የሱዳን ሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤት ሊቀመንበር ጄነራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን ለሁለት ቀናት የሥራ ጉብኝት አዲስ ፈበባ ገብተዋል።
ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ኢትዮ ቴሌኮምን በዓመት ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ሊያሳጣ በሚችል ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
*****************
(ኢ.ፕ.ድ)
ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ኢትዮ ቴሌኮምን በዓመት ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ሊያሳጣ በሚችል ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ።
የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ከተማ የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀል በሚፈፀምባቸው ቦታዎች ላይ ጥብቅ የመረጃና የክትትል ሥራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል።
በዚህም ትናንት በአዲስ አበባ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 እና ልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 በተካሄደ ኦፕሬሽን በህገ ወጥ መልኩ ዓለም አቀፍ የስልክ ጥሪዎችን በመጥለፍ በራሳቸው መስመሮች ለደንበኞች በማቅረብ ሕገወጥ ድርጊት ሲፈፅሙ የነበሩ ሦስት ተጠርጣሪዎች በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አማካኝነት በህግ በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ ማድረጉን አገልግሎት መስሪያ ቤቱ አስታውቋል።
ተጠርጣሪዎቹ ከኢትዮ ቴሌኮም አውቅና ውጪ በኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የስልክ ጥሪዎችን በማስተላለፍ የራሳቸውን ገቢ ሲሰበስቡ መቆየታቸውን የገለፀው ብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት፤ ሕገ ወጥ ድርጊቱ ባይከሽፍ ኖሮ፤ ኢትዮ ቴሌኮምን በዓመት ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ሊያሳጣው እንደሚችልም ጠቁሟል።
በወንጀል ድርጊቱ የተጠረጠሩት ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ሲውሉ፤ ሲገለገሉባቸው የነበሩ 10 ጌትዌይ (ሲምቦክስ)፣ 17 ቲፕሊንክ፣ 59 ሲዲኤምኤ፣ 3 ራውተር፣ 2 ሺህ ሲምካርድ፣ 3 ላፕቶፕ፣ የባንክ ደብተሮች፣ ሲፒኦዎችና ሌሎች ሕገ ወጥ መሳሪያዎች በኢግዚቢትነት መያዛቸውን ብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አስታውቋል።
ሕገ ወጦችን በቁጥጥር ሥር ለማዋል በነበረው ሂደት ህብረተሰቡ ላሳየው የላቀ ተሳትፎ አገልግሎት መስሪያ ቤቱ ምስጋና አቅርቧል።
በቀጣይም ህብረተሰቡ ሕገ ወጦችን በማጋለጥ ረገድ የተለመደ ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል አገልግሎት መስሪያ ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።
*****************
(ኢ.ፕ.ድ)
ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ኢትዮ ቴሌኮምን በዓመት ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ሊያሳጣ በሚችል ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ።
የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ከተማ የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀል በሚፈፀምባቸው ቦታዎች ላይ ጥብቅ የመረጃና የክትትል ሥራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል።
በዚህም ትናንት በአዲስ አበባ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 እና ልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 በተካሄደ ኦፕሬሽን በህገ ወጥ መልኩ ዓለም አቀፍ የስልክ ጥሪዎችን በመጥለፍ በራሳቸው መስመሮች ለደንበኞች በማቅረብ ሕገወጥ ድርጊት ሲፈፅሙ የነበሩ ሦስት ተጠርጣሪዎች በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አማካኝነት በህግ በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ ማድረጉን አገልግሎት መስሪያ ቤቱ አስታውቋል።
ተጠርጣሪዎቹ ከኢትዮ ቴሌኮም አውቅና ውጪ በኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የስልክ ጥሪዎችን በማስተላለፍ የራሳቸውን ገቢ ሲሰበስቡ መቆየታቸውን የገለፀው ብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት፤ ሕገ ወጥ ድርጊቱ ባይከሽፍ ኖሮ፤ ኢትዮ ቴሌኮምን በዓመት ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ሊያሳጣው እንደሚችልም ጠቁሟል።
በወንጀል ድርጊቱ የተጠረጠሩት ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ሲውሉ፤ ሲገለገሉባቸው የነበሩ 10 ጌትዌይ (ሲምቦክስ)፣ 17 ቲፕሊንክ፣ 59 ሲዲኤምኤ፣ 3 ራውተር፣ 2 ሺህ ሲምካርድ፣ 3 ላፕቶፕ፣ የባንክ ደብተሮች፣ ሲፒኦዎችና ሌሎች ሕገ ወጥ መሳሪያዎች በኢግዚቢትነት መያዛቸውን ብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አስታውቋል።
ሕገ ወጦችን በቁጥጥር ሥር ለማዋል በነበረው ሂደት ህብረተሰቡ ላሳየው የላቀ ተሳትፎ አገልግሎት መስሪያ ቤቱ ምስጋና አቅርቧል።
በቀጣይም ህብረተሰቡ ሕገ ወጦችን በማጋለጥ ረገድ የተለመደ ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል አገልግሎት መስሪያ ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።
"የኢትዮጵያ እና የሱዳን ሕዝቦች በባህልና ታሪክ የተሳሰረ ጠንካራ ግንኙነት አላቸው"
ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢትዮጵያ እና የሱዳን ሕዝቦች በባህል እና በታሪክ የተሳሰረ ጠንካራ ግንኙነት እንዳላቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ አህመድ ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከጄነራል አልቡርሀን ጋር የአዳማ ከተማን የጎበኙ ሲሆን፤ በዚሁ ወቅት አባ ገዳዎች ለጄነራል አልቡርሃን ፈረስ እና ጋሻ ሸልመዋል።
ጠቅላይ ሚኒስር ዶ/ ር አብይ አህመድ በማህበራዊ ገጻቸው፤ "አባገዳዎች የሁለቱ ሕዝቦች ትስስር ይጠብቅ ዘንድ መርቀውናል። ለጄነራል አልቡርሃን ፈረስ እና ጋሻ በመሸለም አክብሮታችንን ገልጸንለታል" ሲሉም አስታውቀዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢትዮጵያ እና የሱዳን ሕዝቦች በባህል እና በታሪክ የተሳሰረ ጠንካራ ግንኙነት እንዳላቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ አህመድ ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከጄነራል አልቡርሀን ጋር የአዳማ ከተማን የጎበኙ ሲሆን፤ በዚሁ ወቅት አባ ገዳዎች ለጄነራል አልቡርሃን ፈረስ እና ጋሻ ሸልመዋል።
ጠቅላይ ሚኒስር ዶ/ ር አብይ አህመድ በማህበራዊ ገጻቸው፤ "አባገዳዎች የሁለቱ ሕዝቦች ትስስር ይጠብቅ ዘንድ መርቀውናል። ለጄነራል አልቡርሃን ፈረስ እና ጋሻ በመሸለም አክብሮታችንን ገልጸንለታል" ሲሉም አስታውቀዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ ባለቤታቸው የማይታወቁ ቦታዎች፣ ህንጻዎች እና ቤቶች መገኘታቸውን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በከተማው ያሉ ህገ-ወጥ ተግባራትን ለመከላከልና ወደ ህጋዊ መስመር ለማምጣት ባደረገው ማጣራት ባለቤታቸው የማይታወቁ ቦታዎች፣ ህንጻዎች እና ቤቶች መገኘታቸውን አስታወቀ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ፅህፈት ቤት ዛሬ ማምሻውን ባወጣው የጥሪ ማስታወቂያ፤ የከተማ አስተዳደሩ በከተማው ያሉ ህገ-ወጥ ተግባራትን ለመከላከልና ወደ ህጋዊ መስመር ለማምጣት የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ መሆኑ ገልጿል።
