በመከላከያ ሰራዊቱ አባላት ላይ የፈጸመው ጥቃት ውድቀቱን አፋጥኖለታል።
መከላከያ ሰራዊቱም ለዚህ የሚመች ሃይል አለመሆኑን አሳይቷል። በመሆኑም የተሻለ ዓላማ ለህዝብ በሚጠቅም ሃሳብ ይዞ ከመስራት ባለፈ በሃይል ወንበር ለመያዝ የሚደረግ ሙከራ የማይጠቅም፤ ይልቁኑም ያንን ኃይል የሚጎዳ መሆኑን መገንዘብ ይገባል፡፡
እንደ ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ ገለጻ፤ የጁንታው ቡድን በህዝቡ ውስጥ ብቻ ሳይሆን መከላከያ ሰራዊትን የማጠልሸት እና የመከፋፈል ስራዎች ቀድሞ ሲያከናውን ነበር። ሰራዊቱ በአንድ መምሪያ እና ተቋም ስር ሆኖ ሳለ የሰሜን እዝ መጥፎ ነው ምዕራብ አሊያም ምስራቅ ዕዝ ጥሩ ነው የሚል መከፋፈል ሲታይ ቆይቷል። በማህበራዊ ድረገጾች እና በአካል ጭምር ሰራዊቱን የማጠልሸት ስራዎችን አከናውነዋል፤ በቻሉት መጠን የሰራዊቱን የውስጥ አንድነት ያናጋል ብለው የሚያስቡትን ለማድረግ ያልወረወሩት ጠጠር የለም።
https://www.press.et/Ama/?p=37845
*******************
( ኢ ፕ ድ)
ጥሩ አላማ እና ህዝብ ይጠቅማል የሚል ሃሳብ ይዞ ከመቅረብ ያለፈ በሃይል ወንበር እይዛለሁ ብሎ የሚመጣ ማንኛውም ኃይል ከመጎዳት ያለፈ ምንም እንደማይጠቀም የህወሓት ጁንታ አፍኗቸው ከነበሩት መካከል አንዱ የሆኑት የሰሜን ዕዝ ምክትል ኦፕሬሽን አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ መንግስቴ ተናገሩ።መከላከያ ሰራዊቱም በሰላማዊ መንገድና በዴሞክራሲያዊ አካሄድ የሚመጣውን ብቻ ተቀብሎ ለመሄድ የሚሰራ እንደሆነም አስገንዝበዋል።
ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ እንደተናገሩት፤ የህወሓት ጁንታ ቡድን ለዓመታት የሀሰት ፕሮፖጋንዳ ላይ ተጠምዶ ከማሳለፉ ባሻገር በሃይል ወንበር ለመያዝ እንዲያመቸው በመከላከያ ሰራዊቱ አባላት ላይ የፈጸመው ጥቃት ውድቀቱን አፋጥኖለታል።
መከላከያ ሰራዊቱም ለዚህ የሚመች ሃይል አለመሆኑን አሳይቷል። በመሆኑም የተሻለ ዓላማ ለህዝብ በሚጠቅም ሃሳብ ይዞ ከመስራት ባለፈ በሃይል ወንበር ለመያዝ የሚደረግ ሙከራ የማይጠቅም፤ ይልቁኑም ያንን ኃይል የሚጎዳ መሆኑን መገንዘብ ይገባል፡፡
እንደ ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ ገለጻ፤ የጁንታው ቡድን በህዝቡ ውስጥ ብቻ ሳይሆን መከላከያ ሰራዊትን የማጠልሸት እና የመከፋፈል ስራዎች ቀድሞ ሲያከናውን ነበር። ሰራዊቱ በአንድ መምሪያ እና ተቋም ስር ሆኖ ሳለ የሰሜን እዝ መጥፎ ነው ምዕራብ አሊያም ምስራቅ ዕዝ ጥሩ ነው የሚል መከፋፈል ሲታይ ቆይቷል። በማህበራዊ ድረገጾች እና በአካል ጭምር ሰራዊቱን የማጠልሸት ስራዎችን አከናውነዋል፤ በቻሉት መጠን የሰራዊቱን የውስጥ አንድነት ያናጋል ብለው የሚያስቡትን ለማድረግ ያልወረወሩት ጠጠር የለም።
https://www.press.et/Ama/?p=37845
www.press.et
“በኃይል ወንበር እይዛለሁ ብሎ የሚመጣ ይጎዳል እንጂ አይጠቀምም ” ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ መንግስቴ | የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት
ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት እንዲልኩ ትምህርት ሚኒስቴር ጥሪ አቀረበ
********************
(ኢ ፕ ድ)
ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት እንዲልኩ ትምህርት ሚኒስቴር ጥሪ አቀረበ፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ፣ የመማር ማስተማር ስራ ድጋሚ የተጀመረ ሲሆን አሁንም ወደ ትምህርት ገበታቸው ያልተመለሱ ተማሪዎች እንዳሉ ጠቅሰው ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት እንዲልኩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የኮቪድ 19 ወረርሽኝን በመከላከል የመማር ማስተማር ስራው ቢጀመርም በርካታ ተማሪዎች በትምህርት ገበታቸው ላይ መገኘት አልቻሉም ተብሏል።
የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች በበይነ መረብ መክረዋል።
ትምህርት ላይ የሚሰሩ አጋር አካላትና ከትምህርት ዘርፍ ውጭ ያሉ ተቋማትም ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ እየተደረገ ያለውን ጥረት እንዲደግፉ ጥሪ ቀርቧል፡፡
"ወደ ትምህርት ቤት እንመለስ" በሚል ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታቸው የመመለስ ዘመቻም እንደሚጀመር ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
********************
(ኢ ፕ ድ)
ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት እንዲልኩ ትምህርት ሚኒስቴር ጥሪ አቀረበ፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ፣ የመማር ማስተማር ስራ ድጋሚ የተጀመረ ሲሆን አሁንም ወደ ትምህርት ገበታቸው ያልተመለሱ ተማሪዎች እንዳሉ ጠቅሰው ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት እንዲልኩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የኮቪድ 19 ወረርሽኝን በመከላከል የመማር ማስተማር ስራው ቢጀመርም በርካታ ተማሪዎች በትምህርት ገበታቸው ላይ መገኘት አልቻሉም ተብሏል።
የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች በበይነ መረብ መክረዋል።
ትምህርት ላይ የሚሰሩ አጋር አካላትና ከትምህርት ዘርፍ ውጭ ያሉ ተቋማትም ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ እየተደረገ ያለውን ጥረት እንዲደግፉ ጥሪ ቀርቧል፡፡
"ወደ ትምህርት ቤት እንመለስ" በሚል ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታቸው የመመለስ ዘመቻም እንደሚጀመር ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
"ይሄንን ጽኑና አስተዋይ ሕዝብ ይዘን ችግሮች እንዳይደገሙ አድርገን እንፈታዋለን"
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
አስተዋይ ሕዝብ ይዘን ችግሮች እንዳይደገሙ አድርገን እንፈታዋለን" ሲሉ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ አስታወቁ።
ዛሬ በመከተል ተገኝተው በውቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከህዝቡ ጋር የተወያዩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ " ጠላቶች ኢትዮጵያን በብሔርና በሃይማኖት ለመከፋፈል ያላቸው ፍላጎት ዛሬም አልጠፋም፡፡ በጽናትና በአንድነት ስንታገለው ግን ይህ ፍላጎት መና ሆኖ ይቀራል" ሲሉ በማህበራዊ ገጻቸው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ገልጸዋል።
በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከመተከል ነዋሪዎች ጋር ባደረጉት ውይይት የተመለከቱት ሕዝቡ ለአንድነት፣ ለሰላም፣ ለልማትና ለብልጽግና ያለው ፍላጎት ከማንኛውም ከፋፋይ አጀንዳ እንደሚበልጥ ነው የገለጹት ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕታቸውም፤ " ይሄንን ጽኑና አስተዋይ ሕዝብ ይዘን ችግሮችን እንዳይደገሙ አድርገን እንፈታቸዋለን" ሲሉ አስታውቀዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
አስተዋይ ሕዝብ ይዘን ችግሮች እንዳይደገሙ አድርገን እንፈታዋለን" ሲሉ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ አስታወቁ።
ዛሬ በመከተል ተገኝተው በውቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከህዝቡ ጋር የተወያዩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ " ጠላቶች ኢትዮጵያን በብሔርና በሃይማኖት ለመከፋፈል ያላቸው ፍላጎት ዛሬም አልጠፋም፡፡ በጽናትና በአንድነት ስንታገለው ግን ይህ ፍላጎት መና ሆኖ ይቀራል" ሲሉ በማህበራዊ ገጻቸው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ገልጸዋል።
በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከመተከል ነዋሪዎች ጋር ባደረጉት ውይይት የተመለከቱት ሕዝቡ ለአንድነት፣ ለሰላም፣ ለልማትና ለብልጽግና ያለው ፍላጎት ከማንኛውም ከፋፋይ አጀንዳ እንደሚበልጥ ነው የገለጹት ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕታቸውም፤ " ይሄንን ጽኑና አስተዋይ ሕዝብ ይዘን ችግሮችን እንዳይደገሙ አድርገን እንፈታቸዋለን" ሲሉ አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያ ሁለተኛዋ የመሬት ምልከታ ሳተላይት በቻይና ሄይናን ክፍለ ሀገር ዌን ቻንግ የሳተላይት ማስወንጨፊያ ማዕከል ወደ ህዋ መጥቃለች
*****************************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ሁለተኛዋ የመሬት ምልከታ ሳተላይት በቻይና ሄይናን ክፍለ ሀገር ዌን ቻንግ የሳተላይት ማስወንጨፊያ ማዕከል ወደ ህዋ ማምጠቋን በቻይና የኢትዮጵያ ኢምባሲ አስታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ቻይና - ቤጂንግ ከሚገኘው Smart Satellite Technology Corporation Limited ከተባለ ኩባንያ ጋር በትብብር ሳተላይት ለማልማትና ጥቅም ላይ ለማዋል ባለፈው የፈረንጆች ዓመት በደረሰው ስምምነት መሠረት የግንባታ ሥራዋ ሲካሄድ የቆየውና ለሀገራችን ሁለተኛ የሆነችው “ET-SMART-RSS” የመሬት ምልከታ ሳተላይት በትላንትናው ዕለት በቻይና ሰዓት አቆጣጠር 12:37 ላይ በቻይና ሄይናን ክፍለ ሀገር ዌን ቻንግ የሳተላይት ማስወንጨፊያ ማዕከል ወደ ህዋ መጥቃለች።
የሳተላይቷ ወደ ህዋ መምጠቅ በቻይና እና ኢትዮጵያ መካከል ያለውን ወዳጅነት፤ በመንግሥታቱ መካከል ያለው የትብብር መንፈስ በግሉም ሴክተር እየታየ ለመምጣቱ ከኩባንያው ጋር ሳተላይቷን በማልማት የተሰራው የተቀናጀ ሥራ አመላካች ነው።
