"በኢትዮጵያውያን ላይ እየተፈጸመ ባለው ማንነትን መሠረት ባደረገው ጥቃት እጅግ ማዘኔን እገልጣለሁ"
- ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር)
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ጠላቶች፤ "ወይ እኛ እንገዛለን፤ ወይ ሀገር አትኖርም" ብለው ተነሥተዋል። ለዚህም የጥፋት ዐቅማቸውን ሁሉ እየተጠቀሙ ነው። አንደኛው ዒላማቸውም የሕዝባችንን ቅስም መስበር ነው።
ለዚህ እየተጠቀሙበት ያለው ስልት ግራ ቀኝ የሜያውቁ ሰዎችን እየሰበሰቡ በማሠልጠንና በማስታጠቅ በየአካባቢው ማንነትን መሠረት ያደረገ አረመኔያዊ ጥቃት ማድረስ ነው። ይህ ተግባር ሕዝቡ እንዲደናገጥ፣ እንዲፈራና በስሜት ያልተገባ ርምጃ እንዲወስድ የታለመ ነው።
መንግሥት በተለያዩ ቦታዎች ሊፈጠሩ ይችላሉ ያላቸውን ጥፋቶች በቅድሚያ መረጃ ሰብስቦ ርምጃ በመውሰድ ሲያከሽፍ ቆይቷል። ነገር ግን ያለፈው ሥርዓት ያወረሰንን ቀዳዳዎች ሁሉ በጥቂት ጊዜ ውስጥ ደፍኖ መጨረስ አልተቻለም።
የጥፋት ኃይሎች ከውጭ ላኪዎቻቸውና በመንግሥት መዋቅር ውስጥ በሚገኙ ባልጠሩ አድር ባዮች ትብብር በሕዝባችን ላይ አሳዛኝ ጥቃት እያደረሱ ነው። ሁኔታው እንደ መሪም እንደ ዜጋም ልብ ይሰብራል።
ይህ ግን ከመንገዳችን ወደኋላ፣ ከግባችን ወደ ሌላ አያደርገንም። ተስፋ ቆርጠን እንድናቆም፣ ተሸንፈን እንድናፈገፍግ አያደርገንም። ከምንጊዜውም በላይ ኃይላችንን አሰባስበን እንድንነሣ ያደርገናል እንጂ።
መንግሥት ሁሉንም ዓይነት አማራጮች ተጠቅሞ የችግሩን ሰንኮፍ ይነቅለዋል። የጸጥታ አካላት ጥቃቱ ወደተፈጸመበት አካባቢ ተሠማርተዋል። ርምጃም እየወሰዱ ነው። በቀጣይም የሕዝባችንን ደኅንነት ለማስጠበቅ መንግሥት የመንግሥትነቱን ሥራ በቁርጥና በጽናት ይሠራል።
ሕዝቡ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጸጥታ አካላት።፣ ምሁራንና ሌሎችም፧ መንግሥት ችግሩን ከምንጩ ለማድረቅ የሚወስደውን ርምጃ በመደገፍ የሚጠበቅባቸውን እንዲያደርጉ ጥሪ አቀርባለሁ።
- ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር)
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ጠላቶች፤ "ወይ እኛ እንገዛለን፤ ወይ ሀገር አትኖርም" ብለው ተነሥተዋል። ለዚህም የጥፋት ዐቅማቸውን ሁሉ እየተጠቀሙ ነው። አንደኛው ዒላማቸውም የሕዝባችንን ቅስም መስበር ነው።
ለዚህ እየተጠቀሙበት ያለው ስልት ግራ ቀኝ የሜያውቁ ሰዎችን እየሰበሰቡ በማሠልጠንና በማስታጠቅ በየአካባቢው ማንነትን መሠረት ያደረገ አረመኔያዊ ጥቃት ማድረስ ነው። ይህ ተግባር ሕዝቡ እንዲደናገጥ፣ እንዲፈራና በስሜት ያልተገባ ርምጃ እንዲወስድ የታለመ ነው።
መንግሥት በተለያዩ ቦታዎች ሊፈጠሩ ይችላሉ ያላቸውን ጥፋቶች በቅድሚያ መረጃ ሰብስቦ ርምጃ በመውሰድ ሲያከሽፍ ቆይቷል። ነገር ግን ያለፈው ሥርዓት ያወረሰንን ቀዳዳዎች ሁሉ በጥቂት ጊዜ ውስጥ ደፍኖ መጨረስ አልተቻለም።
የጥፋት ኃይሎች ከውጭ ላኪዎቻቸውና በመንግሥት መዋቅር ውስጥ በሚገኙ ባልጠሩ አድር ባዮች ትብብር በሕዝባችን ላይ አሳዛኝ ጥቃት እያደረሱ ነው። ሁኔታው እንደ መሪም እንደ ዜጋም ልብ ይሰብራል።
ይህ ግን ከመንገዳችን ወደኋላ፣ ከግባችን ወደ ሌላ አያደርገንም። ተስፋ ቆርጠን እንድናቆም፣ ተሸንፈን እንድናፈገፍግ አያደርገንም። ከምንጊዜውም በላይ ኃይላችንን አሰባስበን እንድንነሣ ያደርገናል እንጂ።
መንግሥት ሁሉንም ዓይነት አማራጮች ተጠቅሞ የችግሩን ሰንኮፍ ይነቅለዋል። የጸጥታ አካላት ጥቃቱ ወደተፈጸመበት አካባቢ ተሠማርተዋል። ርምጃም እየወሰዱ ነው። በቀጣይም የሕዝባችንን ደኅንነት ለማስጠበቅ መንግሥት የመንግሥትነቱን ሥራ በቁርጥና በጽናት ይሠራል።
ሕዝቡ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጸጥታ አካላት።፣ ምሁራንና ሌሎችም፧ መንግሥት ችግሩን ከምንጩ ለማድረቅ የሚወስደውን ርምጃ በመደገፍ የሚጠበቅባቸውን እንዲያደርጉ ጥሪ አቀርባለሁ።
የኢፌዲሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ በንፁኃን ዜጎች ላይ የተፈፀመውን አሰቃቂ ጭፍጨፋ በማስመልከት መልዕክት አስተላልፈዋል።
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
የተከበራችሁ የሃገራችን ህዝቦች!
በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ በንፁኃን ዜጎች ላይ የተፈፀመው አሰቃቂ ጭፍጨፋ የተሰማኝን ሃዘን እየገለፅኩ፤ ለሟች ቤተሰቦች መፅናናትን እመኛለሁ፡፡
በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ቀደም ሲል ብሄርን፣ ሃይማኖትን እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት የማድረስ ዓላማ ያላቸው ጥቃቶችና ጭፍጨፋዎች ተካሂደዋል፡፡ በተመሳሳይ በምዕራብ ወለጋ ዞን በንፁኃን ዜጎች ላይ አሰቃቂ ጭፍጨፋ ተፈፅሟል፡፡
በተለይ የአማራን ማህበረሰብ ትኩረት ያደረገና በንፁኃን ዜጎች ላይ የሚካሄደው ጭፍጨፋ ፍፁም አረመኔያዊና በፍጥነት መቆም ያለበት እኩይ ድርጊት ነው፡፡ ድርጊቱ አስቀድሞ መዋቅራዊ በሆነ መልኩ ሲዘራ የቆየ በመሆኑ፤ ችግሩን የሚመጥን መፍትሄ በዘላቂነት ለማበጀት አስፈላጊው ሁሉ ይደረጋል፡፡
ከዚህ አኳያ የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ እንዲሁም ከሁሉም አቅጣጫ የሚቃጡ ጥቃቶችን ለመመከት የመንግስትና ህዝብ ቅንጅታዊ ርብርብ ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
የተከበራችሁ የሃገራችን ህዝቦች!
በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ በንፁኃን ዜጎች ላይ የተፈፀመው አሰቃቂ ጭፍጨፋ የተሰማኝን ሃዘን እየገለፅኩ፤ ለሟች ቤተሰቦች መፅናናትን እመኛለሁ፡፡
በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ቀደም ሲል ብሄርን፣ ሃይማኖትን እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት የማድረስ ዓላማ ያላቸው ጥቃቶችና ጭፍጨፋዎች ተካሂደዋል፡፡ በተመሳሳይ በምዕራብ ወለጋ ዞን በንፁኃን ዜጎች ላይ አሰቃቂ ጭፍጨፋ ተፈፅሟል፡፡
በተለይ የአማራን ማህበረሰብ ትኩረት ያደረገና በንፁኃን ዜጎች ላይ የሚካሄደው ጭፍጨፋ ፍፁም አረመኔያዊና በፍጥነት መቆም ያለበት እኩይ ድርጊት ነው፡፡ ድርጊቱ አስቀድሞ መዋቅራዊ በሆነ መልኩ ሲዘራ የቆየ በመሆኑ፤ ችግሩን የሚመጥን መፍትሄ በዘላቂነት ለማበጀት አስፈላጊው ሁሉ ይደረጋል፡፡
ከዚህ አኳያ የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ እንዲሁም ከሁሉም አቅጣጫ የሚቃጡ ጥቃቶችን ለመመከት የመንግስትና ህዝብ ቅንጅታዊ ርብርብ ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
የምክር ቤቱ አባላት በምዕራብ ወለጋ ዞን ከተፈጸመው ግድያ ጀርባ አሉ የተባሉት እንደ ህወሓት ያሉ ድርጅቶች በአሸባሪነት ሊፈረጁ ይገባል ሲሉ ጠየቁ
👉 ጉዳዩን በተመለከተ የሚመለከተው የመንግስት አካል ማብራሪያ እንዲሰጥበት እንደሚደረግ አፈጉበኤው አስታውቀዋል
******************
(ኢ ፕ ድ)
የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት በምዕራብ ወለጋ ዞን በንጹሀን ዜጎች ላይ ማንነትን መሰረት አድርጎ በተፈጸመው ግድያ ላይ እጃቸው አለበት የተባሉት እንደ ህወሓት እና ሸኔ ያሉ ድርጅቶች በአሸባሪነት ሊፈረጁ ይገባል ሲሉ ጠየቁ።
ዛሬ ለመደበኛ ስብሰባ የተጠራው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከመደበኛ አጀንዳዎች አስቀድሞ በንጹሀን ዜጎች ግድያ ላይ መወያያት አለብን በሚል በጥቃቱ ዙሪያ ሰፊ ውይይት አድርጓል።
በዚሁ ውይይት ላይ የምክር ቤቱ አባላት እንደተናገሩት፤ በምዕራብ ወለጋ ዞን በንጹሀን ዜጎች ላይ ማንነትን መሰረት አድርጎ በተፈጸመው ግድያ ላይ እጃቸው አለበት የተባሉት እንደ ህወሓት እና ኦነግ ሸኔ ያሉ ድርጅቶች በአሸባሪነት ሊፈረጁ ይገባል ብለዋል።
የትናንት በስቲያውን ጨምሮ ባለፉት ሁለት አመታት ማንነት ላይ የተመሰረቱ ግድያዎችን የፈጸሙ፣ የመለመሉ ድጋፍ ያደረጉ እንደ ህወሓት ያሉ አካላትን በተመለከተ መረጃና ማስረጃ አደራጅቶ በሽብርተኝነት ሊፈረጁ ይገባል ያሉት አባላቱ፤ የሚመለከተው የመንግስት አካል ይሄንን መረጃ አደራጅቶ ለምክር ቤቱ እንዲያቀርብም ነው የጠየቁት።
አባላቱ በዚሁ ውይይታቸውም በግድያው ዙሪያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የሰላም ሚኒስቴር እና የመከላከያ የስራ ሃላፊዎች በጉዳዩ ላይ ምክር ቤት ቀርበው ማብራሪያ ሊሰጡ ይገባል ሲሉ አንስተዋል።
አፈጉበኤው በምላሻቸው የምክር ቤቱ አባላት በግድያው ዙሪያ ስሜታቸውን በዚህ አግባብ መግለጻቸው ትክክል መሆኑን በመጥቀስ፤ ጉዳዩን በተመለከተ የሚመለከተው የመንግስት አካል ማብራሪያ እንዲሰጥበት እንደሚደረግ አስታውቀዋል።
በጌትነት ተስፋማርያም
👉 ጉዳዩን በተመለከተ የሚመለከተው የመንግስት አካል ማብራሪያ እንዲሰጥበት እንደሚደረግ አፈጉበኤው አስታውቀዋል