ከነዚህ ተግባራትም ውስጥ አንደኛው እና ዋነኛው ህገ-ወጥ የመሬት ወረራና ህገ-ወጥ ግንባታ ሲሆን ይህንኑ በከተማው የሚታየውን ህገ-ወጥ ድርጊት ለማጣራት እና መረጃ ለማሰባሰብ በየደረጃው ግብረሃይል በማደራጀት እና ህዝቡን በማሳተፍ ከአንድ ወር በላይ የማጣራት ስራ ሲሰራ መቆየቱ የሚጠቀስ ነው ብሏል፡፡
ግበረ ሀይሉ ባደረገው ማጣራትም የደረሰባቸው ዋና ዋና ግኝቶቹን የገለጸ ሲሆን፤ በህገ-ወጥ መንገድ የታጠሩ እና ባለቤትነታቸውን ማረጋገጥ ያልተቻለ ቦታዎችን፣ በህገ-ወጥ መንገድ መገንባት የተጀመሩ ግንባታዎች መኖራቸውን እና ባለቤቶቻቸው ያልታወቁ ቤቶች እና ህንፃዎች መገኘታቸውን አስታውቋል።
የከተማ አስተዳደሩ በግኝቶቹ ላይ ውሳኔ ወስኖ እርምጃ ከመውሠዱ በፊት የኔ ነው ባይ ካለ አንድ እድል ለመስጠት እንደሚፈልግ ጠቅሶ፤ ህጋዊ ማስረጃ አለኝ የሚል አካልም ሆነ ግለሰብ ከነገ (ጥቅምት 23/02/2013) ጀምሮ ለ3 ተከታታይ ቀናት መረጃም ሆነ ማስረጃ በመያዝ ለዚሁ ጉዳይ በየክፍለ ከተማው በተዋቀረ ግብረሃይል ጋር በመቅረብ እንዲያስረዳ የከተማ አስተዳድሩ አሳስቧል።
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በከተማው ያሉ ህገ-ወጥ ተግባራትን ለመከላከልና ወደ ህጋዊ መስመር ለማምጣት ባደረገው ማጣራት ባለቤታቸው የማይታወቁ ቦታዎች፣ ህንጻዎች እና ቤቶች መገኘታቸውን አስታወቀ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ፅህፈት ቤት ዛሬ ማምሻውን ባወጣው የጥሪ ማስታወቂያ፤ የከተማ አስተዳደሩ በከተማው ያሉ ህገ-ወጥ ተግባራትን ለመከላከልና ወደ ህጋዊ መስመር ለማምጣት የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ መሆኑ ገልጿል።
ከነዚህ ተግባራትም ውስጥ አንደኛው እና ዋነኛው ህገ-ወጥ የመሬት ወረራና ህገ-ወጥ ግንባታ ሲሆን ይህንኑ በከተማው የሚታየውን ህገ-ወጥ ድርጊት ለማጣራት እና መረጃ ለማሰባሰብ በየደረጃው ግብረሃይል በማደራጀት እና ህዝቡን በማሳተፍ ከአንድ ወር በላይ የማጣራት ስራ ሲሰራ መቆየቱ የሚጠቀስ ነው ብሏል፡፡
ግበረ ሀይሉ ባደረገው ማጣራትም የደረሰባቸው ዋና ዋና ግኝቶቹን የገለጸ ሲሆን፤ በህገ-ወጥ መንገድ የታጠሩ እና ባለቤትነታቸውን ማረጋገጥ ያልተቻለ ቦታዎችን፣ በህገ-ወጥ መንገድ መገንባት የተጀመሩ ግንባታዎች መኖራቸውን እና ባለቤቶቻቸው ያልታወቁ ቤቶች እና ህንፃዎች መገኘታቸውን አስታውቋል።
የከተማ አስተዳደሩ በግኝቶቹ ላይ ውሳኔ ወስኖ እርምጃ ከመውሠዱ በፊት የኔ ነው ባይ ካለ አንድ እድል ለመስጠት እንደሚፈልግ ጠቅሶ፤ ህጋዊ ማስረጃ አለኝ የሚል አካልም ሆነ ግለሰብ ከነገ (ጥቅምት 23/02/2013) ጀምሮ ለ3 ተከታታይ ቀናት መረጃም ሆነ ማስረጃ በመያዝ ለዚሁ ጉዳይ በየክፍለ ከተማው በተዋቀረ ግብረሃይል ጋር በመቅረብ እንዲያስረዳ የከተማ አስተዳድሩ አሳስቧል።
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ የሰላማዊ ሰዎችን ሕይወት ባጠፋው ኦነግ ሸኔ ላይ እርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ
****************************
(ኢ ፕ ድ)
በምዕራብ ወለጋ ሰላማዊ ዜጎች ጭካኔ በተሞላበት መንገድ በአንድ ስፍራ ህይወታቸው እንዲያልፍ ባደረገው የኦነግ ሸኔ ቡድን ላይ እርምጃ እንደሚወስድ የኦሮሚያ ክልል መንግስት አስታወቀ።
የክልሉ መንግስት ባወጣው መግለጫ፥ መንግስት የህዝቡን ፍላጎትና ጥያቄ በማገናዘብ የልማት ስራዎችን፣ የሰላም እና የስርዓት ግንባታ ላይ እየሰራ ባለበት በአሁኑ ወቅት፤ ከለውጡ በተቃራኒ የቆሙ ሀይሎች በህዝቡ ላይ አሰቃቂ አደጋ እያደረሱ መሆኑን አስታውቋል።
የጥፋት ሀይሎቹ መንግስት የፖለቲካ እና የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት እየሰራ ባለበት ወቅት በተቃራኒው በመቆም ጭቃኔ የተሞላበት ተግባር በህዝቡ ላይ እየፈፀሙ ነው ብሏል።
የኦነግ ሸኔ ሽፍታ ከህውሃት ጋር በመሻረክ በኦሮሚያ ክልል እና በሀገሪቱ ሰላም እና መረጋጋት እንዳይኖር ሲሰሩ መቆየታቸውን ያስታወሰው መግለጫው፤ በተለያዩ ወቅቶች የግጭት አጀንዳዎችን በማዘጋጀት በሚዲያ በማሰራጨት እንዲሁም በህገ ወጥ መንገድ በገቡ የጦር መሳሪያዎች በፀጥታ ሀይሎች፣ በመንግስት መዋቅር እና በተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ የግድያ እርምጃ በመውሰድ ችግሮችን ሲፈጥሩ ቆይተዋል ብሏል መግለጫው።
ጭካኔ በተሞላበት መንገድ በተፈፀሙ በእነዚህ ተግባራትም በህብረተሰቡ ላይ የስነ ልቦና ጫና እንዲፈጠር፣ በስጋት እንዲሞላ እና ከዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ራሱን ቆጥቡ በረሃብ እና በጥማት እንዲጎዳ እያደረጉ ነውም ብሏል።
በተለይም በምዕራብ ኦሮሚያ አቅጣጫ በሚገኙ ዞኖች ህፃናት፣ ሴቶች፣ አዛውንቶች እና ወጣቶችን ጨምሮ ጭካኔ በተሞላበት መንገድ እንዲገደሉ፣ በእሳት እንዲቃጠሉ፣ የአካል ጉዳት እንዲደርስባቸው እንዲሁም የስነ ልቦና ጉዳት እንዲደርስባቸው ማድረጉ ይታወቃልም ብሏል፡፡
ከሁሉም በላይ በጫካ ውስጥ መሽጎ ከቦታ ቦታ የሚዘዋወረው ኦነግ ሸኔ ሰዎችን ጠልፎ በመውሰድ ጉዳት ሲያደርስ መቆየቱ ያወሳው መግለጫው፤ በተለያዩ ጊዜያትም የፀጥታ እና የአስተዳደር አካላት በተመሳሳይ መንገድ ጫካ ውስጥ በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወታቸው እንዲያልፍ ሲያደርግ ቆይቷልም ነው ያለው።
የኦነግ ሸኔ ሽፍታ እስካሁን በፈፀማቸው የሽብር ተግባራት በርካታ ቤተሰቦች ተበትነዋል፣ ህፃናትን ያለ አባትና እናት አስቀርቷል ያለው መግለጫው፥ የህዝቡና የግለሰቦች ሀብትም እንዲጠፋ ማድረጉን አስታውሷል።
የኦሮሚያ ክልል መንግስት የህዝቡን ሰላም ለማረጋገጥ ያለውን ተልዕኮ እና ሀላፊነት ለመወጣት ህዝቡን ባሳተፈ መልኩ የህግ የበላይነትን የማስከበር ስራ በስፋት እያከናወነ መሆኑንም ጠቅሷል፡፡
የህወሓት ተላላኪ የሆነው ይህ የኦነግ ሸኔ ቡድን ህዝቡ እና መንግስት በጋራ በመሆን የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ እየወሰዱት ባለው እርምጃ ለመጥፋት መቃረቡንም መግለጫው አመላክቷል።
እየተወሰደ ባለው እርምጃ የመቃብር አፋፍ ላይ የደረሰው ይህ ቡድን ተስፋ በመቁረጡ በአንድ ስፍራ በሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ ጥቃት እያደረሰ መሆኑም ተገልጿል።
በትናትናው እለትም በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ ጋዋ ቀናቲ ቀበሌ ጨለማን ተገን በማድረግ በፈፀመው የሽብር ጥቃት ሰላማዊ ዜጎችን ጭካኔ በተሞላበት መንገድ በአንድ ስፍራ ህይወታቸው እንዲያልፍ ማድረጉንም ነው የገለጸው።
የኦሮሚያ ክልል መንግስት ከህዝቡ እንዲሁም የፀጥታ እና አስተዳደር አካላት ጋር በመሆን እነዚህ ሽፍታዎች የገቡበት ቦታ በመግባት አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስድም ገልጿል።
በተፈፀመው ጥቃት ለተሰው ወገኖች የተሰማውን ሀዘን የገለፀው የክልሉ መንግስት ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን ተመኝቷል።
****************************
(ኢ ፕ ድ)
በምዕራብ ወለጋ ሰላማዊ ዜጎች ጭካኔ በተሞላበት መንገድ በአንድ ስፍራ ህይወታቸው እንዲያልፍ ባደረገው የኦነግ ሸኔ ቡድን ላይ እርምጃ እንደሚወስድ የኦሮሚያ ክልል መንግስት አስታወቀ።
የክልሉ መንግስት ባወጣው መግለጫ፥ መንግስት የህዝቡን ፍላጎትና ጥያቄ በማገናዘብ የልማት ስራዎችን፣ የሰላም እና የስርዓት ግንባታ ላይ እየሰራ ባለበት በአሁኑ ወቅት፤ ከለውጡ በተቃራኒ የቆሙ ሀይሎች በህዝቡ ላይ አሰቃቂ አደጋ እያደረሱ መሆኑን አስታውቋል።
የጥፋት ሀይሎቹ መንግስት የፖለቲካ እና የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት እየሰራ ባለበት ወቅት በተቃራኒው በመቆም ጭቃኔ የተሞላበት ተግባር በህዝቡ ላይ እየፈፀሙ ነው ብሏል።
የኦነግ ሸኔ ሽፍታ ከህውሃት ጋር በመሻረክ በኦሮሚያ ክልል እና በሀገሪቱ ሰላም እና መረጋጋት እንዳይኖር ሲሰሩ መቆየታቸውን ያስታወሰው መግለጫው፤ በተለያዩ ወቅቶች የግጭት አጀንዳዎችን በማዘጋጀት በሚዲያ በማሰራጨት እንዲሁም በህገ ወጥ መንገድ በገቡ የጦር መሳሪያዎች በፀጥታ ሀይሎች፣ በመንግስት መዋቅር እና በተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ የግድያ እርምጃ በመውሰድ ችግሮችን ሲፈጥሩ ቆይተዋል ብሏል መግለጫው።
