አየር መንገዱ አምስት ተጨማሪ ቦይንግ 777 የዕቃ ጫኝ አውሮፕላኖች ሊገዛ መሆኑን አስታወቀ
(እለታዊ የኢትዩትዩብ መረጃዎች)
በአፍሪካ ትልቁ እና ቀዳሚው የአቪዬሽን ግሩፕ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቦይንግ የዕቃ ጫኝ አውሮፕላኖቹን ቁጥር ለማሳደግ አምስት ተጨማሪ ቦይንግ 777 የቅርብ ጊዜ ዘመናዊ የዕቃ ጫኝ አውሮፕላኖች ማዘዙን አስታውቋል።
አዲሱ ትዕዛዝ አየር መንገዱ ከቦይንግ ኩባንያ ጋር ያለውን አጋርነት የበለጠ ከማጠናከር ባሻገር የዕቃ ጫኝ አውሮፕላኖች መጠን ማደጉ የድርጅቱን የማጓጓዣ አገልግሎት አቅምን እና ቅልጥፍናን ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያደርሰውም ተጠቁሟል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሁኑ ሰዓት ዘጠኝ ቦይንግ 777 የዕቃ ጫኝ አውሮፕላኖች ባለቤት ሲሆን፤ አምስት ተጨማሪ አውሮፕላኖችን ያዘዘው የጭነት አገልግሎቱን ከፍ ለማድረግ መሆኑ ተገልጿል።
በአሁኑ ሰዓት በገበያው ላይ መሪ የሆነው ቦይንግ 777 የዕቃ ጫኝ አውሮፕላን የዓለማችን ግዙፉ እና ረጅም ርቀት መጓዝ የሚችል ባለሁለት ሞተር አውሮፕላን መሆኑን አየር መንገዱ ገልጿል።
ከቀድሞዎቹ ጋር ሲነፃፀርም በ17% ያነሰ ነዳጅ የሚጠቀም እና አነስተኛ የበካይ ጋዝ ልቀትን መያዝ ይችላል ተብሏል።
ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ
የኢትዩትዩብ ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ። ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
YouTube: https://youtube.com/ethiotube
Instagram: https://instagram.com/ethiotube
Twitter: https://twitter.com/EthioTube
Facebook: https://facebook.com/EthioTube
Telegram: https://t.me/ethiotubemedia
(እለታዊ የኢትዩትዩብ መረጃዎች)
በአፍሪካ ትልቁ እና ቀዳሚው የአቪዬሽን ግሩፕ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቦይንግ የዕቃ ጫኝ አውሮፕላኖቹን ቁጥር ለማሳደግ አምስት ተጨማሪ ቦይንግ 777 የቅርብ ጊዜ ዘመናዊ የዕቃ ጫኝ አውሮፕላኖች ማዘዙን አስታውቋል።
አዲሱ ትዕዛዝ አየር መንገዱ ከቦይንግ ኩባንያ ጋር ያለውን አጋርነት የበለጠ ከማጠናከር ባሻገር የዕቃ ጫኝ አውሮፕላኖች መጠን ማደጉ የድርጅቱን የማጓጓዣ አገልግሎት አቅምን እና ቅልጥፍናን ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያደርሰውም ተጠቁሟል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሁኑ ሰዓት ዘጠኝ ቦይንግ 777 የዕቃ ጫኝ አውሮፕላኖች ባለቤት ሲሆን፤ አምስት ተጨማሪ አውሮፕላኖችን ያዘዘው የጭነት አገልግሎቱን ከፍ ለማድረግ መሆኑ ተገልጿል።
በአሁኑ ሰዓት በገበያው ላይ መሪ የሆነው ቦይንግ 777 የዕቃ ጫኝ አውሮፕላን የዓለማችን ግዙፉ እና ረጅም ርቀት መጓዝ የሚችል ባለሁለት ሞተር አውሮፕላን መሆኑን አየር መንገዱ ገልጿል።
ከቀድሞዎቹ ጋር ሲነፃፀርም በ17% ያነሰ ነዳጅ የሚጠቀም እና አነስተኛ የበካይ ጋዝ ልቀትን መያዝ ይችላል ተብሏል።
ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ
የኢትዩትዩብ ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ። ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
YouTube: https://youtube.com/ethiotube
Instagram: https://instagram.com/ethiotube
Twitter: https://twitter.com/EthioTube
Facebook: https://facebook.com/EthioTube
Telegram: https://t.me/ethiotubemedia
በባቡር የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማቶች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት አሳሳቢ ደረጃ ደርሷል ተባለ
(እለታዊ የኢትዩትዩብ መረጃዎች)
ለአዲስ አበባ ከተማ ቀላል ባቡር ትራንዚት አገልግሎት በተዘረጉ የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማቶች ላይ የሚፈፀመው የስርቆት ወንጀል አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ሲል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ።
በ2013 በጀት ዓመት ብቻ 1 ሚሊዮን 293 ሺህ 350 ብር የሚገመት ርዝመቱ 1 ሺህ 55 ሜትር የኤሌክትሪክ ኬብል ስርቆት የተፈፀመ ሲሆን በ2014 በጀት ዓመትም 24 ሚሊዮን 800 ሺህ 725 ብር በላይ የሚገመት ርዝመቱ 15 ሺህ 347 ሜትር የኤሌክትሪክ ኬብል ስርቆት ተፈጽሟል።
በኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ስርቆት ሲፈፅም የተገኘ ማንኛውም ግለሰብ በሃገሪቱ የወንጀል ሕግ ከ15 ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እስራት ይቀጣል። በሽያጭ፣ በተውሶ፣ በስጦታ፣ በመያዣነት የተቀበለ ወይም በማናቸውም አኳኋን የወሰደ፣ የተገለገለ የደበቀ ወይም ያስቀመጠ፣ ማንኛውም ግለሰብ ደግሞ ከ5 ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እስራትና በገንዘብ መቀጮ ይቀጣል።
ተቋሙ ስርቆቱን ለመከላከል ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ ቢሆንም ድርጊቱን በሚፈፅሙ ግለሰቦች ላይ የሚወሰደው እርምጃ አስተማሪ ባለመሆኑ ችግሩ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ማስተባበሪያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ቡልቱማ ቂጣታ ገልፀዋል፡፡
በ2014 በጀት ዓመት 11 ወራት በተደረገ ክትትልና የማጣራት ስራ በአዲስ አበባ ከተማ ቀላል ባቡር የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ላይ በቁጥር ከ37 በላይ ‘’የስርቆትና ጉዳት ማድረስ’’ የወንጀል ተግባራት ተፈፅመው ለተለያዩ የክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያዎች ክስ ተመስርቶ በምርመራና በፍርድ ሂደት ላይ ናቸው።
የኢትዩትዩብ ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ። ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
YouTube: https://youtube.com/ethiotube
Instagram: https://instagram.com/ethiotube
Twitter: https://twitter.com/EthioTube
Facebook: https://facebook.com/EthioTube
Telegram: https://t.me/ethiotubemedia
(እለታዊ የኢትዩትዩብ መረጃዎች)
ለአዲስ አበባ ከተማ ቀላል ባቡር ትራንዚት አገልግሎት በተዘረጉ የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማቶች ላይ የሚፈፀመው የስርቆት ወንጀል አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ሲል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ።
በ2013 በጀት ዓመት ብቻ 1 ሚሊዮን 293 ሺህ 350 ብር የሚገመት ርዝመቱ 1 ሺህ 55 ሜትር የኤሌክትሪክ ኬብል ስርቆት የተፈፀመ ሲሆን በ2014 በጀት ዓመትም 24 ሚሊዮን 800 ሺህ 725 ብር በላይ የሚገመት ርዝመቱ 15 ሺህ 347 ሜትር የኤሌክትሪክ ኬብል ስርቆት ተፈጽሟል።
በኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ስርቆት ሲፈፅም የተገኘ ማንኛውም ግለሰብ በሃገሪቱ የወንጀል ሕግ ከ15 ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እስራት ይቀጣል። በሽያጭ፣ በተውሶ፣ በስጦታ፣ በመያዣነት የተቀበለ ወይም በማናቸውም አኳኋን የወሰደ፣ የተገለገለ የደበቀ ወይም ያስቀመጠ፣ ማንኛውም ግለሰብ ደግሞ ከ5 ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እስራትና በገንዘብ መቀጮ ይቀጣል።
ተቋሙ ስርቆቱን ለመከላከል ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ ቢሆንም ድርጊቱን በሚፈፅሙ ግለሰቦች ላይ የሚወሰደው እርምጃ አስተማሪ ባለመሆኑ ችግሩ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ማስተባበሪያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ቡልቱማ ቂጣታ ገልፀዋል፡፡
በ2014 በጀት ዓመት 11 ወራት በተደረገ ክትትልና የማጣራት ስራ በአዲስ አበባ ከተማ ቀላል ባቡር የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ላይ በቁጥር ከ37 በላይ ‘’የስርቆትና ጉዳት ማድረስ’’ የወንጀል ተግባራት ተፈፅመው ለተለያዩ የክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያዎች ክስ ተመስርቶ በምርመራና በፍርድ ሂደት ላይ ናቸው።
የኢትዩትዩብ ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ። ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
YouTube: https://youtube.com/ethiotube
Instagram: https://instagram.com/ethiotube
Twitter: https://twitter.com/EthioTube
Facebook: https://facebook.com/EthioTube
Telegram: https://t.me/ethiotubemedia
የሎጂስቲክስ ወጪን ለመቀነስ በተከናወኑ ተግባራት 2 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
(እለታዊ የኢትዩትዩብ መረጃዎች)
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ባለፉት 10 ወራት የሎጂስቲክስ ወጪን ለመቀነስ በተከናወኑ ተግባራት 2 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ ማዳን መቻሉን አስታወቀ፡፡