******************
(ኢ ፕ ድ)
የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት በምዕራብ ወለጋ ዞን በንጹሀን ዜጎች ላይ ማንነትን መሰረት አድርጎ በተፈጸመው ግድያ ላይ እጃቸው አለበት የተባሉት እንደ ህወሓት እና ሸኔ ያሉ ድርጅቶች በአሸባሪነት ሊፈረጁ ይገባል ሲሉ ጠየቁ።
ዛሬ ለመደበኛ ስብሰባ የተጠራው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከመደበኛ አጀንዳዎች አስቀድሞ በንጹሀን ዜጎች ግድያ ላይ መወያያት አለብን በሚል በጥቃቱ ዙሪያ ሰፊ ውይይት አድርጓል።
በዚሁ ውይይት ላይ የምክር ቤቱ አባላት እንደተናገሩት፤ በምዕራብ ወለጋ ዞን በንጹሀን ዜጎች ላይ ማንነትን መሰረት አድርጎ በተፈጸመው ግድያ ላይ እጃቸው አለበት የተባሉት እንደ ህወሓት እና ኦነግ ሸኔ ያሉ ድርጅቶች በአሸባሪነት ሊፈረጁ ይገባል ብለዋል።
የትናንት በስቲያውን ጨምሮ ባለፉት ሁለት አመታት ማንነት ላይ የተመሰረቱ ግድያዎችን የፈጸሙ፣ የመለመሉ ድጋፍ ያደረጉ እንደ ህወሓት ያሉ አካላትን በተመለከተ መረጃና ማስረጃ አደራጅቶ በሽብርተኝነት ሊፈረጁ ይገባል ያሉት አባላቱ፤ የሚመለከተው የመንግስት አካል ይሄንን መረጃ አደራጅቶ ለምክር ቤቱ እንዲያቀርብም ነው የጠየቁት።
አባላቱ በዚሁ ውይይታቸውም በግድያው ዙሪያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የሰላም ሚኒስቴር እና የመከላከያ የስራ ሃላፊዎች በጉዳዩ ላይ ምክር ቤት ቀርበው ማብራሪያ ሊሰጡ ይገባል ሲሉ አንስተዋል።
አፈጉበኤው በምላሻቸው የምክር ቤቱ አባላት በግድያው ዙሪያ ስሜታቸውን በዚህ አግባብ መግለጻቸው ትክክል መሆኑን በመጥቀስ፤ ጉዳዩን በተመለከተ የሚመለከተው የመንግስት አካል ማብራሪያ እንዲሰጥበት እንደሚደረግ አስታውቀዋል።
በጌትነት ተስፋማርያም
“ለሀገርና ለህዝብ ጥቅም ሲባል ልናሰምረው እና ልናከብረው የሚገባን ቀይ መስመር ተጥሷል”
- የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለ-ወርቅ ዘውዴ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለ-ወርቅ ዘውዴ በምዕራብ ወለጋ ዞን በንጹሀን ዜጎች ላይ የተፈጸመውን ግድያ በማስመልከት ያስተላለፉት መልዕክት።
የሰማሁት አሰቃቂ ግድያ ልቤን በእጅጉ ሰብሮታል:: ንጹሀን ዜጎች በሌሎች እብደት ውድ ሕይወታቸውን የሚከፍሉበት ንብረታቸው የሚወድምበት መሄጃ አጥተው የሚንከራተቱበት ምንም ምክንያት የለም:: የዛሬ ዓመት በ 30/10/2019 የጻፍኩትን ትዊት ልድገመው::
ዘርና ሀይማኖት ለፖለቲካ ጥቅም እንዲውሉ ሲደረግ፤ ንጹሀን ዜጎቻችን በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደሉ፣ ሲፈናቀሉና ሲንከራተቱ ስናይ ስሜትን ለመግለጽ ቃላት ያጥራል: ለቅሶ፣ድንጋጤና ሥጋት የብዙዎችን በር አንኳኩቷል ሃዘናቸው ሃዘኔ/ሃዘናችን ነው::
ለሀገርና ለህዝብ ጥቅም ሲባል ልናሰምረው እና ልናከብረው የሚገባን ቀይ መስመር ተጥሷል፡ አገራችንን ካንዣበበባት ክፉ አዳጋ ለማዳን ሁላችንም ሚና አለን፡የሚመለከታቸው ሁሉ የበኩላቸውን መወጣት አለባቸው፡ቀይ መስመር መጣስ የለበትም እንበል::
የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ
- የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለ-ወርቅ ዘውዴ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለ-ወርቅ ዘውዴ በምዕራብ ወለጋ ዞን በንጹሀን ዜጎች ላይ የተፈጸመውን ግድያ በማስመልከት ያስተላለፉት መልዕክት።
የሰማሁት አሰቃቂ ግድያ ልቤን በእጅጉ ሰብሮታል:: ንጹሀን ዜጎች በሌሎች እብደት ውድ ሕይወታቸውን የሚከፍሉበት ንብረታቸው የሚወድምበት መሄጃ አጥተው የሚንከራተቱበት ምንም ምክንያት የለም:: የዛሬ ዓመት በ 30/10/2019 የጻፍኩትን ትዊት ልድገመው::
ዘርና ሀይማኖት ለፖለቲካ ጥቅም እንዲውሉ ሲደረግ፤ ንጹሀን ዜጎቻችን በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደሉ፣ ሲፈናቀሉና ሲንከራተቱ ስናይ ስሜትን ለመግለጽ ቃላት ያጥራል: ለቅሶ፣ድንጋጤና ሥጋት የብዙዎችን በር አንኳኩቷል ሃዘናቸው ሃዘኔ/ሃዘናችን ነው::
ለሀገርና ለህዝብ ጥቅም ሲባል ልናሰምረው እና ልናከብረው የሚገባን ቀይ መስመር ተጥሷል፡ አገራችንን ካንዣበበባት ክፉ አዳጋ ለማዳን ሁላችንም ሚና አለን፡የሚመለከታቸው ሁሉ የበኩላቸውን መወጣት አለባቸው፡ቀይ መስመር መጣስ የለበትም እንበል::
የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ
ሕወሓት በትግራይ በሚገኘው የመከላከያ ካምፕ ላይ ጥቃት ማድረሱና በዳልሻሕ በኩልም ጦርነት መክፈቱ ተገለጸ
********************
(ኢ ፕ ድ)
ሕወሓት በትግራይ በሚገኘው የመከላከያ ካምፕ ላይ ጥቃት ማድረሱ እና በዳልሻሕ በኩልም ጦርነት መክፈቱ ተገለጸ።
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ እንዳስታወቁት ህወሓት የሰሜን ዕዝንም ለመዝረፍ ሙከራ አድርጓል።
እንድ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጻ፤ ይህ ሠራዊት ከሃያ ዓመታት በላይ የትግራይን ሕዝብ ሲጠብቅ የቆየ ሠራዊት ነው። በቦታው የሚገኘውም የትግራይን ሕዝብ ከጥቃት ለመከላከል ነው። ሕወሐት ግን እንደ ባዕድና እንደ ወራሪ ሀገር ሠራዊት ቆጥሮ፤ የመከላከያ ሠራዊቱን ለመምታትና ለመዝረፍ ተነሥቷል።
ህወሓት በዳልሻሕ በኩልም ጦርነት ከፍቷል።
መንግሥት የትግራይ ሕዝብ እንዳይጎዳ በማሰብ፣ ጦርነት እንዳይፈጠር የትእግሥቱ ጫፍ ድረስ ታግሷል ያሉት ዶ/ር አብይ፤ ጦርነት የሚቀረው ግን በአንድ ወገን ፍላጎት ብቻ አይደለም ነው ያለት።
"የመከላከያ ሠራዊታችን በኮማንድ ፖስት እየተመራ ሀገሩን የማዳን ተልዕኮውን እንዲወጣ ትእዛዝ ተሰጥቶታል። ቀዩ መሥመር የመጨረሻው ነጥብ ታልፏል። ሀገርና ሕዝብ ለማዳን ሲባል ኃይል የመጨረሻው አማራጭ ሆኗል" ብለዋል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ ነገሮችን በሰከነ መንፈስ እንዲከታተል፣ በየአካባቢው ሊከሠቱ የሚችሉ ትንኮሳዎች በንቃት እንዲቃኝና ከመከላከያ ሠራዊታችን ጎን እንዲቆም ጥሪ አቀርባለሁ ብለዋል።
********************
(ኢ ፕ ድ)
ሕወሓት በትግራይ በሚገኘው የመከላከያ ካምፕ ላይ ጥቃት ማድረሱ እና በዳልሻሕ በኩልም ጦርነት መክፈቱ ተገለጸ።
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ እንዳስታወቁት ህወሓት የሰሜን ዕዝንም ለመዝረፍ ሙከራ አድርጓል።
እንድ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጻ፤ ይህ ሠራዊት ከሃያ ዓመታት በላይ የትግራይን ሕዝብ ሲጠብቅ የቆየ ሠራዊት ነው። በቦታው የሚገኘውም የትግራይን ሕዝብ ከጥቃት ለመከላከል ነው። ሕወሐት ግን እንደ ባዕድና እንደ ወራሪ ሀገር ሠራዊት ቆጥሮ፤ የመከላከያ ሠራዊቱን ለመምታትና ለመዝረፍ ተነሥቷል።
ህወሓት በዳልሻሕ በኩልም ጦርነት ከፍቷል።
መንግሥት የትግራይ ሕዝብ እንዳይጎዳ በማሰብ፣ ጦርነት እንዳይፈጠር የትእግሥቱ ጫፍ ድረስ ታግሷል ያሉት ዶ/ር አብይ፤ ጦርነት የሚቀረው ግን በአንድ ወገን ፍላጎት ብቻ አይደለም ነው ያለት።
"የመከላከያ ሠራዊታችን በኮማንድ ፖስት እየተመራ ሀገሩን የማዳን ተልዕኮውን እንዲወጣ ትእዛዝ ተሰጥቶታል። ቀዩ መሥመር የመጨረሻው ነጥብ ታልፏል። ሀገርና ሕዝብ ለማዳን ሲባል ኃይል የመጨረሻው አማራጭ ሆኗል" ብለዋል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ ነገሮችን በሰከነ መንፈስ እንዲከታተል፣ በየአካባቢው ሊከሠቱ የሚችሉ ትንኮሳዎች በንቃት እንዲቃኝና ከመከላከያ ሠራዊታችን ጎን እንዲቆም ጥሪ አቀርባለሁ ብለዋል።
በአዲስ አበባ በተለምዶ አዋሬ ገበያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የተነሳው የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጸ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
ከሌሊቱ 10 ሰአት አካባቢ የተነሳው የእሳት አደጋ በአዲስ አበባ ከተማ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የእሳት አደጋ መከላከል ባለሙያዎች ፣ፖሊሶች እና የአካባቢው ወጣቶች በቁጥጥር ስር መዋሉን የየካ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አስፋው ተክሌ ተናግረዋል፡፡
የእሳት አደጋውን መንስኤ እና ያደረሰውን ጉዳት በፖሊስ እየተጣራ መሆንን ዋና ስራ አስፈጻሚው ገልጸዋል፡፡
ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ከየካ ክፍለ ከተማ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በቦታው ተገኝተው የጉዳቱን መጠን በመመልከት ጉዳት የደረሰባቸውን ነዋሪዎች በማጽናናት ላይ ናቸው።
በእሳት አደጋው የደረሰውን ጉዳት በማጣራት በቀጣይ ሰዓታት የሚገለጽ ይሆናል ተብሏል፡፡