ጭካኔ በተሞላበት መንገድ በተፈፀሙ በእነዚህ ተግባራትም በህብረተሰቡ ላይ የስነ ልቦና ጫና እንዲፈጠር፣ በስጋት እንዲሞላ እና ከዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ራሱን ቆጥቡ በረሃብ እና በጥማት እንዲጎዳ እያደረጉ ነውም ብሏል።
በተለይም በምዕራብ ኦሮሚያ አቅጣጫ በሚገኙ ዞኖች ህፃናት፣ ሴቶች፣ አዛውንቶች እና ወጣቶችን ጨምሮ ጭካኔ በተሞላበት መንገድ እንዲገደሉ፣ በእሳት እንዲቃጠሉ፣ የአካል ጉዳት እንዲደርስባቸው እንዲሁም የስነ ልቦና ጉዳት እንዲደርስባቸው ማድረጉ ይታወቃልም ብሏል፡፡
ከሁሉም በላይ በጫካ ውስጥ መሽጎ ከቦታ ቦታ የሚዘዋወረው ኦነግ ሸኔ ሰዎችን ጠልፎ በመውሰድ ጉዳት ሲያደርስ መቆየቱ ያወሳው መግለጫው፤ በተለያዩ ጊዜያትም የፀጥታ እና የአስተዳደር አካላት በተመሳሳይ መንገድ ጫካ ውስጥ በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወታቸው እንዲያልፍ ሲያደርግ ቆይቷልም ነው ያለው።
የኦነግ ሸኔ ሽፍታ እስካሁን በፈፀማቸው የሽብር ተግባራት በርካታ ቤተሰቦች ተበትነዋል፣ ህፃናትን ያለ አባትና እናት አስቀርቷል ያለው መግለጫው፥ የህዝቡና የግለሰቦች ሀብትም እንዲጠፋ ማድረጉን አስታውሷል።
የኦሮሚያ ክልል መንግስት የህዝቡን ሰላም ለማረጋገጥ ያለውን ተልዕኮ እና ሀላፊነት ለመወጣት ህዝቡን ባሳተፈ መልኩ የህግ የበላይነትን የማስከበር ስራ በስፋት እያከናወነ መሆኑንም ጠቅሷል፡፡
የህወሓት ተላላኪ የሆነው ይህ የኦነግ ሸኔ ቡድን ህዝቡ እና መንግስት በጋራ በመሆን የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ እየወሰዱት ባለው እርምጃ ለመጥፋት መቃረቡንም መግለጫው አመላክቷል።
እየተወሰደ ባለው እርምጃ የመቃብር አፋፍ ላይ የደረሰው ይህ ቡድን ተስፋ በመቁረጡ በአንድ ስፍራ በሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ ጥቃት እያደረሰ መሆኑም ተገልጿል።
በትናትናው እለትም በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ ጋዋ ቀናቲ ቀበሌ ጨለማን ተገን በማድረግ በፈፀመው የሽብር ጥቃት ሰላማዊ ዜጎችን ጭካኔ በተሞላበት መንገድ በአንድ ስፍራ ህይወታቸው እንዲያልፍ ማድረጉንም ነው የገለጸው።
የኦሮሚያ ክልል መንግስት ከህዝቡ እንዲሁም የፀጥታ እና አስተዳደር አካላት ጋር በመሆን እነዚህ ሽፍታዎች የገቡበት ቦታ በመግባት አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስድም ገልጿል።
በተፈፀመው ጥቃት ለተሰው ወገኖች የተሰማውን ሀዘን የገለፀው የክልሉ መንግስት ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን ተመኝቷል።
በቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የፌደራል ፖሊስ ገለጸ
************************************
(ኢ.ፕ.ድ)
በአዲስ አበባ ከተማ ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማና በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ፣ በቴሌኮም ማጭበርበር የተጠረጠሩ በርካታ ግለሰቦች ከነመሳሪያዎቻቸው በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ አስታወቀ፡፡
ተጠርጣሪዎቹ ህጋዊ ፈቃድ ሳይኖራቸው የቴሌኮም መሳሪያዎችን ወደ ሀገር በማስገባትና ከውጭ ሀገር ወደ ኢትዮጵያ የሚደረጉ የስልክ ጥሪዎች ኢትዮ ቴሌኮም በዘረጋው ኔትወርክ ሳይሆን ራሳቸው በዘረጉት መስመሮች ለደንበኞች ሲያቀርቡ መቆየታቸውን በፋይናንስ ተቋማት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ምርመራ ዲቪዥን ኃላፊ ኢንስፔክተር ሳሙኤል ሰለሞን ገልፀዋል።
ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ መሰረት የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት፣ ከኢንሳ፣ ከኢትዮ ቴሌኮም፣ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንና ከሌሎች ባለ ድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ባደረገው ክትትል ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ኢንስፔክተር ሳሙኤል ተናግረዋል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ ለዚህ ህገ-ወጥ ተግባር ሲጠቀሙባቸው የነበሩ 6 ጌትወይ፣ ከ570 በላይ ሲም ካርዶች፣ ቲፕሊንኮችና ሌሎች ህገ-ወጥ የቴሌኮሙኒኬሽን መሳሪያዎች መያዛቸውም ተገልጿል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ በሁለቱ ክፍለ ከተሞች ከቴሌኮም እውቅና ውጭ ማሽኖቹን በመጠቀምና የራሳቸውን ኔትወርክ በመፍጠር የውጭ ሀገር ጥሪዎችን በማስተላለፍ በቴሌኮም ላይ ኪሳራ ሲያደርሱ መቆየታቸንውን ኢንስፔክተር ሳሙኤል ሰለሞን በመግለፅ ህብረተሰቡ ለፖሊስ ባደረሰው ጥቆማ መሰረት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ጠቁመዋል፡፡
የወንጀል ምርመራ ቢሮው ከፍርድ ቤት የብርበራ ትዕዛዝ በማውጣት ማሽኖቹን ከነ አክሰሰሪዎቹ በመያዝ በኢትዮ ቴሌኮም መሰረተ ልማት ላይ ተጠርጣሪዎቹ ያደረሱትን ኪሳራ ለማጣራት መሳሪያዎቹን ለብሔራዊ መረጃና ደህንነት ልኮ የምርመራ ውጤቱን እየተጠባበቀ ይገኛልም ብለዋል፡፡
ህብረተሰቡ ቤቱን ከማከራየቱ በፊት ስለ ተከራዮች ማንነት በቂ መረጃ በመያዝ በትክክል ማጣራት እንዳለበትና እንደዚህ አይነት ህግ-ወጥ ተግባራት ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችን ሲመለከት በአካባቢው ለሚገኙ የፀጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠት የተለመደ ትብብሩን እንዲያደርግም ኢንስፔክተር ሳሙኤል ሰለሞን ጥሪ አቅርበዋል፡፡
************************************
(ኢ.ፕ.ድ)
በአዲስ አበባ ከተማ ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማና በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ፣ በቴሌኮም ማጭበርበር የተጠረጠሩ በርካታ ግለሰቦች ከነመሳሪያዎቻቸው በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ አስታወቀ፡፡
ተጠርጣሪዎቹ ህጋዊ ፈቃድ ሳይኖራቸው የቴሌኮም መሳሪያዎችን ወደ ሀገር በማስገባትና ከውጭ ሀገር ወደ ኢትዮጵያ የሚደረጉ የስልክ ጥሪዎች ኢትዮ ቴሌኮም በዘረጋው ኔትወርክ ሳይሆን ራሳቸው በዘረጉት መስመሮች ለደንበኞች ሲያቀርቡ መቆየታቸውን በፋይናንስ ተቋማት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ምርመራ ዲቪዥን ኃላፊ ኢንስፔክተር ሳሙኤል ሰለሞን ገልፀዋል።
ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ መሰረት የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት፣ ከኢንሳ፣ ከኢትዮ ቴሌኮም፣ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንና ከሌሎች ባለ ድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ባደረገው ክትትል ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ኢንስፔክተር ሳሙኤል ተናግረዋል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ ለዚህ ህገ-ወጥ ተግባር ሲጠቀሙባቸው የነበሩ 6 ጌትወይ፣ ከ570 በላይ ሲም ካርዶች፣ ቲፕሊንኮችና ሌሎች ህገ-ወጥ የቴሌኮሙኒኬሽን መሳሪያዎች መያዛቸውም ተገልጿል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ በሁለቱ ክፍለ ከተሞች ከቴሌኮም እውቅና ውጭ ማሽኖቹን በመጠቀምና የራሳቸውን ኔትወርክ በመፍጠር የውጭ ሀገር ጥሪዎችን በማስተላለፍ በቴሌኮም ላይ ኪሳራ ሲያደርሱ መቆየታቸንውን ኢንስፔክተር ሳሙኤል ሰለሞን በመግለፅ ህብረተሰቡ ለፖሊስ ባደረሰው ጥቆማ መሰረት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ጠቁመዋል፡፡
የወንጀል ምርመራ ቢሮው ከፍርድ ቤት የብርበራ ትዕዛዝ በማውጣት ማሽኖቹን ከነ አክሰሰሪዎቹ በመያዝ በኢትዮ ቴሌኮም መሰረተ ልማት ላይ ተጠርጣሪዎቹ ያደረሱትን ኪሳራ ለማጣራት መሳሪያዎቹን ለብሔራዊ መረጃና ደህንነት ልኮ የምርመራ ውጤቱን እየተጠባበቀ ይገኛልም ብለዋል፡፡