ሳተላይቷ በአካባቢ ጥበቃና ተፈጥሮ እንክብካቤ ረገድ ከምትሰጠው ጠቀሜታ በላይ በማልማቱ ሂደት የተሳተፉ ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች ያገኙት ዕውቀትና ክህሎት ሀገሪቱ በቀጣይ ለምታመጥቃቸው ሳተላይቶች መሰረት የሚጥል ነው ተብሏል፡፡
ወደፊት በሀገር ውስጥ ሳተላይት ለማበልጸግ ለምታደርገው ጥረት ከፍተኛ አቅም የሚፈጥርም ነው። የሳተላይቷ ወደ ህዋ መምጠቅ በቀጣይ የኮሙኒኬሽን ሳተላይት ግንባታ አቅም የሚፈጥር መሆኑም ታውቋል።
የኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ የመሬት ምልከታ ሳተላይት “ETRSS-1” እስካሁን በህዋ ላይ በነበራት ቆይታ ለአየር ንብረት ለውጥ፣ ለግብርና፣ ለደን፣ ለውሀ ሃብትና ለመሳሰሉት የምርምርና የክትትል ስራዎች የሚያገለግል 800GB የምስል ዳታ እንጦጦ ለሚገኘው የምድር መቆጣጠሪያ ጣቢያ ልካለች።
አሁን ወደ ህዋ የተመነጠቀችው ሁለተኛዋ ሳተላይት ተመሳሳይ ጠቀሜታ የሚኖራት ሲሆን ከመጀመሪያዋ ጋር ስትወዳደር የዕይታ ጥራቷ የተሻለ መሆኑ በዘርፉ ባለሙያዎች መግለጻቸውን በቤጂንግ የኢትዮጵያ ኢምባሲ አስታውቋል፡፡
*****************************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ሁለተኛዋ የመሬት ምልከታ ሳተላይት በቻይና ሄይናን ክፍለ ሀገር ዌን ቻንግ የሳተላይት ማስወንጨፊያ ማዕከል ወደ ህዋ ማምጠቋን በቻይና የኢትዮጵያ ኢምባሲ አስታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ቻይና - ቤጂንግ ከሚገኘው Smart Satellite Technology Corporation Limited ከተባለ ኩባንያ ጋር በትብብር ሳተላይት ለማልማትና ጥቅም ላይ ለማዋል ባለፈው የፈረንጆች ዓመት በደረሰው ስምምነት መሠረት የግንባታ ሥራዋ ሲካሄድ የቆየውና ለሀገራችን ሁለተኛ የሆነችው “ET-SMART-RSS” የመሬት ምልከታ ሳተላይት በትላንትናው ዕለት በቻይና ሰዓት አቆጣጠር 12:37 ላይ በቻይና ሄይናን ክፍለ ሀገር ዌን ቻንግ የሳተላይት ማስወንጨፊያ ማዕከል ወደ ህዋ መጥቃለች።
የሳተላይቷ ወደ ህዋ መምጠቅ በቻይና እና ኢትዮጵያ መካከል ያለውን ወዳጅነት፤ በመንግሥታቱ መካከል ያለው የትብብር መንፈስ በግሉም ሴክተር እየታየ ለመምጣቱ ከኩባንያው ጋር ሳተላይቷን በማልማት የተሰራው የተቀናጀ ሥራ አመላካች ነው።
ሳተላይቷ በአካባቢ ጥበቃና ተፈጥሮ እንክብካቤ ረገድ ከምትሰጠው ጠቀሜታ በላይ በማልማቱ ሂደት የተሳተፉ ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች ያገኙት ዕውቀትና ክህሎት ሀገሪቱ በቀጣይ ለምታመጥቃቸው ሳተላይቶች መሰረት የሚጥል ነው ተብሏል፡፡
ወደፊት በሀገር ውስጥ ሳተላይት ለማበልጸግ ለምታደርገው ጥረት ከፍተኛ አቅም የሚፈጥርም ነው። የሳተላይቷ ወደ ህዋ መምጠቅ በቀጣይ የኮሙኒኬሽን ሳተላይት ግንባታ አቅም የሚፈጥር መሆኑም ታውቋል።
የኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ የመሬት ምልከታ ሳተላይት “ETRSS-1” እስካሁን በህዋ ላይ በነበራት ቆይታ ለአየር ንብረት ለውጥ፣ ለግብርና፣ ለደን፣ ለውሀ ሃብትና ለመሳሰሉት የምርምርና የክትትል ስራዎች የሚያገለግል 800GB የምስል ዳታ እንጦጦ ለሚገኘው የምድር መቆጣጠሪያ ጣቢያ ልካለች።
አሁን ወደ ህዋ የተመነጠቀችው ሁለተኛዋ ሳተላይት ተመሳሳይ ጠቀሜታ የሚኖራት ሲሆን ከመጀመሪያዋ ጋር ስትወዳደር የዕይታ ጥራቷ የተሻለ መሆኑ በዘርፉ ባለሙያዎች መግለጻቸውን በቤጂንግ የኢትዮጵያ ኢምባሲ አስታውቋል፡፡