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ እያካሄደ ባለው 6ኛ ዙር 1ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ጉባዔ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴርን የ2014 በጀት ዓመት የ10 ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እያዳመጠ ይገኛል፡፡
ሪፖርቱን ያቀረቡት የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዳግማዊት ሞገስ ባለፉት 10 ወራት የሎጂስቲክስ ወጪን ለመቀነስ በተከናወኑ ተግባራት 2 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ ማዳን መቻሉን አብራርተዋል።
በአጠቃላይ በቀረበው ሪፖርት መነሻነት የከተማ መሠረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስተያየትና ጥያቄ እየቀረበ ሲሆን በሚኒስቴሩ የሥራ ኃላፊዎች ምላሽ እየተሰጠ መሆኑን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡
ምንጭ፦ ዋልታ
የኢትዩትዩብ ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ። ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
YouTube: https://youtube.com/ethiotube
Instagram: https://instagram.com/ethiotube
Twitter: https://twitter.com/EthioTube
Facebook: https://facebook.com/EthioTube
Telegram: https://t.me/ethiotubemedia
(እለታዊ የኢትዩትዩብ መረጃዎች)
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ባለፉት 10 ወራት የሎጂስቲክስ ወጪን ለመቀነስ በተከናወኑ ተግባራት 2 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ ማዳን መቻሉን አስታወቀ፡፡
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ እያካሄደ ባለው 6ኛ ዙር 1ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ጉባዔ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴርን የ2014 በጀት ዓመት የ10 ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እያዳመጠ ይገኛል፡፡
ሪፖርቱን ያቀረቡት የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዳግማዊት ሞገስ ባለፉት 10 ወራት የሎጂስቲክስ ወጪን ለመቀነስ በተከናወኑ ተግባራት 2 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ ማዳን መቻሉን አብራርተዋል።
በአጠቃላይ በቀረበው ሪፖርት መነሻነት የከተማ መሠረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስተያየትና ጥያቄ እየቀረበ ሲሆን በሚኒስቴሩ የሥራ ኃላፊዎች ምላሽ እየተሰጠ መሆኑን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡
ምንጭ፦ ዋልታ
የኢትዩትዩብ ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ። ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
YouTube: https://youtube.com/ethiotube
Instagram: https://instagram.com/ethiotube
Twitter: https://twitter.com/EthioTube
Facebook: https://facebook.com/EthioTube
Telegram: https://t.me/ethiotubemedia
ጋዜጠኛው የሲቪል ልብስ በለበሱ ኃይሎች ከሚሰራበት ቢሮ ተወሰደ
(እለታዊ የኢትዩትዩብ መረጃዎች)
የ“ፍትሕ” መጽሔት ማኔጄንግ ዳይሬክተር የሆነው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ዛሬ ሐሙስ ግንቦት 18 ረፋዱን ከቢሮው በጸጥታ ኃይሎች መወሰዱን ባልደረቦቹ ተናገሩ።
ጋዜጠኛ ተመስገንን ከቀኑ አምስት ሰዓት ገደማ በቁጥጥር ስር ያዋሉት የሲቪል ልብስ የለበሱ እና ጠመንጃ ያነገቱ የጸጥታ ኃይሎች መሆናቸውን ነው ባልደረቦቹ የገለፁት።
እስከ አሁን በምን ጉዳይ እና ለምን እንደተወሰደ የተገለፀ ነገር ባይኖርም ጉዳዩን ተከታትለን የምናሳውቃችሁ ይሆናል።
ምንጭ፦ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር
የኢትዩትዩብ ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ። ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
YouTube: https://youtube.com/ethiotube
Instagram: https://instagram.com/ethiotube
Twitter: https://twitter.com/EthioTube
Facebook: https://facebook.com/EthioTube
Telegram: https://t.me/ethiotubemedia
(እለታዊ የኢትዩትዩብ መረጃዎች)
የ“ፍትሕ” መጽሔት ማኔጄንግ ዳይሬክተር የሆነው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ዛሬ ሐሙስ ግንቦት 18 ረፋዱን ከቢሮው በጸጥታ ኃይሎች መወሰዱን ባልደረቦቹ ተናገሩ።