**********************
(ኢ ፕ ድ)
ከሌሊቱ 10 ሰአት አካባቢ የተነሳው የእሳት አደጋ በአዲስ አበባ ከተማ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የእሳት አደጋ መከላከል ባለሙያዎች ፣ፖሊሶች እና የአካባቢው ወጣቶች በቁጥጥር ስር መዋሉን የየካ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አስፋው ተክሌ ተናግረዋል፡፡
የእሳት አደጋውን መንስኤ እና ያደረሰውን ጉዳት በፖሊስ እየተጣራ መሆንን ዋና ስራ አስፈጻሚው ገልጸዋል፡፡
ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ከየካ ክፍለ ከተማ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በቦታው ተገኝተው የጉዳቱን መጠን በመመልከት ጉዳት የደረሰባቸውን ነዋሪዎች በማጽናናት ላይ ናቸው።
በእሳት አደጋው የደረሰውን ጉዳት በማጣራት በቀጣይ ሰዓታት የሚገለጽ ይሆናል ተብሏል፡፡
👉 በየጊዜው የሸረሪት ድር ስናፀዳ አንኖርም፤
👉 ትህነግ አልመዳ በሚባለው የጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ውስጥ የኤርትር
የመከላከያ ሰራዊት አልባሳትን በማምረት የኤርትራ ሰራዊት ወረረህ ለማለት
ዝግጅት ያደረገ ነው፤
👉 በአማራ ክልል በሶሮቃና ቅርቃር አካባቢ ትህነግ የጦርነት ሙከራ አድረጓል፤
ነገር ግን በአማራ ክልል ልዩ ኃይል ሙሉ በሙሉ ተመክቶ ተመልሷል፤
👉 ትህነግን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመደምሰስ ለሚደረገው ርምጀ ህዝቡ፣
ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ ከመንግስት ጎን ቆመው ሊያግዙና አካባቢያቸውን
ሊጠብቁ ይገባል፤
አቶ ተመሥገን ጥሩነህ
የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር
👉 ትህነግ አልመዳ በሚባለው የጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ውስጥ የኤርትር
የመከላከያ ሰራዊት አልባሳትን በማምረት የኤርትራ ሰራዊት ወረረህ ለማለት
ዝግጅት ያደረገ ነው፤
👉 በአማራ ክልል በሶሮቃና ቅርቃር አካባቢ ትህነግ የጦርነት ሙከራ አድረጓል፤
ነገር ግን በአማራ ክልል ልዩ ኃይል ሙሉ በሙሉ ተመክቶ ተመልሷል፤
👉 ትህነግን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመደምሰስ ለሚደረገው ርምጀ ህዝቡ፣
ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ ከመንግስት ጎን ቆመው ሊያግዙና አካባቢያቸውን
ሊጠብቁ ይገባል፤
አቶ ተመሥገን ጥሩነህ
የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር
ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር አቢይ አሕመድ በሰጡት መግለጫ ያነሷቸው ዋናዋና ነጥቦች
👉 ውድ የሀገሬ ህዝብ ሆይ! ዛሬ ከሃዲ ኢትዮጵያውያን ኢትዮጵያን
ወግተዋታል፤
👉 ኢትዮጵያ ያጎረሰ እጇ ያጠባ ጡቷ ተነክሷል፤
👉 ላለፉት 20 ዓመታት የቀበሮ ምሽግ ውስጥ በመሆን ሀገሬን ወገኔን
ህዝቤን ብሎ በብዙ ሺዎች መስዋዕትነት ከፍሎ ቆስሎ ደምቶ ሀገሩንና
ህዝቡን የታደገው የመከላከያ ሰራዊት ላይ ዛሬ ምሽት ከመቀሌ ጀምሮ
በበርካታ ስፍራዎች በካሃዲው ኃይሎች እና ባደራጁት ኃይል ጥቃት
ተፈፅሞበታል።
👉 ይህ ጥቃት በሀገራችን እስካሁን ከደረሱት ጥቃቶች እጅግ አሰፋሪ
የሚያደርገው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ሰላም ለማስከበር በተለያዩ
ሀገራት በተሰማራበት ሀገር በውጭ ኃይል እንኳ አጋጥሞት
በማያውቀው ሁኔታ በገዛ ወገኑ ከጀርባው ጥቃት ተፈፀሞበታል።
👉 በዳንሻ በኩል በአማራ ክልል ላይ የፈፀሙት ጥቃት በአማራ ክልል
በነበረው ኃይል ተመክቷል
👉 የትግራይ ሕዝብ ወገናችን ነው ለጥቂት እኩዮች ሲባል ምንም እንኳ
የእኩዮች መሸሸጊያ ዋሻ ቢሆንም ሕዝባችን ላይ ጥቃት አንሰነዝርም
ብሎ በትዕግስት በቆየው ሰራዊት ላይ ጥቃት ተፈፅሞበታል
👉 በመላ ሀገራችን ቀድመው ባሰለጠኑት ባሰማሩት ባዘጋጁት ኃይል
በተለያየ ቦታ በተለያየ ከተማ በንፁሃን ዜጎች ላይ ጥቃት ሊፈፅሙ
ስለሚችል መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ከሚሊሻው ከፖሊስ ሰራዊት
እንዲሁም በአካባቢያቸው ከሚገኝ የመከለከያ ሰራዊት ጋር
በመተባበር ቀያችሁን ሰፈራችሁን እንድትጠብቁ አሳስባለሁ
👉 የመከላከያ ሰራዊት ከጠቅላይ ሰፍር በሚሰጥ ትዕዛዝ መለዮውን
ሀገሩንና ህዝቡን እንዲከላከል ለሚከፍለው መስዋዕትነት ዛሬም
እንደተለመደው በታሪኩ ውስጥ የሚታሰብ መሆኑን እገልፃለሁ።
👉 ይህ እኩይ ኃይል መጥፊያው በመድረሱ በሰላም በንግግር
በውይይት ሊፈቱ የሚችሉ ነገሮችን ባለፉት ጥቂት ቀናት ካለምንም
ሀፍረት በሚዲያ በመውጣት ከየትኛውም የውጭ ኃይል ጋር
በመተባበር ኢትዮጵያን እወጋለሁ ብሎ ሲያውጅ የነበረው ኃይል
ይህን ለማመን የሚያስቸግር ንግግር በተግባር ማዋሉን በዚህ ምሽት
አረጋግጧል።
👉 የትግራይ ህዝብ ወገኔ ዘመዴ ሕዝቤ ብሎ ላለፉት 20 ዓመታት
በቀበሮ ምሽግ ውስጥ በመሆኑ በብዙሺዎች የሚቆጠር መስዋዕትነት
የከፈለውን አንተን ለመጠበቅ አስፈላጊውን ሁሉ ያደረገው
የመከላከያ ሰራዊት የደረሰበት ጥቃት ጥቃትህ መሆኑን በመገንዘብ
ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ጎን በመቆም ሀገርህን ከነዚህ ከሃዲ ኃይሎች
እንድትከላከልና በንቃት እንድትጠብቅ አሳስባለሁ።
👉 ይህ ጉዳይ ለኢትዮጵያ አሳዘኝ አሳፈሪም ተግባር ቢሆንም ዛሬም
እንደተለመደው በተደመረ በተባበረ ክንድ ይህንን ከሃዲ ጡት ነካሽ
ኃይል ለማሳፈርና ለመደምሰስ እስፈላጊውን ሁሉ የምናደርግ
መሆኑን እገልፃለሁ።
👉 ይህ አሳፋሪ ተግባር በማይደገምበት ሁኔታ የሚቀለበስበትን ተግባር
መላው የኢትዮጵያ ህዝብና የሀገር መከላከያ ሰራዊት በመተባበር
የሚፈፅሙት ይሆናል።
👉 ለመላው የሀገራችን ህዝቦች አስፈላጊውን መረጃ በየጊዜው
በሚመለከታቸው የመንግስት አከላት የሚሰጥ መሆኑን
እገልፃለሁ።
👉 ውድ የሀገሬ ህዝብ ሆይ! ዛሬ ከሃዲ ኢትዮጵያውያን ኢትዮጵያን
ወግተዋታል፤
👉 ኢትዮጵያ ያጎረሰ እጇ ያጠባ ጡቷ ተነክሷል፤
👉 ላለፉት 20 ዓመታት የቀበሮ ምሽግ ውስጥ በመሆን ሀገሬን ወገኔን
ህዝቤን ብሎ በብዙ ሺዎች መስዋዕትነት ከፍሎ ቆስሎ ደምቶ ሀገሩንና
ህዝቡን የታደገው የመከላከያ ሰራዊት ላይ ዛሬ ምሽት ከመቀሌ ጀምሮ
በበርካታ ስፍራዎች በካሃዲው ኃይሎች እና ባደራጁት ኃይል ጥቃት
ተፈፅሞበታል።
👉 ይህ ጥቃት በሀገራችን እስካሁን ከደረሱት ጥቃቶች እጅግ አሰፋሪ
የሚያደርገው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ሰላም ለማስከበር በተለያዩ
ሀገራት በተሰማራበት ሀገር በውጭ ኃይል እንኳ አጋጥሞት
በማያውቀው ሁኔታ በገዛ ወገኑ ከጀርባው ጥቃት ተፈፀሞበታል።
👉 በዳንሻ በኩል በአማራ ክልል ላይ የፈፀሙት ጥቃት በአማራ ክልል
በነበረው ኃይል ተመክቷል
👉 የትግራይ ሕዝብ ወገናችን ነው ለጥቂት እኩዮች ሲባል ምንም እንኳ
የእኩዮች መሸሸጊያ ዋሻ ቢሆንም ሕዝባችን ላይ ጥቃት አንሰነዝርም
ብሎ በትዕግስት በቆየው ሰራዊት ላይ ጥቃት ተፈፅሞበታል
👉 በመላ ሀገራችን ቀድመው ባሰለጠኑት ባሰማሩት ባዘጋጁት ኃይል
በተለያየ ቦታ በተለያየ ከተማ በንፁሃን ዜጎች ላይ ጥቃት ሊፈፅሙ
ስለሚችል መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ከሚሊሻው ከፖሊስ ሰራዊት
እንዲሁም በአካባቢያቸው ከሚገኝ የመከለከያ ሰራዊት ጋር
በመተባበር ቀያችሁን ሰፈራችሁን እንድትጠብቁ አሳስባለሁ
👉 የመከላከያ ሰራዊት ከጠቅላይ ሰፍር በሚሰጥ ትዕዛዝ መለዮውን
ሀገሩንና ህዝቡን እንዲከላከል ለሚከፍለው መስዋዕትነት ዛሬም
እንደተለመደው በታሪኩ ውስጥ የሚታሰብ መሆኑን እገልፃለሁ።
👉 ይህ እኩይ ኃይል መጥፊያው በመድረሱ በሰላም በንግግር
በውይይት ሊፈቱ የሚችሉ ነገሮችን ባለፉት ጥቂት ቀናት ካለምንም
ሀፍረት በሚዲያ በመውጣት ከየትኛውም የውጭ ኃይል ጋር
በመተባበር ኢትዮጵያን እወጋለሁ ብሎ ሲያውጅ የነበረው ኃይል
ይህን ለማመን የሚያስቸግር ንግግር በተግባር ማዋሉን በዚህ ምሽት
አረጋግጧል።
👉 የትግራይ ህዝብ ወገኔ ዘመዴ ሕዝቤ ብሎ ላለፉት 20 ዓመታት
በቀበሮ ምሽግ ውስጥ በመሆኑ በብዙሺዎች የሚቆጠር መስዋዕትነት
የከፈለውን አንተን ለመጠበቅ አስፈላጊውን ሁሉ ያደረገው
የመከላከያ ሰራዊት የደረሰበት ጥቃት ጥቃትህ መሆኑን በመገንዘብ
ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ጎን በመቆም ሀገርህን ከነዚህ ከሃዲ ኃይሎች
እንድትከላከልና በንቃት እንድትጠብቅ አሳስባለሁ።
👉 ይህ ጉዳይ ለኢትዮጵያ አሳዘኝ አሳፈሪም ተግባር ቢሆንም ዛሬም
እንደተለመደው በተደመረ በተባበረ ክንድ ይህንን ከሃዲ ጡት ነካሽ
ኃይል ለማሳፈርና ለመደምሰስ እስፈላጊውን ሁሉ የምናደርግ
መሆኑን እገልፃለሁ።
👉 ይህ አሳፋሪ ተግባር በማይደገምበት ሁኔታ የሚቀለበስበትን ተግባር
መላው የኢትዮጵያ ህዝብና የሀገር መከላከያ ሰራዊት በመተባበር
የሚፈፅሙት ይሆናል።
👉 ለመላው የሀገራችን ህዝቦች አስፈላጊውን መረጃ በየጊዜው
በሚመለከታቸው የመንግስት አከላት የሚሰጥ መሆኑን
