በአቶ ሽመልስ አብዲሳ የተመራው ቡድን ቦረና ዞን ገብተዋል
***************
(ኢ ፕ ድ)
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የተመራው ቡድን ቦረና ዞን ገብተዋል፡፡
እንደ ኦቢኤን ዘገባ ልዑክ ቡድኑ ከድርቅ ማገገም በሚቻልበት ሂደት ዙሪያ ከነዋሪዎቹ ጋር ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
***************
(ኢ ፕ ድ)
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የተመራው ቡድን ቦረና ዞን ገብተዋል፡፡
እንደ ኦቢኤን ዘገባ ልዑክ ቡድኑ ከድርቅ ማገገም በሚቻልበት ሂደት ዙሪያ ከነዋሪዎቹ ጋር ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ስምንተኛው የአፍሪካ ተማሪዎች ምገባ ቀን እየተከበረ ነው
**************
(ኢ ፕ ድ)
ስምንተኛው አገረ በቀል የአፍሪካ ትምህርት ቤት ምገባ ቀን " የአገር ውስጥ የምገባ ፍጆታ ግዥ ስረአትና ቀጠናዊ የአቅርቦት እሴቶችን በማሳደግ ቀጣይነት ያለው አገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባን ማሻሻል" በሚል መሪ ቃል በአፍሪካ ህብረት የመሰብሰቢያ አዳራሽ በመከበር ላይ ነው።
የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በመርሀ ግብሩ ባደረጉት ንግግር አገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባ የተማሪዎችን ጤንነት ለመጠበቅና የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ከሚያግዙ ተግባራት ውስጥ አንዱ መሆኑን ገልጸዋል። እንደ አህጉርም ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት የሚደግፍ እንደሆነ ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያ ከአምስት ነጥብ ሶስት ሚሊየን በላይ ተማሪዎችን እየመገበች መሆኗን አስታውቀዋል።
የብራዚል አምባሳደር በኢትዮጵያ ጃንዳራ ፌረር ዶሳንቶስ፣ የትምህርት ቤት ምገባ የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጥ፣ የአመጋገብ ስርአትን የሚጠብቅ እንዲሁም የትምህርት ስትራቴጂዎችና ፖሊሲዎችን የሚደግፍ ነው ብለዋል።
በዚህ ዙሪያ ብራዚል የዳበረ ተሞክሮ እንዳላትና ይህንኑ ልምድ ለአፍሪካ አገራት ለማጋራትና ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል።
በመርሀ ግብሩ፣ ተማሪዎች፣ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ በአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ ሳይንስ ፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ሞሐመድ ቤልሆሲንና የአለም አቀፍ ድርጀቶች ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
በአዲሱ ገረመው
**************
(ኢ ፕ ድ)
ስምንተኛው አገረ በቀል የአፍሪካ ትምህርት ቤት ምገባ ቀን " የአገር ውስጥ የምገባ ፍጆታ ግዥ ስረአትና ቀጠናዊ የአቅርቦት እሴቶችን በማሳደግ ቀጣይነት ያለው አገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባን ማሻሻል" በሚል መሪ ቃል በአፍሪካ ህብረት የመሰብሰቢያ አዳራሽ በመከበር ላይ ነው።
የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በመርሀ ግብሩ ባደረጉት ንግግር አገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባ የተማሪዎችን ጤንነት ለመጠበቅና የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ከሚያግዙ ተግባራት ውስጥ አንዱ መሆኑን ገልጸዋል። እንደ አህጉርም ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት የሚደግፍ እንደሆነ ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያ ከአምስት ነጥብ ሶስት ሚሊየን በላይ ተማሪዎችን እየመገበች መሆኗን አስታውቀዋል።
የብራዚል አምባሳደር በኢትዮጵያ ጃንዳራ ፌረር ዶሳንቶስ፣ የትምህርት ቤት ምገባ የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጥ፣ የአመጋገብ ስርአትን የሚጠብቅ እንዲሁም የትምህርት ስትራቴጂዎችና ፖሊሲዎችን የሚደግፍ ነው ብለዋል።
በዚህ ዙሪያ ብራዚል የዳበረ ተሞክሮ እንዳላትና ይህንኑ ልምድ ለአፍሪካ አገራት ለማጋራትና ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል።