ህብረተሰቡ ቤቱን ከማከራየቱ በፊት ስለ ተከራዮች ማንነት በቂ መረጃ በመያዝ በትክክል ማጣራት እንዳለበትና እንደዚህ አይነት ህግ-ወጥ ተግባራት ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችን ሲመለከት በአካባቢው ለሚገኙ የፀጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠት የተለመደ ትብብሩን እንዲያደርግም ኢንስፔክተር ሳሙኤል ሰለሞን ጥሪ አቅርበዋል፡፡
"በኢትዮጵያውያን ላይ እየተፈጸመ ባለው ማንነትን መሠረት ባደረገው ጥቃት እጅግ ማዘኔን እገልጣለሁ"
- ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር)
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ጠላቶች፤ "ወይ እኛ እንገዛለን፤ ወይ ሀገር አትኖርም" ብለው ተነሥተዋል። ለዚህም የጥፋት ዐቅማቸውን ሁሉ እየተጠቀሙ ነው። አንደኛው ዒላማቸውም የሕዝባችንን ቅስም መስበር ነው።
ለዚህ እየተጠቀሙበት ያለው ስልት ግራ ቀኝ የሜያውቁ ሰዎችን እየሰበሰቡ በማሠልጠንና በማስታጠቅ በየአካባቢው ማንነትን መሠረት ያደረገ አረመኔያዊ ጥቃት ማድረስ ነው። ይህ ተግባር ሕዝቡ እንዲደናገጥ፣ እንዲፈራና በስሜት ያልተገባ ርምጃ እንዲወስድ የታለመ ነው።
መንግሥት በተለያዩ ቦታዎች ሊፈጠሩ ይችላሉ ያላቸውን ጥፋቶች በቅድሚያ መረጃ ሰብስቦ ርምጃ በመውሰድ ሲያከሽፍ ቆይቷል። ነገር ግን ያለፈው ሥርዓት ያወረሰንን ቀዳዳዎች ሁሉ በጥቂት ጊዜ ውስጥ ደፍኖ መጨረስ አልተቻለም።
የጥፋት ኃይሎች ከውጭ ላኪዎቻቸውና በመንግሥት መዋቅር ውስጥ በሚገኙ ባልጠሩ አድር ባዮች ትብብር በሕዝባችን ላይ አሳዛኝ ጥቃት እያደረሱ ነው። ሁኔታው እንደ መሪም እንደ ዜጋም ልብ ይሰብራል።
ይህ ግን ከመንገዳችን ወደኋላ፣ ከግባችን ወደ ሌላ አያደርገንም። ተስፋ ቆርጠን እንድናቆም፣ ተሸንፈን እንድናፈገፍግ አያደርገንም። ከምንጊዜውም በላይ ኃይላችንን አሰባስበን እንድንነሣ ያደርገናል እንጂ።
መንግሥት ሁሉንም ዓይነት አማራጮች ተጠቅሞ የችግሩን ሰንኮፍ ይነቅለዋል። የጸጥታ አካላት ጥቃቱ ወደተፈጸመበት አካባቢ ተሠማርተዋል። ርምጃም እየወሰዱ ነው። በቀጣይም የሕዝባችንን ደኅንነት ለማስጠበቅ መንግሥት የመንግሥትነቱን ሥራ በቁርጥና በጽናት ይሠራል።
ሕዝቡ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጸጥታ አካላት።፣ ምሁራንና ሌሎችም፧ መንግሥት ችግሩን ከምንጩ ለማድረቅ የሚወስደውን ርምጃ በመደገፍ የሚጠበቅባቸውን እንዲያደርጉ ጥሪ አቀርባለሁ።
- ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር)
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ጠላቶች፤ "ወይ እኛ እንገዛለን፤ ወይ ሀገር አትኖርም" ብለው ተነሥተዋል። ለዚህም የጥፋት ዐቅማቸውን ሁሉ እየተጠቀሙ ነው። አንደኛው ዒላማቸውም የሕዝባችንን ቅስም መስበር ነው።
ለዚህ እየተጠቀሙበት ያለው ስልት ግራ ቀኝ የሜያውቁ ሰዎችን እየሰበሰቡ በማሠልጠንና በማስታጠቅ በየአካባቢው ማንነትን መሠረት ያደረገ አረመኔያዊ ጥቃት ማድረስ ነው። ይህ ተግባር ሕዝቡ እንዲደናገጥ፣ እንዲፈራና በስሜት ያልተገባ ርምጃ እንዲወስድ የታለመ ነው።
መንግሥት በተለያዩ ቦታዎች ሊፈጠሩ ይችላሉ ያላቸውን ጥፋቶች በቅድሚያ መረጃ ሰብስቦ ርምጃ በመውሰድ ሲያከሽፍ ቆይቷል። ነገር ግን ያለፈው ሥርዓት ያወረሰንን ቀዳዳዎች ሁሉ በጥቂት ጊዜ ውስጥ ደፍኖ መጨረስ አልተቻለም።
የጥፋት ኃይሎች ከውጭ ላኪዎቻቸውና በመንግሥት መዋቅር ውስጥ በሚገኙ ባልጠሩ አድር ባዮች ትብብር በሕዝባችን ላይ አሳዛኝ ጥቃት እያደረሱ ነው። ሁኔታው እንደ መሪም እንደ ዜጋም ልብ ይሰብራል።
ይህ ግን ከመንገዳችን ወደኋላ፣ ከግባችን ወደ ሌላ አያደርገንም። ተስፋ ቆርጠን እንድናቆም፣ ተሸንፈን እንድናፈገፍግ አያደርገንም። ከምንጊዜውም በላይ ኃይላችንን አሰባስበን እንድንነሣ ያደርገናል እንጂ።
መንግሥት ሁሉንም ዓይነት አማራጮች ተጠቅሞ የችግሩን ሰንኮፍ ይነቅለዋል። የጸጥታ አካላት ጥቃቱ ወደተፈጸመበት አካባቢ ተሠማርተዋል። ርምጃም እየወሰዱ ነው። በቀጣይም የሕዝባችንን ደኅንነት ለማስጠበቅ መንግሥት የመንግሥትነቱን ሥራ በቁርጥና በጽናት ይሠራል።
ሕዝቡ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጸጥታ አካላት።፣ ምሁራንና ሌሎችም፧ መንግሥት ችግሩን ከምንጩ ለማድረቅ የሚወስደውን ርምጃ በመደገፍ የሚጠበቅባቸውን እንዲያደርጉ ጥሪ አቀርባለሁ።
የኢፌዲሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ በንፁኃን ዜጎች ላይ የተፈፀመውን አሰቃቂ ጭፍጨፋ በማስመልከት መልዕክት አስተላልፈዋል።
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
የተከበራችሁ የሃገራችን ህዝቦች!
በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ በንፁኃን ዜጎች ላይ የተፈፀመው አሰቃቂ ጭፍጨፋ የተሰማኝን ሃዘን እየገለፅኩ፤ ለሟች ቤተሰቦች መፅናናትን እመኛለሁ፡፡
በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ቀደም ሲል ብሄርን፣ ሃይማኖትን እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት የማድረስ ዓላማ ያላቸው ጥቃቶችና ጭፍጨፋዎች ተካሂደዋል፡፡ በተመሳሳይ በምዕራብ ወለጋ ዞን በንፁኃን ዜጎች ላይ አሰቃቂ ጭፍጨፋ ተፈፅሟል፡፡
በተለይ የአማራን ማህበረሰብ ትኩረት ያደረገና በንፁኃን ዜጎች ላይ የሚካሄደው ጭፍጨፋ ፍፁም አረመኔያዊና በፍጥነት መቆም ያለበት እኩይ ድርጊት ነው፡፡ ድርጊቱ አስቀድሞ መዋቅራዊ በሆነ መልኩ ሲዘራ የቆየ በመሆኑ፤ ችግሩን የሚመጥን መፍትሄ በዘላቂነት ለማበጀት አስፈላጊው ሁሉ ይደረጋል፡፡
ከዚህ አኳያ የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ እንዲሁም ከሁሉም አቅጣጫ የሚቃጡ ጥቃቶችን ለመመከት የመንግስትና ህዝብ ቅንጅታዊ ርብርብ ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
የተከበራችሁ የሃገራችን ህዝቦች!
በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ በንፁኃን ዜጎች ላይ የተፈፀመው አሰቃቂ ጭፍጨፋ የተሰማኝን ሃዘን እየገለፅኩ፤ ለሟች ቤተሰቦች መፅናናትን እመኛለሁ፡፡
በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ቀደም ሲል ብሄርን፣ ሃይማኖትን እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት የማድረስ ዓላማ ያላቸው ጥቃቶችና ጭፍጨፋዎች ተካሂደዋል፡፡ በተመሳሳይ በምዕራብ ወለጋ ዞን በንፁኃን ዜጎች ላይ አሰቃቂ ጭፍጨፋ ተፈፅሟል፡፡
በተለይ የአማራን ማህበረሰብ ትኩረት ያደረገና በንፁኃን ዜጎች ላይ የሚካሄደው ጭፍጨፋ ፍፁም አረመኔያዊና በፍጥነት መቆም ያለበት እኩይ ድርጊት ነው፡፡ ድርጊቱ አስቀድሞ መዋቅራዊ በሆነ መልኩ ሲዘራ የቆየ በመሆኑ፤ ችግሩን የሚመጥን መፍትሄ በዘላቂነት ለማበጀት አስፈላጊው ሁሉ ይደረጋል፡፡
ከዚህ አኳያ የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ እንዲሁም ከሁሉም አቅጣጫ የሚቃጡ ጥቃቶችን ለመመከት የመንግስትና ህዝብ ቅንጅታዊ ርብርብ ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
የምክር ቤቱ አባላት በምዕራብ ወለጋ ዞን ከተፈጸመው ግድያ ጀርባ አሉ የተባሉት እንደ ህወሓት ያሉ ድርጅቶች በአሸባሪነት ሊፈረጁ ይገባል ሲሉ ጠየቁ
👉 ጉዳዩን በተመለከተ የሚመለከተው የመንግስት አካል ማብራሪያ እንዲሰጥበት እንደሚደረግ አፈጉበኤው አስታውቀዋል
******************
(ኢ ፕ ድ)
የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት በምዕራብ ወለጋ ዞን በንጹሀን ዜጎች ላይ ማንነትን መሰረት አድርጎ በተፈጸመው ግድያ ላይ እጃቸው አለበት የተባሉት እንደ ህወሓት እና ሸኔ ያሉ ድርጅቶች በአሸባሪነት ሊፈረጁ ይገባል ሲሉ ጠየቁ።
ዛሬ ለመደበኛ ስብሰባ የተጠራው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከመደበኛ አጀንዳዎች አስቀድሞ በንጹሀን ዜጎች ግድያ ላይ መወያያት አለብን በሚል በጥቃቱ ዙሪያ ሰፊ ውይይት አድርጓል።
በዚሁ ውይይት ላይ የምክር ቤቱ አባላት እንደተናገሩት፤ በምዕራብ ወለጋ ዞን በንጹሀን ዜጎች ላይ ማንነትን መሰረት አድርጎ በተፈጸመው ግድያ ላይ እጃቸው አለበት የተባሉት እንደ ህወሓት እና ኦነግ ሸኔ ያሉ ድርጅቶች በአሸባሪነት ሊፈረጁ ይገባል ብለዋል።