እገልፃለሁ።
የኢፌድሪ ሚኒስትሮች ምክር ቤት በትግራይ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጀ
***********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢፌድሪ ሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ጥቅምት 25/2013 ባደረገው 21ኛ አስቸኳይ ልዩ ስብሰባ መንግሥት የሀገርን ሰላምና ሕልውና፣ የሕዝብንና የዜጎችን ደህንነት የማረጋገጥ እና ሀገሪቷን ወደ ሁከትና ብጥብጥ የሚወስዱ ማናቸውንም ድርጊቶችን የመከላከል ሕገ መንግሥታዊ ኃላፊነት ያለበት መሆኑን በመገንዘብ፤
እንዲሁም በትግራይ ብሔራዊ ክልል ውስጥ ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን እንዲሁም የሕዝብን ሰላምና ፀጥታ አደጋ ላይ የሚጥሉ በተለይም የሀገርን ሉዐላዊነት የሚገዳደሩ፣ የፌደራል መንግሥት በሕገ መንግሥቱ የተሰጠውን ሥልጣንና ኃላፊነት በክልሉ እንዳይወጣ እና ሀገሪቷን የጦር አውድማ የሚያደርጉ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔዎችን ጭምር በመጣስ በርካታ ሕገ ወጥ ተግባራት እየተፈፀሙ በመሆኑ፤
ይህን ሁኔታ በመደበኛው የሕግ ማስከበር ሥርዓት ለመከላከልና ለመቆጣጠር የማይቻልበት ደረጃ ላይ መደረሱን በመረዳት፤ በሕገ መንግሥቱ በተደነገገው መሠረት ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ለመጠበቅ ልዩ እርምጃዎችን መውሰድ የሚያስችል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በመደንገግ እና ተግባራዊ በማድረግ ሁኔታውን በመቆጣጠር በሀገሪቱ ሰላምና ሕልውና ላይ የተጋረጠውን አደጋ መከላከል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 93/1/ሀ መሰረት የሚከተለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታውጇል።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ለስድስት ወራት ተፈጻሚ የሚሆን ሲሆን፣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የሚያስፈፅም በኢፌድሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ሰብሳቢነት የሚመራና አግባብነት ካላቸው አካላት የተወጣጡ አባላት ያሉት ግብረኃይል በዚህ አዋጅ ተቋቁሟል።
ግብረኃይሉ ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲሆን ‘‘የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ግብረሀይል’’ ተብሎ ይጠራል።
አዋጁ በመላው የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መስተዳድር ተፈፃሚ የሚደረግ ሲሆን፣ እንደያስፈላጊነቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተፈፃሚ ወይም ቀሪ የሚሆንባቸውን ተጨማሪ አካባቢዎችን ግብረኃይሉ በሚያወጣው በመመሪያ ይወስናል።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አስመልክቶ ዝርዝር መርጃዎች በየጊዜው ለህብረተሰቡ የሚሰጡ ይሆናል።
***********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢፌድሪ ሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ጥቅምት 25/2013 ባደረገው 21ኛ አስቸኳይ ልዩ ስብሰባ መንግሥት የሀገርን ሰላምና ሕልውና፣ የሕዝብንና የዜጎችን ደህንነት የማረጋገጥ እና ሀገሪቷን ወደ ሁከትና ብጥብጥ የሚወስዱ ማናቸውንም ድርጊቶችን የመከላከል ሕገ መንግሥታዊ ኃላፊነት ያለበት መሆኑን በመገንዘብ፤
እንዲሁም በትግራይ ብሔራዊ ክልል ውስጥ ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን እንዲሁም የሕዝብን ሰላምና ፀጥታ አደጋ ላይ የሚጥሉ በተለይም የሀገርን ሉዐላዊነት የሚገዳደሩ፣ የፌደራል መንግሥት በሕገ መንግሥቱ የተሰጠውን ሥልጣንና ኃላፊነት በክልሉ እንዳይወጣ እና ሀገሪቷን የጦር አውድማ የሚያደርጉ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔዎችን ጭምር በመጣስ በርካታ ሕገ ወጥ ተግባራት እየተፈፀሙ በመሆኑ፤
ይህን ሁኔታ በመደበኛው የሕግ ማስከበር ሥርዓት ለመከላከልና ለመቆጣጠር የማይቻልበት ደረጃ ላይ መደረሱን በመረዳት፤ በሕገ መንግሥቱ በተደነገገው መሠረት ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ለመጠበቅ ልዩ እርምጃዎችን መውሰድ የሚያስችል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በመደንገግ እና ተግባራዊ በማድረግ ሁኔታውን በመቆጣጠር በሀገሪቱ ሰላምና ሕልውና ላይ የተጋረጠውን አደጋ መከላከል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 93/1/ሀ መሰረት የሚከተለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታውጇል።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ለስድስት ወራት ተፈጻሚ የሚሆን ሲሆን፣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የሚያስፈፅም በኢፌድሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ሰብሳቢነት የሚመራና አግባብነት ካላቸው አካላት የተወጣጡ አባላት ያሉት ግብረኃይል በዚህ አዋጅ ተቋቁሟል።
ግብረኃይሉ ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲሆን ‘‘የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ግብረሀይል’’ ተብሎ ይጠራል።
አዋጁ በመላው የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መስተዳድር ተፈፃሚ የሚደረግ ሲሆን፣ እንደያስፈላጊነቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተፈፃሚ ወይም ቀሪ የሚሆንባቸውን ተጨማሪ አካባቢዎችን ግብረኃይሉ በሚያወጣው በመመሪያ ይወስናል።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አስመልክቶ ዝርዝር መርጃዎች በየጊዜው ለህብረተሰቡ የሚሰጡ ይሆናል።
"መከላከያ ሠራዊት የሀገር አንድነት እና ሰላምን ለማስከበር የሚወስዳቸውን እርምጃዎች በመደገፍ የኢዜማ አባላት እና አመራር ከጎኑ እንደሚሰለፉ ፓርቲው አስታወቀ
************************************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ሕወሓት በትግራይ ክልል በሚገኘው የኢፌዴሪ መከላለከያ ሠራዊት ላይ የከፈተውን ጥቃት በፅኑ እንደሚያወግዘው ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።
በተለያየ ጊዜ ሕወሃት ሲያስተላልፋቸው የነበሩ የሥርዓት አልበኝነት ጥሪዎች እና በክልሉ ሕግን ተላልፎ ሲፈጽም የነበራቸው ድርጊቶች አልበቃ ብለው የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ምልክት የሆነው መከላከያ ሠራዊታችን ላይ የፈፀመው ጥቃት በፍፁም በዝምታ የሚታለፍ እንዳልሆነ እናምናለን ብሏል፤ ኢዜማ በመግለጫው።
የነበረው ችግር በንግግር መፈታት ከሚችልበት ምዕራፍ አልፎ አሁን የደረሰበት ደረጃ መድረሱ በጣም አሳዝኖናል ሲልም ነው ያስታወቀው።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የሀገር አንድነት እና ሰላምን ለማስከበር የሚወስዳቸውን እርምጃዎች በመደገፍ የኢዜማ አባላት እና አመራር ከጎኑ እንደምንሰለፍ እናሳውቃለን ያለው ኢዜማ፤ በሚወሰዱ እርምጃዎች ሰላማዊ ዜጎችን ምንም ዓይነት ጉዳት እንዳይደርስባቸው አስፈላጊው ጥንቃቄ መደረግ እንደሚገባው ለማስታወስ እንወዳለን ሲልም አሳስቧል።
የትግራይ ሕዝብ የሚወሰደው እርምጃ ለሀገር አንድነት እና ሰላም ማስከበር ብቻ እንደሆነ በመረዳት ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ጎን እንዲቆም ኢዜማ ጠይቋል።
"መላው የኢትዮጵያ ሕዝብም ይህንኑ በመረዳት አብሮነታችንን አደጋ ላይ የሚጥሉ እና ለሰላም እና ደህንነት እንቅፋት የሚሆኑ ማንኛውንም እንቅስቃሴዎች ከማድረግ ተቆጥበን አካባቢያችንን በንቃት እየጠበቅን ለሰላም እና ደህንነት መከበር ከፀጥታ አስከባሪዎች ጋር ትብብር እንድናደርግ የአደራ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን" ሲልም ኢዜማ ገልጿል።
************************************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ሕወሓት በትግራይ ክልል በሚገኘው የኢፌዴሪ መከላለከያ ሠራዊት ላይ የከፈተውን ጥቃት በፅኑ እንደሚያወግዘው ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።
በተለያየ ጊዜ ሕወሃት ሲያስተላልፋቸው የነበሩ የሥርዓት አልበኝነት ጥሪዎች እና በክልሉ ሕግን ተላልፎ ሲፈጽም የነበራቸው ድርጊቶች አልበቃ ብለው የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ምልክት የሆነው መከላከያ ሠራዊታችን ላይ የፈፀመው ጥቃት በፍፁም በዝምታ የሚታለፍ እንዳልሆነ እናምናለን ብሏል፤ ኢዜማ በመግለጫው።
