“መከላከያ ውስጥ ያየኋት ኢትዮጵያ የሰርጓ ቀን የደረሰ ሙሽራን ትመስላለች፡፡ የሰራዊቱ አባላት ፊታቸው ላይ የሚታየው ስሜት ውጊያ አይደለም የሚመስለው፡፡ ሁሉም ለኢትዮጵያ ሲሉ በወኔና በደስታ ነው የሚዋጉት። በይበልጥ ደግሞ አዲስ አበባ ላይ ተወልደው ያደጉ ልጆች ይህ ስሜት እንዲጋባባቸው እፈልጋለሁ”
ጋዜጠኛ ኑረዲን አወል
የአዲስ ቲቪ ጋዜጠኛ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት 80ኛ አመት የምስረታ በአሉን አመቱን ሙሉ በተለያቱ መድረኮች እያከበረ ይገኛል። የበአሉ አካል በማድረግም በህግ ማስከበር ዘመቻው ላይ ለተሳተፉ የመገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች የምስጋና እና የውይይት መድረክ አካሂዷል።
በዚሁ መርሀ ግብር ላይም ወደ ግንባር ከተላኩ ጋዜጠኞች መካከል የአዲስ ቲቪው ጋዜጠኛ ኑረዲን አወል የተመለከተውን እንዲህ ተናግሯል።
👉 ከግንባር ከመጣሁ በኋላ ጓደኞቼ ተሰበሰቡ፤ እስኪ ስለአገራችን ስለኢትዮጵያ የገጠመህን ንገረን አሉኝ፡፡ ስለየትኛዋ ኢትዮጵያ፤ መከላከያ ውስጥ ስላለችው ነው? ወይንስ እዚህ ቁርስ ስላልበላን ትፈርሳለች ስለምትባለዋ ኢትዮጵያ ነው ’የምነግራችሁ? አልኳቸው፡፡
👉 መከላከያ ውስጥ ያየኋት ኢትዮጵያ የሰርጓ ቀን የደረሰ ሙሽራን ትመስላለች፡፡ የሰራዊቱ አባላት ፊታቸው ላይ የሚታየው ስሜት ውጊያ አይደለም የሚመስለው፡፡ ሁሉም ለኢትዮጵያ ሲሉ በወኔና በደስታ ነው የሚዋጉት። በይበልጥ ደግሞ አዲስ አበባ ላይ ተወልደው ያደጉ ልጆች ይህ ስሜት እንዲጋባባቸው እፈልጋለሁ፡፡
👉ኢትዮጵያ ስትባል ብዙ ነገር ነች፡፡ ግን ከምንናገረው በላይ በመከላከያ ሰራዊታችን ላይ የሚታየው ኢትዮጵያዊነት ለእኛ በሕይወታችን ላይ ትልቅ ጥቅም አለው ብዬ አምናለሁ፡፡
👉 በዚህ አጋጣሚ ለእኔ ትውልድ ለሆኑት ወጣቶች መምከር የምፈልገው ነገር አለ፡፡ ለእኛ መኖር ትልቅ መስዕዋትነት የሚከፍሉልን የመከላከያ ሰራዊቶች አሉና እነሱን እንዲያመሰግኑልኝ፤ ማመስገን ብቻም ሳይሆን እንደ ግዴታ ሆኖ የትኛውም ወጣት መዝመት አለበት ብዬ ነው የማምነው፡፡
👉 የምንዘምተው ለምንድን ነው አንደኛ ፍቅርን የምናገኘው እዚያ ነው፡፡ ስርዓትን የምናገኘው እዛ ነው፡፡ ለሰው መኖር መቻል እንዳለብን የሚገባን እዚያ ነው፡፡ ከሚበሉት ነገር ቆርሰው እና በሐይላንድ ቁራጭ ከሚጠጡት ሻይ ከፍለው ለእንደእኔ አይነቱ እንግዳ አስቀድመው ይሰጣሉ፡፡
👉 እኔ እንደዛ ነወይ የምኖረው? አይደለም፡፡ እነሱ ግን እንደዚህ መተዛዘን በተሞላበት መንገድ ነው የሚኖሩት፡፡ ያ ነገር ለወጣቱ ትውልድ ትልቅ ትርፍ የምናተርፍበትና ትልቅ ጥቅም የምናገኝበት ነው፡፡
👉 እኔ በሕይወቴ አሁን ብቻ አይደለም ወደፊትም ይሄን አይነት ትምህርት አገኛለሁ ብዬ አላስብም፡፡ ኮሮና የገባ ጊዜ ምን እንል ነበር ‹‹ፈጣሪ ሆይ ይችን ኮሮና ያሳልፍልን እንጂ ወደ እምነት ተቋሜ ተመልሼ አንተን አገለግላለሁ›› ብለን ነበር፡፡ አለፈ ፤ እኛም አልሄድንም፤ በነበርንበት እንደቀጠልን እንገኛለን፡፡
👉 ይህ ደግሞ ሁለተኛ የመማሪያ እድል ነው የተሰጠን ብዬ አምናለሁ፡፡ ሁሌም መጥፎ ነገሮች የምንማራቸው ስለሆኑ የእኔ ትውልድና በእኔ የእድሜ እኩያ የሚገኙ ወጣቶች አሁን ትልቅ ትምህርት የምናገኝበት ጊዜ ነው፡፡ ምንድን ነው ከአጠገባችን ያለ ሰው ጠላታችን ሊሆን ይችላል፡፡
👉እርግጠኞች አንሆንም፡፡ እኔን የማያውቁኝ ሰዎች ስለ እኔ እዚያ ጋ ይሞታሉ፡፡አያውቁኝም እኮ፡፡ እኔ ኑረዲን መኖሬን አያውቁም እኮ፡፡ ነገር ግን እዚያ ጋ ኢትዮጵያዊ የሚባል የሚጎዳ ዜጋ አለና መጎዳት የለበትም ብሎ ለእኔ የሚያስብና ሕይወቱን መስዕዋት የሚያደርግ ብዙ ኢትዮጵያውያን ጀግኖች የመከላከያ ሰራዊቶች አሉና እኔ ከመቀመጫዬ ተነስቼ ላመሰግናቸው እወዳለሁ፡፡
👉 ከዚህ በመቀጠል እኛ የነበርንበት አካባቢ ትንሽ መልክዓም ምድሩ ከባድ ነበር፡፡ መልክዓም ምድሩን ሳይ ለምን መጣሁ አልኩኝ፡፡ከዚያ በኅላ ግን ወታደሩ ፊት ላይ የሚታዬው ስሜት፣ፍቅር ጥልቅ ነው፡፡ አሁን እኔ ያንን በቃል ልግለጸው ብል ማርከስ ነው የሚሆንብኝ፡፡በቃል ባወራው ማሳነስ ነው የሚሆንብኝ፡፡
👉 ማውራት ያለብን ስለግለሰብ ጀብድ አይደለም ብዬ አስባለሁ፡፡ ይሄን ታሪክ የሰራው ሙሉ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ነው፡፡የዚያ ታሪክ ተጋሪ በመሆኔ እድለኛ ነኝ ብዬ አስባለሁ፡፡ እኔ ያንን አስቸጋሪ መልክዓ ምድር በመኪና ነው የወጣሁት፡፡ ነገር ግን ሴት የመከላከያ ሰራዊት በእግራቸው የሚተኩሱትን መሳሪያ ተሸክመው ሲወጡት ሳይ ለእኔ ብለው መሆኑን አይቼ አዘንኩ፡፡
👉 እኔ ለዚህች ኢትዮጵያ ለምትባለው አገር ምንድን ነው ያደረኩላት? እኛ እንጠይቅ ነበር፡፡ ደመወዝ ተጨመረልን ወይ ብለን፡፡ ቤት መንግስት ይሰጠን ይሆን ወይ ብለን፡፡ እዚያ ጋ ግን ደመወዝ የማይጠይቅ፣ ቤት ይሰጠኝ ይሆን ብሎ የማያስብ፣ ከፊት ለፊቱ ሞትን እያዬ ለአገሩ ክብር የሚገሰግሰውን የመከላከያ ሰራዊት አይቻለሁና ደስ ብሎኛል፡፡ እጅግ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡
👉 ከመደሰትም በላይ በእኔ ዙሪያ ያሉ ብዙ ወጣቶች አሉ፡፡እነዚያ ወጣቶች ብዙ ሊማሩበት ይገባል፡፡ ይሄን የምለው ለፕሮፖጋንዳ ትርፍ አይደለም፡፡ በሕይወት የኖርንባት እያንዳንዷ ቀን ትልቅ ትርጉም እንዲኖራ ከፈለግን ኢትዮጵያን እንወቃት፡፡ ለማወቅ ከፈለግን ደግሞ አገር መከላከያ ሰራዊት ውስጥ እንግባ እላለሁ፡፡ አመሰግናለሁ፡፡
ጋዜጠኛ ኑረዲን አወል
የአዲስ ቲቪ ጋዜጠኛ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት 80ኛ አመት የምስረታ በአሉን አመቱን ሙሉ በተለያቱ መድረኮች እያከበረ ይገኛል። የበአሉ አካል በማድረግም በህግ ማስከበር ዘመቻው ላይ ለተሳተፉ የመገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች የምስጋና እና የውይይት መድረክ አካሂዷል።
በዚሁ መርሀ ግብር ላይም ወደ ግንባር ከተላኩ ጋዜጠኞች መካከል የአዲስ ቲቪው ጋዜጠኛ ኑረዲን አወል የተመለከተውን እንዲህ ተናግሯል።
👉 ከግንባር ከመጣሁ በኋላ ጓደኞቼ ተሰበሰቡ፤ እስኪ ስለአገራችን ስለኢትዮጵያ የገጠመህን ንገረን አሉኝ፡፡ ስለየትኛዋ ኢትዮጵያ፤ መከላከያ ውስጥ ስላለችው ነው? ወይንስ እዚህ ቁርስ ስላልበላን ትፈርሳለች ስለምትባለዋ ኢትዮጵያ ነው ’የምነግራችሁ? አልኳቸው፡፡
👉 መከላከያ ውስጥ ያየኋት ኢትዮጵያ የሰርጓ ቀን የደረሰ ሙሽራን ትመስላለች፡፡ የሰራዊቱ አባላት ፊታቸው ላይ የሚታየው ስሜት ውጊያ አይደለም የሚመስለው፡፡ ሁሉም ለኢትዮጵያ ሲሉ በወኔና በደስታ ነው የሚዋጉት። በይበልጥ ደግሞ አዲስ አበባ ላይ ተወልደው ያደጉ ልጆች ይህ ስሜት እንዲጋባባቸው እፈልጋለሁ፡፡
👉ኢትዮጵያ ስትባል ብዙ ነገር ነች፡፡ ግን ከምንናገረው በላይ በመከላከያ ሰራዊታችን ላይ የሚታየው ኢትዮጵያዊነት ለእኛ በሕይወታችን ላይ ትልቅ ጥቅም አለው ብዬ አምናለሁ፡፡
👉 በዚህ አጋጣሚ ለእኔ ትውልድ ለሆኑት ወጣቶች መምከር የምፈልገው ነገር አለ፡፡ ለእኛ መኖር ትልቅ መስዕዋትነት የሚከፍሉልን የመከላከያ ሰራዊቶች አሉና እነሱን እንዲያመሰግኑልኝ፤ ማመስገን ብቻም ሳይሆን እንደ ግዴታ ሆኖ የትኛውም ወጣት መዝመት አለበት ብዬ ነው የማምነው፡፡
👉 የምንዘምተው ለምንድን ነው አንደኛ ፍቅርን የምናገኘው እዚያ ነው፡፡ ስርዓትን የምናገኘው እዛ ነው፡፡ ለሰው መኖር መቻል እንዳለብን የሚገባን እዚያ ነው፡፡ ከሚበሉት ነገር ቆርሰው እና በሐይላንድ ቁራጭ ከሚጠጡት ሻይ ከፍለው ለእንደእኔ አይነቱ እንግዳ አስቀድመው ይሰጣሉ፡፡
👉 እኔ እንደዛ ነወይ የምኖረው? አይደለም፡፡ እነሱ ግን እንደዚህ መተዛዘን በተሞላበት መንገድ ነው የሚኖሩት፡፡ ያ ነገር ለወጣቱ ትውልድ ትልቅ ትርፍ የምናተርፍበትና ትልቅ ጥቅም የምናገኝበት ነው፡፡
👉 እኔ በሕይወቴ አሁን ብቻ አይደለም ወደፊትም ይሄን አይነት ትምህርት አገኛለሁ ብዬ አላስብም፡፡ ኮሮና የገባ ጊዜ ምን እንል ነበር ‹‹ፈጣሪ ሆይ ይችን ኮሮና ያሳልፍልን እንጂ ወደ እምነት ተቋሜ ተመልሼ አንተን አገለግላለሁ›› ብለን ነበር፡፡ አለፈ ፤ እኛም አልሄድንም፤ በነበርንበት እንደቀጠልን እንገኛለን፡፡
👉 ይህ ደግሞ ሁለተኛ የመማሪያ እድል ነው የተሰጠን ብዬ አምናለሁ፡፡ ሁሌም መጥፎ ነገሮች የምንማራቸው ስለሆኑ የእኔ ትውልድና በእኔ የእድሜ እኩያ የሚገኙ ወጣቶች አሁን ትልቅ ትምህርት የምናገኝበት ጊዜ ነው፡፡ ምንድን ነው ከአጠገባችን ያለ ሰው ጠላታችን ሊሆን ይችላል፡፡
👉እርግጠኞች አንሆንም፡፡ እኔን የማያውቁኝ ሰዎች ስለ እኔ እዚያ ጋ ይሞታሉ፡፡አያውቁኝም እኮ፡፡ እኔ ኑረዲን መኖሬን አያውቁም እኮ፡፡ ነገር ግን እዚያ ጋ ኢትዮጵያዊ የሚባል የሚጎዳ ዜጋ አለና መጎዳት የለበትም ብሎ ለእኔ የሚያስብና ሕይወቱን መስዕዋት የሚያደርግ ብዙ ኢትዮጵያውያን ጀግኖች የመከላከያ ሰራዊቶች አሉና እኔ ከመቀመጫዬ ተነስቼ ላመሰግናቸው እወዳለሁ፡፡
👉 ከዚህ በመቀጠል እኛ የነበርንበት አካባቢ ትንሽ መልክዓም ምድሩ ከባድ ነበር፡፡ መልክዓም ምድሩን ሳይ ለምን መጣሁ አልኩኝ፡፡ከዚያ በኅላ ግን ወታደሩ ፊት ላይ የሚታዬው ስሜት፣ፍቅር ጥልቅ ነው፡፡ አሁን እኔ ያንን በቃል ልግለጸው ብል ማርከስ ነው የሚሆንብኝ፡፡በቃል ባወራው ማሳነስ ነው የሚሆንብኝ፡፡
👉 ማውራት ያለብን ስለግለሰብ ጀብድ አይደለም ብዬ አስባለሁ፡፡ ይሄን ታሪክ የሰራው ሙሉ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ነው፡፡የዚያ ታሪክ ተጋሪ በመሆኔ እድለኛ ነኝ ብዬ አስባለሁ፡፡ እኔ ያንን አስቸጋሪ መልክዓ ምድር በመኪና ነው የወጣሁት፡፡ ነገር ግን ሴት የመከላከያ ሰራዊት በእግራቸው የሚተኩሱትን መሳሪያ ተሸክመው ሲወጡት ሳይ ለእኔ ብለው መሆኑን አይቼ አዘንኩ፡፡
👉 እኔ ለዚህች ኢትዮጵያ ለምትባለው አገር ምንድን ነው ያደረኩላት? እኛ እንጠይቅ ነበር፡፡ ደመወዝ ተጨመረልን ወይ ብለን፡፡ ቤት መንግስት ይሰጠን ይሆን ወይ ብለን፡፡ እዚያ ጋ ግን ደመወዝ የማይጠይቅ፣ ቤት ይሰጠኝ ይሆን ብሎ የማያስብ፣ ከፊት ለፊቱ ሞትን እያዬ ለአገሩ ክብር የሚገሰግሰውን የመከላከያ ሰራዊት አይቻለሁና ደስ ብሎኛል፡፡ እጅግ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡
👉 ከመደሰትም በላይ በእኔ ዙሪያ ያሉ ብዙ ወጣቶች አሉ፡፡እነዚያ ወጣቶች ብዙ ሊማሩበት ይገባል፡፡ ይሄን የምለው ለፕሮፖጋንዳ ትርፍ አይደለም፡፡ በሕይወት የኖርንባት እያንዳንዷ ቀን ትልቅ ትርጉም እንዲኖራ ከፈለግን ኢትዮጵያን እንወቃት፡፡ ለማወቅ ከፈለግን ደግሞ አገር መከላከያ ሰራዊት ውስጥ እንግባ እላለሁ፡፡ አመሰግናለሁ፡፡
“እናትና አባትህ ይክዱኛል ብለህ የማትጠብቅበት አይነት ሁኔታ ውስጥ በሰራዊቱ ላይ ክህደት ተፈጽሟል። ቤታችን ነው ሰላም ነው ባልንበት ቦታ በተደራጀ ሃይል አፈና ተካሂዶብናል”
👉 የጁንታው አመራሮች በቅርበት ይከታተሉን ስለነበር የአየር ሀይላችን እነርሱን ነጥሎ ጠባብ መንገድ ላይ በአየር ድብደባ ተሸከርካሪዎቻቸውን አቃጥሏል፤
👉 የጁንታው አመራሮች ወደኋላ ሲመለሱ ደግሞ ተሸከርካሪዎቻቸውን በመምታት መንገዱ እንዲዘጋባቸው አድርጓል፤
👉 የጁንታው አመራሮች መሄጃ በማጣታቸው የነበራቸውን ተሽከረካሪዎች እና ንብረት እየጣሉና እያንጠባጠቡ ሲበታተኑ መከላከያ ሰራዊታችን ደርሶ አብረውኝ የነበሩትን ሁሉ ነጻ አውጥቷል፤
👉 ሰራዊቱ የታፈኑትን ነጻ ሲያወጣ ጠላትና ወገንን የለየ ምርጥ ኦፕሬሽን አከናውኗል፤
ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ መንግስቴ
የሰሜን ዕዝ ምክትል ኦፕሬሽን አዛዥ
******************************
(ኢ ፕ ድ)
ሽሬ:- መከላከያ ሰራዊት በጁንታው ታጣቂዎች አማካኝነት የታፈኑትን የሰራዊቱ አመራርና አባላትን ነጻ ሲያወጣ ጠላትና ወገንን የለየ ምርጥ ኦፕሬሽን አከናውኗል ሲሉ ከታጋቾቹ መካከል አንዱ የነበሩት የሰሜን ዕዝ ምክትል ኦፕሬሽን አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ መንግስቴ ተናገሩ።
የሰሜን ዕዝ ምክትል ኦፕሬሽን አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ መንግስቴ እንደገለጹት፤ መከላከያ ሰራዊቱ ታጋቾችን እና የጁንታውን ታጣቂ ለመለየት የተጠቀመው እርምጃ የሚደነቅ ነው። የሰራዊቱ አመራርና አባላትን በማይጎዳ መልኩ ጥንቃቄ የተሞላበት ኦፕሬሽን በተሳካ ሁኔታ ፈጽሟል።