በመርሀ ግብሩ፣ ተማሪዎች፣ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ በአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ ሳይንስ ፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ሞሐመድ ቤልሆሲንና የአለም አቀፍ ድርጀቶች ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
በአዲሱ ገረመው
74 የፌዴራል ተቋማት የፋይናንስ ግዥ ስርዓታቸውን በኤሌክትሮኒክስ በመፈፀም ላይ ናቸው
👉726 ጨረታዎች በኤሌክትሮኒክስ ተፈፅሟል፣
****
(ኢ ፕ ድ)
74 የፌዴራል ተቋማት የፋይናንስ ግዥ ስርዓታቸውን በኤሌክትሮኒክስ መፈፀማቸውን የመንግስት ግዢና ንብረት ባለስልጣን አስታወቀ።
የመንግስት ግዢና ንብረት ባለስልጣን የኤሌክትሮኒክ የመንግስት ግዥ ስረዓትን ተግባራዊ ከሚያደርጉ የፌዴራል ተቋማት ጋር ምክክር በማድረግ ላይ ይገኛል።
በምክክር መድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የመንግስት ግዢና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሃጂ ኢብሳ እንደተናገሩት፤ የኤሌክትሮኒክ የግዥ ስርዓት መንግስት ትኩረት ከሰጣቸው ዋነኛ የስራ ዘርፎች አንዱ ነው። ኢትዮጵያ በኤሌክትሮኒክ የግዥ ስርዓት በመተግበር ከአፍሪካ በስድስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
እንቅስቃሴዎች የተጀመሩት ከዛሬ አራት ዓመት በፍት ነው ምንም እንኳን አጭር ግዜ ቢሆንም አሁን ላይ 74 የፌዴራል ተቋማት የፋይናንስ ግዥ ስርዓታቸውን በኤሌክትሮኒክስ መፈፀማቸውን ተናግረዋል።
በያዝነው ዓመት ብቻ 726 ጨረታዎች በኤሌክትሮኒክስ መፈፀማቸውን ገልፀው። ጨረታዎችን ለመሳተፍ ከክልል ከተሞች ወይም ከሌሎች ሀገራት የሚደረገውን ጉዞና ለስራው ዜጎች ያባክኑ ከሁሉም በላይ በዘርፉ የሚካሄደውን የሙስና ሰንሰለት መቁረጥ እንደተቻለ ጠቁመዋል።
በመጀመሪያ ወቅት የኤሌክትሮኒክ የግዥ ስርዓት መንግስት ለመተግበር በሚሞክርበት ወቅት የተቋማት ፍቃደኝነት እንዳልነበረ አስታውሰው አሁን ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ሳይሆን እራሳቸው ወደ ተቋሙ በመምጣት የኤሌክትሮኒክ የግዥ ስርዓት እንዲዘረጋላቸው ጥያቄ እያቀረቡ እንደሆነ አብራርተዋል።
በቅርቡ የፌዴራል ተቋማትን አጠናቀን ወደ ክልሎች በመውረድ የኤሌክትሮኒክ የግዥ ስርዓት እንደምዘረጋ ተናግረዋል።
የኤሌክትሮኒክ የግዥ ስርዓት በመተግበር የተሻለ አፈፃፀሞ ያሳዩ አራት የፌዴራል ተቋማት የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቱ፣ የቅርስና ጥበቃ ባለስልጣን፣የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤትና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኒዎሎጂ ዩንቨርስቲ ተሞክሮዎቻቸውን በማቅረብ ላይ ይገኛሉ።
በውይይቱም የኢ-ጂፒ ፕሮጀክት አፈፃፀም ላይ ሰፊ ውይይቶች ይደረጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በቃልኪዳን አሳዬ
👉726 ጨረታዎች በኤሌክትሮኒክስ ተፈፅሟል፣
****
(ኢ ፕ ድ)
74 የፌዴራል ተቋማት የፋይናንስ ግዥ ስርዓታቸውን በኤሌክትሮኒክስ መፈፀማቸውን የመንግስት ግዢና ንብረት ባለስልጣን አስታወቀ።
የመንግስት ግዢና ንብረት ባለስልጣን የኤሌክትሮኒክ የመንግስት ግዥ ስረዓትን ተግባራዊ ከሚያደርጉ የፌዴራል ተቋማት ጋር ምክክር በማድረግ ላይ ይገኛል።
በምክክር መድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የመንግስት ግዢና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሃጂ ኢብሳ እንደተናገሩት፤ የኤሌክትሮኒክ የግዥ ስርዓት መንግስት ትኩረት ከሰጣቸው ዋነኛ የስራ ዘርፎች አንዱ ነው። ኢትዮጵያ በኤሌክትሮኒክ የግዥ ስርዓት በመተግበር ከአፍሪካ በስድስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
እንቅስቃሴዎች የተጀመሩት ከዛሬ አራት ዓመት በፍት ነው ምንም እንኳን አጭር ግዜ ቢሆንም አሁን ላይ 74 የፌዴራል ተቋማት የፋይናንስ ግዥ ስርዓታቸውን በኤሌክትሮኒክስ መፈፀማቸውን ተናግረዋል።
በያዝነው ዓመት ብቻ 726 ጨረታዎች በኤሌክትሮኒክስ መፈፀማቸውን ገልፀው። ጨረታዎችን ለመሳተፍ ከክልል ከተሞች ወይም ከሌሎች ሀገራት የሚደረገውን ጉዞና ለስራው ዜጎች ያባክኑ ከሁሉም በላይ በዘርፉ የሚካሄደውን የሙስና ሰንሰለት መቁረጥ እንደተቻለ ጠቁመዋል።