የነበረው ችግር በንግግር መፈታት ከሚችልበት ምዕራፍ አልፎ አሁን የደረሰበት ደረጃ መድረሱ በጣም አሳዝኖናል ሲልም ነው ያስታወቀው።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የሀገር አንድነት እና ሰላምን ለማስከበር የሚወስዳቸውን እርምጃዎች በመደገፍ የኢዜማ አባላት እና አመራር ከጎኑ እንደምንሰለፍ እናሳውቃለን ያለው ኢዜማ፤ በሚወሰዱ እርምጃዎች ሰላማዊ ዜጎችን ምንም ዓይነት ጉዳት እንዳይደርስባቸው አስፈላጊው ጥንቃቄ መደረግ እንደሚገባው ለማስታወስ እንወዳለን ሲልም አሳስቧል።
የትግራይ ሕዝብ የሚወሰደው እርምጃ ለሀገር አንድነት እና ሰላም ማስከበር ብቻ እንደሆነ በመረዳት ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ጎን እንዲቆም ኢዜማ ጠይቋል።
"መላው የኢትዮጵያ ሕዝብም ይህንኑ በመረዳት አብሮነታችንን አደጋ ላይ የሚጥሉ እና ለሰላም እና ደህንነት እንቅፋት የሚሆኑ ማንኛውንም እንቅስቃሴዎች ከማድረግ ተቆጥበን አካባቢያችንን በንቃት እየጠበቅን ለሰላም እና ደህንነት መከበር ከፀጥታ አስከባሪዎች ጋር ትብብር እንድናደርግ የአደራ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን" ሲልም ኢዜማ ገልጿል።
በአማራ ክልል ለቤተ እምነቶች ጥበቃ ሊደረግ እንደሚገባ ጥሪ ቀረበ
******************
(ኢ ፕ ድ)
በአማራ ክልል ለቤተ እምነቶች ጥበቃ ሊደረግ እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል፡፡
ከጸጥታ አካላት ባገኘው መረጃ መሰረት፣ የኦርቶዶክስ አልባሳት ለብሶ መስጅድ፣ እንዲሁም የሙስሊም አልባሳት ለብሶ ቤተ ክርስቲያን ላይ ጥቃት ለመፈፀም ተልዕኮ የያዙ አካላት ወደ ክልሉ ገብተዋል ሲል የዘገበው ኢቢሲ ነው።
በመሆኑም በክልሉ ያሉ ሁሉም አማኞች ቤተ እምነታቸውን በመጠበቅ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል፡፡
******************
(ኢ ፕ ድ)
በአማራ ክልል ለቤተ እምነቶች ጥበቃ ሊደረግ እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል፡፡
ከጸጥታ አካላት ባገኘው መረጃ መሰረት፣ የኦርቶዶክስ አልባሳት ለብሶ መስጅድ፣ እንዲሁም የሙስሊም አልባሳት ለብሶ ቤተ ክርስቲያን ላይ ጥቃት ለመፈፀም ተልዕኮ የያዙ አካላት ወደ ክልሉ ገብተዋል ሲል የዘገበው ኢቢሲ ነው።
በመሆኑም በክልሉ ያሉ ሁሉም አማኞች ቤተ እምነታቸውን በመጠበቅ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ ገለጻ አደረገ
******
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢፌዲሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ አምባሳደሮችና ዓለም አቀፍ ድርጅቶቸ ሃለፊዎች ዛሬ (ጥቅምት 25 ቀን 2013 ዓ.ም) ገለጻ አድርገዋል።
ገለጻውን ተከተሎ ለተነሱ ጥያቄዎችም አምባሳደር ዲና ተጨማሪ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
******
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢፌዲሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ አምባሳደሮችና ዓለም አቀፍ ድርጅቶቸ ሃለፊዎች ዛሬ (ጥቅምት 25 ቀን 2013 ዓ.ም) ገለጻ አድርገዋል።
ገለጻውን ተከተሎ ለተነሱ ጥያቄዎችም አምባሳደር ዲና ተጨማሪ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በተፈጠረው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንቅስቃሴ መገታቱን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
በተፈጠረው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንቅስቃሴ መገታቱን የኢፌድሪ ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ተማሪዎች ባስተላለፈው መልዕክት፤ በኮቪድ-19 ምክንያት ተቋርጦ የነበረዉን ትምህርት ለማስቀጠል ዩኒቨርሲቲዎች ከጥቅምት 23/2013 ዓ/ም ጀምሮ ተማሪዎቻቸው ሪፖርት እንዲያደርጉ ማስታወቂያ ማውጣታቸዉን አስታውሶ፤ በተፈጠረው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ የተማሪዎችን እንቅስቃሴ ለጊዜዉ መገታቱን ገልጿል።
የሚኒስቴሩ መልዕክት እንደሚከተለው ቀርቧል፤
❶ እስካሁን ዩኒቨርሲቲወቻችሁ ላይ የደረሳችሁ ተማሪወች በግቢያችሁ እንድትቆዩና በየግቢያችሁ የሚሰጣችሁን ማሳሰቢያ እየተከታተላችሁ እንድትንቀሳቀሱ፤ አካባቢያችሁ ያለ የትኛውም የተለየ ጉዳይ ለተቋሞቻችሁ ሃላፊዎች እንድታሳውቁ
❷ እስካሁን ከወላጆቻችሁ አካባቢ ያልተነሳችሁ በቀጣይ ተለዋጭ ማስታወቂያ እስኪወጣ ድረስ ከወላጆቻችሁ ጋር እንድትቆዩ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
በተፈጠረው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንቅስቃሴ መገታቱን የኢፌድሪ ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ተማሪዎች ባስተላለፈው መልዕክት፤ በኮቪድ-19 ምክንያት ተቋርጦ የነበረዉን ትምህርት ለማስቀጠል ዩኒቨርሲቲዎች ከጥቅምት 23/2013 ዓ/ም ጀምሮ ተማሪዎቻቸው ሪፖርት እንዲያደርጉ ማስታወቂያ ማውጣታቸዉን አስታውሶ፤ በተፈጠረው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ የተማሪዎችን እንቅስቃሴ ለጊዜዉ መገታቱን ገልጿል።
የሚኒስቴሩ መልዕክት እንደሚከተለው ቀርቧል፤
❶ እስካሁን ዩኒቨርሲቲወቻችሁ ላይ የደረሳችሁ ተማሪወች በግቢያችሁ እንድትቆዩና በየግቢያችሁ የሚሰጣችሁን ማሳሰቢያ እየተከታተላችሁ እንድትንቀሳቀሱ፤ አካባቢያችሁ ያለ የትኛውም የተለየ ጉዳይ ለተቋሞቻችሁ ሃላፊዎች እንድታሳውቁ
❷ እስካሁን ከወላጆቻችሁ አካባቢ ያልተነሳችሁ በቀጣይ ተለዋጭ ማስታወቂያ እስኪወጣ ድረስ ከወላጆቻችሁ ጋር እንድትቆዩ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
"በከሃዲና ፅንፈኛ ቡድን ሴራ ህብረ ብሄራዊ አንድነታችን አይናድም"
*******************************************************************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ የሰጠው መግለጫ፤
ባለፉት ሁለት ዓመታት ተኩል በሃገራችን እየተካሄደ ባለው ሁለንተናዊ ለውጥ የትግራይ ህዝብ ተሳታፊነትና ተጠቃሚነትን በእጅጉ የሚጎዱ ተግባራትን ሲያካሂድ የቆየው በህወሃት ውስጥ መሽጎ የሚገኝ የማይለወጥና ቆሞ ቀር ቡድን ራሱን ከለውጡ ጋር በማላመድ የሃገራችንን ትንሳኤ ለማረጋገጥ በሚደረገው የለውጡ ጉዞ ውስጥ የራሱን አስተዋፅኦ እንዲያበረክት ከፍተኛ ጥረት ሲደረግ ቆይቷል፡፡
ይሁንና ይህ አጥፊና ህገ ወጥ ቡድን ከጅምሩ ጀምሮ ለውጡ እንዲደናቀፍ የተለያዩ ሴራዎችን በመሸረብ የሰው ህይወት እንዲጠፋ፤አካል እንዲጎድል፤ንብረት እንዲወድምና በህዝቦች መካከል ግጭት እንዲፈጠር ሲያደርግ መቆየቱ አይዘነጋም፡፡
ይባስ ብሎ የሰራዊታችንን ሰላማዊ እንቅስቃሴ ሲገድብ የቆየው አሸባሪ ቡድን የሃገር ምልክትና የኢትዮጵያ ህዝቦች ተምሳሌት በሆነው በመከላከያ ሰራዊታችን ላይ ጥቃት ከፍቷል፡፡
የሃገር መከላከያ ሰራዊታችን የሃገርን ሉአላዊ ክብር ለማስጠበቅ በተሰማራበት የትግራይ ክልል በጽንፈኛና ከሃዲ ቡድኖች የተሰነዘረበትን ጥቃት በተደራጀ መልኩ በታላቅ ሃገራዊ ፍቅርና የጀግንነት ስሜት እየመከተ ይገኛል፡፡
ጽንፈኛውና ከሃዲው ቡድን አነስተኛ የሰው ሃይል ባለበት የሰራዊታችን ካምፖች ድንገተኝነትን ተጠቅሞ ጥቃት ቢፈፅምም ጀግናው ሰራዊታችን ግን ወትሮም ዋጋ ከፍሎ ሃገርን ማዳን ልምዱ ነውና የተቃጣበትን ጥቃት ለመመከት ፅንፈኞችን በመፋለም ላይ ነው፡፡
በሃገር ንብረት ዘረፋ፤በግድያ ፤በአካል ማጉደልና በሰብአዊ መብት ጥሰቶች የሚታወቀው ከሃዲውና ጽንፈኛው ቡድን በአልመዳ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ የሰራዊታችንንና የሌሎች ሃገራትን ዪኒፎርም አስቀድሞ አመሳስሎ በማምረትና የራሱን ሃይል በማልበስ ገድለናል፤ማርከናል የሚል የተለመደ ማደናገሪያውን የክልሉን ሚዲያ ተጠቅሞ በመንዛት ላይ ይገኛል፡፡
እውነታው ግን ጀግናው ሰራዊታችን በታላቅ ጀግንነት፤በፍፁም የሃገር ፍቅር ስሜትና በአንድነት መንፈስ የፅንፈኛውና የከሃዲውን ጥቃት መመከቱ ነው፡፡
እንደሚታወቀው እኔ ከሌለሁ ኢትዮጵያ ትፍረስ የሚለው የስልጣን ጥመኛው ቡድን ያሰባሰበው የልዩ ሃይልና ሚሊሻ በአንዳንድ አካባቢዎች የመዋጋት ፍላጎት የሌለው ሲሆን መንግስት ዋስትና እንዲሰጠውም ይፈልጋል፡፡
ተገዳችሁና ሳትፈልጉ ወደ ጦርነት የገባችሁ የትግራይ ክልል ልዩ ሃይል አባላት!