የትናንት በስቲያውን ጨምሮ ባለፉት ሁለት አመታት ማንነት ላይ የተመሰረቱ ግድያዎችን የፈጸሙ፣ የመለመሉ ድጋፍ ያደረጉ እንደ ህወሓት ያሉ አካላትን በተመለከተ መረጃና ማስረጃ አደራጅቶ በሽብርተኝነት ሊፈረጁ ይገባል ያሉት አባላቱ፤ የሚመለከተው የመንግስት አካል ይሄንን መረጃ አደራጅቶ ለምክር ቤቱ እንዲያቀርብም ነው የጠየቁት።
አባላቱ በዚሁ ውይይታቸውም በግድያው ዙሪያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የሰላም ሚኒስቴር እና የመከላከያ የስራ ሃላፊዎች በጉዳዩ ላይ ምክር ቤት ቀርበው ማብራሪያ ሊሰጡ ይገባል ሲሉ አንስተዋል።
አፈጉበኤው በምላሻቸው የምክር ቤቱ አባላት በግድያው ዙሪያ ስሜታቸውን በዚህ አግባብ መግለጻቸው ትክክል መሆኑን በመጥቀስ፤ ጉዳዩን በተመለከተ የሚመለከተው የመንግስት አካል ማብራሪያ እንዲሰጥበት እንደሚደረግ አስታውቀዋል።
በጌትነት ተስፋማርያም
👉 ጉዳዩን በተመለከተ የሚመለከተው የመንግስት አካል ማብራሪያ እንዲሰጥበት እንደሚደረግ አፈጉበኤው አስታውቀዋል
******************
(ኢ ፕ ድ)
የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት በምዕራብ ወለጋ ዞን በንጹሀን ዜጎች ላይ ማንነትን መሰረት አድርጎ በተፈጸመው ግድያ ላይ እጃቸው አለበት የተባሉት እንደ ህወሓት እና ሸኔ ያሉ ድርጅቶች በአሸባሪነት ሊፈረጁ ይገባል ሲሉ ጠየቁ።
ዛሬ ለመደበኛ ስብሰባ የተጠራው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከመደበኛ አጀንዳዎች አስቀድሞ በንጹሀን ዜጎች ግድያ ላይ መወያያት አለብን በሚል በጥቃቱ ዙሪያ ሰፊ ውይይት አድርጓል።
በዚሁ ውይይት ላይ የምክር ቤቱ አባላት እንደተናገሩት፤ በምዕራብ ወለጋ ዞን በንጹሀን ዜጎች ላይ ማንነትን መሰረት አድርጎ በተፈጸመው ግድያ ላይ እጃቸው አለበት የተባሉት እንደ ህወሓት እና ኦነግ ሸኔ ያሉ ድርጅቶች በአሸባሪነት ሊፈረጁ ይገባል ብለዋል።
የትናንት በስቲያውን ጨምሮ ባለፉት ሁለት አመታት ማንነት ላይ የተመሰረቱ ግድያዎችን የፈጸሙ፣ የመለመሉ ድጋፍ ያደረጉ እንደ ህወሓት ያሉ አካላትን በተመለከተ መረጃና ማስረጃ አደራጅቶ በሽብርተኝነት ሊፈረጁ ይገባል ያሉት አባላቱ፤ የሚመለከተው የመንግስት አካል ይሄንን መረጃ አደራጅቶ ለምክር ቤቱ እንዲያቀርብም ነው የጠየቁት።
አባላቱ በዚሁ ውይይታቸውም በግድያው ዙሪያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የሰላም ሚኒስቴር እና የመከላከያ የስራ ሃላፊዎች በጉዳዩ ላይ ምክር ቤት ቀርበው ማብራሪያ ሊሰጡ ይገባል ሲሉ አንስተዋል።
አፈጉበኤው በምላሻቸው የምክር ቤቱ አባላት በግድያው ዙሪያ ስሜታቸውን በዚህ አግባብ መግለጻቸው ትክክል መሆኑን በመጥቀስ፤ ጉዳዩን በተመለከተ የሚመለከተው የመንግስት አካል ማብራሪያ እንዲሰጥበት እንደሚደረግ አስታውቀዋል።
በጌትነት ተስፋማርያም
“ለሀገርና ለህዝብ ጥቅም ሲባል ልናሰምረው እና ልናከብረው የሚገባን ቀይ መስመር ተጥሷል”
- የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለ-ወርቅ ዘውዴ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለ-ወርቅ ዘውዴ በምዕራብ ወለጋ ዞን በንጹሀን ዜጎች ላይ የተፈጸመውን ግድያ በማስመልከት ያስተላለፉት መልዕክት።
የሰማሁት አሰቃቂ ግድያ ልቤን በእጅጉ ሰብሮታል:: ንጹሀን ዜጎች በሌሎች እብደት ውድ ሕይወታቸውን የሚከፍሉበት ንብረታቸው የሚወድምበት መሄጃ አጥተው የሚንከራተቱበት ምንም ምክንያት የለም:: የዛሬ ዓመት በ 30/10/2019 የጻፍኩትን ትዊት ልድገመው::
ዘርና ሀይማኖት ለፖለቲካ ጥቅም እንዲውሉ ሲደረግ፤ ንጹሀን ዜጎቻችን በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደሉ፣ ሲፈናቀሉና ሲንከራተቱ ስናይ ስሜትን ለመግለጽ ቃላት ያጥራል: ለቅሶ፣ድንጋጤና ሥጋት የብዙዎችን በር አንኳኩቷል ሃዘናቸው ሃዘኔ/ሃዘናችን ነው::
ለሀገርና ለህዝብ ጥቅም ሲባል ልናሰምረው እና ልናከብረው የሚገባን ቀይ መስመር ተጥሷል፡ አገራችንን ካንዣበበባት ክፉ አዳጋ ለማዳን ሁላችንም ሚና አለን፡የሚመለከታቸው ሁሉ የበኩላቸውን መወጣት አለባቸው፡ቀይ መስመር መጣስ የለበትም እንበል::
የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ
- የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለ-ወርቅ ዘውዴ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለ-ወርቅ ዘውዴ በምዕራብ ወለጋ ዞን በንጹሀን ዜጎች ላይ የተፈጸመውን ግድያ በማስመልከት ያስተላለፉት መልዕክት።
የሰማሁት አሰቃቂ ግድያ ልቤን በእጅጉ ሰብሮታል:: ንጹሀን ዜጎች በሌሎች እብደት ውድ ሕይወታቸውን የሚከፍሉበት ንብረታቸው የሚወድምበት መሄጃ አጥተው የሚንከራተቱበት ምንም ምክንያት የለም:: የዛሬ ዓመት በ 30/10/2019 የጻፍኩትን ትዊት ልድገመው::
ዘርና ሀይማኖት ለፖለቲካ ጥቅም እንዲውሉ ሲደረግ፤ ንጹሀን ዜጎቻችን በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደሉ፣ ሲፈናቀሉና ሲንከራተቱ ስናይ ስሜትን ለመግለጽ ቃላት ያጥራል: ለቅሶ፣ድንጋጤና ሥጋት የብዙዎችን በር አንኳኩቷል ሃዘናቸው ሃዘኔ/ሃዘናችን ነው::
ለሀገርና ለህዝብ ጥቅም ሲባል ልናሰምረው እና ልናከብረው የሚገባን ቀይ መስመር ተጥሷል፡ አገራችንን ካንዣበበባት ክፉ አዳጋ ለማዳን ሁላችንም ሚና አለን፡የሚመለከታቸው ሁሉ የበኩላቸውን መወጣት አለባቸው፡ቀይ መስመር መጣስ የለበትም እንበል::
የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ
ሕወሓት በትግራይ በሚገኘው የመከላከያ ካምፕ ላይ ጥቃት ማድረሱና በዳልሻሕ በኩልም ጦርነት መክፈቱ ተገለጸ
********************
(ኢ ፕ ድ)
ሕወሓት በትግራይ በሚገኘው የመከላከያ ካምፕ ላይ ጥቃት ማድረሱ እና በዳልሻሕ በኩልም ጦርነት መክፈቱ ተገለጸ።
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ እንዳስታወቁት ህወሓት የሰሜን ዕዝንም ለመዝረፍ ሙከራ አድርጓል።
እንድ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጻ፤ ይህ ሠራዊት ከሃያ ዓመታት በላይ የትግራይን ሕዝብ ሲጠብቅ የቆየ ሠራዊት ነው። በቦታው የሚገኘውም የትግራይን ሕዝብ ከጥቃት ለመከላከል ነው። ሕወሐት ግን እንደ ባዕድና እንደ ወራሪ ሀገር ሠራዊት ቆጥሮ፤ የመከላከያ ሠራዊቱን ለመምታትና ለመዝረፍ ተነሥቷል።
ህወሓት በዳልሻሕ በኩልም ጦርነት ከፍቷል።
መንግሥት የትግራይ ሕዝብ እንዳይጎዳ በማሰብ፣ ጦርነት እንዳይፈጠር የትእግሥቱ ጫፍ ድረስ ታግሷል ያሉት ዶ/ር አብይ፤ ጦርነት የሚቀረው ግን በአንድ ወገን ፍላጎት ብቻ አይደለም ነው ያለት።
"የመከላከያ ሠራዊታችን በኮማንድ ፖስት እየተመራ ሀገሩን የማዳን ተልዕኮውን እንዲወጣ ትእዛዝ ተሰጥቶታል። ቀዩ መሥመር የመጨረሻው ነጥብ ታልፏል። ሀገርና ሕዝብ ለማዳን ሲባል ኃይል የመጨረሻው አማራጭ ሆኗል" ብለዋል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ ነገሮችን በሰከነ መንፈስ እንዲከታተል፣ በየአካባቢው ሊከሠቱ የሚችሉ ትንኮሳዎች በንቃት እንዲቃኝና ከመከላከያ ሠራዊታችን ጎን እንዲቆም ጥሪ አቀርባለሁ ብለዋል።
********************
(ኢ ፕ ድ)
ሕወሓት በትግራይ በሚገኘው የመከላከያ ካምፕ ላይ ጥቃት ማድረሱ እና በዳልሻሕ በኩልም ጦርነት መክፈቱ ተገለጸ።
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ እንዳስታወቁት ህወሓት የሰሜን ዕዝንም ለመዝረፍ ሙከራ አድርጓል።
እንድ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጻ፤ ይህ ሠራዊት ከሃያ ዓመታት በላይ የትግራይን ሕዝብ ሲጠብቅ የቆየ ሠራዊት ነው። በቦታው የሚገኘውም የትግራይን ሕዝብ ከጥቃት ለመከላከል ነው። ሕወሐት ግን እንደ ባዕድና እንደ ወራሪ ሀገር ሠራዊት ቆጥሮ፤ የመከላከያ ሠራዊቱን ለመምታትና ለመዝረፍ ተነሥቷል።
ህወሓት በዳልሻሕ በኩልም ጦርነት ከፍቷል።
መንግሥት የትግራይ ሕዝብ እንዳይጎዳ በማሰብ፣ ጦርነት እንዳይፈጠር የትእግሥቱ ጫፍ ድረስ ታግሷል ያሉት ዶ/ር አብይ፤ ጦርነት የሚቀረው ግን በአንድ ወገን ፍላጎት ብቻ አይደለም ነው ያለት።
"የመከላከያ ሠራዊታችን በኮማንድ ፖስት እየተመራ ሀገሩን የማዳን ተልዕኮውን እንዲወጣ ትእዛዝ ተሰጥቶታል። ቀዩ መሥመር የመጨረሻው ነጥብ ታልፏል። ሀገርና ሕዝብ ለማዳን ሲባል ኃይል የመጨረሻው አማራጭ ሆኗል" ብለዋል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ ነገሮችን በሰከነ መንፈስ እንዲከታተል፣ በየአካባቢው ሊከሠቱ የሚችሉ ትንኮሳዎች በንቃት እንዲቃኝና ከመከላከያ ሠራዊታችን ጎን እንዲቆም ጥሪ አቀርባለሁ ብለዋል።