"መከላከያ ሰራዊታችን እኛ የታፈንነውን አመራርና አባላት ላይ አደጋ እንዳይደርስ ጥንቃቄ በተሞላው መንገድ እርምጃ ወስዷል። በተለይ የጁንታው አመራሮች በቅርበት ይከታተሉን ስለነበር እነርሱን በሚነጥል ሁኔታ በአየር ከፊት ጠባብ መንገድ ላይ ተሸከርካሪዎቻቸውን አቃጥሏል።
መከላከያ ሰራዊቱ የጁንታው አመራሮች ወደኋላ ሊመለሱ ሲሄዱ ከኋላ ተሸከርካሪዎቻቸውም በመምታት መንገዱ እንዲዘጋባቸው አድርጓል። በዚህ ወቅት የጁንታው አመራሮች መሄጃ በማጣታቸው የነበራቸውን ተሽከረካሪዎች እና ንብረት እየጣሉና እያንጠባጠቡ ሲበታተኑ መከላከያ ሰራዊታችን ደርሶ አብረውኝ የነበሩትን ሁሉ ታጋቾችን ነጻ አውጥቷል" በማለት የሰራዊቱን እርምጃ አወድሰዋል።
ሰራዊቱ የታፈኑትን ነጻ ሲያወጣ ጠላትና ወገንን የለየ ምርጥ ኦፕሬሽን አከናውኗል ያሉት ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ፤ መላው የኢትዮጵያ ህዝብም ደስተኛ የሆነበት እና ጥሩ ስራ የተከናወነበት ነው በማለት ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል። <<መከላከያ ሰራዊታችንን በግሌም ሆነ አብረውኝ በነበሩ አመራሮች ስም ላመሰግን እወዳለሁ። በመከላከያ ሰራዊታችን ኮርተንበታል>> ብለዋል።
በአፈናው ወቅት ስለነበረው ሁናቴ ሲያስረዱም “ስሜቱን መግለጽ ያጥረኛል። እናትና አባትህ ይክዱኛል ብለህ በማትጠብቅበት ሰዓት በሰራዊቱ ላይ ክህደት ተፈጽሟል። ቤታችን ነው ሰላም ነው ባልንበት ቦታ በተደራጀ ሃይል አፈና ተካሂዶብናል” ነው ያሉት።
የአፈናው ጊዜ በሙሉ በርካታ ውጣ ውረዶች ያሉት ነው፤ ረጅም የእግር ጉዞዎች በቀንም በሌሊትም ያለዕረፍት ነበረው። ዞሮ ዞሮ ህይወታችንን ካተረፉን የመከላከያ ሰራዊት ወንድሞቻችን ጋር ሆነን ታሪኩን በጽሁፍ በሰፊው የምናቀርበው ይሆናል በማለት ሁኔታውን በአጭሩ አስረድተዋል።
ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም ላይ በጁንታው ቡድን ታጣቂዎች ጥቃት ተፈጽሞባቸው የታፈኑት የሰሜን እዝ መከላከያ ሰራዊት አመራሮች ሽሬ ከተማ ሲደርሱ በሰራዊቱ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። በርካታ የሰራዊቱ አባላት ታፍነው የሰነበቱ አመራሮቹን እና ጓደኞቻቸውን ሲያገኙም ወደሰማይ በተተኮሰ የጥይት ድምጽ እና በጭፈራ ደስታቸውን ገልጸዋል።
ህዳር 30 ቀን ከሰዓት በኋላ የጁንታው ቡድን አጋቾች አዴት በተባለ አካባቢ በእግር ሲያጓጉዟቸው የነበሩትን ከ1ሺህ በላይ የሰራዊቱን መኮንኖች በመልቀቅ በየአቅጣጫው መበታተኑ ታውቋል። ታፍነው የሰነበቱ የሰራዊቱ አመራሮች መንግስት ላደረገው የህይወት አድን ጥረት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በጌትነት ተስፋማርያም
👉 የጁንታው አመራሮች በቅርበት ይከታተሉን ስለነበር የአየር ሀይላችን እነርሱን ነጥሎ ጠባብ መንገድ ላይ በአየር ድብደባ ተሸከርካሪዎቻቸውን አቃጥሏል፤
👉 የጁንታው አመራሮች ወደኋላ ሲመለሱ ደግሞ ተሸከርካሪዎቻቸውን በመምታት መንገዱ እንዲዘጋባቸው አድርጓል፤
👉 የጁንታው አመራሮች መሄጃ በማጣታቸው የነበራቸውን ተሽከረካሪዎች እና ንብረት እየጣሉና እያንጠባጠቡ ሲበታተኑ መከላከያ ሰራዊታችን ደርሶ አብረውኝ የነበሩትን ሁሉ ነጻ አውጥቷል፤
👉 ሰራዊቱ የታፈኑትን ነጻ ሲያወጣ ጠላትና ወገንን የለየ ምርጥ ኦፕሬሽን አከናውኗል፤
ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ መንግስቴ
የሰሜን ዕዝ ምክትል ኦፕሬሽን አዛዥ
******************************
(ኢ ፕ ድ)
ሽሬ:- መከላከያ ሰራዊት በጁንታው ታጣቂዎች አማካኝነት የታፈኑትን የሰራዊቱ አመራርና አባላትን ነጻ ሲያወጣ ጠላትና ወገንን የለየ ምርጥ ኦፕሬሽን አከናውኗል ሲሉ ከታጋቾቹ መካከል አንዱ የነበሩት የሰሜን ዕዝ ምክትል ኦፕሬሽን አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ መንግስቴ ተናገሩ።
የሰሜን ዕዝ ምክትል ኦፕሬሽን አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ መንግስቴ እንደገለጹት፤ መከላከያ ሰራዊቱ ታጋቾችን እና የጁንታውን ታጣቂ ለመለየት የተጠቀመው እርምጃ የሚደነቅ ነው። የሰራዊቱ አመራርና አባላትን በማይጎዳ መልኩ ጥንቃቄ የተሞላበት ኦፕሬሽን በተሳካ ሁኔታ ፈጽሟል።
"መከላከያ ሰራዊታችን እኛ የታፈንነውን አመራርና አባላት ላይ አደጋ እንዳይደርስ ጥንቃቄ በተሞላው መንገድ እርምጃ ወስዷል። በተለይ የጁንታው አመራሮች በቅርበት ይከታተሉን ስለነበር እነርሱን በሚነጥል ሁኔታ በአየር ከፊት ጠባብ መንገድ ላይ ተሸከርካሪዎቻቸውን አቃጥሏል።
መከላከያ ሰራዊቱ የጁንታው አመራሮች ወደኋላ ሊመለሱ ሲሄዱ ከኋላ ተሸከርካሪዎቻቸውም በመምታት መንገዱ እንዲዘጋባቸው አድርጓል። በዚህ ወቅት የጁንታው አመራሮች መሄጃ በማጣታቸው የነበራቸውን ተሽከረካሪዎች እና ንብረት እየጣሉና እያንጠባጠቡ ሲበታተኑ መከላከያ ሰራዊታችን ደርሶ አብረውኝ የነበሩትን ሁሉ ታጋቾችን ነጻ አውጥቷል" በማለት የሰራዊቱን እርምጃ አወድሰዋል።
ሰራዊቱ የታፈኑትን ነጻ ሲያወጣ ጠላትና ወገንን የለየ ምርጥ ኦፕሬሽን አከናውኗል ያሉት ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ፤ መላው የኢትዮጵያ ህዝብም ደስተኛ የሆነበት እና ጥሩ ስራ የተከናወነበት ነው በማለት ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል። <<መከላከያ ሰራዊታችንን በግሌም ሆነ አብረውኝ በነበሩ አመራሮች ስም ላመሰግን እወዳለሁ። በመከላከያ ሰራዊታችን ኮርተንበታል>> ብለዋል።
በአፈናው ወቅት ስለነበረው ሁናቴ ሲያስረዱም “ስሜቱን መግለጽ ያጥረኛል። እናትና አባትህ ይክዱኛል ብለህ በማትጠብቅበት ሰዓት በሰራዊቱ ላይ ክህደት ተፈጽሟል። ቤታችን ነው ሰላም ነው ባልንበት ቦታ በተደራጀ ሃይል አፈና ተካሂዶብናል” ነው ያሉት።
የአፈናው ጊዜ በሙሉ በርካታ ውጣ ውረዶች ያሉት ነው፤ ረጅም የእግር ጉዞዎች በቀንም በሌሊትም ያለዕረፍት ነበረው። ዞሮ ዞሮ ህይወታችንን ካተረፉን የመከላከያ ሰራዊት ወንድሞቻችን ጋር ሆነን ታሪኩን በጽሁፍ በሰፊው የምናቀርበው ይሆናል በማለት ሁኔታውን በአጭሩ አስረድተዋል።
ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም ላይ በጁንታው ቡድን ታጣቂዎች ጥቃት ተፈጽሞባቸው የታፈኑት የሰሜን እዝ መከላከያ ሰራዊት አመራሮች ሽሬ ከተማ ሲደርሱ በሰራዊቱ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። በርካታ የሰራዊቱ አባላት ታፍነው የሰነበቱ አመራሮቹን እና ጓደኞቻቸውን ሲያገኙም ወደሰማይ በተተኮሰ የጥይት ድምጽ እና በጭፈራ ደስታቸውን ገልጸዋል።
ህዳር 30 ቀን ከሰዓት በኋላ የጁንታው ቡድን አጋቾች አዴት በተባለ አካባቢ በእግር ሲያጓጉዟቸው የነበሩትን ከ1ሺህ በላይ የሰራዊቱን መኮንኖች በመልቀቅ በየአቅጣጫው መበታተኑ ታውቋል። ታፍነው የሰነበቱ የሰራዊቱ አመራሮች መንግስት ላደረገው የህይወት አድን ጥረት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በጌትነት ተስፋማርያም
ለምዕራብ ትግራይ ተፈናቃዮች 31 ሺ 500 ኩንታል የስንዴና የታሸጉ ምግቦች ድጋፍ ቀረበ
******^*****^*
(ኢ.ፕ.ድ)
ሽሬ:- ከምዕራብ ትግራይ አካባቢዎች ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚውል 31ሺ 500 ኩንታል ስንዴ እና የታሸጉ ምግቦች ድጋፍ መቅረቡን የብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ።
የብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አደጋ ምላሽና ክትትል ቡድን መሪ እና በትግራይ ክልል ለሚቀርበው ድጋፍ አስተባባሪ አቶ ታዬ ጌታቸው እንደገለጹት፤ በምዕራብ ትግራይ አካባቢዎች አፋጣኝ የምግብ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች ስንዴ እና ለህጻናት፣ እናቶችና አረጋውያን የሚሆኑ ፓስታ፣ ሩዝ፣ ዘይት፣ አልሚ ምግብ እና የማብሰያ ቁሳቁሶች ቀርቧል።
እንደ አቶ ታዬ ገለጻ፤ መንግስት ያቀረበውን ድጋፍ ለተፈናቃይ ዜጎች ለማከፋፈል በትግራይ ክልል ከተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር በጋራ እየተሰራ ይገኛል። በተለያዩ ማዕከላት ተጠልለው የሚገኙ ተፈናቃዮች አፋጣኝ ድጋፍ እንዲደረግላቸው ተለይተዋል። ማምረት እና መስራት የማይችሉ ዜጎች ጭምር ቤት ለቤት የምግብ ድጋፉ ይቀርብላቸዋል። አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል ተብለው የተለዩ 13ሺ ዜጎች ቅድሚያ ድጋፉ እየቀረበላቸው ይገኛል።
የሽሬ እንዳስላሴ ከተማ ጊዜያዊ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሃጎስ በርሄ በበኩላቸው እንደገለጹት ፤ ከምዕራብ ትግራይ ተፈናቅለው በሽሬ ከተማዋ የሚገኙ ዜጎች በዩኒቨርሲቲ እና በትምህርት ቤቶች ተጠልለው ይገኛሉ።
እንደ አቶ ሃጎስ ገለጻ፤ መንግስት ችግሩን ተገንዝቦ ለተፈናቃዮች እርዳታውን በተጠየቀ ጊዜ ቶሎ በማድረሱ ምስጋና ይገባዋል። ድጋፉን በፍትሃዊነት ለማከፋፈል እንዲቻል በጊዜያዊ አስተዳደሩከቀበሌ አንስቶ እስከ ከተማ አስተዳደር ጀምሮ የሰዎች ምደባ ተደርጓል።
በከተማ ደረጃ ህብረተሰቡን ለማረጋጋት እና ድጋፎችን ለማከፋፈል አምስት የካቢኔ አካላት እና 25 የወረዳ ምክር ቤት አባላት ተመርጠዋል። በየቀበሌው አምስት አመራር እና 15 ጊዜያዊ የምክር ቤት አባላት አሉ። በተጨማሪ የድጋፍ ክፍፍሉን የሚያስተባብሩ አካላት ከኅብረተሰቡ ተመርጠው በተቻለ መጠን ድጋፉ ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ጥረት እየተደረገ ይገኛል።
አሁን ላይ ሃብታሙም ድሃውም ህብረተሰብ የባንክ አገልግሎት ባለመኖሩ ምክንያት እኩል የሆኑበት አጋጣሚ አለ የሚሉት አቶ ሃጎስ፤ ይሁንና ችግሩን ቀስ በቀስ ለመፍታት ጥረት በማድረግ በቅድሚያ ግን ህጻናት፣ ጧሪ የሌላቸው አረጋውያን እና በልመና የሚተዳደሩ ዜጎች አስቸኳይ ድጋፉ እንደሚሰጣቸው አስረድተዋል። ድጋፉ ሲዳረስም የመንግስት ሰራተኞችን ጨምሮ ደመወዛቸው በባንክ ያሉ ነዋሪዎች እና ለሌሎች ዜጎች ድጋፍ ማቅረብ እንደሚቻል ገልጸዋል።
ከተለያዩ የፌዴራል ተቋማት የተላኩ ተወካዮች በትግራይ ክልል የሚኖሩ ዜጎች ያሉባቸውን የሰብአዊ ድጋፍ እና አስቸኳይ የመሰረተ ልማት አቅርቦቶች እንዲሁም ተያያዥ ችግሮች በቀጣይነት የሚፈቱበት ሁኔታ ላይ በትግራይ ከተቋቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር ተወያይተዋል።
ህብረተሰቡ በውሃ በኩል ያለበትን ችግር መፍትሄ እንዲያገኝ ከውሃ መስኖ ሚኒስቴር የመጡ ተወካዮች እንደሚያስተባብሩ ታውቋል። የህጻናት፣ እናቶችን እና አረጋውያን ጉዳዮችን ደግሞ የሴቶችና ህጻናት ሚኒስቴር ተወካዮች ያስተባብራሉ።
ቀድሞ በሴፍቲ ኔት ታግዘው ድጋፍ ሲያገኙ የነበሩ ስር የሰደደ የምድብ አቅርቦት ችግር ያለባቸውን ዜጎችን ጉዳይ ደግሞ የግብርና ሚኒስቴር እንደሚስተባብር ታውቋል።
በጌትነት ተስፋማርያም
******^*****^*
(ኢ.ፕ.ድ)
ሽሬ:- ከምዕራብ ትግራይ አካባቢዎች ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚውል 31ሺ 500 ኩንታል ስንዴ እና የታሸጉ ምግቦች ድጋፍ መቅረቡን የብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ።
የብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አደጋ ምላሽና ክትትል ቡድን መሪ እና በትግራይ ክልል ለሚቀርበው ድጋፍ አስተባባሪ አቶ ታዬ ጌታቸው እንደገለጹት፤ በምዕራብ ትግራይ አካባቢዎች አፋጣኝ የምግብ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች ስንዴ እና ለህጻናት፣ እናቶችና አረጋውያን የሚሆኑ ፓስታ፣ ሩዝ፣ ዘይት፣ አልሚ ምግብ እና የማብሰያ ቁሳቁሶች ቀርቧል።
እንደ አቶ ታዬ ገለጻ፤ መንግስት ያቀረበውን ድጋፍ ለተፈናቃይ ዜጎች ለማከፋፈል በትግራይ ክልል ከተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር በጋራ እየተሰራ ይገኛል። በተለያዩ ማዕከላት ተጠልለው የሚገኙ ተፈናቃዮች አፋጣኝ ድጋፍ እንዲደረግላቸው ተለይተዋል። ማምረት እና መስራት የማይችሉ ዜጎች ጭምር ቤት ለቤት የምግብ ድጋፉ ይቀርብላቸዋል። አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል ተብለው የተለዩ 13ሺ ዜጎች ቅድሚያ ድጋፉ እየቀረበላቸው ይገኛል።