በሰላማዊ መንገድ ወደ አጎራባች ክልሎችና በአቅራቢያችሁ ወዳለው የመከላከያ ሰራዊት ከገባችሁ መንግስት ሙሉና አስተማማኝ ዋስትና እንደሚሰጣችሁ ያረጋግጥላችyል፡፡
ውድ የትግራይ ህዝቦች!
ሰላማችሁን ለማስጠበቅ ከሃያ አመታት በላይ ከጎናችሁ ተሰልፎ የተዋደቀውን የሃገር መከላከያ ሰራዊት፤ችግራችሁን እየተካፈለና ልማታችሁን እየደገፈ አብሯችሁ በመልካም ወንድማማችነት የኖረውን ይህንን ጀግና ሰራዊት፤መውጋት ታሪክ ይቅር የማይለው የትግራይን ህዝብ የማይመጥን ከመሆኑ ባሻገር በዓለም ታሪክ አንድ መደበኛ ጦር በደባና በአሻጥር በገዛ ወገኑ ተወግቶ የማያውቅ መሆኑን ተረድታችሁ በዚህ አሳፋሪ ድርጊት ባለመሳተፍና ከሰራዊታችን ጎን በመሰለፍ የተለመደ ጀግንነትና ቁርጠኝነታችሁን እንድታረጋግጡ ጥሪ እናቀርብላችyለን፡፡
ለመላው የኢትዮጵያ ህዝቦች!
የሃገርን ሉአላዊ ክብር ለማስጠበቅ የቆመን ሰራዊት፤ሃገር እንጂ ብሄር የሌለውን ሰራዊት ፤የኢትዮጵያ ህዝቦች ትክክለኛ ተምሳሌት የሆነን ህብረ ብሄራዊ ሰራዊት፤ከሃገር አልፎ በአለም አቀፍ ሰላም ላይ ዝናና አክብሮትን ያተረፈን ሰራዊት ማጥቃት ሃገርን ተኩሶ እንደ መግደልና የኢትዮጵያውያንን ክብር እንደ መንካት ይቆጠራል፡፡
የሃገር መከላከያ ሰራዊት ትናንት ከላብ ጠብታ እስከ ህይወት መስዋእትነት በመክፈል ዛሬም በገንዘቡና በጉልበቱ መላ ህዝቡን እየደገፈ የመጣ ምስጋና እንጂ ጥቃት የማይገባው የህዝብ ልጅ መሆኑን አስታውሳችሁ ይህንን ታሪክ ይቅር የማይለው ስህተት እንድታወግዙትና የሃገራችንን ህብረ ብሄራዊ አንድነት ለማስከበርና አጠናክሮ ለማስቀጠል በምንወስደው እርምጃ ከጎናችን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
ድል ለህብረ ብሄራዊ አንድነታችን
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት
ጥቅምት 25 ቀን 2013 ዓ.ም
አዲስ አበባ
*******************************************************************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ የሰጠው መግለጫ፤
ባለፉት ሁለት ዓመታት ተኩል በሃገራችን እየተካሄደ ባለው ሁለንተናዊ ለውጥ የትግራይ ህዝብ ተሳታፊነትና ተጠቃሚነትን በእጅጉ የሚጎዱ ተግባራትን ሲያካሂድ የቆየው በህወሃት ውስጥ መሽጎ የሚገኝ የማይለወጥና ቆሞ ቀር ቡድን ራሱን ከለውጡ ጋር በማላመድ የሃገራችንን ትንሳኤ ለማረጋገጥ በሚደረገው የለውጡ ጉዞ ውስጥ የራሱን አስተዋፅኦ እንዲያበረክት ከፍተኛ ጥረት ሲደረግ ቆይቷል፡፡
ይሁንና ይህ አጥፊና ህገ ወጥ ቡድን ከጅምሩ ጀምሮ ለውጡ እንዲደናቀፍ የተለያዩ ሴራዎችን በመሸረብ የሰው ህይወት እንዲጠፋ፤አካል እንዲጎድል፤ንብረት እንዲወድምና በህዝቦች መካከል ግጭት እንዲፈጠር ሲያደርግ መቆየቱ አይዘነጋም፡፡
ይባስ ብሎ የሰራዊታችንን ሰላማዊ እንቅስቃሴ ሲገድብ የቆየው አሸባሪ ቡድን የሃገር ምልክትና የኢትዮጵያ ህዝቦች ተምሳሌት በሆነው በመከላከያ ሰራዊታችን ላይ ጥቃት ከፍቷል፡፡
የሃገር መከላከያ ሰራዊታችን የሃገርን ሉአላዊ ክብር ለማስጠበቅ በተሰማራበት የትግራይ ክልል በጽንፈኛና ከሃዲ ቡድኖች የተሰነዘረበትን ጥቃት በተደራጀ መልኩ በታላቅ ሃገራዊ ፍቅርና የጀግንነት ስሜት እየመከተ ይገኛል፡፡
ጽንፈኛውና ከሃዲው ቡድን አነስተኛ የሰው ሃይል ባለበት የሰራዊታችን ካምፖች ድንገተኝነትን ተጠቅሞ ጥቃት ቢፈፅምም ጀግናው ሰራዊታችን ግን ወትሮም ዋጋ ከፍሎ ሃገርን ማዳን ልምዱ ነውና የተቃጣበትን ጥቃት ለመመከት ፅንፈኞችን በመፋለም ላይ ነው፡፡
በሃገር ንብረት ዘረፋ፤በግድያ ፤በአካል ማጉደልና በሰብአዊ መብት ጥሰቶች የሚታወቀው ከሃዲውና ጽንፈኛው ቡድን በአልመዳ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ የሰራዊታችንንና የሌሎች ሃገራትን ዪኒፎርም አስቀድሞ አመሳስሎ በማምረትና የራሱን ሃይል በማልበስ ገድለናል፤ማርከናል የሚል የተለመደ ማደናገሪያውን የክልሉን ሚዲያ ተጠቅሞ በመንዛት ላይ ይገኛል፡፡
እውነታው ግን ጀግናው ሰራዊታችን በታላቅ ጀግንነት፤በፍፁም የሃገር ፍቅር ስሜትና በአንድነት መንፈስ የፅንፈኛውና የከሃዲውን ጥቃት መመከቱ ነው፡፡
እንደሚታወቀው እኔ ከሌለሁ ኢትዮጵያ ትፍረስ የሚለው የስልጣን ጥመኛው ቡድን ያሰባሰበው የልዩ ሃይልና ሚሊሻ በአንዳንድ አካባቢዎች የመዋጋት ፍላጎት የሌለው ሲሆን መንግስት ዋስትና እንዲሰጠውም ይፈልጋል፡፡
ተገዳችሁና ሳትፈልጉ ወደ ጦርነት የገባችሁ የትግራይ ክልል ልዩ ሃይል አባላት!
በሰላማዊ መንገድ ወደ አጎራባች ክልሎችና በአቅራቢያችሁ ወዳለው የመከላከያ ሰራዊት ከገባችሁ መንግስት ሙሉና አስተማማኝ ዋስትና እንደሚሰጣችሁ ያረጋግጥላችyል፡፡
ውድ የትግራይ ህዝቦች!
ሰላማችሁን ለማስጠበቅ ከሃያ አመታት በላይ ከጎናችሁ ተሰልፎ የተዋደቀውን የሃገር መከላከያ ሰራዊት፤ችግራችሁን እየተካፈለና ልማታችሁን እየደገፈ አብሯችሁ በመልካም ወንድማማችነት የኖረውን ይህንን ጀግና ሰራዊት፤መውጋት ታሪክ ይቅር የማይለው የትግራይን ህዝብ የማይመጥን ከመሆኑ ባሻገር በዓለም ታሪክ አንድ መደበኛ ጦር በደባና በአሻጥር በገዛ ወገኑ ተወግቶ የማያውቅ መሆኑን ተረድታችሁ በዚህ አሳፋሪ ድርጊት ባለመሳተፍና ከሰራዊታችን ጎን በመሰለፍ የተለመደ ጀግንነትና ቁርጠኝነታችሁን እንድታረጋግጡ ጥሪ እናቀርብላችyለን፡፡
ለመላው የኢትዮጵያ ህዝቦች!