በአዲስ አበባ በተለምዶ አዋሬ ገበያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የተነሳው የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጸ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
ከሌሊቱ 10 ሰአት አካባቢ የተነሳው የእሳት አደጋ በአዲስ አበባ ከተማ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የእሳት አደጋ መከላከል ባለሙያዎች ፣ፖሊሶች እና የአካባቢው ወጣቶች በቁጥጥር ስር መዋሉን የየካ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አስፋው ተክሌ ተናግረዋል፡፡
የእሳት አደጋውን መንስኤ እና ያደረሰውን ጉዳት በፖሊስ እየተጣራ መሆንን ዋና ስራ አስፈጻሚው ገልጸዋል፡፡
ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ከየካ ክፍለ ከተማ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በቦታው ተገኝተው የጉዳቱን መጠን በመመልከት ጉዳት የደረሰባቸውን ነዋሪዎች በማጽናናት ላይ ናቸው።
በእሳት አደጋው የደረሰውን ጉዳት በማጣራት በቀጣይ ሰዓታት የሚገለጽ ይሆናል ተብሏል፡፡
**********************
(ኢ ፕ ድ)
ከሌሊቱ 10 ሰአት አካባቢ የተነሳው የእሳት አደጋ በአዲስ አበባ ከተማ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የእሳት አደጋ መከላከል ባለሙያዎች ፣ፖሊሶች እና የአካባቢው ወጣቶች በቁጥጥር ስር መዋሉን የየካ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አስፋው ተክሌ ተናግረዋል፡፡
የእሳት አደጋውን መንስኤ እና ያደረሰውን ጉዳት በፖሊስ እየተጣራ መሆንን ዋና ስራ አስፈጻሚው ገልጸዋል፡፡
ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ከየካ ክፍለ ከተማ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በቦታው ተገኝተው የጉዳቱን መጠን በመመልከት ጉዳት የደረሰባቸውን ነዋሪዎች በማጽናናት ላይ ናቸው።
በእሳት አደጋው የደረሰውን ጉዳት በማጣራት በቀጣይ ሰዓታት የሚገለጽ ይሆናል ተብሏል፡፡
👉 በየጊዜው የሸረሪት ድር ስናፀዳ አንኖርም፤
👉 ትህነግ አልመዳ በሚባለው የጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ውስጥ የኤርትር
የመከላከያ ሰራዊት አልባሳትን በማምረት የኤርትራ ሰራዊት ወረረህ ለማለት
ዝግጅት ያደረገ ነው፤
👉 በአማራ ክልል በሶሮቃና ቅርቃር አካባቢ ትህነግ የጦርነት ሙከራ አድረጓል፤
ነገር ግን በአማራ ክልል ልዩ ኃይል ሙሉ በሙሉ ተመክቶ ተመልሷል፤
👉 ትህነግን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመደምሰስ ለሚደረገው ርምጀ ህዝቡ፣
ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ ከመንግስት ጎን ቆመው ሊያግዙና አካባቢያቸውን
ሊጠብቁ ይገባል፤
አቶ ተመሥገን ጥሩነህ
የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር
👉 ትህነግ አልመዳ በሚባለው የጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ውስጥ የኤርትር
የመከላከያ ሰራዊት አልባሳትን በማምረት የኤርትራ ሰራዊት ወረረህ ለማለት
ዝግጅት ያደረገ ነው፤
👉 በአማራ ክልል በሶሮቃና ቅርቃር አካባቢ ትህነግ የጦርነት ሙከራ አድረጓል፤
ነገር ግን በአማራ ክልል ልዩ ኃይል ሙሉ በሙሉ ተመክቶ ተመልሷል፤
👉 ትህነግን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመደምሰስ ለሚደረገው ርምጀ ህዝቡ፣
ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ ከመንግስት ጎን ቆመው ሊያግዙና አካባቢያቸውን
ሊጠብቁ ይገባል፤
አቶ ተመሥገን ጥሩነህ
የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር
ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር አቢይ አሕመድ በሰጡት መግለጫ ያነሷቸው ዋናዋና ነጥቦች
👉 ውድ የሀገሬ ህዝብ ሆይ! ዛሬ ከሃዲ ኢትዮጵያውያን ኢትዮጵያን
ወግተዋታል፤
👉 ኢትዮጵያ ያጎረሰ እጇ ያጠባ ጡቷ ተነክሷል፤
👉 ላለፉት 20 ዓመታት የቀበሮ ምሽግ ውስጥ በመሆን ሀገሬን ወገኔን
ህዝቤን ብሎ በብዙ ሺዎች መስዋዕትነት ከፍሎ ቆስሎ ደምቶ ሀገሩንና
ህዝቡን የታደገው የመከላከያ ሰራዊት ላይ ዛሬ ምሽት ከመቀሌ ጀምሮ
በበርካታ ስፍራዎች በካሃዲው ኃይሎች እና ባደራጁት ኃይል ጥቃት
ተፈፅሞበታል።
👉 ይህ ጥቃት በሀገራችን እስካሁን ከደረሱት ጥቃቶች እጅግ አሰፋሪ
የሚያደርገው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ሰላም ለማስከበር በተለያዩ
ሀገራት በተሰማራበት ሀገር በውጭ ኃይል እንኳ አጋጥሞት
በማያውቀው ሁኔታ በገዛ ወገኑ ከጀርባው ጥቃት ተፈፀሞበታል።
👉 በዳንሻ በኩል በአማራ ክልል ላይ የፈፀሙት ጥቃት በአማራ ክልል
በነበረው ኃይል ተመክቷል
👉 የትግራይ ሕዝብ ወገናችን ነው ለጥቂት እኩዮች ሲባል ምንም እንኳ
የእኩዮች መሸሸጊያ ዋሻ ቢሆንም ሕዝባችን ላይ ጥቃት አንሰነዝርም
ብሎ በትዕግስት በቆየው ሰራዊት ላይ ጥቃት ተፈፅሞበታል
👉 በመላ ሀገራችን ቀድመው ባሰለጠኑት ባሰማሩት ባዘጋጁት ኃይል
በተለያየ ቦታ በተለያየ ከተማ በንፁሃን ዜጎች ላይ ጥቃት ሊፈፅሙ
ስለሚችል መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ከሚሊሻው ከፖሊስ ሰራዊት
እንዲሁም በአካባቢያቸው ከሚገኝ የመከለከያ ሰራዊት ጋር
በመተባበር ቀያችሁን ሰፈራችሁን እንድትጠብቁ አሳስባለሁ
👉 የመከላከያ ሰራዊት ከጠቅላይ ሰፍር በሚሰጥ ትዕዛዝ መለዮውን
ሀገሩንና ህዝቡን እንዲከላከል ለሚከፍለው መስዋዕትነት ዛሬም
እንደተለመደው በታሪኩ ውስጥ የሚታሰብ መሆኑን እገልፃለሁ።
👉 ይህ እኩይ ኃይል መጥፊያው በመድረሱ በሰላም በንግግር
በውይይት ሊፈቱ የሚችሉ ነገሮችን ባለፉት ጥቂት ቀናት ካለምንም
ሀፍረት በሚዲያ በመውጣት ከየትኛውም የውጭ ኃይል ጋር
በመተባበር ኢትዮጵያን እወጋለሁ ብሎ ሲያውጅ የነበረው ኃይል
ይህን ለማመን የሚያስቸግር ንግግር በተግባር ማዋሉን በዚህ ምሽት
አረጋግጧል።
👉 የትግራይ ህዝብ ወገኔ ዘመዴ ሕዝቤ ብሎ ላለፉት 20 ዓመታት
በቀበሮ ምሽግ ውስጥ በመሆኑ በብዙሺዎች የሚቆጠር መስዋዕትነት
የከፈለውን አንተን ለመጠበቅ አስፈላጊውን ሁሉ ያደረገው
የመከላከያ ሰራዊት የደረሰበት ጥቃት ጥቃትህ መሆኑን በመገንዘብ
ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ጎን በመቆም ሀገርህን ከነዚህ ከሃዲ ኃይሎች
እንድትከላከልና በንቃት እንድትጠብቅ አሳስባለሁ።
👉 ይህ ጉዳይ ለኢትዮጵያ አሳዘኝ አሳፈሪም ተግባር ቢሆንም ዛሬም
እንደተለመደው በተደመረ በተባበረ ክንድ ይህንን ከሃዲ ጡት ነካሽ
ኃይል ለማሳፈርና ለመደምሰስ እስፈላጊውን ሁሉ የምናደርግ
መሆኑን እገልፃለሁ።
👉 ይህ አሳፋሪ ተግባር በማይደገምበት ሁኔታ የሚቀለበስበትን ተግባር
መላው የኢትዮጵያ ህዝብና የሀገር መከላከያ ሰራዊት በመተባበር
የሚፈፅሙት ይሆናል።
👉 ለመላው የሀገራችን ህዝቦች አስፈላጊውን መረጃ በየጊዜው
በሚመለከታቸው የመንግስት አከላት የሚሰጥ መሆኑን
እገልፃለሁ።
👉 ውድ የሀገሬ ህዝብ ሆይ! ዛሬ ከሃዲ ኢትዮጵያውያን ኢትዮጵያን
ወግተዋታል፤
👉 ኢትዮጵያ ያጎረሰ እጇ ያጠባ ጡቷ ተነክሷል፤
👉 ላለፉት 20 ዓመታት የቀበሮ ምሽግ ውስጥ በመሆን ሀገሬን ወገኔን
ህዝቤን ብሎ በብዙ ሺዎች መስዋዕትነት ከፍሎ ቆስሎ ደምቶ ሀገሩንና
ህዝቡን የታደገው የመከላከያ ሰራዊት ላይ ዛሬ ምሽት ከመቀሌ ጀምሮ
በበርካታ ስፍራዎች በካሃዲው ኃይሎች እና ባደራጁት ኃይል ጥቃት
ተፈፅሞበታል።
👉 ይህ ጥቃት በሀገራችን እስካሁን ከደረሱት ጥቃቶች እጅግ አሰፋሪ
የሚያደርገው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ሰላም ለማስከበር በተለያዩ
ሀገራት በተሰማራበት ሀገር በውጭ ኃይል እንኳ አጋጥሞት
በማያውቀው ሁኔታ በገዛ ወገኑ ከጀርባው ጥቃት ተፈፀሞበታል።
👉 በዳንሻ በኩል በአማራ ክልል ላይ የፈፀሙት ጥቃት በአማራ ክልል
በነበረው ኃይል ተመክቷል
👉 የትግራይ ሕዝብ ወገናችን ነው ለጥቂት እኩዮች ሲባል ምንም እንኳ
የእኩዮች መሸሸጊያ ዋሻ ቢሆንም ሕዝባችን ላይ ጥቃት አንሰነዝርም
ብሎ በትዕግስት በቆየው ሰራዊት ላይ ጥቃት ተፈፅሞበታል
👉 በመላ ሀገራችን ቀድመው ባሰለጠኑት ባሰማሩት ባዘጋጁት ኃይል
በተለያየ ቦታ በተለያየ ከተማ በንፁሃን ዜጎች ላይ ጥቃት ሊፈፅሙ