የሽሬ እንዳስላሴ ከተማ ጊዜያዊ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሃጎስ በርሄ በበኩላቸው እንደገለጹት ፤ ከምዕራብ ትግራይ ተፈናቅለው በሽሬ ከተማዋ የሚገኙ ዜጎች በዩኒቨርሲቲ እና በትምህርት ቤቶች ተጠልለው ይገኛሉ።
እንደ አቶ ሃጎስ ገለጻ፤ መንግስት ችግሩን ተገንዝቦ ለተፈናቃዮች እርዳታውን በተጠየቀ ጊዜ ቶሎ በማድረሱ ምስጋና ይገባዋል። ድጋፉን በፍትሃዊነት ለማከፋፈል እንዲቻል በጊዜያዊ አስተዳደሩከቀበሌ አንስቶ እስከ ከተማ አስተዳደር ጀምሮ የሰዎች ምደባ ተደርጓል።
በከተማ ደረጃ ህብረተሰቡን ለማረጋጋት እና ድጋፎችን ለማከፋፈል አምስት የካቢኔ አካላት እና 25 የወረዳ ምክር ቤት አባላት ተመርጠዋል። በየቀበሌው አምስት አመራር እና 15 ጊዜያዊ የምክር ቤት አባላት አሉ። በተጨማሪ የድጋፍ ክፍፍሉን የሚያስተባብሩ አካላት ከኅብረተሰቡ ተመርጠው በተቻለ መጠን ድጋፉ ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ጥረት እየተደረገ ይገኛል።
አሁን ላይ ሃብታሙም ድሃውም ህብረተሰብ የባንክ አገልግሎት ባለመኖሩ ምክንያት እኩል የሆኑበት አጋጣሚ አለ የሚሉት አቶ ሃጎስ፤ ይሁንና ችግሩን ቀስ በቀስ ለመፍታት ጥረት በማድረግ በቅድሚያ ግን ህጻናት፣ ጧሪ የሌላቸው አረጋውያን እና በልመና የሚተዳደሩ ዜጎች አስቸኳይ ድጋፉ እንደሚሰጣቸው አስረድተዋል። ድጋፉ ሲዳረስም የመንግስት ሰራተኞችን ጨምሮ ደመወዛቸው በባንክ ያሉ ነዋሪዎች እና ለሌሎች ዜጎች ድጋፍ ማቅረብ እንደሚቻል ገልጸዋል።
ከተለያዩ የፌዴራል ተቋማት የተላኩ ተወካዮች በትግራይ ክልል የሚኖሩ ዜጎች ያሉባቸውን የሰብአዊ ድጋፍ እና አስቸኳይ የመሰረተ ልማት አቅርቦቶች እንዲሁም ተያያዥ ችግሮች በቀጣይነት የሚፈቱበት ሁኔታ ላይ በትግራይ ከተቋቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር ተወያይተዋል።
ህብረተሰቡ በውሃ በኩል ያለበትን ችግር መፍትሄ እንዲያገኝ ከውሃ መስኖ ሚኒስቴር የመጡ ተወካዮች እንደሚያስተባብሩ ታውቋል። የህጻናት፣ እናቶችን እና አረጋውያን ጉዳዮችን ደግሞ የሴቶችና ህጻናት ሚኒስቴር ተወካዮች ያስተባብራሉ።
ቀድሞ በሴፍቲ ኔት ታግዘው ድጋፍ ሲያገኙ የነበሩ ስር የሰደደ የምድብ አቅርቦት ችግር ያለባቸውን ዜጎችን ጉዳይ ደግሞ የግብርና ሚኒስቴር እንደሚስተባብር ታውቋል።
በጌትነት ተስፋማርያም
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በትግራይ ክልል የድርጅቱ ሰራተኞች ለፈጸሙት ድርጊት ይቅርታ ጠየቀ
*******************
( ኢ ፕ ድ)
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) በትግራይ ክልል የድርጅቱ ሰራተኞች ለፈጸሙት ድርጊት ይቅርታ መጠየቁን የሰላም ሚኒስቴር አስታወቀ።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ፍሰት ቃል አቀባይ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ሕዳር 29 ቀን 2013 ዓ.ም በትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ ለውጭ መገናኛ ብዙሃን መግለጫ መስጠታቸው የሚታወስ ነው።
በመግለጫው ላይ ከጋዜጠኞች ከተነሳው ጥያቄዎች አንዱ መንግስት በትግራይ ክልል በተመድ ሰራተኞች ላይ ተኩሷል መንግስት በዚህ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ ቢሰጥ የሚል ነበር።
አምባሳደር ሬድዋን በትግራይ ክልል የፍተሻ ጣቢያዎችን የጣሱ የተመድ ሰራተኞች ላይ መተኮሱንና በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ከተደረገ በኋላ መለቀቃቸውን ገልጸዋል።
የድርጅቱ ሰራተኞች ወዳልተፈቀደላቸው ቦታ ሲያመሩ እንደነበረና ሁለት የፍተሻ ጣቢያዎችን ካለፉ በኋላ ሶስተኛ የፍተሻ ጣቢያ ጥሰው ሊያልፉ ሲሞክሩ ነበር በቁጥጥር ስር የዋሉት።
ተመድን ጨምሮ ሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት የመንግስትን መመሪያ ማክበር እንደሚገባቸውና መንግስት ከስጋት ነጻ ናቸው ብሎ ቦታዎችን ከለየ በኋላ ሰብአዊ ድጋፍ ማድረግ እንደሚችሉ አምባሳደር ሬድዋን በመግለጫቸው አንስተው ነበር።
የኢፌዴሪ ሰላም ሚኒስቴር በተመድ ሰራተኞች ድርጊትና በፍተሻ ጣቢያው በተፈጠረው ክስተት ዙሪያ መግለጫ አውጥቷል።
ተመድ በትግራይ ክልል የድርጅቱ ሰራተኞች ለፈጸሙት ድርጊት መንግስትን ይቅርታ መጠየቁንም ሰላም ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መግለጫ አመልክቷል።
የተመድ የኢትዮጵያ የሰብአዊ ጉዳዮች አስተባባሪ ዶክተር ካትሪን ሶዚ የጠየቁትን ይቅርታ የኢትዮጵያ መንግስት መቀበሉን ገልጿል።
ተመድ የሰብአዊ ድጋፍ ትብብር የሚሸረሽሩና ከፍተኛ የአደጋ ስጋት የሚደቅኑ ተመሳሳይ ጥሰቶች ዳግም እንዳይፈጸሙ የሚያስችሉ ስርዓቶችን እንደሚዘረጋ መግለጹንም አመልክቷል።
መንግስት ሕዳር 20 ቀን 2013 ዓ.ም ከተመድ ጋር በደረሰው ስምምነት አማካኝነት በትግራይ ክልል ለሚደረገው ድጋፍ በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ነው የሚኒስቴሩ መግለጫ የሚያመለክተው።
በስምምነቱ መሰረት ድርጅቱ ከመንግስት ጋር በመሆን አስፈላጊውን የሰብአዊ ድጋፍ ማድረግ እንደሚችልም ጠቁሟል።
ዓለም አቀፍ የሰብአዊ እርዳታ ተቋማት በትግራይ ክልል አስቸኳይ የድጋፍ አቅርቦት እንዲደርስ ያላቸውን ፍላጎት መንግስት እንደሚረዳና ተቋማቱ ድጋፉን ማድረግ የሚችሉት ከፌዴራል ተቋማት አስፈላጊውን ፈቃድ ሲያገኙ እንደሆነ ሊረዱት እንደሚገባ ገልጿል።
ሁሉም የሰብአዊ ድጋፍ ሰራተኞች መንግስት ያወጣውን መመሪያ መከተል እንደሚገባቸውና መንግስት ሰራተኞቹና የድጋፍ አቅርቦቶች ደህንነታቸው እንዲጠበቅ ያለበትን ግዴታ እንደሚወጣም ነው የሰላም ሚኒስቴር ያስታወቀው።
የኢትዮጵያ መንግስት ከተመድ ኤጀንሲዎች ጋር ላለው ትብብርና ኤጀንሲዎቹ ለኢትዮጵያ የልማት ፕሮግራሞችና የአደጋ ስጋት ቅነሳ ስራዎች ለሚያደርጉት ወሳኝ ድጋፍ ትልቅ አክብሮት እንዳለውም ተጠቅሷል።
የኢትዮጵያ መንግስት በሚችለው አቅም በትግራይ ክልልና በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች ላሉ የሰብአዊ ጉዳይ ፈተናዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም ተገልጿል።
ዓለም አቀፍ የእርዳታ ተቋማት በአስፈላጊው ጊዜ ለተቸገሩ ዜጎች ለሚያደርጉት ወሳኝ ድጋፍ የኢትዮጵያ መንግስትና ሕዝብ ምስጋውን እንደሚገልጽ የሰላም ሚኒስቴር በመግለጫው ያተተው።
መንግስት በትግራይ ክልል ያለው የሕግ ማስከበር እርምጃ ተጠናቆ ተልዕኮው ወደ "ወንጀሎችን የማደንና መልሶ ግንባታ" ምዕራፍ መሸጋገሩን መግለጹ የሚታወስ ነው።
*******************
( ኢ ፕ ድ)
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) በትግራይ ክልል የድርጅቱ ሰራተኞች ለፈጸሙት ድርጊት ይቅርታ መጠየቁን የሰላም ሚኒስቴር አስታወቀ።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ፍሰት ቃል አቀባይ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ሕዳር 29 ቀን 2013 ዓ.ም በትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ ለውጭ መገናኛ ብዙሃን መግለጫ መስጠታቸው የሚታወስ ነው።
በመግለጫው ላይ ከጋዜጠኞች ከተነሳው ጥያቄዎች አንዱ መንግስት በትግራይ ክልል በተመድ ሰራተኞች ላይ ተኩሷል መንግስት በዚህ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ ቢሰጥ የሚል ነበር።
አምባሳደር ሬድዋን በትግራይ ክልል የፍተሻ ጣቢያዎችን የጣሱ የተመድ ሰራተኞች ላይ መተኮሱንና በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ከተደረገ በኋላ መለቀቃቸውን ገልጸዋል።
የድርጅቱ ሰራተኞች ወዳልተፈቀደላቸው ቦታ ሲያመሩ እንደነበረና ሁለት የፍተሻ ጣቢያዎችን ካለፉ በኋላ ሶስተኛ የፍተሻ ጣቢያ ጥሰው ሊያልፉ ሲሞክሩ ነበር በቁጥጥር ስር የዋሉት።
ተመድን ጨምሮ ሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት የመንግስትን መመሪያ ማክበር እንደሚገባቸውና መንግስት ከስጋት ነጻ ናቸው ብሎ ቦታዎችን ከለየ በኋላ ሰብአዊ ድጋፍ ማድረግ እንደሚችሉ አምባሳደር ሬድዋን በመግለጫቸው አንስተው ነበር።
የኢፌዴሪ ሰላም ሚኒስቴር በተመድ ሰራተኞች ድርጊትና በፍተሻ ጣቢያው በተፈጠረው ክስተት ዙሪያ መግለጫ አውጥቷል።
ተመድ በትግራይ ክልል የድርጅቱ ሰራተኞች ለፈጸሙት ድርጊት መንግስትን ይቅርታ መጠየቁንም ሰላም ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መግለጫ አመልክቷል።
የተመድ የኢትዮጵያ የሰብአዊ ጉዳዮች አስተባባሪ ዶክተር ካትሪን ሶዚ የጠየቁትን ይቅርታ የኢትዮጵያ መንግስት መቀበሉን ገልጿል።
ተመድ የሰብአዊ ድጋፍ ትብብር የሚሸረሽሩና ከፍተኛ የአደጋ ስጋት የሚደቅኑ ተመሳሳይ ጥሰቶች ዳግም እንዳይፈጸሙ የሚያስችሉ ስርዓቶችን እንደሚዘረጋ መግለጹንም አመልክቷል።
መንግስት ሕዳር 20 ቀን 2013 ዓ.ም ከተመድ ጋር በደረሰው ስምምነት አማካኝነት በትግራይ ክልል ለሚደረገው ድጋፍ በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ነው የሚኒስቴሩ መግለጫ የሚያመለክተው።
በስምምነቱ መሰረት ድርጅቱ ከመንግስት ጋር በመሆን አስፈላጊውን የሰብአዊ ድጋፍ ማድረግ እንደሚችልም ጠቁሟል።
ዓለም አቀፍ የሰብአዊ እርዳታ ተቋማት በትግራይ ክልል አስቸኳይ የድጋፍ አቅርቦት እንዲደርስ ያላቸውን ፍላጎት መንግስት እንደሚረዳና ተቋማቱ ድጋፉን ማድረግ የሚችሉት ከፌዴራል ተቋማት አስፈላጊውን ፈቃድ ሲያገኙ እንደሆነ ሊረዱት እንደሚገባ ገልጿል።
ሁሉም የሰብአዊ ድጋፍ ሰራተኞች መንግስት ያወጣውን መመሪያ መከተል እንደሚገባቸውና መንግስት ሰራተኞቹና የድጋፍ አቅርቦቶች ደህንነታቸው እንዲጠበቅ ያለበትን ግዴታ እንደሚወጣም ነው የሰላም ሚኒስቴር ያስታወቀው።
የኢትዮጵያ መንግስት ከተመድ ኤጀንሲዎች ጋር ላለው ትብብርና ኤጀንሲዎቹ ለኢትዮጵያ የልማት ፕሮግራሞችና የአደጋ ስጋት ቅነሳ ስራዎች ለሚያደርጉት ወሳኝ ድጋፍ ትልቅ አክብሮት እንዳለውም ተጠቅሷል።
የኢትዮጵያ መንግስት በሚችለው አቅም በትግራይ ክልልና በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች ላሉ የሰብአዊ ጉዳይ ፈተናዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም ተገልጿል።
ዓለም አቀፍ የእርዳታ ተቋማት በአስፈላጊው ጊዜ ለተቸገሩ ዜጎች ለሚያደርጉት ወሳኝ ድጋፍ የኢትዮጵያ መንግስትና ሕዝብ ምስጋውን እንደሚገልጽ የሰላም ሚኒስቴር በመግለጫው ያተተው።
መንግስት በትግራይ ክልል ያለው የሕግ ማስከበር እርምጃ ተጠናቆ ተልዕኮው ወደ "ወንጀሎችን የማደንና መልሶ ግንባታ" ምዕራፍ መሸጋገሩን መግለጹ የሚታወስ ነው።
ከታጋቾች አንደበት
👉 ዋናው ነገር የሃገር ጉዳይ ነው፤ እኛ ብንሞትም ብንኖርም ለሀገር ስለሆነ ችግር የለውም፤ ጓደኞቻችን ግን ነጻ አውጥተውናል፤
👉 የጁንታው ታጣቂዎች የሰራዊቱ አባላት ትጥቃቸውን እንዲፈቱ መልዕክት በግዳጅ እንዲያስተላልፉ አዘዟቸው፤
👉 “እኔ ትጥቄን ፈትቻለሁ እናንተም ፍቱ፤ እኔን ግን ከዚህ በኋላ አታገኙኝም” በሚል ለሰራዊቱ ውስጠ ወይራ መልዕክት አስተላለፉ፤
👉 በኦሮምኛ ደግሞ ለሰራዊቱ ትጥቅ እንዳይፈታ የሚያዝዝ መልዕክት አስተላለፋ፤
ብርጋዴር ጄኔራል ኑሩ ሙዘይን የመከላከያ ሰራዊት 20ኛ ክፍለጦር አዛዥ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
በጁንታው ቡድን ታግተው ከቆዩ የመከላከያ ሰራዊት አመራሮች መካከል አንዱ የነበሩት ብርጋዴር ጄኔራል ኑሩ ሙዘይን ናቸው። ብርጋዴር ጄኔራል ኑሩ በወቅቱ የጁንታው ታጣቂዎች የሰራዊቱ አባላት ትጥቃቸውን እንዲፈቱ መልዕክት በግዳጅ እንዲያስተላልፉ አዘዟቸው። እርሳቸውም “እኔ ትጥቄን ፈትቻለሁ እናንተም ፍቱ፤ እኔን ግን ከዚህ በኋላ አታገኙኝም” በሚል ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የሚገልጽ ውስጠ ወይራ መልዕክት አስተላለፉ። አክለውም በኦሮምኛ ለሰራዊቱ ትጥቅ እንዳይፈታ የሚያግዝ መልዕክት ማስተላለፋቸውን ያስታውሳሉ።