የሃገርን ሉአላዊ ክብር ለማስጠበቅ የቆመን ሰራዊት፤ሃገር እንጂ ብሄር የሌለውን ሰራዊት ፤የኢትዮጵያ ህዝቦች ትክክለኛ ተምሳሌት የሆነን ህብረ ብሄራዊ ሰራዊት፤ከሃገር አልፎ በአለም አቀፍ ሰላም ላይ ዝናና አክብሮትን ያተረፈን ሰራዊት ማጥቃት ሃገርን ተኩሶ እንደ መግደልና የኢትዮጵያውያንን ክብር እንደ መንካት ይቆጠራል፡፡
የሃገር መከላከያ ሰራዊት ትናንት ከላብ ጠብታ እስከ ህይወት መስዋእትነት በመክፈል ዛሬም በገንዘቡና በጉልበቱ መላ ህዝቡን እየደገፈ የመጣ ምስጋና እንጂ ጥቃት የማይገባው የህዝብ ልጅ መሆኑን አስታውሳችሁ ይህንን ታሪክ ይቅር የማይለው ስህተት እንድታወግዙትና የሃገራችንን ህብረ ብሄራዊ አንድነት ለማስከበርና አጠናክሮ ለማስቀጠል በምንወስደው እርምጃ ከጎናችን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
ድል ለህብረ ብሄራዊ አንድነታችን
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት
ጥቅምት 25 ቀን 2013 ዓ.ም
አዲስ አበባ
መንግስትና ህዝቡ ከሀዲ ቡድኑ እየፈጸመ ያለውን አሳፋሪ ተግባር ለማክሸፍና የውርደት ካባውን ለማከናነብ መረባረብ አለባቸው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን አስታወቁ
**********************
(ኢ.ፕ.ድ)
መንግስትና ህዝቡ ከሀዲ ቡድኑ እየፈጸመ ያለውን አሳፋሪ ተግባር ለማክሽፍና የውርደት ካባውን ለማከናነብ መረባረብ አለባቸው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን አስታወቁ።
ከሀዲ ቡድኑ እየፈጸመ ያለውን አሳፋሪ ተግባር ለማክሽፍና የውርደት ካባውን ለማከናነብ ከመቼውም ጊዜ በላይ መረባረብ እንደሚያስፈልግ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ገለጹ፡፡
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ ላይ መሰጡት መግለጫ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ህዝብ የክብር፣ የሉዓላዊነት መለያ የሆነው የመከላከያ ሰራዊት በተልዕኮ ላይ እያለ በገዛ ወገኑ፣በካሀዲ ቡድን ጥቃት ተፈጸሞበታል፡፡
ቡድኑ ከትናትናው ዕለት ጀምሮ ልዩ ሀይሉን በማንቀሳቀስ በአማራ ህዝብ ላይ ወረራ ለማካሄድ ከፍተኛ ርብርብ በማሄድ ላይ ይገኛል ያሉት አቶ ደመቀ፤ ይህ ድርጊት የክፋት የመጨረሻው ጥግና ጡት ነካሽነት በመሆኑ መንግስትና ህዝቡ ይህን አሰፋሪ ተግባር ለማክሽፍ እና የውርደት ካባውን ለማከናነብ ከመቼውም ጊዜ በላይ መረባረብ ይኖርብናል ብለዋል፡፡
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ፍሰት ሴክሬታሪያት ኃላፊ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በበኩላቸው፤ የተፈጠረው ግጭት በአጠቃላይ በፌደራል መንግስቱ እና በትግራይ ክልል መንግስት መካከል ሳይሆን ከተወሰኑ ጥቅመኛ ስብስቦች ጋር የተፈጠረ መሆኑን የክልሉ ህዝብ ሊረዳ ይግባል ብለዋል።
በጌትነት ምህረቴ
**********************
(ኢ.ፕ.ድ)
መንግስትና ህዝቡ ከሀዲ ቡድኑ እየፈጸመ ያለውን አሳፋሪ ተግባር ለማክሽፍና የውርደት ካባውን ለማከናነብ መረባረብ አለባቸው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን አስታወቁ።
ከሀዲ ቡድኑ እየፈጸመ ያለውን አሳፋሪ ተግባር ለማክሽፍና የውርደት ካባውን ለማከናነብ ከመቼውም ጊዜ በላይ መረባረብ እንደሚያስፈልግ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ገለጹ፡፡
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ ላይ መሰጡት መግለጫ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ህዝብ የክብር፣ የሉዓላዊነት መለያ የሆነው የመከላከያ ሰራዊት በተልዕኮ ላይ እያለ በገዛ ወገኑ፣በካሀዲ ቡድን ጥቃት ተፈጸሞበታል፡፡
ቡድኑ ከትናትናው ዕለት ጀምሮ ልዩ ሀይሉን በማንቀሳቀስ በአማራ ህዝብ ላይ ወረራ ለማካሄድ ከፍተኛ ርብርብ በማሄድ ላይ ይገኛል ያሉት አቶ ደመቀ፤ ይህ ድርጊት የክፋት የመጨረሻው ጥግና ጡት ነካሽነት በመሆኑ መንግስትና ህዝቡ ይህን አሰፋሪ ተግባር ለማክሽፍ እና የውርደት ካባውን ለማከናነብ ከመቼውም ጊዜ በላይ መረባረብ ይኖርብናል ብለዋል፡፡
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ፍሰት ሴክሬታሪያት ኃላፊ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በበኩላቸው፤ የተፈጠረው ግጭት በአጠቃላይ በፌደራል መንግስቱ እና በትግራይ ክልል መንግስት መካከል ሳይሆን ከተወሰኑ ጥቅመኛ ስብስቦች ጋር የተፈጠረ መሆኑን የክልሉ ህዝብ ሊረዳ ይግባል ብለዋል።
በጌትነት ምህረቴ
“የትግራይ ልዩ ሀይልና ሚሊሺያ በፌደራል መንግስቱ እና በአማራ ክልል መንግስት የተደረገለትን የሰላም ጥሪ በሙሉ እምነት መቀበል አለበት” - - - ዶ/ር አብርሃም በላይ
የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር
*************************
(ኢ.ፕ.ድ)
የትግራይ ልዩ ሀይልና ሚሊሺያ በፌደራል መንግስቱ እና በአማራ ክልል መንግስት የተደረገለትን የሰላም ጥሪ በሙሉ እምነት መቀበል አለበት ሲሉ የትግራይ ብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር ዶ/ር አብርሃም በላይ አስታወቁ።
የትግራይ ልዩ ሀይልና ሚሊሺያ በፌደራል መንግስቱ እና በአማራ ክልል መንግስት የተደረገለትን የሰላም ጥሪ በሙሉ እምነት በመቀበል ከአማራ ህዝብ ጋር በሰላም እንዲቀላቀልና ከአካባቢው መስተዳድር አካላት ጋር በቅርበት በመስራት ፈጣን ሰላማዊ ሽግግር ለማስፈን የሚያስችል ድጋፍ እንዲያደርግ ዶ/ር አብረሀም ጠይቀዋል።
ለአመታት ዋጋ እየከፈለ ባለው የአገር የመከላከያ ሰራዊት የሰሜን እዝ ላይ በወሰደው አሳፋሪ የጥቃት ትንኰሳና ዝርፊያ መነሻነት የፌደራሉ መንግስት መጠነ ሰፊ ህግ የማስከበር እርምጃ ለመውሰድ መገደዱን ዶ/ር አብረሀም ተናግረዋል።
በአይነቱና በታሪክም ፍፁም እንግዳ የሆነ የክህደት ተግባር ለአገራቸው አንድነትና ክብር ለአመታት መስዋእትነት ለከፈሉ ህዝቦች ጠላፊው ቡድን ያለውን ንቀት ያሳየበት ነው፤ ያለዑት ዶ/ር አብረሀም፤ በዚህ የለየለት እብደቱም የአገርን ሉአላዊነት አደጋ ላይ የጣሰ በመሆኑ አስፈላጊው ህጋዊ እርምጃዎች በሙሉ እየተወሰደበት ይገኛል ብለዋል።
መንግስት ሰላምና መረጋጋትን በመላው ትግራይ ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ልዩ ልዩ የህግ ተግባራትን በመደበኛው የህግ አግባብ ለማስፈፀም አዳጋች መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት በዛሬው እለት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ ለስድስት ወራት የሚቆይ የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ ማወጁን ተናግረዋል።
"በአገር ላይ የተቃጣውን የክህደት ተግባር መላው የትግራይ ህዝብ ከመከላከያ ሐይል እና ከመላው የአገራችን ህዞቦች ጋር በጋራ በመቆም በፅናት እንድትመክቱና ይህንን አስከፊ የክህደት ተግባርም በጥብቅ በማውገዝ ከመንግስት ጎን እንትቆሙ ጥሪዬን አቀርባለሁ" ብለዋል፤ ዶ/ር አብረሀም።
የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር
*************************
(ኢ.ፕ.ድ)
የትግራይ ልዩ ሀይልና ሚሊሺያ በፌደራል መንግስቱ እና በአማራ ክልል መንግስት የተደረገለትን የሰላም ጥሪ በሙሉ እምነት መቀበል አለበት ሲሉ የትግራይ ብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር ዶ/ር አብርሃም በላይ አስታወቁ።
የትግራይ ልዩ ሀይልና ሚሊሺያ በፌደራል መንግስቱ እና በአማራ ክልል መንግስት የተደረገለትን የሰላም ጥሪ በሙሉ እምነት በመቀበል ከአማራ ህዝብ ጋር በሰላም እንዲቀላቀልና ከአካባቢው መስተዳድር አካላት ጋር በቅርበት በመስራት ፈጣን ሰላማዊ ሽግግር ለማስፈን የሚያስችል ድጋፍ እንዲያደርግ ዶ/ር አብረሀም ጠይቀዋል።
ለአመታት ዋጋ እየከፈለ ባለው የአገር የመከላከያ ሰራዊት የሰሜን እዝ ላይ በወሰደው አሳፋሪ የጥቃት ትንኰሳና ዝርፊያ መነሻነት የፌደራሉ መንግስት መጠነ ሰፊ ህግ የማስከበር እርምጃ ለመውሰድ መገደዱን ዶ/ር አብረሀም ተናግረዋል።
በአይነቱና በታሪክም ፍፁም እንግዳ የሆነ የክህደት ተግባር ለአገራቸው አንድነትና ክብር ለአመታት መስዋእትነት ለከፈሉ ህዝቦች ጠላፊው ቡድን ያለውን ንቀት ያሳየበት ነው፤ ያለዑት ዶ/ር አብረሀም፤ በዚህ የለየለት እብደቱም የአገርን ሉአላዊነት አደጋ ላይ የጣሰ በመሆኑ አስፈላጊው ህጋዊ እርምጃዎች በሙሉ እየተወሰደበት ይገኛል ብለዋል።
መንግስት ሰላምና መረጋጋትን በመላው ትግራይ ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ልዩ ልዩ የህግ ተግባራትን በመደበኛው የህግ አግባብ ለማስፈፀም አዳጋች መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት በዛሬው እለት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ ለስድስት ወራት የሚቆይ የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ ማወጁን ተናግረዋል።
"በአገር ላይ የተቃጣውን የክህደት ተግባር መላው የትግራይ ህዝብ ከመከላከያ ሐይል እና ከመላው የአገራችን ህዞቦች ጋር በጋራ በመቆም በፅናት እንድትመክቱና ይህንን አስከፊ የክህደት ተግባርም በጥብቅ በማውገዝ ከመንግስት ጎን እንትቆሙ ጥሪዬን አቀርባለሁ" ብለዋል፤ ዶ/ር አብረሀም።
ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር በሚያዋስናት ድንበር ዙሪያ የተጠናከረ የጋራ የጸጥታ ጥበቃን እንደምታከናውን አስታወቀች።
*****************************************
(ኢ.ፕ.ድ)
የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት ኃላፊ አብደል ፈታህ አል-ቡርሃን አገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር በሚያዋስናት ድንበር ዙሪያ የተጠናከረ የጋራ የጸጥታ ጥበቃን ለማከናወን ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር መስማማታቸውን የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት ኃላፊ አብደል ፈታህ አል-ቡርሃን የሁለት ቀናት የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ወደ አገራቸው መመለሳቸው ይታወቃል።