ስለሚችል መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ከሚሊሻው ከፖሊስ ሰራዊት
እንዲሁም በአካባቢያቸው ከሚገኝ የመከለከያ ሰራዊት ጋር
በመተባበር ቀያችሁን ሰፈራችሁን እንድትጠብቁ አሳስባለሁ
👉 የመከላከያ ሰራዊት ከጠቅላይ ሰፍር በሚሰጥ ትዕዛዝ መለዮውን
ሀገሩንና ህዝቡን እንዲከላከል ለሚከፍለው መስዋዕትነት ዛሬም
እንደተለመደው በታሪኩ ውስጥ የሚታሰብ መሆኑን እገልፃለሁ።
👉 ይህ እኩይ ኃይል መጥፊያው በመድረሱ በሰላም በንግግር
በውይይት ሊፈቱ የሚችሉ ነገሮችን ባለፉት ጥቂት ቀናት ካለምንም
ሀፍረት በሚዲያ በመውጣት ከየትኛውም የውጭ ኃይል ጋር
በመተባበር ኢትዮጵያን እወጋለሁ ብሎ ሲያውጅ የነበረው ኃይል
ይህን ለማመን የሚያስቸግር ንግግር በተግባር ማዋሉን በዚህ ምሽት
አረጋግጧል።
👉 የትግራይ ህዝብ ወገኔ ዘመዴ ሕዝቤ ብሎ ላለፉት 20 ዓመታት
በቀበሮ ምሽግ ውስጥ በመሆኑ በብዙሺዎች የሚቆጠር መስዋዕትነት
የከፈለውን አንተን ለመጠበቅ አስፈላጊውን ሁሉ ያደረገው
የመከላከያ ሰራዊት የደረሰበት ጥቃት ጥቃትህ መሆኑን በመገንዘብ
ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ጎን በመቆም ሀገርህን ከነዚህ ከሃዲ ኃይሎች
እንድትከላከልና በንቃት እንድትጠብቅ አሳስባለሁ።
👉 ይህ ጉዳይ ለኢትዮጵያ አሳዘኝ አሳፈሪም ተግባር ቢሆንም ዛሬም
እንደተለመደው በተደመረ በተባበረ ክንድ ይህንን ከሃዲ ጡት ነካሽ
ኃይል ለማሳፈርና ለመደምሰስ እስፈላጊውን ሁሉ የምናደርግ
መሆኑን እገልፃለሁ።
👉 ይህ አሳፋሪ ተግባር በማይደገምበት ሁኔታ የሚቀለበስበትን ተግባር
መላው የኢትዮጵያ ህዝብና የሀገር መከላከያ ሰራዊት በመተባበር
የሚፈፅሙት ይሆናል።
👉 ለመላው የሀገራችን ህዝቦች አስፈላጊውን መረጃ በየጊዜው
በሚመለከታቸው የመንግስት አከላት የሚሰጥ መሆኑን
እገልፃለሁ።
የኢፌድሪ ሚኒስትሮች ምክር ቤት በትግራይ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጀ
***********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢፌድሪ ሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ጥቅምት 25/2013 ባደረገው 21ኛ አስቸኳይ ልዩ ስብሰባ መንግሥት የሀገርን ሰላምና ሕልውና፣ የሕዝብንና የዜጎችን ደህንነት የማረጋገጥ እና ሀገሪቷን ወደ ሁከትና ብጥብጥ የሚወስዱ ማናቸውንም ድርጊቶችን የመከላከል ሕገ መንግሥታዊ ኃላፊነት ያለበት መሆኑን በመገንዘብ፤
እንዲሁም በትግራይ ብሔራዊ ክልል ውስጥ ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን እንዲሁም የሕዝብን ሰላምና ፀጥታ አደጋ ላይ የሚጥሉ በተለይም የሀገርን ሉዐላዊነት የሚገዳደሩ፣ የፌደራል መንግሥት በሕገ መንግሥቱ የተሰጠውን ሥልጣንና ኃላፊነት በክልሉ እንዳይወጣ እና ሀገሪቷን የጦር አውድማ የሚያደርጉ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔዎችን ጭምር በመጣስ በርካታ ሕገ ወጥ ተግባራት እየተፈፀሙ በመሆኑ፤
ይህን ሁኔታ በመደበኛው የሕግ ማስከበር ሥርዓት ለመከላከልና ለመቆጣጠር የማይቻልበት ደረጃ ላይ መደረሱን በመረዳት፤ በሕገ መንግሥቱ በተደነገገው መሠረት ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ለመጠበቅ ልዩ እርምጃዎችን መውሰድ የሚያስችል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በመደንገግ እና ተግባራዊ በማድረግ ሁኔታውን በመቆጣጠር በሀገሪቱ ሰላምና ሕልውና ላይ የተጋረጠውን አደጋ መከላከል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 93/1/ሀ መሰረት የሚከተለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታውጇል።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ለስድስት ወራት ተፈጻሚ የሚሆን ሲሆን፣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የሚያስፈፅም በኢፌድሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ሰብሳቢነት የሚመራና አግባብነት ካላቸው አካላት የተወጣጡ አባላት ያሉት ግብረኃይል በዚህ አዋጅ ተቋቁሟል።
ግብረኃይሉ ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲሆን ‘‘የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ግብረሀይል’’ ተብሎ ይጠራል።
አዋጁ በመላው የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መስተዳድር ተፈፃሚ የሚደረግ ሲሆን፣ እንደያስፈላጊነቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተፈፃሚ ወይም ቀሪ የሚሆንባቸውን ተጨማሪ አካባቢዎችን ግብረኃይሉ በሚያወጣው በመመሪያ ይወስናል።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አስመልክቶ ዝርዝር መርጃዎች በየጊዜው ለህብረተሰቡ የሚሰጡ ይሆናል።
***********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢፌድሪ ሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ጥቅምት 25/2013 ባደረገው 21ኛ አስቸኳይ ልዩ ስብሰባ መንግሥት የሀገርን ሰላምና ሕልውና፣ የሕዝብንና የዜጎችን ደህንነት የማረጋገጥ እና ሀገሪቷን ወደ ሁከትና ብጥብጥ የሚወስዱ ማናቸውንም ድርጊቶችን የመከላከል ሕገ መንግሥታዊ ኃላፊነት ያለበት መሆኑን በመገንዘብ፤
እንዲሁም በትግራይ ብሔራዊ ክልል ውስጥ ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን እንዲሁም የሕዝብን ሰላምና ፀጥታ አደጋ ላይ የሚጥሉ በተለይም የሀገርን ሉዐላዊነት የሚገዳደሩ፣ የፌደራል መንግሥት በሕገ መንግሥቱ የተሰጠውን ሥልጣንና ኃላፊነት በክልሉ እንዳይወጣ እና ሀገሪቷን የጦር አውድማ የሚያደርጉ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔዎችን ጭምር በመጣስ በርካታ ሕገ ወጥ ተግባራት እየተፈፀሙ በመሆኑ፤
ይህን ሁኔታ በመደበኛው የሕግ ማስከበር ሥርዓት ለመከላከልና ለመቆጣጠር የማይቻልበት ደረጃ ላይ መደረሱን በመረዳት፤ በሕገ መንግሥቱ በተደነገገው መሠረት ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ለመጠበቅ ልዩ እርምጃዎችን መውሰድ የሚያስችል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በመደንገግ እና ተግባራዊ በማድረግ ሁኔታውን በመቆጣጠር በሀገሪቱ ሰላምና ሕልውና ላይ የተጋረጠውን አደጋ መከላከል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 93/1/ሀ መሰረት የሚከተለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታውጇል።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ለስድስት ወራት ተፈጻሚ የሚሆን ሲሆን፣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የሚያስፈፅም በኢፌድሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ሰብሳቢነት የሚመራና አግባብነት ካላቸው አካላት የተወጣጡ አባላት ያሉት ግብረኃይል በዚህ አዋጅ ተቋቁሟል።
ግብረኃይሉ ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲሆን ‘‘የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ግብረሀይል’’ ተብሎ ይጠራል።
አዋጁ በመላው የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መስተዳድር ተፈፃሚ የሚደረግ ሲሆን፣ እንደያስፈላጊነቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተፈፃሚ ወይም ቀሪ የሚሆንባቸውን ተጨማሪ አካባቢዎችን ግብረኃይሉ በሚያወጣው በመመሪያ ይወስናል።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አስመልክቶ ዝርዝር መርጃዎች በየጊዜው ለህብረተሰቡ የሚሰጡ ይሆናል።
"መከላከያ ሠራዊት የሀገር አንድነት እና ሰላምን ለማስከበር የሚወስዳቸውን እርምጃዎች በመደገፍ የኢዜማ አባላት እና አመራር ከጎኑ እንደሚሰለፉ ፓርቲው አስታወቀ