መከላከያ ሰራዊቱም ጥቃቱ ከተፈጸመ ማግስት ጀምሮ በመከላከልና የህግ ማስከበር እርምጃ በመፈጸም ህይወት የማዳን እና አጥፊዎቹን የመቅጣር እርምጃውን ገፋበት። በርካታ የሰራዊቱ አባላት እና አመራሮችም ከብዙ እንግልት በኋላ ከጁንታው እጅ ነጻ ወጡ። ከታጋቾች መካከል አንዱ የነበሩት ብርጋዴር ጄኔራል ኑሩ ነጻ ከወጡ በኋላ ሲቃ በተሞላበት ንግግራቸው ሁናቴውን አስረድተዋል።
<<ከሁሉ በፊት ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ለመከላከያ ሰራዊትም እንኳን እንኳን ለዚህ ድል አበቃን ፤ እኛንም ከአንድ ወር ልፋትና እንግልት በኋላ እንኳን በሰላም አገናኘን። ዋናው ነገር የሃገር ጉዳይ ነው፤ እኛ ብንሞትም ብንኖርም ለሀገር ስለሆነ ችግር የለውም በሚል ተስፋ ቆርጠን ነበር። ጓደኞቻችን ግን መስከረም 30 ቀን 2013 ዓ.ም ላይ ኦፕሬሽናቸውን በመፈጸም ነጻ አውጥተውናል።
በርካታ ቀናትን ያለምግብ እና ውሃ በተለያየ መልከአምድር ላይ ተንገላተናል። በርካታ የሰራዊት አባላትም ይህን እንግልት ተቋቁመን አሁን የደረስንበት ደረጃ በመድረሳችን በታጋቾች እና በእራሴ ስም ለመከላከያ ሰራዊት ሆነ ለኢትዮጵያ ህዝብ ምስጋና ማቅረብ እፈልጋለሁ።
በአጠቃላይ በሰራዊታችንም ሆነ በህዝባችን ሲከናወን የነበረውን ነገር በተለያየ መንገድ የሰማነው ስለሆነ እኛም ደስ ብሎናል። ለመከላከያ ሰራዊትም ሆነ ለኢትዮጵያ ህዝብ ለድል ያበቃችሁን አንድነታችሁን በማጠናከር የቀሩትን ስራዎችም እንድታጠናቅቁ አደራ ማለት እፈልጋለሁ፤
ለአንድ ወር ከስድስት ቀን በጁንታው ታጣቂዎች ጥቃት ከተፈጸመባቸው በኋላ ታግተው በረሃብና በእንግልተ የቆዩት የመከላከያ ሰራዊት መኮንኖች በሰራዊቱ አማካኘነት ነጻ ከወጡ በኋላ ህይወታቸውን ለማትረፍ ለተደረገው ጥንቃቄ የተሞላበት ጥረት ምስጋና አቅርበዋል።
በጌትነት ተስፋማርያም
👉 ዋናው ነገር የሃገር ጉዳይ ነው፤ እኛ ብንሞትም ብንኖርም ለሀገር ስለሆነ ችግር የለውም፤ ጓደኞቻችን ግን ነጻ አውጥተውናል፤
👉 የጁንታው ታጣቂዎች የሰራዊቱ አባላት ትጥቃቸውን እንዲፈቱ መልዕክት በግዳጅ እንዲያስተላልፉ አዘዟቸው፤
👉 “እኔ ትጥቄን ፈትቻለሁ እናንተም ፍቱ፤ እኔን ግን ከዚህ በኋላ አታገኙኝም” በሚል ለሰራዊቱ ውስጠ ወይራ መልዕክት አስተላለፉ፤
👉 በኦሮምኛ ደግሞ ለሰራዊቱ ትጥቅ እንዳይፈታ የሚያዝዝ መልዕክት አስተላለፋ፤
ብርጋዴር ጄኔራል ኑሩ ሙዘይን የመከላከያ ሰራዊት 20ኛ ክፍለጦር አዛዥ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
በጁንታው ቡድን ታግተው ከቆዩ የመከላከያ ሰራዊት አመራሮች መካከል አንዱ የነበሩት ብርጋዴር ጄኔራል ኑሩ ሙዘይን ናቸው። ብርጋዴር ጄኔራል ኑሩ በወቅቱ የጁንታው ታጣቂዎች የሰራዊቱ አባላት ትጥቃቸውን እንዲፈቱ መልዕክት በግዳጅ እንዲያስተላልፉ አዘዟቸው። እርሳቸውም “እኔ ትጥቄን ፈትቻለሁ እናንተም ፍቱ፤ እኔን ግን ከዚህ በኋላ አታገኙኝም” በሚል ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የሚገልጽ ውስጠ ወይራ መልዕክት አስተላለፉ። አክለውም በኦሮምኛ ለሰራዊቱ ትጥቅ እንዳይፈታ የሚያግዝ መልዕክት ማስተላለፋቸውን ያስታውሳሉ።
መከላከያ ሰራዊቱም ጥቃቱ ከተፈጸመ ማግስት ጀምሮ በመከላከልና የህግ ማስከበር እርምጃ በመፈጸም ህይወት የማዳን እና አጥፊዎቹን የመቅጣር እርምጃውን ገፋበት። በርካታ የሰራዊቱ አባላት እና አመራሮችም ከብዙ እንግልት በኋላ ከጁንታው እጅ ነጻ ወጡ። ከታጋቾች መካከል አንዱ የነበሩት ብርጋዴር ጄኔራል ኑሩ ነጻ ከወጡ በኋላ ሲቃ በተሞላበት ንግግራቸው ሁናቴውን አስረድተዋል።
<<ከሁሉ በፊት ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ለመከላከያ ሰራዊትም እንኳን እንኳን ለዚህ ድል አበቃን ፤ እኛንም ከአንድ ወር ልፋትና እንግልት በኋላ እንኳን በሰላም አገናኘን። ዋናው ነገር የሃገር ጉዳይ ነው፤ እኛ ብንሞትም ብንኖርም ለሀገር ስለሆነ ችግር የለውም በሚል ተስፋ ቆርጠን ነበር። ጓደኞቻችን ግን መስከረም 30 ቀን 2013 ዓ.ም ላይ ኦፕሬሽናቸውን በመፈጸም ነጻ አውጥተውናል።
በርካታ ቀናትን ያለምግብ እና ውሃ በተለያየ መልከአምድር ላይ ተንገላተናል። በርካታ የሰራዊት አባላትም ይህን እንግልት ተቋቁመን አሁን የደረስንበት ደረጃ በመድረሳችን በታጋቾች እና በእራሴ ስም ለመከላከያ ሰራዊት ሆነ ለኢትዮጵያ ህዝብ ምስጋና ማቅረብ እፈልጋለሁ።
በአጠቃላይ በሰራዊታችንም ሆነ በህዝባችን ሲከናወን የነበረውን ነገር በተለያየ መንገድ የሰማነው ስለሆነ እኛም ደስ ብሎናል። ለመከላከያ ሰራዊትም ሆነ ለኢትዮጵያ ህዝብ ለድል ያበቃችሁን አንድነታችሁን በማጠናከር የቀሩትን ስራዎችም እንድታጠናቅቁ አደራ ማለት እፈልጋለሁ፤
ለአንድ ወር ከስድስት ቀን በጁንታው ታጣቂዎች ጥቃት ከተፈጸመባቸው በኋላ ታግተው በረሃብና በእንግልተ የቆዩት የመከላከያ ሰራዊት መኮንኖች በሰራዊቱ አማካኘነት ነጻ ከወጡ በኋላ ህይወታቸውን ለማትረፍ ለተደረገው ጥንቃቄ የተሞላበት ጥረት ምስጋና አቅርበዋል።
በጌትነት ተስፋማርያም
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በመቀሌ ከከፍተኛ የጦር መኮንኖች ጋር ተወያዩ
**********
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የሕግ ማስከበር ሂደቱን ከመሩ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ጋር መቀሌ ላይ ተወያይተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ በአካባቢው ለሕዝቡ እየተደረገ ያለው ሠብዓዊ ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
መቀሌ ላይ በተካሄደው ውይይት ጄኔራል አበባው ታደሰና ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌን ጨምሮ በርካታ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ተሳትፈዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ መሆኑን በውይይቱ ላይ ተናግረዋል።
በጁንታው ላይ የተገኘው ድል የሚያኩራራ ሳይሆን 'የምንማርበትና የኢትዮጵያን ቀጣይነት የምናረጋግጥበት ነው' ማለታቸውን ኢዜአ ከስፍራው ዘግቧል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የትግራይን ክልል መልሶ ለማቋቋም መንግስት በሙሉ ትኩረት ይሰራል ብለዋል።
በአካባቢው ለሕዝቡ የተጀመረው ሠብዓዊ ድጋፍ እንደሚቀጥልና መንግስት በሕግ ማስከበሩ ወቅት ጉዳት የደረሰባቸውን እንደሚደግፍ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተጨማሪም ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አመራር አባላት ጋር በወቅታዊ የክልሉ ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል።
በተለይም ክልሉን መልሶ ለማቋቋም በሚሰሩ ስራዎች ላይ መምከራቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
**********
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የሕግ ማስከበር ሂደቱን ከመሩ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ጋር መቀሌ ላይ ተወያይተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ በአካባቢው ለሕዝቡ እየተደረገ ያለው ሠብዓዊ ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
መቀሌ ላይ በተካሄደው ውይይት ጄኔራል አበባው ታደሰና ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌን ጨምሮ በርካታ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ተሳትፈዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ መሆኑን በውይይቱ ላይ ተናግረዋል።
በጁንታው ላይ የተገኘው ድል የሚያኩራራ ሳይሆን 'የምንማርበትና የኢትዮጵያን ቀጣይነት የምናረጋግጥበት ነው' ማለታቸውን ኢዜአ ከስፍራው ዘግቧል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የትግራይን ክልል መልሶ ለማቋቋም መንግስት በሙሉ ትኩረት ይሰራል ብለዋል።
በአካባቢው ለሕዝቡ የተጀመረው ሠብዓዊ ድጋፍ እንደሚቀጥልና መንግስት በሕግ ማስከበሩ ወቅት ጉዳት የደረሰባቸውን እንደሚደግፍ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተጨማሪም ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አመራር አባላት ጋር በወቅታዊ የክልሉ ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል።
በተለይም ክልሉን መልሶ ለማቋቋም በሚሰሩ ስራዎች ላይ መምከራቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በመቀሌ ቆይታቸው
👉ከሀገር መከለከያ ሰራዊት አመራሮች ጋርም በድሉ ዙሪያ ውይይት
አድርገዋል፤ በዚሁ ወቅት የተናገሯቸው ዋና ዋና ነጥቦች
*********************
(ኢ ፕ ድ)
👉 ጠላት በርከት ያሉ የእኛን መኮንኖች ይዞ ስለቆየ እነሱን ይዞ ነበር የሚንቀሳቀሰው፤ ስለሆነም ማታ ማታ በምናደርገው ኦፕሬሸን በርከት ያለ ሰው በሚኖርበት ሰአት ይህ ሀይል የእኛ ሃይል ሊሆን ይችላል በሚል ያቆየናቸው ሚሳየሎችና ቦንቦች ዛሬ ያኮሩኛል። ያንን ተጠቅመን ቢሆን ኖሮ ዛሬ በመካከላችን ያሉትን መኮንኖች አናያቸውም ነበር፤
👉 ይህ ኢትዮጵያን የመታደግ ኢትዮጵያን የማኩራት ብቃት፤ ተልዕኮን በአጭር ጊዜ የመፈጸም ብቃት የተቋማችን የሁልጊዜ አርማ መሆን አለበት፤
👉 በተደጋጋሚ እንዳልኩት የመከላከያ ሰራዊት የብልጽግና ሰራዊት አይደለም፤ የአብይ ሰራዊት አይደለም፤ የኢትዮጵያ ህዝብ መከታና ኩራት የሆነ ወታደር ነው፤
👉 እኛ የምንፈልገው ፕሮፌሽናል ጠንካራ አርሚ እንድትሆኑ እንጂ ለአንድ ፓርቲ የሚገዛ እንድትሆኑ አንፈልግም፤
👉 ኢትዮጵያ ከብልጽግናም ከፓርቲም በላይ ናት፤ ትልቋን አገር የመታደግ ሃላፊነት ተጥሎባችኋል፤
👉 ፖለቲካው የተበላሸ ነው፤ የማያውቀውን የደም ስር እና ሀረግ እየፈለገ የሚቧደን ነው፤ እናንተ ግን ጀግኖች ብቻ ሳትሆኑ ንጹህ ኢትዮጵያዊ ናችሁ፤
👉 ጦርነቱን ስንጀምር በጣም ብዙ ሰዎች በአጠረ ጊዜም ብቻ ሳይሆን ማሸነፍም ይከብዳል የሚል ግምግማና ግምት ይናገሩ ነበር፤ ይሄ አልሆነም፤
👉 እኛን የሚዋጉን ሰዎች ዘመናዊ ጦርነት አያውቁም፤ የጦርነት ሳይንስ አያውቁም፤ የሚያውቁት የሽምቅ ውጊያ ነው፤ እሱ የሽፍቶች ውጊያ ነው፤ እሱ በሰው ሃይልና በተተኳሽ ቁጥር ማሸነፍ የምናረጋግጠብት ውጊያ ነው፤
👉 የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ስንት ሺህ ወጣት እንዳስከፈለን ስንት ጊዜ እንደወሰደ እናውቀዋልን፤ ይሄ የአሁኑ ኦፕሬሽን ደግሞ በምን ያህል ባነሰ የሰው ሃይልና መስዋዕትነት ለድል እንደበቃን ታውቃላችሁ፤
👉 ከሁመራ መቀሌ በእግር መጓዝ ማለት ብዙዎች አዲስ አባበ ሆነው ዝም ብሎ ጀግና እንደሚሉት አይደለም፤ በዚህ መልክዐ ምድር በዚህ ሙቀት ስንቅና ትጥቅ ተሸክሞ ይሄንን ያህል ጉዞ መጓዝ የማንም አገር ወታደር አይደግመውም፤
👉 ይሄንን ጀግንነት ወንጀለኞችን በመያዝ መድገም ያስፈልጋል፤ ወታደሩ የተሰጠውን ተልዕኮ መቶ በመቶ አሳክቷል፤ የሚቀረው ወንጀለኞችን ለህግ ማቅረብ ነው እሱንም በፍጥነት ማከናወን ያስፈልጋል፤
👉 ወንጀለኞችን ለህግ ለማቅረብ የትግራይ ህዝብ ሃላፊነት አለበት፤ የተደበቁትን ሰዎች፣ ከመኪና ወርደው እግረኛ የሆኑትን ሰዎች በመያዝ ለሀገር መከላከያ ሰራዊትና ለትግራይ አስተዳደር ማስረከብ አለበት፤ ያ ካልሆነ ወታደሩ አገር የመጠገን ጊዜውን ወንጀለኛ በማደን ስለሚያሳልፍ የሚጎዳው ራሱ ህዝቡ ነው፤
👉 ከኢትዮጵያ መንግስት ልማት ድጋፍ መጠየቅ ተገቢ ነው፤ ነገር ግን ወንጀለኞችን አሳልፈው መስጠት ደግሞ ግዴታ ነው፤ ይህ ስምምነት ካለ ነው ስራችንን በአጭር ጊዜ በማከናወን ወደልማት የምንገባው፤
በርካታ ወንጀለኞችን እንደተያዙ፤ የተቀሩትም የት እንዳሉ መረጃው አለኝ፤
👉 የሀገር መከላከያ ሰራዊት የኢትዮጵያ ህዝቦች ኩራት መሆኑን፤ በዚህ ቀጣና የሚነሳ ማንኛውንም አደጋ በሚፈለገው ልክ ለመመከት የሚያስችል ብቃት ያለው ጦር መሆኑን በድጋሜ አረጋግጧል፤