ትእምት (ኢፈርት) በጥቂቶች ተይዞ ቢቆይም የህዝብ ሃብት ስለሆነ ስራው እንዲቀጥል መንግስት መወሰኑን የትግራይ ብልፅግና ከፍተኛ አመራር ዶ/ር አብርሃም በላይ አስታወቁ
*****************
(ኢ.ፕ.ድ)
ትእምት (ኢፈርት) ምንም እንኳ በጥቂቶች ተይዞ ቢቆይም የህዝብ ሃብት ስለሆነ ስራው እንዲቀጥል መንግስት መወሰኑን የትግራይ ብልፅግና ከፍተኛ አመራር ዶ/ር አብርሃም በላይ አስታወቁ።
ዶ/ር አብርሃም ዛሬ ለጋዜጠኞች በመቐለ ከተማ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፤ ትእምት (ኢፈርት) በጥቂት የጁንታው አባላት ተይዞ ቆይቷል። ይሁን እንጂ ተቋሙ የህዝብ ሃብት ስለሆነ ስራው እንዲቀጥል መንግስት ወስኗል።
እንደ ዶ/ር አብርሃም ማብራሪያ፤ በተቋሙ ላይ የተጀመረው የፍርድ ቤት ጉዳይ ጎን ጎን ይቀጥላል።
የትእምት ሰራተኞች ስራቸውን እንዲጀምሩ አቅጣጫ መቀመጡን የገለጹት ዶ/ር አብረሃም፤ አመራሩ በባለአደራ እንዲመራ መንግስት አምኖበት ለፍርድ ቤት ለውሳኔ አቅርቧል ነው ያሉት።
የባለ አደራ ቦርድ አባላቱ 7 አባላት አሉት፤ 5ቱ በትምህርት እና በተመሳሳይ ዘርፍ ልምድ ያላቸው ናቸው ያሉት ዶ/ር አብርሃም፤ ሁለቱ ደግሞ ከገንዘብ እና ከንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የተመረጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የትእምት ጉዳይ በፍርድ ቤት የተያዘ ቢሆንም የተወረሰ ነገር የለም ያሉት ዶ/ር አብረሃም፤ የተቋሟቱ ሰራተኞች ደሞዝ እንዲከፈል እና ሰራተኞቹ ስራ እንዲጀምሩ መንግስት ወስኗል ብለዋል።
ከህግ ማስከበር ዘመቻው በተቃራኒ በመቆም በውግያ የተሳተፉ የተቋማቱ ተንቀሳቃሽ ንብረቶች ጉዳይም በህግ አግባብ ይታያል ነው ያሉት ዶ/ር አብረሃም።
*****************
(ኢ.ፕ.ድ)
ትእምት (ኢፈርት) ምንም እንኳ በጥቂቶች ተይዞ ቢቆይም የህዝብ ሃብት ስለሆነ ስራው እንዲቀጥል መንግስት መወሰኑን የትግራይ ብልፅግና ከፍተኛ አመራር ዶ/ር አብርሃም በላይ አስታወቁ።
ዶ/ር አብርሃም ዛሬ ለጋዜጠኞች በመቐለ ከተማ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፤ ትእምት (ኢፈርት) በጥቂት የጁንታው አባላት ተይዞ ቆይቷል። ይሁን እንጂ ተቋሙ የህዝብ ሃብት ስለሆነ ስራው እንዲቀጥል መንግስት ወስኗል።
እንደ ዶ/ር አብርሃም ማብራሪያ፤ በተቋሙ ላይ የተጀመረው የፍርድ ቤት ጉዳይ ጎን ጎን ይቀጥላል።
የትእምት ሰራተኞች ስራቸውን እንዲጀምሩ አቅጣጫ መቀመጡን የገለጹት ዶ/ር አብረሃም፤ አመራሩ በባለአደራ እንዲመራ መንግስት አምኖበት ለፍርድ ቤት ለውሳኔ አቅርቧል ነው ያሉት።
የባለ አደራ ቦርድ አባላቱ 7 አባላት አሉት፤ 5ቱ በትምህርት እና በተመሳሳይ ዘርፍ ልምድ ያላቸው ናቸው ያሉት ዶ/ር አብርሃም፤ ሁለቱ ደግሞ ከገንዘብ እና ከንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የተመረጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የትእምት ጉዳይ በፍርድ ቤት የተያዘ ቢሆንም የተወረሰ ነገር የለም ያሉት ዶ/ር አብረሃም፤ የተቋሟቱ ሰራተኞች ደሞዝ እንዲከፈል እና ሰራተኞቹ ስራ እንዲጀምሩ መንግስት ወስኗል ብለዋል።
ከህግ ማስከበር ዘመቻው በተቃራኒ በመቆም በውግያ የተሳተፉ የተቋማቱ ተንቀሳቃሽ ንብረቶች ጉዳይም በህግ አግባብ ይታያል ነው ያሉት ዶ/ር አብረሃም።