************************************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ሕወሓት በትግራይ ክልል በሚገኘው የኢፌዴሪ መከላለከያ ሠራዊት ላይ የከፈተውን ጥቃት በፅኑ እንደሚያወግዘው ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።
በተለያየ ጊዜ ሕወሃት ሲያስተላልፋቸው የነበሩ የሥርዓት አልበኝነት ጥሪዎች እና በክልሉ ሕግን ተላልፎ ሲፈጽም የነበራቸው ድርጊቶች አልበቃ ብለው የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ምልክት የሆነው መከላከያ ሠራዊታችን ላይ የፈፀመው ጥቃት በፍፁም በዝምታ የሚታለፍ እንዳልሆነ እናምናለን ብሏል፤ ኢዜማ በመግለጫው።
የነበረው ችግር በንግግር መፈታት ከሚችልበት ምዕራፍ አልፎ አሁን የደረሰበት ደረጃ መድረሱ በጣም አሳዝኖናል ሲልም ነው ያስታወቀው።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የሀገር አንድነት እና ሰላምን ለማስከበር የሚወስዳቸውን እርምጃዎች በመደገፍ የኢዜማ አባላት እና አመራር ከጎኑ እንደምንሰለፍ እናሳውቃለን ያለው ኢዜማ፤ በሚወሰዱ እርምጃዎች ሰላማዊ ዜጎችን ምንም ዓይነት ጉዳት እንዳይደርስባቸው አስፈላጊው ጥንቃቄ መደረግ እንደሚገባው ለማስታወስ እንወዳለን ሲልም አሳስቧል።
የትግራይ ሕዝብ የሚወሰደው እርምጃ ለሀገር አንድነት እና ሰላም ማስከበር ብቻ እንደሆነ በመረዳት ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ጎን እንዲቆም ኢዜማ ጠይቋል።
"መላው የኢትዮጵያ ሕዝብም ይህንኑ በመረዳት አብሮነታችንን አደጋ ላይ የሚጥሉ እና ለሰላም እና ደህንነት እንቅፋት የሚሆኑ ማንኛውንም እንቅስቃሴዎች ከማድረግ ተቆጥበን አካባቢያችንን በንቃት እየጠበቅን ለሰላም እና ደህንነት መከበር ከፀጥታ አስከባሪዎች ጋር ትብብር እንድናደርግ የአደራ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን" ሲልም ኢዜማ ገልጿል።
************************************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ሕወሓት በትግራይ ክልል በሚገኘው የኢፌዴሪ መከላለከያ ሠራዊት ላይ የከፈተውን ጥቃት በፅኑ እንደሚያወግዘው ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።
በተለያየ ጊዜ ሕወሃት ሲያስተላልፋቸው የነበሩ የሥርዓት አልበኝነት ጥሪዎች እና በክልሉ ሕግን ተላልፎ ሲፈጽም የነበራቸው ድርጊቶች አልበቃ ብለው የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ምልክት የሆነው መከላከያ ሠራዊታችን ላይ የፈፀመው ጥቃት በፍፁም በዝምታ የሚታለፍ እንዳልሆነ እናምናለን ብሏል፤ ኢዜማ በመግለጫው።
የነበረው ችግር በንግግር መፈታት ከሚችልበት ምዕራፍ አልፎ አሁን የደረሰበት ደረጃ መድረሱ በጣም አሳዝኖናል ሲልም ነው ያስታወቀው።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የሀገር አንድነት እና ሰላምን ለማስከበር የሚወስዳቸውን እርምጃዎች በመደገፍ የኢዜማ አባላት እና አመራር ከጎኑ እንደምንሰለፍ እናሳውቃለን ያለው ኢዜማ፤ በሚወሰዱ እርምጃዎች ሰላማዊ ዜጎችን ምንም ዓይነት ጉዳት እንዳይደርስባቸው አስፈላጊው ጥንቃቄ መደረግ እንደሚገባው ለማስታወስ እንወዳለን ሲልም አሳስቧል።
የትግራይ ሕዝብ የሚወሰደው እርምጃ ለሀገር አንድነት እና ሰላም ማስከበር ብቻ እንደሆነ በመረዳት ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ጎን እንዲቆም ኢዜማ ጠይቋል።
"መላው የኢትዮጵያ ሕዝብም ይህንኑ በመረዳት አብሮነታችንን አደጋ ላይ የሚጥሉ እና ለሰላም እና ደህንነት እንቅፋት የሚሆኑ ማንኛውንም እንቅስቃሴዎች ከማድረግ ተቆጥበን አካባቢያችንን በንቃት እየጠበቅን ለሰላም እና ደህንነት መከበር ከፀጥታ አስከባሪዎች ጋር ትብብር እንድናደርግ የአደራ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን" ሲልም ኢዜማ ገልጿል።
በአማራ ክልል ለቤተ እምነቶች ጥበቃ ሊደረግ እንደሚገባ ጥሪ ቀረበ
******************
(ኢ ፕ ድ)
በአማራ ክልል ለቤተ እምነቶች ጥበቃ ሊደረግ እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል፡፡
ከጸጥታ አካላት ባገኘው መረጃ መሰረት፣ የኦርቶዶክስ አልባሳት ለብሶ መስጅድ፣ እንዲሁም የሙስሊም አልባሳት ለብሶ ቤተ ክርስቲያን ላይ ጥቃት ለመፈፀም ተልዕኮ የያዙ አካላት ወደ ክልሉ ገብተዋል ሲል የዘገበው ኢቢሲ ነው።
በመሆኑም በክልሉ ያሉ ሁሉም አማኞች ቤተ እምነታቸውን በመጠበቅ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል፡፡
******************
(ኢ ፕ ድ)
በአማራ ክልል ለቤተ እምነቶች ጥበቃ ሊደረግ እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል፡፡
ከጸጥታ አካላት ባገኘው መረጃ መሰረት፣ የኦርቶዶክስ አልባሳት ለብሶ መስጅድ፣ እንዲሁም የሙስሊም አልባሳት ለብሶ ቤተ ክርስቲያን ላይ ጥቃት ለመፈፀም ተልዕኮ የያዙ አካላት ወደ ክልሉ ገብተዋል ሲል የዘገበው ኢቢሲ ነው።
በመሆኑም በክልሉ ያሉ ሁሉም አማኞች ቤተ እምነታቸውን በመጠበቅ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ ገለጻ አደረገ
******
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢፌዲሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ አምባሳደሮችና ዓለም አቀፍ ድርጅቶቸ ሃለፊዎች ዛሬ (ጥቅምት 25 ቀን 2013 ዓ.ም) ገለጻ አድርገዋል።
ገለጻውን ተከተሎ ለተነሱ ጥያቄዎችም አምባሳደር ዲና ተጨማሪ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
******
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢፌዲሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ አምባሳደሮችና ዓለም አቀፍ ድርጅቶቸ ሃለፊዎች ዛሬ (ጥቅምት 25 ቀን 2013 ዓ.ም) ገለጻ አድርገዋል።
ገለጻውን ተከተሎ ለተነሱ ጥያቄዎችም አምባሳደር ዲና ተጨማሪ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በተፈጠረው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንቅስቃሴ መገታቱን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
በተፈጠረው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንቅስቃሴ መገታቱን የኢፌድሪ ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ተማሪዎች ባስተላለፈው መልዕክት፤ በኮቪድ-19 ምክንያት ተቋርጦ የነበረዉን ትምህርት ለማስቀጠል ዩኒቨርሲቲዎች ከጥቅምት 23/2013 ዓ/ም ጀምሮ ተማሪዎቻቸው ሪፖርት እንዲያደርጉ ማስታወቂያ ማውጣታቸዉን አስታውሶ፤ በተፈጠረው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ የተማሪዎችን እንቅስቃሴ ለጊዜዉ መገታቱን ገልጿል።
የሚኒስቴሩ መልዕክት እንደሚከተለው ቀርቧል፤
❶ እስካሁን ዩኒቨርሲቲወቻችሁ ላይ የደረሳችሁ ተማሪወች በግቢያችሁ እንድትቆዩና በየግቢያችሁ የሚሰጣችሁን ማሳሰቢያ እየተከታተላችሁ እንድትንቀሳቀሱ፤ አካባቢያችሁ ያለ የትኛውም የተለየ ጉዳይ ለተቋሞቻችሁ ሃላፊዎች እንድታሳውቁ
❷ እስካሁን ከወላጆቻችሁ አካባቢ ያልተነሳችሁ በቀጣይ ተለዋጭ ማስታወቂያ እስኪወጣ ድረስ ከወላጆቻችሁ ጋር እንድትቆዩ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
በተፈጠረው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንቅስቃሴ መገታቱን የኢፌድሪ ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ተማሪዎች ባስተላለፈው መልዕክት፤ በኮቪድ-19 ምክንያት ተቋርጦ የነበረዉን ትምህርት ለማስቀጠል ዩኒቨርሲቲዎች ከጥቅምት 23/2013 ዓ/ም ጀምሮ ተማሪዎቻቸው ሪፖርት እንዲያደርጉ ማስታወቂያ ማውጣታቸዉን አስታውሶ፤ በተፈጠረው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ የተማሪዎችን እንቅስቃሴ ለጊዜዉ መገታቱን ገልጿል።
የሚኒስቴሩ መልዕክት እንደሚከተለው ቀርቧል፤
❶ እስካሁን ዩኒቨርሲቲወቻችሁ ላይ የደረሳችሁ ተማሪወች በግቢያችሁ እንድትቆዩና በየግቢያችሁ የሚሰጣችሁን ማሳሰቢያ እየተከታተላችሁ እንድትንቀሳቀሱ፤ አካባቢያችሁ ያለ የትኛውም የተለየ ጉዳይ ለተቋሞቻችሁ ሃላፊዎች እንድታሳውቁ
❷ እስካሁን ከወላጆቻችሁ አካባቢ ያልተነሳችሁ በቀጣይ ተለዋጭ ማስታወቂያ እስኪወጣ ድረስ ከወላጆቻችሁ ጋር እንድትቆዩ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