👉 የጁንታው ሃይል በቁጥር ከ80 ሺህ በላይ ይገመታል፤ አዳዲስ መሳሪያዎችን ታጥቋል፤ ከፍተኛ የተተኳሽ ዲፖዎች ነበሩት፤ ኮማንዶ ሜካናይዝድ ሮኬት መተኮስ የሚችሉም ሰዎችነበሩት፤ እኛ ግን መቀሌ እስከገባንበት ቀን ድረስ ሮኬት አልተኮስንም በእኛና በጁንታው መካከል ያለው ልዩነት ይሄ ነው፤ እኛ ያልተኮስነው ህዝባችን እዚህ እንዳለ ስለምናውቅ ነው፤
👉 እኛ ሮኬት የተጠቀምነው ጁንታው መቀሌን ለቆ በረሀ ለበረሃ ለማምለጥ ሲሞክር ነው፤ ይሄ የእውነት ይሄ የፍትሃዊነት ልዩነታችን አሸናፊ አድርጎናል፤
👉ከሀገር መከለከያ ሰራዊት አመራሮች ጋርም በድሉ ዙሪያ ውይይት
አድርገዋል፤ በዚሁ ወቅት የተናገሯቸው ዋና ዋና ነጥቦች
*********************
(ኢ ፕ ድ)
👉 ጠላት በርከት ያሉ የእኛን መኮንኖች ይዞ ስለቆየ እነሱን ይዞ ነበር የሚንቀሳቀሰው፤ ስለሆነም ማታ ማታ በምናደርገው ኦፕሬሸን በርከት ያለ ሰው በሚኖርበት ሰአት ይህ ሀይል የእኛ ሃይል ሊሆን ይችላል በሚል ያቆየናቸው ሚሳየሎችና ቦንቦች ዛሬ ያኮሩኛል። ያንን ተጠቅመን ቢሆን ኖሮ ዛሬ በመካከላችን ያሉትን መኮንኖች አናያቸውም ነበር፤
👉 ይህ ኢትዮጵያን የመታደግ ኢትዮጵያን የማኩራት ብቃት፤ ተልዕኮን በአጭር ጊዜ የመፈጸም ብቃት የተቋማችን የሁልጊዜ አርማ መሆን አለበት፤
👉 በተደጋጋሚ እንዳልኩት የመከላከያ ሰራዊት የብልጽግና ሰራዊት አይደለም፤ የአብይ ሰራዊት አይደለም፤ የኢትዮጵያ ህዝብ መከታና ኩራት የሆነ ወታደር ነው፤
👉 እኛ የምንፈልገው ፕሮፌሽናል ጠንካራ አርሚ እንድትሆኑ እንጂ ለአንድ ፓርቲ የሚገዛ እንድትሆኑ አንፈልግም፤
👉 ኢትዮጵያ ከብልጽግናም ከፓርቲም በላይ ናት፤ ትልቋን አገር የመታደግ ሃላፊነት ተጥሎባችኋል፤
👉 ፖለቲካው የተበላሸ ነው፤ የማያውቀውን የደም ስር እና ሀረግ እየፈለገ የሚቧደን ነው፤ እናንተ ግን ጀግኖች ብቻ ሳትሆኑ ንጹህ ኢትዮጵያዊ ናችሁ፤
👉 ጦርነቱን ስንጀምር በጣም ብዙ ሰዎች በአጠረ ጊዜም ብቻ ሳይሆን ማሸነፍም ይከብዳል የሚል ግምግማና ግምት ይናገሩ ነበር፤ ይሄ አልሆነም፤
👉 እኛን የሚዋጉን ሰዎች ዘመናዊ ጦርነት አያውቁም፤ የጦርነት ሳይንስ አያውቁም፤ የሚያውቁት የሽምቅ ውጊያ ነው፤ እሱ የሽፍቶች ውጊያ ነው፤ እሱ በሰው ሃይልና በተተኳሽ ቁጥር ማሸነፍ የምናረጋግጠብት ውጊያ ነው፤
👉 የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ስንት ሺህ ወጣት እንዳስከፈለን ስንት ጊዜ እንደወሰደ እናውቀዋልን፤ ይሄ የአሁኑ ኦፕሬሽን ደግሞ በምን ያህል ባነሰ የሰው ሃይልና መስዋዕትነት ለድል እንደበቃን ታውቃላችሁ፤
👉 ከሁመራ መቀሌ በእግር መጓዝ ማለት ብዙዎች አዲስ አባበ ሆነው ዝም ብሎ ጀግና እንደሚሉት አይደለም፤ በዚህ መልክዐ ምድር በዚህ ሙቀት ስንቅና ትጥቅ ተሸክሞ ይሄንን ያህል ጉዞ መጓዝ የማንም አገር ወታደር አይደግመውም፤
👉 ይሄንን ጀግንነት ወንጀለኞችን በመያዝ መድገም ያስፈልጋል፤ ወታደሩ የተሰጠውን ተልዕኮ መቶ በመቶ አሳክቷል፤ የሚቀረው ወንጀለኞችን ለህግ ማቅረብ ነው እሱንም በፍጥነት ማከናወን ያስፈልጋል፤
👉 ወንጀለኞችን ለህግ ለማቅረብ የትግራይ ህዝብ ሃላፊነት አለበት፤ የተደበቁትን ሰዎች፣ ከመኪና ወርደው እግረኛ የሆኑትን ሰዎች በመያዝ ለሀገር መከላከያ ሰራዊትና ለትግራይ አስተዳደር ማስረከብ አለበት፤ ያ ካልሆነ ወታደሩ አገር የመጠገን ጊዜውን ወንጀለኛ በማደን ስለሚያሳልፍ የሚጎዳው ራሱ ህዝቡ ነው፤
👉 ከኢትዮጵያ መንግስት ልማት ድጋፍ መጠየቅ ተገቢ ነው፤ ነገር ግን ወንጀለኞችን አሳልፈው መስጠት ደግሞ ግዴታ ነው፤ ይህ ስምምነት ካለ ነው ስራችንን በአጭር ጊዜ በማከናወን ወደልማት የምንገባው፤
በርካታ ወንጀለኞችን እንደተያዙ፤ የተቀሩትም የት እንዳሉ መረጃው አለኝ፤
👉 የሀገር መከላከያ ሰራዊት የኢትዮጵያ ህዝቦች ኩራት መሆኑን፤ በዚህ ቀጣና የሚነሳ ማንኛውንም አደጋ በሚፈለገው ልክ ለመመከት የሚያስችል ብቃት ያለው ጦር መሆኑን በድጋሜ አረጋግጧል፤
👉 የጁንታው ሃይል በቁጥር ከ80 ሺህ በላይ ይገመታል፤ አዳዲስ መሳሪያዎችን ታጥቋል፤ ከፍተኛ የተተኳሽ ዲፖዎች ነበሩት፤ ኮማንዶ ሜካናይዝድ ሮኬት መተኮስ የሚችሉም ሰዎችነበሩት፤ እኛ ግን መቀሌ እስከገባንበት ቀን ድረስ ሮኬት አልተኮስንም በእኛና በጁንታው መካከል ያለው ልዩነት ይሄ ነው፤ እኛ ያልተኮስነው ህዝባችን እዚህ እንዳለ ስለምናውቅ ነው፤
👉 እኛ ሮኬት የተጠቀምነው ጁንታው መቀሌን ለቆ በረሀ ለበረሃ ለማምለጥ ሲሞክር ነው፤ ይሄ የእውነት ይሄ የፍትሃዊነት ልዩነታችን አሸናፊ አድርጎናል፤
የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ መቀሌ ላይ ሆነው መግለጫ ሰጥተዋል
****************
(ኢ ፕ ድ)
ከጁንታው መደምሰስ በኋላ በመላ ኢትዮጵያ ሰላም መስፈኑን የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ አስታወቁ።
ላለፉት ሁለትና ሶስት አመታት ራሱን እያደራጃ በመላ አገሪቷ ግጭት እየለኮሰ የቆየው የህወሓት ጁንታ ከተደመሰሰ በኋላ በመላ ኢትዮጵያ ሰላም መስፈኑን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ዛሬ መቀሌ ላይ ሆነው በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።
እንደ ጄኔራል ብርሃኑ ገለጻ፤ ጁንታው በመደምሰሱ የኢትዮጰያ ህዝብ እፎይታ አግኝቷል፤ በመላ አገሪቱ አሁን ሰላም ነው።
ቀደም ባሉት ሁለትና ሶስት አመታት በየቦታው እነሱ ግጭት ይለኩሱ እንደነበረ ያስታወሱት ጄኔራል ብርሃኑ፤ በአሁኑ ወቅት እነሱ በመመታታቸው ምክንያት ሁሉም አካባቢ እፎይታ ሰፍኗል ሲሉም ነው ያስታወቁት።
“የኢትዮጵያ ህዝብ ከእነዚህ መሰሪና በጣም አስቸጋሪ ሰዎች ተገላግሏል” ያሉት ጄኔራል ብርሃኑ፤ የትግራይ ህዝብም ነጻ ወጥቷል፤ ከዚህ በሁዋላ እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ማግኘት የሚገባውና በጁንታው ተቋርጠው የነበሩ የመሰረተ ልማት ስራዎች በፍጥነት ይከናወናሉ ብለዋል።
ጁንታው ላለፉት ሶስት አመታት ህግ መንግስቱ የሚፈቅድለትን መብት በመጠቀም ራሱን በልዩ ሃይል ስም ሲያደራጅ መቆየቱን፤ በቅርብ ቀናትም አዲስ አበባ እንደሚገቡ ለህዝቡ መንገራቸውን፤ ለጎረቤት አገራትም 250 ሺ ሰራዊት አደራጅተናል፤ ሰሜን ዕዝን ደምስሰናል ትጥቅ ወስደናል ስለዚህ ፌዴራል መንግስት አቅም የለውም ከአሁን በሁዋላ ኢትዮጵያ በእኛ እጅ ናት በሚል ውስጥ ለውስጥ ፕሮፖጋንዳ ሰርተዋል” ያሉት ጄኔራሉ መከላከያ ሰራዊት ይህንን የትምክህት፣ የገዥ መደብና የድንቁርና አስተሳሰብ አምክኖታል ብለዋል።
****************
(ኢ ፕ ድ)
ከጁንታው መደምሰስ በኋላ በመላ ኢትዮጵያ ሰላም መስፈኑን የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ አስታወቁ።
ላለፉት ሁለትና ሶስት አመታት ራሱን እያደራጃ በመላ አገሪቷ ግጭት እየለኮሰ የቆየው የህወሓት ጁንታ ከተደመሰሰ በኋላ በመላ ኢትዮጵያ ሰላም መስፈኑን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ዛሬ መቀሌ ላይ ሆነው በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።
እንደ ጄኔራል ብርሃኑ ገለጻ፤ ጁንታው በመደምሰሱ የኢትዮጰያ ህዝብ እፎይታ አግኝቷል፤ በመላ አገሪቱ አሁን ሰላም ነው።
ቀደም ባሉት ሁለትና ሶስት አመታት በየቦታው እነሱ ግጭት ይለኩሱ እንደነበረ ያስታወሱት ጄኔራል ብርሃኑ፤ በአሁኑ ወቅት እነሱ በመመታታቸው ምክንያት ሁሉም አካባቢ እፎይታ ሰፍኗል ሲሉም ነው ያስታወቁት።
“የኢትዮጵያ ህዝብ ከእነዚህ መሰሪና በጣም አስቸጋሪ ሰዎች ተገላግሏል” ያሉት ጄኔራል ብርሃኑ፤ የትግራይ ህዝብም ነጻ ወጥቷል፤ ከዚህ በሁዋላ እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ማግኘት የሚገባውና በጁንታው ተቋርጠው የነበሩ የመሰረተ ልማት ስራዎች በፍጥነት ይከናወናሉ ብለዋል።
ጁንታው ላለፉት ሶስት አመታት ህግ መንግስቱ የሚፈቅድለትን መብት በመጠቀም ራሱን በልዩ ሃይል ስም ሲያደራጅ መቆየቱን፤ በቅርብ ቀናትም አዲስ አበባ እንደሚገቡ ለህዝቡ መንገራቸውን፤ ለጎረቤት አገራትም 250 ሺ ሰራዊት አደራጅተናል፤ ሰሜን ዕዝን ደምስሰናል ትጥቅ ወስደናል ስለዚህ ፌዴራል መንግስት አቅም የለውም ከአሁን በሁዋላ ኢትዮጵያ በእኛ እጅ ናት በሚል ውስጥ ለውስጥ ፕሮፖጋንዳ ሰርተዋል” ያሉት ጄኔራሉ መከላከያ ሰራዊት ይህንን የትምክህት፣ የገዥ መደብና የድንቁርና አስተሳሰብ አምክኖታል ብለዋል።
የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎችን የልማትና የጸጥታ ጥያቄዎችን ምላሽ ለመስጠት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የከተማዋ ጊዜያዊ አስተዳደር ከንቲባ አስታወቁ
********************
(ኢ ፕ ድ)
የከተማዋ ከንቲባ አቶ አታክልቲ ኃይለስላሴ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዛሬ እንደተናገሩት፤ ከህግ ማስከበር ዘመቻው ጋር ተያይዞ ጁንታው ሆን ብሎ በከተማዋ ዝርፊያ እንዲፈጸም አድርጓል፤ የመንግስት አገልግሎት እንዲቋረጥ ተደርጓል። ይህንን ተከትሎ የተፈጠረውን የነዋሪዎችን የልማትና የጸጥታ ስጋት ለመቅረፍ አስተዳደሩ ከመከለከያ ሰራዊት ጋር በመሆን የተጠናከረ ስራ እያከናወነ ይገኛል።
በመጀመሪያ ከዝርፊያ ጋር ተያይዞ የነበሩት ሁኔታዎች አሁን ላይ ቀንሰዋል ያሉት ከንቲባው፤ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ውስጥ የሚገኙ ሰነዶችን ለማጥፋትና ለመውሰድ ሆን ተብለው በጁንታው አማካኝነት እንዲዘረፉ ተደርገዋል ብለዋል።
የከተማ አስተዳደሩ የከንቲባ ጽፈት ቤት፣ የሕዝብ አገልግሎት መስጫዎች፣ የፍትህ፣ የማዘጋጃ ቤቶች፣ ፍርድ ቤቶች አጠቃላይ አገልግሎት የሚሰጡባቸው ዶክመንቶችን አዘርፈዋቸዋል ያሉት ከንቲባው፤ ከዚያ በኋላ ተዘርፎ ነው እንዲባል ተቋማቱ ክፍት ተትተዋል፤ ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም ሌሎች ዘራፊዎች እየገቡ ኮምፒውተሮችና አንዳንድ ነገሮችን መዝረፋቸውን አብራርተዋል።
በወንጀል ተይዘው እስር ላይ የነበሩ በርካታ ሰዎች መቀሌ ላይ ተሰብስበው እንዲለቀቁ ስለተደረገ የግለሰቦች ሱቆች ሳይቀሩ እንዲዘረፉ ተደርጓል ያሉት ከንቲባው፤ የዚህ ዝርፊያ ዓላማም ህዝቡ መከላከያ ሰራዊት ላይ እምነት እንዲያጣና በዚህ የተነሳ ወደ ስጋት እንዲገባ መሆኑን አብራርተዋል።
የመከላከያ ሰራዊት መቀሌ ከተማ ከገባ በኋላ ከመከላከያ አመራሮች፣ ከክልሉ ጊዜያዊ መስተዳድር ከፍተኛ አመራሮች ጋር ቁጭ ብለን በመነጋገርና በመወያየት ቅድሚያ ሰጥተን መስራት ያለብን ጉዳይ ምንድን ነው? የሚለውን በቅደም ተከተል አውጥተን በመስራት ላይ እንገኛለን” ያሉት ከንቲባው፤ የሕዝቡ ዋና ዋና ጥያቄዎች የነበሩት የመብራት፣ እና የውሃ አገልገሎት ሙሉ በሙሉ ምላሽ እንዲያገኝም የተደረገ ሲሆን የስልክ አገልግሎትም በከፊል መመለሱን አስታውቀዋል።
የከተማ ውስጥ የታክሲ የትራንስፖርት አገልግሎት እና ሌሎች የመስሪያ ቤት አገልግሎቶች በመጀመር ላይ ይገኛሉ ያሉት ከንቲባው፤ አብዛኛው አገልግሎት የሚሰጡ የገበያ ቦታዎች መከፈታቸውንና ህዝቡም ከስጋት እየወጣ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴው መመለስ መጀመሩን አስታውቀዋል።
በየክፍለከተማው በተዋቀረው የአስተዳደር አካል በተመረጡ ተወካዮች፣ በአስተዳደሩ አመራር አማካኝነት ድጋፍ ለሚፈልጉ የከተማዋ ነዋሪዎች እርዳታ በማከፋፈል ላይ ነው የምንገኘው ያሉት ከንቲባው፤ የሕክምና ቁሳቁሶችም ለህክምና ተቋማት በማድረስ ላይ መሆናቸውንና ሆስፒታሎቹ በሙሉ በመደበኛ ስራቸው ላይ እንደሆኑ አብራርተዋል።
ጎደሉ የሚባሉ ነገሮች ካሉም በየጊዜው ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ቅድሚያ ሰጥተን በመስራት ላይ ነው የምንገኘው ያሉት አቶ አታክልቲ፤ በመረጃ ማጣት ምክንያት ውዥንብር ውስጥ የገባው የህብረተሰብ ክፍል አሁን ላይ መብራት በመለቀቁ ምክንያት እወነታውን እየተረዳ ወደመደበኛ እንቅስቃሴው መመለስ መጀመሩን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ተናግረዋል።
በመሀመድ ሁሴን
********************
(ኢ ፕ ድ)