በመጀመሪያ ወቅት የኤሌክትሮኒክ የግዥ ስርዓት መንግስት ለመተግበር በሚሞክርበት ወቅት የተቋማት ፍቃደኝነት እንዳልነበረ አስታውሰው አሁን ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ሳይሆን እራሳቸው ወደ ተቋሙ በመምጣት የኤሌክትሮኒክ የግዥ ስርዓት እንዲዘረጋላቸው ጥያቄ እያቀረቡ እንደሆነ አብራርተዋል።
በቅርቡ የፌዴራል ተቋማትን አጠናቀን ወደ ክልሎች በመውረድ የኤሌክትሮኒክ የግዥ ስርዓት እንደምዘረጋ ተናግረዋል።
የኤሌክትሮኒክ የግዥ ስርዓት በመተግበር የተሻለ አፈፃፀሞ ያሳዩ አራት የፌዴራል ተቋማት የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቱ፣ የቅርስና ጥበቃ ባለስልጣን፣የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤትና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኒዎሎጂ ዩንቨርስቲ ተሞክሮዎቻቸውን በማቅረብ ላይ ይገኛሉ።
በውይይቱም የኢ-ጂፒ ፕሮጀክት አፈፃፀም ላይ ሰፊ ውይይቶች ይደረጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በቃልኪዳን አሳዬ
በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች የሚስተዋሉ ችግሮችን በጋራ ለመፍታት አቅጣጫ ተቀምጦ እየተሰራ መሆኑን የየክልሎቹ ኮምንኬሽን ቢሮ ኃላፊዎች አስታወቁ
******************
(ኢ.ፕ.ድ)
በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች የሚስተዋሉ ችግሮችን በጋራ ለመፍታት አቅጣጫ ተቀምጦ እየተሰራ መሆኑን የሁለቱም ክልሎች የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊዎች ዛሬ በጋራ በስጡት መግለጫ አስታወቀዋል።
የአማራ ክልል የመንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ትናንት የሁለቱም ክልሎች ከፍተኛ አመራሮች በአገራዊ፣ ክልላዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።
በውይይቱ ከፍተኛ አመራሮች የተሳተፉበት መሆኑን የጠቀሱት አቶ ግዛቸው፤ መልካም የሆኑ የልማት ስራዎችን በጋራ ለማስቀጠል፣ ፈተናዎችና ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ውጤታማ ውይይት ተደርጓል ብለዋል።
የኦሮሚያ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ ሃይሉ አዱኛ በበኩላቸው፤ በሁለቱ ክልሎች መካከል የመልካም አስተዳደር፣ የልማት፣ የማህበራዊና ፖለቲካዊ ግንኙነትቶችን ለማጠናከር የሚያስችል ውይይት በከፍተኛ አመራሮች መካከል መካሄዱን አስታውቀዋል።
ሁለቱ ክልሎች በመናበብ የጋራ የሆኑ ፈተናዎችንና ችግሮችን ለመፍታት ስምምነት ላይ ተደርሷልም ብለዋል።
ውይይቱ በአመራሩ ብቻ የሚወሰን ሳይሆን በቀጣይም በምሁራን፣ በአገር ሽማግሌዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መካከል ይደረጋል ተብሏል።
በሞገስ ተስፋ
******************
(ኢ.ፕ.ድ)
በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች የሚስተዋሉ ችግሮችን በጋራ ለመፍታት አቅጣጫ ተቀምጦ እየተሰራ መሆኑን የሁለቱም ክልሎች የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊዎች ዛሬ በጋራ በስጡት መግለጫ አስታወቀዋል።
የአማራ ክልል የመንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ትናንት የሁለቱም ክልሎች ከፍተኛ አመራሮች በአገራዊ፣ ክልላዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።
በውይይቱ ከፍተኛ አመራሮች የተሳተፉበት መሆኑን የጠቀሱት አቶ ግዛቸው፤ መልካም የሆኑ የልማት ስራዎችን በጋራ ለማስቀጠል፣ ፈተናዎችና ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ውጤታማ ውይይት ተደርጓል ብለዋል።
የኦሮሚያ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ ሃይሉ አዱኛ በበኩላቸው፤ በሁለቱ ክልሎች መካከል የመልካም አስተዳደር፣ የልማት፣ የማህበራዊና ፖለቲካዊ ግንኙነትቶችን ለማጠናከር የሚያስችል ውይይት በከፍተኛ አመራሮች መካከል መካሄዱን አስታውቀዋል።
ሁለቱ ክልሎች በመናበብ የጋራ የሆኑ ፈተናዎችንና ችግሮችን ለመፍታት ስምምነት ላይ ተደርሷልም ብለዋል።
ውይይቱ በአመራሩ ብቻ የሚወሰን ሳይሆን በቀጣይም በምሁራን፣ በአገር ሽማግሌዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መካከል ይደረጋል ተብሏል።
በሞገስ ተስፋ