ጉብኝቱን እና የተደረጉ ውይይትችን በማስመልከት የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ኦሜር ጋማር ኤልዲን እንደተናገሩት፤ ሁለቱ አገራት በተለይም በድንበርና በቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል። ሁለቱ ወገኖች “በድንበር፣ በልማትና በቀጠናዊ የፀጥታ ጉዳዮች ላይ በትብብር ለመስራት ስምምነት ላይ ደርሰዋል።
የአል-ቡርሀን ጉብኝት የተካሄደው የኢትዮጵያ ማዕከላዊ መንግስት ከትግራይ ክልል ጋር ችግር ውስጥ ባለበት ወቅት መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትሩ፤ ቀደም ሲል ሱዳን የድንበር አካባቢዎችን ለመቆጣጠር እና በግዛቷ በኩል የአማፅያን ጥቃቶችን በመከላከል ለኢትዮጵያ ስታደርግ የቆየችውን ድጋፍ አጠናክራ ትቀጥላለች ብለዋል።
የሁለቱን አገራት ታሪካዊ ግንኙነት በማጠናከር የሁለቱን ህዝቦች ፍላጎት መሰረት በማድረግ መስራት እንደሚያሰፈልግም መሪዎቹ ተስማምተዋል ብለዋል ፡፡
የድንበር ጥቃቶችን ለመከላከልና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን ለመዋጋት ሁለቱ አገራት መስማማታቸውንም ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡
በወንድማገኝ አሸብር
*****************************************
(ኢ.ፕ.ድ)
የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት ኃላፊ አብደል ፈታህ አል-ቡርሃን አገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር በሚያዋስናት ድንበር ዙሪያ የተጠናከረ የጋራ የጸጥታ ጥበቃን ለማከናወን ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር መስማማታቸውን የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት ኃላፊ አብደል ፈታህ አል-ቡርሃን የሁለት ቀናት የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ወደ አገራቸው መመለሳቸው ይታወቃል።
ጉብኝቱን እና የተደረጉ ውይይትችን በማስመልከት የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ኦሜር ጋማር ኤልዲን እንደተናገሩት፤ ሁለቱ አገራት በተለይም በድንበርና በቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል። ሁለቱ ወገኖች “በድንበር፣ በልማትና በቀጠናዊ የፀጥታ ጉዳዮች ላይ በትብብር ለመስራት ስምምነት ላይ ደርሰዋል።
የአል-ቡርሀን ጉብኝት የተካሄደው የኢትዮጵያ ማዕከላዊ መንግስት ከትግራይ ክልል ጋር ችግር ውስጥ ባለበት ወቅት መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትሩ፤ ቀደም ሲል ሱዳን የድንበር አካባቢዎችን ለመቆጣጠር እና በግዛቷ በኩል የአማፅያን ጥቃቶችን በመከላከል ለኢትዮጵያ ስታደርግ የቆየችውን ድጋፍ አጠናክራ ትቀጥላለች ብለዋል።
የሁለቱን አገራት ታሪካዊ ግንኙነት በማጠናከር የሁለቱን ህዝቦች ፍላጎት መሰረት በማድረግ መስራት እንደሚያሰፈልግም መሪዎቹ ተስማምተዋል ብለዋል ፡፡
የድንበር ጥቃቶችን ለመከላከልና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን ለመዋጋት ሁለቱ አገራት መስማማታቸውንም ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡
በወንድማገኝ አሸብር
በተፈጠረው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንቅስቃሴ መገታቱን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ
*******************
(ኢ.ፕ.ድ)
በተፈጠረው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንቅስቃሴ መገታቱን የኢፌድሪ ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ተማሪዎች ባስተላለፈው መልዕክት፤ በኮቪድ-19 ምክንያት ተቋርጦ የነበረዉን ትምህርት ለማስቀጠል ዩኒቨርሲቲዎች ከጥቅምት 23/2013 ዓ/ም ጀምሮ ተማሪዎቻቸው ሪፖርት እንዲያደርጉ ማስታወቂያ ማውጣታቸዉን አስታውሶ፤ በተፈጠረው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ የተማሪዎችን እንቅስቃሴ ለጊዜዉ መገታቱን ገልጿል።
የሚኒስቴሩ መልዕክት እንደሚከተለው ቀርቧል፤
❶ እስካሁን ዩኒቨርሲቲወቻችሁ ላይ የደረሳችሁ ተማሪወች በግቢያችሁ እንድትቆዩና በየግቢያችሁ የሚሰጣችሁን ማሳሰቢያ እየተከታተላችሁ እንድትንቀሳቀሱ፤ አካባቢያችሁ ያለ የትኛውም የተለየ ጉዳይ ለተቋሞቻችሁ ሃላፊዎች እንድታሳውቁ
❷ እስካሁን ከወላጆቻችሁ አካባቢ ያልተነሳችሁ በቀጣይ ተለዋጭ ማስታወቂያ እስኪወጣ ድረስ ከወላጆቻችሁ ጋር እንድትቆዩ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
*******************
(ኢ.ፕ.ድ)
በተፈጠረው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንቅስቃሴ መገታቱን የኢፌድሪ ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ተማሪዎች ባስተላለፈው መልዕክት፤ በኮቪድ-19 ምክንያት ተቋርጦ የነበረዉን ትምህርት ለማስቀጠል ዩኒቨርሲቲዎች ከጥቅምት 23/2013 ዓ/ም ጀምሮ ተማሪዎቻቸው ሪፖርት እንዲያደርጉ ማስታወቂያ ማውጣታቸዉን አስታውሶ፤ በተፈጠረው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ የተማሪዎችን እንቅስቃሴ ለጊዜዉ መገታቱን ገልጿል።
የሚኒስቴሩ መልዕክት እንደሚከተለው ቀርቧል፤
❶ እስካሁን ዩኒቨርሲቲወቻችሁ ላይ የደረሳችሁ ተማሪወች በግቢያችሁ እንድትቆዩና በየግቢያችሁ የሚሰጣችሁን ማሳሰቢያ እየተከታተላችሁ እንድትንቀሳቀሱ፤ አካባቢያችሁ ያለ የትኛውም የተለየ ጉዳይ ለተቋሞቻችሁ ሃላፊዎች እንድታሳውቁ
❷ እስካሁን ከወላጆቻችሁ አካባቢ ያልተነሳችሁ በቀጣይ ተለዋጭ ማስታወቂያ እስኪወጣ ድረስ ከወላጆቻችሁ ጋር እንድትቆዩ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
የሀገር መከላከያ ሰራዊት የተቃጣበትን ጥቃት በመመከት የህዝቦችን ደህንነትና የሀገሪቱን ሉዓላዊነት በማስጠበቅ ሃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን አስታወቀ
***^*************
(ኢ.ፕ.ድ)
የሀገር መከላከያ ሰራዊት የተቃጣበትን ጥቃት በመመከት የህዝቦችን ደህንነትና የሀገሪቱን ሉዓላዊነት በማስጠበቅ ሃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን አስታወቀ።
ከትናንት ምሽት ጀምሮ በኢፌዴሪ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ላይ የታጠቀ የህወሃት ሃይል ጥቃት በማድረስ ጉዳት ለማስከተል፣ በህዝቦች ደህንነትና በሀገር ሉዓላዊነት ላይ አደጋ በመጋረጥ ሀገሪቱን ለማፍረስ ሙከራ ማድረጉን የኢፌዲሪ መከላከያ አስታውቋል ።
"መከላከያ ሰራዊታችን የተቃጣበትን ጥቃት በመመከትና በማክሸፍ የህዝቦችን ደህንነትና የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት በማስጠበቅ ሃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል" ብሏል።
ይህንኑ በአስተማማኝ መልኩ በመፈጸም ስኬታማ ተግባር በዘላቂነት ለማረጋገጥ ከህዝቡ ጋር እየሰራን እንደምንገኝ ለህዝባችን ማስታወቅ እንወዳለን ሲልም ነው መከላከያ የገለጸው።
***^*************
(ኢ.ፕ.ድ)
የሀገር መከላከያ ሰራዊት የተቃጣበትን ጥቃት በመመከት የህዝቦችን ደህንነትና የሀገሪቱን ሉዓላዊነት በማስጠበቅ ሃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን አስታወቀ።
ከትናንት ምሽት ጀምሮ በኢፌዴሪ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ላይ የታጠቀ የህወሃት ሃይል ጥቃት በማድረስ ጉዳት ለማስከተል፣ በህዝቦች ደህንነትና በሀገር ሉዓላዊነት ላይ አደጋ በመጋረጥ ሀገሪቱን ለማፍረስ ሙከራ ማድረጉን የኢፌዲሪ መከላከያ አስታውቋል ።
"መከላከያ ሰራዊታችን የተቃጣበትን ጥቃት በመመከትና በማክሸፍ የህዝቦችን ደህንነትና የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት በማስጠበቅ ሃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል" ብሏል።
ይህንኑ በአስተማማኝ መልኩ በመፈጸም ስኬታማ ተግባር በዘላቂነት ለማረጋገጥ ከህዝቡ ጋር እየሰራን እንደምንገኝ ለህዝባችን ማስታወቅ እንወዳለን ሲልም ነው መከላከያ የገለጸው።
ሰራዊቱ በሰፈረባቸዉ ካምፖች የተከፈተበትን የከሃዲዎች ጥቃት በብቃት መክቶ ወደ ጸረ ማጥቃት እርምጃ መሽጋገሩን አስታወቀ
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊይ ተኩስ በተከፈተበት ካምፖች ሁሉ በጠንካራ መከላከል ዉጊያ የከሃዲዉን ሃይል በጀግንነት መክቶ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰበት ይገኛል፡፡
መከላከያ ሰራዊትና የአማራ የጸጥታ ሃይል ተቀናጅተዉ በሰሜን ጎንደር ዞን ቀራቅር በተባለ ቦታ የእብሪተኛዉ ቡድን የሰነዘረዉን የማጥቃት ዉጊያ በብቃት በመመከት በዚህ ሃይል ላይ ከፍተኛ ሰብዓዊና ማቴሪያላዊ ኪሳራ አድርሰውበታል።
"ሰራዊታችን በዛሬዉ እለት ከሰዓት በኋላ በወሰደዉ ቅንጅታዊ የማጥቃት እርምጃ ከቀራቅር በቅርብ ርቀት ላይ በሚገኘዉ ከፍተኛ ቦታ ላይ የነበረዉን የእብሪተኛዉ አጥፊ ቡድን ሃይል በከፍተኛ ሁኔታ በማጥቃት ቦታዉን በሰራዊታችን ቁጥጥር ሥር አዉሎታል" ብሏል፡፡
ጀግናዉ ሰራዊት በወሰደዉ የማጥቃት እርምጃ በዚህ ነብሰ በላ ቡድን ሃይል ላይ ከፍተኛ ሰብዓዊ ኪሳራ በማድረስ የቡድንና የነብስ ወከፍ መሳሪያዎችንም መማረኩን አሥታውቊል ፡፡
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊይ ተኩስ በተከፈተበት ካምፖች ሁሉ በጠንካራ መከላከል ዉጊያ የከሃዲዉን ሃይል በጀግንነት መክቶ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰበት ይገኛል፡፡
መከላከያ ሰራዊትና የአማራ የጸጥታ ሃይል ተቀናጅተዉ በሰሜን ጎንደር ዞን ቀራቅር በተባለ ቦታ የእብሪተኛዉ ቡድን የሰነዘረዉን የማጥቃት ዉጊያ በብቃት በመመከት በዚህ ሃይል ላይ ከፍተኛ ሰብዓዊና ማቴሪያላዊ ኪሳራ አድርሰውበታል።
"ሰራዊታችን በዛሬዉ እለት ከሰዓት በኋላ በወሰደዉ ቅንጅታዊ የማጥቃት እርምጃ ከቀራቅር በቅርብ ርቀት ላይ በሚገኘዉ ከፍተኛ ቦታ ላይ የነበረዉን የእብሪተኛዉ አጥፊ ቡድን ሃይል በከፍተኛ ሁኔታ በማጥቃት ቦታዉን በሰራዊታችን ቁጥጥር ሥር አዉሎታል" ብሏል፡፡
ጀግናዉ ሰራዊት በወሰደዉ የማጥቃት እርምጃ በዚህ ነብሰ በላ ቡድን ሃይል ላይ ከፍተኛ ሰብዓዊ ኪሳራ በማድረስ የቡድንና የነብስ ወከፍ መሳሪያዎችንም መማረኩን አሥታውቊል ፡፡