የከተማዋ ከንቲባ አቶ አታክልቲ ኃይለስላሴ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዛሬ እንደተናገሩት፤ ከህግ ማስከበር ዘመቻው ጋር ተያይዞ ጁንታው ሆን ብሎ በከተማዋ ዝርፊያ እንዲፈጸም አድርጓል፤ የመንግስት አገልግሎት እንዲቋረጥ ተደርጓል። ይህንን ተከትሎ የተፈጠረውን የነዋሪዎችን የልማትና የጸጥታ ስጋት ለመቅረፍ አስተዳደሩ ከመከለከያ ሰራዊት ጋር በመሆን የተጠናከረ ስራ እያከናወነ ይገኛል።
በመጀመሪያ ከዝርፊያ ጋር ተያይዞ የነበሩት ሁኔታዎች አሁን ላይ ቀንሰዋል ያሉት ከንቲባው፤ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ውስጥ የሚገኙ ሰነዶችን ለማጥፋትና ለመውሰድ ሆን ተብለው በጁንታው አማካኝነት እንዲዘረፉ ተደርገዋል ብለዋል።
የከተማ አስተዳደሩ የከንቲባ ጽፈት ቤት፣ የሕዝብ አገልግሎት መስጫዎች፣ የፍትህ፣ የማዘጋጃ ቤቶች፣ ፍርድ ቤቶች አጠቃላይ አገልግሎት የሚሰጡባቸው ዶክመንቶችን አዘርፈዋቸዋል ያሉት ከንቲባው፤ ከዚያ በኋላ ተዘርፎ ነው እንዲባል ተቋማቱ ክፍት ተትተዋል፤ ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም ሌሎች ዘራፊዎች እየገቡ ኮምፒውተሮችና አንዳንድ ነገሮችን መዝረፋቸውን አብራርተዋል።
በወንጀል ተይዘው እስር ላይ የነበሩ በርካታ ሰዎች መቀሌ ላይ ተሰብስበው እንዲለቀቁ ስለተደረገ የግለሰቦች ሱቆች ሳይቀሩ እንዲዘረፉ ተደርጓል ያሉት ከንቲባው፤ የዚህ ዝርፊያ ዓላማም ህዝቡ መከላከያ ሰራዊት ላይ እምነት እንዲያጣና በዚህ የተነሳ ወደ ስጋት እንዲገባ መሆኑን አብራርተዋል።
የመከላከያ ሰራዊት መቀሌ ከተማ ከገባ በኋላ ከመከላከያ አመራሮች፣ ከክልሉ ጊዜያዊ መስተዳድር ከፍተኛ አመራሮች ጋር ቁጭ ብለን በመነጋገርና በመወያየት ቅድሚያ ሰጥተን መስራት ያለብን ጉዳይ ምንድን ነው? የሚለውን በቅደም ተከተል አውጥተን በመስራት ላይ እንገኛለን” ያሉት ከንቲባው፤ የሕዝቡ ዋና ዋና ጥያቄዎች የነበሩት የመብራት፣ እና የውሃ አገልገሎት ሙሉ በሙሉ ምላሽ እንዲያገኝም የተደረገ ሲሆን የስልክ አገልግሎትም በከፊል መመለሱን አስታውቀዋል።
የከተማ ውስጥ የታክሲ የትራንስፖርት አገልግሎት እና ሌሎች የመስሪያ ቤት አገልግሎቶች በመጀመር ላይ ይገኛሉ ያሉት ከንቲባው፤ አብዛኛው አገልግሎት የሚሰጡ የገበያ ቦታዎች መከፈታቸውንና ህዝቡም ከስጋት እየወጣ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴው መመለስ መጀመሩን አስታውቀዋል።
በየክፍለከተማው በተዋቀረው የአስተዳደር አካል በተመረጡ ተወካዮች፣ በአስተዳደሩ አመራር አማካኝነት ድጋፍ ለሚፈልጉ የከተማዋ ነዋሪዎች እርዳታ በማከፋፈል ላይ ነው የምንገኘው ያሉት ከንቲባው፤ የሕክምና ቁሳቁሶችም ለህክምና ተቋማት በማድረስ ላይ መሆናቸውንና ሆስፒታሎቹ በሙሉ በመደበኛ ስራቸው ላይ እንደሆኑ አብራርተዋል።
ጎደሉ የሚባሉ ነገሮች ካሉም በየጊዜው ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ቅድሚያ ሰጥተን በመስራት ላይ ነው የምንገኘው ያሉት አቶ አታክልቲ፤ በመረጃ ማጣት ምክንያት ውዥንብር ውስጥ የገባው የህብረተሰብ ክፍል አሁን ላይ መብራት በመለቀቁ ምክንያት እወነታውን እየተረዳ ወደመደበኛ እንቅስቃሴው መመለስ መጀመሩን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ተናግረዋል።
በመሀመድ ሁሴን
ግምታዊ ዋጋቸው አንድ ቢሊዮን 356 ሚሊዮን 119ሺህ የገቢና ወጪ ኮንትሮባንድ ዕቃዎች ተያዙ
*****************************
(ኢ ፕ ድ)
በአምስት ወራት ውስጥ አንድ ቢሊዮን 356 ሚሊዮን 119ሺህ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው ገቢና ወጪ ኮንትሮባንድ ዕቃዎች መያዛቸውን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የንግድ ውድድሩን ፍትሀዊ ለማድረግና የፀረ-ኮንትሮባንድ እንቅስቃሴውን ለቆመጣጠር የገቢዎች ሚኒስቴርና የጉምሩክ ኮሚሽን ባደረጉት እንቅስቃሴ ባለፉት አምስት ወራት ከሀምሌ እስከ ህዳር 30/2013 ዓ/ም ግምታዊ ዋጋቸው አንድ ቢሊዮን 356 ሚሊዮን 118 ሺ ብር የሆነ የወጪና የገቢ የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን መቆጣጠር ተችሏል፡፡
ግምታዊ ዋጋቸው 981 ሚሊዬን 590 ሺህ የሚገመት የገቢ ኮንትሮባንድ ለመያዝ ታቅዶ አንድ ቢሊየን 100 ሚሊዬን 631 ሺህ ብር የሚገመት ገቢ ኮንትሮባንድን ተይዟል፡፡ ከባለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ24 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡
በተመሳሳይ 134 ሚሊዬን 708 ሲህ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው ወጪ ኮንትሮባንድ ለመያዝ ታቅዶ 255 ሚሊዬን 487 ሺህ ዋጋ የሚያወጡ ወጪ ኮንትሮባንድ ተይዘዋል፡፡ አፈፃፀሙ 190 በመቶ ነው፡፡ ከባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 107 ሚሊዬን 276 ሺህ ብልጫ ሲኖረው የ72 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡
በበአምስት ወራት ግምታዊ ዋጋቸው አንድ ቢሊዬን 116 ሚሊዬን 298 ሺህ የሆነ ወጪና ገቢ ኮንትሮባንድን ለመያዝ ታቅዶ ግምታዊ ዋጋቸው አንድ ቢሊዬን 356 ሚሊዬን 118ሺህ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው ወጪና ገቢ ኮንትሮባንድ ለመያዝ ተችሏል፡፡
እነዚህ የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን ለመያዝ ቀን እና ሌሊት በመስራት ትልቅ አስተዋፅኦ ላበረከቱት የጉምሩክ ኮሚሽን፣ የጉምሩክ ኬላ እና መቆጣጠርያ ጣቢያ አመራርና ሠራተኞች እንዲሁም የአገር መከላከያ ሠራዊት አባላት፣ የፌደራልና የክልል የፀጥታ ሀይሎችና ጥቆማ በመስጠት ለተባበሩ አካላት ሁሉ የገቢዎች ሚኒስቴር ምስጋናውን እያቀረበ በቀጣይ ወራትም ህገ ወጥ ንግድና ኮንትሮባንድን በመከላከል የንግድ ውድድሩን ፍትሀዊ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ ከገቢዎች ሚኒስቴር የጠገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
*****************************
(ኢ ፕ ድ)
በአምስት ወራት ውስጥ አንድ ቢሊዮን 356 ሚሊዮን 119ሺህ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው ገቢና ወጪ ኮንትሮባንድ ዕቃዎች መያዛቸውን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የንግድ ውድድሩን ፍትሀዊ ለማድረግና የፀረ-ኮንትሮባንድ እንቅስቃሴውን ለቆመጣጠር የገቢዎች ሚኒስቴርና የጉምሩክ ኮሚሽን ባደረጉት እንቅስቃሴ ባለፉት አምስት ወራት ከሀምሌ እስከ ህዳር 30/2013 ዓ/ም ግምታዊ ዋጋቸው አንድ ቢሊዮን 356 ሚሊዮን 118 ሺ ብር የሆነ የወጪና የገቢ የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን መቆጣጠር ተችሏል፡፡
ግምታዊ ዋጋቸው 981 ሚሊዬን 590 ሺህ የሚገመት የገቢ ኮንትሮባንድ ለመያዝ ታቅዶ አንድ ቢሊየን 100 ሚሊዬን 631 ሺህ ብር የሚገመት ገቢ ኮንትሮባንድን ተይዟል፡፡ ከባለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ24 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡
በተመሳሳይ 134 ሚሊዬን 708 ሲህ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው ወጪ ኮንትሮባንድ ለመያዝ ታቅዶ 255 ሚሊዬን 487 ሺህ ዋጋ የሚያወጡ ወጪ ኮንትሮባንድ ተይዘዋል፡፡ አፈፃፀሙ 190 በመቶ ነው፡፡ ከባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 107 ሚሊዬን 276 ሺህ ብልጫ ሲኖረው የ72 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡
በበአምስት ወራት ግምታዊ ዋጋቸው አንድ ቢሊዬን 116 ሚሊዬን 298 ሺህ የሆነ ወጪና ገቢ ኮንትሮባንድን ለመያዝ ታቅዶ ግምታዊ ዋጋቸው አንድ ቢሊዬን 356 ሚሊዬን 118ሺህ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው ወጪና ገቢ ኮንትሮባንድ ለመያዝ ተችሏል፡፡
እነዚህ የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን ለመያዝ ቀን እና ሌሊት በመስራት ትልቅ አስተዋፅኦ ላበረከቱት የጉምሩክ ኮሚሽን፣ የጉምሩክ ኬላ እና መቆጣጠርያ ጣቢያ አመራርና ሠራተኞች እንዲሁም የአገር መከላከያ ሠራዊት አባላት፣ የፌደራልና የክልል የፀጥታ ሀይሎችና ጥቆማ በመስጠት ለተባበሩ አካላት ሁሉ የገቢዎች ሚኒስቴር ምስጋናውን እያቀረበ በቀጣይ ወራትም ህገ ወጥ ንግድና ኮንትሮባንድን በመከላከል የንግድ ውድድሩን ፍትሀዊ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ ከገቢዎች ሚኒስቴር የጠገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
በዘንድሮው የመኸር እርሻ እስካሁን በ10 ሚሊዮን ሄክታር ላይ ያለው ሰብል መሰብሰቡ ተገለጸ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
ከክልሎች በተሰበሰበው መረጃ መሰረት የዘንድሮው የመኸር ወቅት በዘር ከተሸፈነው 13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር ውስጥ እስካሁን 10 ሚሊዮን የሚጠጋ መሬት ላይ ያለው ሰብል መሰብሰቡን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የእርሻ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ማንደፍሮ ንጉሴ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት የዘንድሮው የመኸር እርሻ በምርትና ምርታማነት በኩል እጅግ ጥሩና ተስፋ ሰጪ ነው፡፡
እንደ ዶክተር ማንደፍሮ ገለፃ በዘር የተሸፈነው መሬት 13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር ሲሆን ከዚህ ውስጥ ደግሞ ሁሉም መረጃ ተጠናቅቆ ባይገባም 10 ሚሊዮን የሚጠጋ ሄክታር መሬት ላይ ያለው ሰብል ተሰብስቧል፡፡ ከዚህ ጋር ታያይዞም አሁን ያለው የሰብል ይዞታ የምርታማነት መጠን በጣም ጥሩ በሚባል ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ያሳያል፡፡
ለዚህ የመኸር ወቅት ውጤታማ መሆን የነበረው የዝናብ መጠን ለሰብል ምርታነማነት የሚመች መሆኑ ተጠቃሽ ነው ያሉት ዶክተር ማንደፍሮ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በኩልም ለግብርና ሥራው አጋዥ ሊሆኑ የሚችሉ ግብዓቶችን በማቅረብ ረገድ ሰፊ ሥራ መሠራቱን አብራርተዋል፡፡
በመኸር የሥራ ወቅት በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍሎች የጎርፍ አደጋዎች መብዛትና የአምበጣ መከሰት በአገሪቱ በተለይም በግብርና ሥራው ላይ ከፍተኛ የሆነ መደናገጥን ፈጥሮ የነበረ ቢሆንም ተጽዕኗቸው ግን የተፈሩትን ያህል አልነበሩም ብለዋል ዶክተር ማንደፍሮ፡፡
እንደ ዶክተር ማንደፍሮ ገለፃ ማሳቸው በጎርፍ የተወሰደባቸው። በአምበጣ የተወረረባቸው አርሶ አደሮች ነበሩ በግለሰብ ደረጃም ከፍተኛ የሆነ ጉዳት አድርሷል፡፡ ነገር ግን እንደ አገር በመኸሩ እርሻ ይገኛል ተብሎ ከታሰበው ውጤት አንፃር ሲገመገም ግን ያን ያህል ከባድ ተጽዕኖ አድርሷል ለማለት እንደማይቻል አብራርተዋል፡፡
https://www.press.et/Ama/?p=37393
*******************
(ኢ ፕ ድ)
ከክልሎች በተሰበሰበው መረጃ መሰረት የዘንድሮው የመኸር ወቅት በዘር ከተሸፈነው 13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር ውስጥ እስካሁን 10 ሚሊዮን የሚጠጋ መሬት ላይ ያለው ሰብል መሰብሰቡን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የእርሻ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ማንደፍሮ ንጉሴ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት የዘንድሮው የመኸር እርሻ በምርትና ምርታማነት በኩል እጅግ ጥሩና ተስፋ ሰጪ ነው፡፡
እንደ ዶክተር ማንደፍሮ ገለፃ በዘር የተሸፈነው መሬት 13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር ሲሆን ከዚህ ውስጥ ደግሞ ሁሉም መረጃ ተጠናቅቆ ባይገባም 10 ሚሊዮን የሚጠጋ ሄክታር መሬት ላይ ያለው ሰብል ተሰብስቧል፡፡ ከዚህ ጋር ታያይዞም አሁን ያለው የሰብል ይዞታ የምርታማነት መጠን በጣም ጥሩ በሚባል ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ያሳያል፡፡
ለዚህ የመኸር ወቅት ውጤታማ መሆን የነበረው የዝናብ መጠን ለሰብል ምርታነማነት የሚመች መሆኑ ተጠቃሽ ነው ያሉት ዶክተር ማንደፍሮ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በኩልም ለግብርና ሥራው አጋዥ ሊሆኑ የሚችሉ ግብዓቶችን በማቅረብ ረገድ ሰፊ ሥራ መሠራቱን አብራርተዋል፡፡
በመኸር የሥራ ወቅት በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍሎች የጎርፍ አደጋዎች መብዛትና የአምበጣ መከሰት በአገሪቱ በተለይም በግብርና ሥራው ላይ ከፍተኛ የሆነ መደናገጥን ፈጥሮ የነበረ ቢሆንም ተጽዕኗቸው ግን የተፈሩትን ያህል አልነበሩም ብለዋል ዶክተር ማንደፍሮ፡፡
እንደ ዶክተር ማንደፍሮ ገለፃ ማሳቸው በጎርፍ የተወሰደባቸው። በአምበጣ የተወረረባቸው አርሶ አደሮች ነበሩ በግለሰብ ደረጃም ከፍተኛ የሆነ ጉዳት አድርሷል፡፡ ነገር ግን እንደ አገር በመኸሩ እርሻ ይገኛል ተብሎ ከታሰበው ውጤት አንፃር ሲገመገም ግን ያን ያህል ከባድ ተጽዕኖ አድርሷል ለማለት እንደማይቻል አብራርተዋል፡፡
https://www.press.et/Ama/?p=37393
www.press.et
በዘንድሮው የመኸር እርሻ እስካሁን በ10 ሚሊዮን ሄክታር ላይ ያለው ሰብል መሰብሰቡ ተገለጸ | የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት
ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በጦር ኃይሎች ሪፈራል ሆስፒታል ተገኝተዉ በህግ ማስከበር ዘመቻዉ የተካፈሉ የመከላከያ አባላትን ጎበኙ
****************************
(ኢ ፕ ድ)
የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ከመከላከያ ድጋፍ አሰባሳቢ የሚኒስትሮች አብይ ኮሚቴ አባላት ጋር በመሆን በጦር ኃይሎች ሪፈራል ሆስፒታል ተገኝተዉ በህግ ማስከበር ዘመቻዉ የተካፈሉ ጀግና የመከላከያ አባላትን ጎብኝተዋል።
ሚኒስትሯ በጉብኝቱ ወቅት እንደገለጹት፤ እዚህ የተገኘነዉ በአጥንታቸዉና በደማቸዉ ስለ ሀገራቸዉና ህዝባቸ ዋጋ የከፈሉ ወገኖቻችንን ባይመጥንም አክብሮታችንን እና አብሮነታችን ለመግለጽ ነዉ ብለዋል።
የህግ የማስከበር ዘመቻው ብዙ ትምህርት የወሰድንበት ነዉ ያሉት ወ/ሮ ሙፈሪሃት፣ ዘመቻዉ ሀገርን የመዉደድ ምስጢር ምን ያህል መሆኑን ያየንበት ነዉ ብለዋል። ለዘላቂ ሰላም የህግ የበላይነትን ማስከበር ዋነኛ ተግባር መሆኑን ገልፀዉ ከዚህ በኋላ በአብሮነት የተሰጠንን ኃላፊነት እንድንወጣ መስመር ያስያዘ ሂደት ነው ብለዋል።
በህግ ማስከበር ዘመቻዉ የተሳተፋትን የመከላከያ ሰራዊት አባላት፣ የአማራና የአፋር ልዩ ኃይል ጨምሮ በሂደቱ የተሳተፉትን ሁሉ በመከላከያ ድጋፍ አሰባሳቢ የሚኒስትሮች አብይ ኮሚቴ ስም አመስግነዋል።
በጉብኝቱ የመከላከያ ድጋፍ አሰባሳቢ የሚኒስትሮች ኮሚቴ ሰብሳቢ የሰላም ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚልን ጨምሮ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ፣ የትራንስፖርት ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ፣ የመከላከያ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ማርታ ሉዊጂ እንዲሁም የሰራዊቱ ከፍተኛ አመራሮች መሳፋቸውን ከሰላም ሚኒስትር የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
****************************
(ኢ ፕ ድ)
የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ከመከላከያ ድጋፍ አሰባሳቢ የሚኒስትሮች አብይ ኮሚቴ አባላት ጋር በመሆን በጦር ኃይሎች ሪፈራል ሆስፒታል ተገኝተዉ በህግ ማስከበር ዘመቻዉ የተካፈሉ ጀግና የመከላከያ አባላትን ጎብኝተዋል።
ሚኒስትሯ በጉብኝቱ ወቅት እንደገለጹት፤ እዚህ የተገኘነዉ በአጥንታቸዉና በደማቸዉ ስለ ሀገራቸዉና ህዝባቸ ዋጋ የከፈሉ ወገኖቻችንን ባይመጥንም አክብሮታችንን እና አብሮነታችን ለመግለጽ ነዉ ብለዋል።
የህግ የማስከበር ዘመቻው ብዙ ትምህርት የወሰድንበት ነዉ ያሉት ወ/ሮ ሙፈሪሃት፣ ዘመቻዉ ሀገርን የመዉደድ ምስጢር ምን ያህል መሆኑን ያየንበት ነዉ ብለዋል። ለዘላቂ ሰላም የህግ የበላይነትን ማስከበር ዋነኛ ተግባር መሆኑን ገልፀዉ ከዚህ በኋላ በአብሮነት የተሰጠንን ኃላፊነት እንድንወጣ መስመር ያስያዘ ሂደት ነው ብለዋል።
በህግ ማስከበር ዘመቻዉ የተሳተፋትን የመከላከያ ሰራዊት አባላት፣ የአማራና የአፋር ልዩ ኃይል ጨምሮ በሂደቱ የተሳተፉትን ሁሉ በመከላከያ ድጋፍ አሰባሳቢ የሚኒስትሮች አብይ ኮሚቴ ስም አመስግነዋል።
በጉብኝቱ የመከላከያ ድጋፍ አሰባሳቢ የሚኒስትሮች ኮሚቴ ሰብሳቢ የሰላም ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚልን ጨምሮ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ፣ የትራንስፖርት ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ፣ የመከላከያ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ማርታ ሉዊጂ እንዲሁም የሰራዊቱ ከፍተኛ አመራሮች መሳፋቸውን ከሰላም ሚኒስትር የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ጁንታው ከመከላከያ ዘርፎ ለጥፋት ዓላማ ይጠቀምባቸው የነበሩ መሳሪያዎች ተጠግነው ወደ አገልግሎት እየተመለሱ ናቸው
************************
(ኢ ፕ ድ)
ጁንታው ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ዘርፎ ለጥፋት ዓላማው ሲጠቀምባቸው የነበሩ የተለያዩ መሳሪያዎች ተጠግነው ወደ አገልግሎት በመመለስ ላይ መሆናቸው ተገለጸ።
የምዕራብ ግንባር የጥገና ኃላፊ ሌተናል ኮሎኔል አባተ ተስፋዬ እንደገለጹት፤ ጁንታው ከመከላከያ ሰራዊት ዘርፎ ለጥፋት ዓላማው ሲጠቀምባቸው የነበሩ በርካታ የሀገር ሀብቶች ከየመንገዱ እየተሰበሰቡ ተጠግነው ወደ አገልግሎት በመመለስ ላይ ናቸው።
እንደ ሌተናል ኮሎኔል አባተ ገለጻ፤ ጁንታው ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም መከላከያ ሰራዊቱ ላይ ጥቃት ሲከፍት ታንኮች፣ መድፎች እና በርካታ ከባድ መሳሪያዎችን ዘርፏል። ከባድ መሳሪያዎቹን ከዘረፈ በኋላ ይዞ ለመዋጋት ቢያስብም በመከላከያ ሰራዊቱ ጥንቃቄ የተሞላበት እርምጃ እና በአየር ኃይል ኢላማቸውን የጠበቁ እርምጃዎች ምክንያት መሳሪያዎቹን እየጣለ ሊፈረጥጥ ግድ ሆኖበታል። አንዳንድ መሳሪያዎቹን በከፊል ሲያወድም የተቀሩትን ግን በየአስፓልት ዳሩ እና በየጫካው አስቀምጦ እግሬ አውጪኝ ብሏል።
ከሃዲው ቡድን ከመከላከያ ሰራዊቱ የደረሰበትን እርምጃ መቋቋም ባለመቻሉ ከሽሬ አንስቶ እስከ ሽራሮ እና ተንቤን ድረስ በየመንገዱ ያንጠባጠባቸው ከባድ ተሽከርካሪዎች፣ የተለያየ አቅም ያላቸው መድፎች፣ ሎቤዶች እና ቢኤም መሳሪያዎች ተጓጉዘው ወደሽሬ የጥገና ማዕከል እየገቡ ይገኛሉ ያሉት ሌተናል ኮሎኔል አባተ፣ የጥገና ባለሙያዎችም መሳሪያዎቹን በመፈተሽ ዳግም ወደስራ ለማስገባት በመረባረብ ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
በርካታ ከባድ መሳሪያዎች እና ተሽከርካሪዎችም ከጥገናቸው በኋላ የተሳካ ሙከራ ተደርጎባቸው ወደስራ መመለሳቸውን ሌተናል ኮሎኔል አባተ ተስፋዬ ተናግረዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=37380
************************
(ኢ ፕ ድ)
ጁንታው ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ዘርፎ ለጥፋት ዓላማው ሲጠቀምባቸው የነበሩ የተለያዩ መሳሪያዎች ተጠግነው ወደ አገልግሎት በመመለስ ላይ መሆናቸው ተገለጸ።
የምዕራብ ግንባር የጥገና ኃላፊ ሌተናል ኮሎኔል አባተ ተስፋዬ እንደገለጹት፤ ጁንታው ከመከላከያ ሰራዊት ዘርፎ ለጥፋት ዓላማው ሲጠቀምባቸው የነበሩ በርካታ የሀገር ሀብቶች ከየመንገዱ እየተሰበሰቡ ተጠግነው ወደ አገልግሎት በመመለስ ላይ ናቸው።
እንደ ሌተናል ኮሎኔል አባተ ገለጻ፤ ጁንታው ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም መከላከያ ሰራዊቱ ላይ ጥቃት ሲከፍት ታንኮች፣ መድፎች እና በርካታ ከባድ መሳሪያዎችን ዘርፏል። ከባድ መሳሪያዎቹን ከዘረፈ በኋላ ይዞ ለመዋጋት ቢያስብም በመከላከያ ሰራዊቱ ጥንቃቄ የተሞላበት እርምጃ እና በአየር ኃይል ኢላማቸውን የጠበቁ እርምጃዎች ምክንያት መሳሪያዎቹን እየጣለ ሊፈረጥጥ ግድ ሆኖበታል። አንዳንድ መሳሪያዎቹን በከፊል ሲያወድም የተቀሩትን ግን በየአስፓልት ዳሩ እና በየጫካው አስቀምጦ እግሬ አውጪኝ ብሏል።
ከሃዲው ቡድን ከመከላከያ ሰራዊቱ የደረሰበትን እርምጃ መቋቋም ባለመቻሉ ከሽሬ አንስቶ እስከ ሽራሮ እና ተንቤን ድረስ በየመንገዱ ያንጠባጠባቸው ከባድ ተሽከርካሪዎች፣ የተለያየ አቅም ያላቸው መድፎች፣ ሎቤዶች እና ቢኤም መሳሪያዎች ተጓጉዘው ወደሽሬ የጥገና ማዕከል እየገቡ ይገኛሉ ያሉት ሌተናል ኮሎኔል አባተ፣ የጥገና ባለሙያዎችም መሳሪያዎቹን በመፈተሽ ዳግም ወደስራ ለማስገባት በመረባረብ ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
በርካታ ከባድ መሳሪያዎች እና ተሽከርካሪዎችም ከጥገናቸው በኋላ የተሳካ ሙከራ ተደርጎባቸው ወደስራ መመለሳቸውን ሌተናል ኮሎኔል አባተ ተስፋዬ ተናግረዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=37380
ጁንታዎቹ ኢትዮጵያን የማፈራረስና ድሮ የነበረውን የዝርፊያ ፍላጎታቸውን ለማስቀጠል፤ በተቻለ መጠን የተዳከመ ወይም የተበተነ መንግስት እንዲኖር ለማድረግና አገሪቱን ወደ እርስበርስ ጦርነት እንድትገባ ለማድረግ ነበር በመከላከያ ላይ ጥቃት የፈፀሙት፤
👉 በመንግስት ከፍተኛ አመራር ቦታ ላይ የነበሩ የጁንታው ሰዎች የሚዘርፉትን ገንዘብ በራሳቸው ስም አያደርጉትም ነበር፤ አብረዋቸው በሚሰሩ ሌሎች ግለሰቦች ስም እያደረጉ ነበር የሚጠቀሙት፤
አቶ ብናልፍ አንዷለም የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
👉 ለውጥ ያስፈልጋል የሚል ግምገማና ክርክር ሲደረግ፣ ህወሓት ከፍተኛ ተፅእኖ ለመፍጠር ሲጥር ነበር፤ ለውጡ በሚፈለገው አቅጣጫ እንዳይሄድ እንቅፋት እየሆነ በአንድ አጀንዳ ላይ ተወያይተን የውሳኔዎቹ ሃሳብ በመግለጫ ከወጡ በኋላ ህወሓት ለብቻው ወጥቶ እንደገና ሌላ መግለጫ ያወጣል፤
👉 አብዮታዊ ዲሞክራሲ በሚል ፍልስፍና ጠላትና ወዳጅ ብሎ የሚለይ፣ ሰዎችን በአመለካከታቸው ብቻ ይሄኛው ጠላቴ ነው፤ ሌላኛው ደግሞ ወዳጄ ብሎ የሚያስቀምጥ ነበር፤
👉 በሕዝቦች መካከል የጥላቻ ግድግዳ ፈጥሯል፤ የሚገርመው ጠላት ወይም ወዳጅ ከሚለው ውጭ ሌላ ሶስተኛ መንገድ አለ ብሎ አያምንም፤
👉 የህወሻት ቡድን «የለውጥ ኃይሉ ስልጣኑን ለማራዘም ሲል ነው ብልፅግናን የሚያቋቁመው፤ አሀዳዊ መንግስት ነው፤ የድሮውን ስርዓት ለመመለስ ነው፤ የፌደራል ስርዓቱን ለማፍረስ ነው» የሚሉ የማያቋርጥ ዘመቻ ሲያካሂድ ነበር፤
👉 በ2012ዓ.ም ሊካሄድ የነበረው ምርጫ እንዲራዘም ሲደረግ፤ «ስልጣን ለማራዘም ነው» የሚሉ በርካታ የስም ማጥፋት ዘመቻቸውን ማድረጋቸውን ቀጠሉ፤ ግን እነሱ ስለተቃወሙት ተግባራዊ ከመሆን አልቀረም፤ እናም ይሄን ተከትሎም ይህ ኃይል «በራሴ ክልል ምርጫ አደርጋለሁ» ብሎ ፍፁም ኢ-ሕገ መንግሥታዊ በሆነ መንገድ ተነሳስቶ አድርጎታል፤
👉 እነዚህ ፅንፈኛ ኃይሎች ሁሌም ትንኮሳ ሲያደርጉ ቢቆዩም፤ በመጨረሻ ቀዩን መስመር አልፈው መከላከያ ላይ ጥቃት ሰነዘሩ፤
👉 እጅግ ዘግናኝ የሆነ በኢትዮጵያ ታሪክ ብቻ ሳይሆን በዓለም ታይቶ የማይታወቅ አሳዛኝ ተግባር ፈፀሙ፤ የትግራይን ሕዝብ ለመጠበቅ ከ20 ዓመታት በላይ ጉድጓድ ውስጥ የኖረ፤ በክፉም ሆነ በደጉ ከትግራይ ህዝብ ጎን ቆሞ የኖረውን ወታደር ከጀርባው ጥቃት ፈጸሙ፤
👉 ኢትዮጵያን የማፈራረስና ድሮ የነበረውን የዝርፊያ ፍላጎታቸውን ማስቀጠል፤ በተቻለ መጠን የተዳከመ ወይም የተበተነ መንግስት እንዲኖር ማድረግና አገሪቱን ወደ እርስበርስ ጦርነት እንድትገባ ለማድረግ ነበር ይህንን ጥቃት የፈፀሙት፤
👉 ከፍተኛ የሆነ ጫና እየፈጠረ፤ ዘረፋ እየፈፀመ የቆየ ቡድን ነው፤ በቤኒሻንጉል፤ በጋምቤላ፣ በኦሮሚያ፣ በሱማሌ እና በአፋር ያሉ የእርሻ መሬቶችን ሲበዘብዝ የኖረ ቡድን ነው፤
👉 ሱማሌ ክልል ላይ በርካታ ሰዎችን በአንድ ጊዜ ረሽኖ በአንድ ጉድጓድ እንዲቀበሩ በማድረግ ትልቅ ግፍ ፈጽሟል፤
👉 የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች በመከፋፈል በጠላትነት እንዲተያይ በማድረግ በጋራ የመሰረቱትን የአንድነት እሴታቸውን እያፈረሰ በልዩነቶቻቸው ላይ እያነጣጠረ በቀየሰው ዘዴ ከፍተኛ የሚባል ጉዳት ደርሷል፤
👉ስርዓቱን ይቃወማሉ ብሎ የሚያስባቸውን ሰዎች እያሸማቀቀ፤ በሽብር ተሳትፈዋል ብሎ በእስር ቤት ያጉራቸዋል፤ ይገርፋቸዋል፤ አካላቸውን ያጎላል፤ ያኮላሻል፣ ይገድላል፤
👉 በኢኮኖሚ ረገድ ኢ-ፍትሃዊነቱን ያባባሰው በልማት ድርጅቶች አማካኝነት የሚደረግ ዘረፋ ነው፤ ለምሳሌ እንደባንክ፥ ቴሌና በመሳሰሉት ተቋማት ላይ በጣም ብዙ ዘረፋዎችና በደሎች ተፈፅመዋል፤
👉 ኢ-ፍትሃዊነት እየነገሰ፤ ግለሰቦች በአጭር ጊዜ እየከበሩ፤ ከምንም ተነስተው ባለሃብት እንዲሆኑ የተደረገበት ስርዓት ፈጥረዋል፤
👉 በመንግስት ከፍተኛ አመራር ቦታ ላይ የነበሩ የጁንታው ሰዎች የሚዘርፉትን ገንዘብ በራሳቸው ስም አያደርጉትም ነበር፤ አብረዋቸው በሚሰሩ ሌሎች ግለሰቦች ስም እያደረጉ ነበር የሚጠቀሙት፤ በዚህ ምክንያት ኢ-ፍትሃዊነቱ እየሰፋ የመጣውና የለውጡ ዋነኛ ሰበብ የሆነው አንዱ ይኸው ጉዳይ ነው፤
👉 እያንዳንዱ ሰው ማንነቱን በራሱ ነው እንዲወስን ሊደረግ የሚገባው፤ የግለሰቦች መብት ሰለሆነ፤ እነዚህ ሰዎች ግን ይህንን መብት ነው የነፈጉት:: የእኔ ማንነት ነው ብለው በራሳቸው ለመወሰን የማይችሉበት ሁኔታ ነው የተፈጠረው:: ስለዚህ ይሄ ቡድን በአገር ክህደት ወንጀል ውስጥ የገባው ቡድን የእነዚህን ሰዎች መብት አፍኖ ነው የኖረው፤
👉 ዛሬም ድረስ ሚዲያ ላይ እየወጡ የአማራ መሬት ማስመለስ ዘመቻ ነው እያሉ ነው በቅርቡ የተወሰደውን የህግ ማስከበር ዘመቻ ሲጠቅሱት የነበረው:: ይህንን ሃሰተኛ ትርክት ለአለምአቀፉ ማህበረሰብ ለማስተላለፍ ሞክረዋል፤ አጀንዳና አቅጣጫ ማሳት ከድሮም ጀምሮ የተካኑበት ባህሪ ነው፤
👉 ይሄ አፋኝ ቡድን ላይመለስ ወደመቃብሩ ወርዷል፤ ከዚህ በኋላ መብት ማፈን፥ መርገጥ ፤ እኔ ብቻ አውቅልሃለሁ ማለት አይፈቀድም፤ አሁን በጀመርነው ለውጥ እንኳን ሊታሰብም አይችልም፤
👉 «ለእኛ ጦርነት ባህላዊ ጨዋታችን ነው» የሚሉ ትዕቢት የተሞላባቸው ንግግሮችን በድፍረት ይናገሩ ነበር:: እውነት ለመናገር እነዚህ ቡድኖች የእብሪታቸው ልክ ወሰን የለውም:: ሁሉም በሚባል ደረጃ ትዕቢትና እብሪት ወጥሮ የያዛቸው ሰዎች ናችው፤
👉 «ከእኛ በላይ ለጦርነት የተፈጠረ የለም፤ ከእኛ በላይ ውጊያ ላሳር ነው» የሚሉ እብሪት የተሞሉ ሰዎች ነበሩ:: ግን ይህንን እብሪታቸውን እንዲፈፀም ያደረጉት በሚያሳዝን ሁኔታ በደሃው ልጅ ላይ ነው፤
👉 የእነሱ ልጆች በዚህ ጦርነት አይማገዱም፣ አይለበለቡም፣ እነዚህ አረመኔ ሰዎች እድሜ ልካቸውን ድሃውን የትግራይ ወጣት በጦርነት ውስጥ እየማገዱ የኖሩ፤ በሕግ ማስከበሩ ዘመቻ የተማረኩት ህፃናት ልጆች ከትምህርት ገበታ ላይ ተነቅለው ተወስደው የተመለመሉ ናቸው፤
👉 ከሃዲው ቡድን ሽንፈቱ አይቀሬ መሆኑን እየተገነዘበ ሲሄድ የያዛቸውንና ምሽግ የሰራባቸውን ቦታዎች እየለቀቀ በሚሄድበት ጊዜ የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን አፈራርሷል፤
👉 በተለቀቁ ቦታዎች ላይ የፈፀሙት ኢ-ሰብአዊ ድርጊት አለ፤ ለምሳሌ ማይካድራ ላይ የተፈፀመው ጭፍጨፋና በደል ታሪክ ይቅር የማይለው በጣም ትልቅ ወንጀል ነው፤
👉 አንዳንዶቹ «ምርጫ መካሄድ የለበትም» የሚል አቋም አላቸው፤ ግን ደግሞ የመንግሥትን ሥልጣን ይፈልጋሉ፤ እነዚህ ሃሳቦች እርስበርሳቸው ይጣረሳሉ፤ ስልጣን የሚፈልጉት በሌላ መንገድ ነው፤
👉 የሽግግር መንግስት እናቋቁም፤ የባላደራ መንግስት ይመስረት የሚል ፍላጎት ያላቸው ፓርቲዎች አሉ፤ ሁሉንም ፓርቲዎች ግን አይገልፅም፤
👉 ስልጣን የሚያዘው በምርጫ ብቻ ብሎ ስለሚደነግግ፤ ከምርጫ ውጭ የሚመጣ ስልጣን ስለሌለ ያንን ታሳቢ አድርጎ ነው እንጂ መሰራት ያለበት በአቋራጭ እንዲህ አይነት መንግስት እናቋቁም የሚለው ነገር አያስኬድም፤
አዲስ ዘመን ጋዜጣ ከአቶ ብናልፍ አንዱዓለም ጋር ያደረገውን ቃለ መጠይቅ ሙሉውን ሊንኩን ተጭነው ያገኙታል።
https://www.press.et/Ama/?p=37198
www.press.et
“ማንነታቸው እውቅና ያልተሰጣቸው ዜጎች ለ30 ዓመታት ሲበደሉና ሲገፉ ቢኖሩም በአመጽ ለመፍታት አንድም ቀን ተንቀሳቅሰው አያውቁም” – አቶ ብናልፍ አንዷለም የብልጽግና ዋና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ | የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት
👉 በመንግስት ከፍተኛ አመራር ቦታ ላይ የነበሩ የጁንታው ሰዎች የሚዘርፉትን ገንዘብ በራሳቸው ስም አያደርጉትም ነበር፤ አብረዋቸው በሚሰሩ ሌሎች ግለሰቦች ስም እያደረጉ ነበር የሚጠቀሙት፤
አቶ ብናልፍ አንዷለም የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
👉 ለውጥ ያስፈልጋል የሚል ግምገማና ክርክር ሲደረግ፣ ህወሓት ከፍተኛ ተፅእኖ ለመፍጠር ሲጥር ነበር፤ ለውጡ በሚፈለገው አቅጣጫ እንዳይሄድ እንቅፋት እየሆነ በአንድ አጀንዳ ላይ ተወያይተን የውሳኔዎቹ ሃሳብ በመግለጫ ከወጡ በኋላ ህወሓት ለብቻው ወጥቶ እንደገና ሌላ መግለጫ ያወጣል፤
👉 አብዮታዊ ዲሞክራሲ በሚል ፍልስፍና ጠላትና ወዳጅ ብሎ የሚለይ፣ ሰዎችን በአመለካከታቸው ብቻ ይሄኛው ጠላቴ ነው፤ ሌላኛው ደግሞ ወዳጄ ብሎ የሚያስቀምጥ ነበር፤
👉 በሕዝቦች መካከል የጥላቻ ግድግዳ ፈጥሯል፤ የሚገርመው ጠላት ወይም ወዳጅ ከሚለው ውጭ ሌላ ሶስተኛ መንገድ አለ ብሎ አያምንም፤
👉 የህወሻት ቡድን «የለውጥ ኃይሉ ስልጣኑን ለማራዘም ሲል ነው ብልፅግናን የሚያቋቁመው፤ አሀዳዊ መንግስት ነው፤ የድሮውን ስርዓት ለመመለስ ነው፤ የፌደራል ስርዓቱን ለማፍረስ ነው» የሚሉ የማያቋርጥ ዘመቻ ሲያካሂድ ነበር፤
👉 በ2012ዓ.ም ሊካሄድ የነበረው ምርጫ እንዲራዘም ሲደረግ፤ «ስልጣን ለማራዘም ነው» የሚሉ በርካታ የስም ማጥፋት ዘመቻቸውን ማድረጋቸውን ቀጠሉ፤ ግን እነሱ ስለተቃወሙት ተግባራዊ ከመሆን አልቀረም፤ እናም ይሄን ተከትሎም ይህ ኃይል «በራሴ ክልል ምርጫ አደርጋለሁ» ብሎ ፍፁም ኢ-ሕገ መንግሥታዊ በሆነ መንገድ ተነሳስቶ አድርጎታል፤
👉 እነዚህ ፅንፈኛ ኃይሎች ሁሌም ትንኮሳ ሲያደርጉ ቢቆዩም፤ በመጨረሻ ቀዩን መስመር አልፈው መከላከያ ላይ ጥቃት ሰነዘሩ፤
👉 እጅግ ዘግናኝ የሆነ በኢትዮጵያ ታሪክ ብቻ ሳይሆን በዓለም ታይቶ የማይታወቅ አሳዛኝ ተግባር ፈፀሙ፤ የትግራይን ሕዝብ ለመጠበቅ ከ20 ዓመታት በላይ ጉድጓድ ውስጥ የኖረ፤ በክፉም ሆነ በደጉ ከትግራይ ህዝብ ጎን ቆሞ የኖረውን ወታደር ከጀርባው ጥቃት ፈጸሙ፤
👉 ኢትዮጵያን የማፈራረስና ድሮ የነበረውን የዝርፊያ ፍላጎታቸውን ማስቀጠል፤ በተቻለ መጠን የተዳከመ ወይም የተበተነ መንግስት እንዲኖር ማድረግና አገሪቱን ወደ እርስበርስ ጦርነት እንድትገባ ለማድረግ ነበር ይህንን ጥቃት የፈፀሙት፤
👉 ከፍተኛ የሆነ ጫና እየፈጠረ፤ ዘረፋ እየፈፀመ የቆየ ቡድን ነው፤ በቤኒሻንጉል፤ በጋምቤላ፣ በኦሮሚያ፣ በሱማሌ እና በአፋር ያሉ የእርሻ መሬቶችን ሲበዘብዝ የኖረ ቡድን ነው፤
👉 ሱማሌ ክልል ላይ በርካታ ሰዎችን በአንድ ጊዜ ረሽኖ በአንድ ጉድጓድ እንዲቀበሩ በማድረግ ትልቅ ግፍ ፈጽሟል፤
👉 የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች በመከፋፈል በጠላትነት እንዲተያይ በማድረግ በጋራ የመሰረቱትን የአንድነት እሴታቸውን እያፈረሰ በልዩነቶቻቸው ላይ እያነጣጠረ በቀየሰው ዘዴ ከፍተኛ የሚባል ጉዳት ደርሷል፤
👉ስርዓቱን ይቃወማሉ ብሎ የሚያስባቸውን ሰዎች እያሸማቀቀ፤ በሽብር ተሳትፈዋል ብሎ በእስር ቤት ያጉራቸዋል፤ ይገርፋቸዋል፤ አካላቸውን ያጎላል፤ ያኮላሻል፣ ይገድላል፤
👉 በኢኮኖሚ ረገድ ኢ-ፍትሃዊነቱን ያባባሰው በልማት ድርጅቶች አማካኝነት የሚደረግ ዘረፋ ነው፤ ለምሳሌ እንደባንክ፥ ቴሌና በመሳሰሉት ተቋማት ላይ በጣም ብዙ ዘረፋዎችና በደሎች ተፈፅመዋል፤
👉 ኢ-ፍትሃዊነት እየነገሰ፤ ግለሰቦች በአጭር ጊዜ እየከበሩ፤ ከምንም ተነስተው ባለሃብት እንዲሆኑ የተደረገበት ስርዓት ፈጥረዋል፤
👉 በመንግስት ከፍተኛ አመራር ቦታ ላይ የነበሩ የጁንታው ሰዎች የሚዘርፉትን ገንዘብ በራሳቸው ስም አያደርጉትም ነበር፤ አብረዋቸው በሚሰሩ ሌሎች ግለሰቦች ስም እያደረጉ ነበር የሚጠቀሙት፤ በዚህ ምክንያት ኢ-ፍትሃዊነቱ እየሰፋ የመጣውና የለውጡ ዋነኛ ሰበብ የሆነው አንዱ ይኸው ጉዳይ ነው፤
👉 እያንዳንዱ ሰው ማንነቱን በራሱ ነው እንዲወስን ሊደረግ የሚገባው፤ የግለሰቦች መብት ሰለሆነ፤ እነዚህ ሰዎች ግን ይህንን መብት ነው የነፈጉት:: የእኔ ማንነት ነው ብለው በራሳቸው ለመወሰን የማይችሉበት ሁኔታ ነው የተፈጠረው:: ስለዚህ ይሄ ቡድን በአገር ክህደት ወንጀል ውስጥ የገባው ቡድን የእነዚህን ሰዎች መብት አፍኖ ነው የኖረው፤
👉 ዛሬም ድረስ ሚዲያ ላይ እየወጡ የአማራ መሬት ማስመለስ ዘመቻ ነው እያሉ ነው በቅርቡ የተወሰደውን የህግ ማስከበር ዘመቻ ሲጠቅሱት የነበረው:: ይህንን ሃሰተኛ ትርክት ለአለምአቀፉ ማህበረሰብ ለማስተላለፍ ሞክረዋል፤ አጀንዳና አቅጣጫ ማሳት ከድሮም ጀምሮ የተካኑበት ባህሪ ነው፤
👉 ይሄ አፋኝ ቡድን ላይመለስ ወደመቃብሩ ወርዷል፤ ከዚህ በኋላ መብት ማፈን፥ መርገጥ ፤ እኔ ብቻ አውቅልሃለሁ ማለት አይፈቀድም፤ አሁን በጀመርነው ለውጥ እንኳን ሊታሰብም አይችልም፤
👉 «ለእኛ ጦርነት ባህላዊ ጨዋታችን ነው» የሚሉ ትዕቢት የተሞላባቸው ንግግሮችን በድፍረት ይናገሩ ነበር:: እውነት ለመናገር እነዚህ ቡድኖች የእብሪታቸው ልክ ወሰን የለውም:: ሁሉም በሚባል ደረጃ ትዕቢትና እብሪት ወጥሮ የያዛቸው ሰዎች ናችው፤
👉 «ከእኛ በላይ ለጦርነት የተፈጠረ የለም፤ ከእኛ በላይ ውጊያ ላሳር ነው» የሚሉ እብሪት የተሞሉ ሰዎች ነበሩ:: ግን ይህንን እብሪታቸውን እንዲፈፀም ያደረጉት በሚያሳዝን ሁኔታ በደሃው ልጅ ላይ ነው፤
👉 የእነሱ ልጆች በዚህ ጦርነት አይማገዱም፣ አይለበለቡም፣ እነዚህ አረመኔ ሰዎች እድሜ ልካቸውን ድሃውን የትግራይ ወጣት በጦርነት ውስጥ እየማገዱ የኖሩ፤ በሕግ ማስከበሩ ዘመቻ የተማረኩት ህፃናት ልጆች ከትምህርት ገበታ ላይ ተነቅለው ተወስደው የተመለመሉ ናቸው፤
👉 ከሃዲው ቡድን ሽንፈቱ አይቀሬ መሆኑን እየተገነዘበ ሲሄድ የያዛቸውንና ምሽግ የሰራባቸውን ቦታዎች እየለቀቀ በሚሄድበት ጊዜ የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን አፈራርሷል፤
👉 በተለቀቁ ቦታዎች ላይ የፈፀሙት ኢ-ሰብአዊ ድርጊት አለ፤ ለምሳሌ ማይካድራ ላይ የተፈፀመው ጭፍጨፋና በደል ታሪክ ይቅር የማይለው በጣም ትልቅ ወንጀል ነው፤
👉 አንዳንዶቹ «ምርጫ መካሄድ የለበትም» የሚል አቋም አላቸው፤ ግን ደግሞ የመንግሥትን ሥልጣን ይፈልጋሉ፤ እነዚህ ሃሳቦች እርስበርሳቸው ይጣረሳሉ፤ ስልጣን የሚፈልጉት በሌላ መንገድ ነው፤
👉 የሽግግር መንግስት እናቋቁም፤ የባላደራ መንግስት ይመስረት የሚል ፍላጎት ያላቸው ፓርቲዎች አሉ፤ ሁሉንም ፓርቲዎች ግን አይገልፅም፤
👉 ስልጣን የሚያዘው በምርጫ ብቻ ብሎ ስለሚደነግግ፤ ከምርጫ ውጭ የሚመጣ ስልጣን ስለሌለ ያንን ታሳቢ አድርጎ ነው እንጂ መሰራት ያለበት በአቋራጭ እንዲህ አይነት መንግስት እናቋቁም የሚለው ነገር አያስኬድም፤
አዲስ ዘመን ጋዜጣ ከአቶ ብናልፍ አንዱዓለም ጋር ያደረገውን ቃለ መጠይቅ ሙሉውን ሊንኩን ተጭነው ያገኙታል።
https://www.press.et/Ama/?p=37198
www.press.et
“ማንነታቸው እውቅና ያልተሰጣቸው ዜጎች ለ30 ዓመታት ሲበደሉና ሲገፉ ቢኖሩም በአመጽ ለመፍታት አንድም ቀን ተንቀሳቅሰው አያውቁም” – አቶ ብናልፍ አንዷለም የብልጽግና ዋና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ | የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት
www.press.et
“ማንነታቸው እውቅና ያልተሰጣቸው ዜጎች ለ30 ዓመታት ሲበደሉና ሲገፉ ቢኖሩም በአመጽ ለመፍታት አንድም ቀን ተንቀሳቅሰው አያውቁም” – አቶ ብናልፍ አንዷለም የብልጽግና ዋና ጽሕፈት ቤት…