ጋዜጠኛ ተመስገንን ከቀኑ አምስት ሰዓት ገደማ በቁጥጥር ስር ያዋሉት የሲቪል ልብስ የለበሱ እና ጠመንጃ ያነገቱ የጸጥታ ኃይሎች መሆናቸውን ነው ባልደረቦቹ የገለፁት።
እስከ አሁን በምን ጉዳይ እና ለምን እንደተወሰደ የተገለፀ ነገር ባይኖርም ጉዳዩን ተከታትለን የምናሳውቃችሁ ይሆናል።
ምንጭ፦ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር
የኢትዩትዩብ ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ። ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
YouTube: https://youtube.com/ethiotube
Instagram: https://instagram.com/ethiotube
Twitter: https://twitter.com/EthioTube
Facebook: https://facebook.com/EthioTube
Telegram: https://t.me/ethiotubemedia
ከጭልጋና አካባቢው ተፈናቅለው የነበሩ ወገኖች ወደ ቦታቸው እየተመለሱ ይገኛሉ
(እለታዊ የኢትዩትዩብ መረጃዎች)
ከትላንት አንስቶ ከአይከል እና በዙሪያዋ ተፈናቅለው የነበሩ 11 ሺህ 938 የህበረተሰብ ክፍሎች ወደ ቦታቸው የመመለስ ስራ እየተሰራ ሲሆን ወደ አይከል ከተማ ሲገቡ ማህበረሰቡ በነቂስ ወጥቶ ተቀብሏቸዋል።
ተፈናቃዮቹ ከዚህ በፊት በአይከል ከተማና በአካባቢዋ ይኖሩ የነበረ ሲሆን ከማንነት ጋር ተያይዞ በተፈጠረው ችግር ምክንያት ከቦታቸው ተፈናቅለው በተለያዬ ቦታ ነበሩ። አሁን ላይ በተፈጠረው አንፃራዊ ሰላም ከትላንት አንስቶ ወደ ቦታቸው የመመለስ ስራ እየተሰራ መሆኑ ተነግሯል።
ምንጭ፦ ቲክቫህ
የኢትዩትዩብ ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ። ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
YouTube: https://youtube.com/ethiotube
Instagram: https://instagram.com/ethiotube
Twitter: https://twitter.com/EthioTube
Facebook: https://facebook.com/EthioTube
Telegram: https://t.me/ethiotubemedia
(እለታዊ የኢትዩትዩብ መረጃዎች)
ከትላንት አንስቶ ከአይከል እና በዙሪያዋ ተፈናቅለው የነበሩ 11 ሺህ 938 የህበረተሰብ ክፍሎች ወደ ቦታቸው የመመለስ ስራ እየተሰራ ሲሆን ወደ አይከል ከተማ ሲገቡ ማህበረሰቡ በነቂስ ወጥቶ ተቀብሏቸዋል።
ተፈናቃዮቹ ከዚህ በፊት በአይከል ከተማና በአካባቢዋ ይኖሩ የነበረ ሲሆን ከማንነት ጋር ተያይዞ በተፈጠረው ችግር ምክንያት ከቦታቸው ተፈናቅለው በተለያዬ ቦታ ነበሩ። አሁን ላይ በተፈጠረው አንፃራዊ ሰላም ከትላንት አንስቶ ወደ ቦታቸው የመመለስ ስራ እየተሰራ መሆኑ ተነግሯል።
ምንጭ፦ ቲክቫህ
የኢትዩትዩብ ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ። ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
YouTube: https://youtube.com/ethiotube
Instagram: https://instagram.com/ethiotube
Twitter: https://twitter.com/EthioTube
Facebook: https://facebook.com/EthioTube
Telegram: https://t.me/ethiotubemedia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ኢኳቶሪያል ጊኒ ርእሰ ከተማ ማላቦ ገቡ
(እለታዊ የኢትዩትዩብ መረጃዎች)
በናይጄሪያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ፣ ጉብኝቱን አጠናቀው በአፍሪካ ሕብረት ልዩ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ነው ከልኡካን ቡድናቸው ጋር ማላቦ የገቡት።
በቆይታቸውም በሰብዓዊ እርዳታ ፣ ፀረ ሽብር ጉዳዮች እና ኢ-ሕገመንግሥታዊ በሆነ መንገድ ሥልጣን ለመያዝ የሚደረጉ ጥረቶችን መከላከል ላይ በሚያተኩረው በሕብረቱ ጉባኤ ላይ ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ማላቦ ሲደርሱ በአገሪቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ምንጭ፦ ኢቢሲ
የኢትዩትዩብ ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ። ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
YouTube: https://youtube.com/ethiotube
Instagram: https://instagram.com/ethiotube
Twitter: https://twitter.com/EthioTube
Facebook: https://facebook.com/EthioTube
Telegram: https://t.me/ethiotubemedia
(እለታዊ የኢትዩትዩብ መረጃዎች)
በናይጄሪያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ፣ ጉብኝቱን አጠናቀው በአፍሪካ ሕብረት ልዩ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ነው ከልኡካን ቡድናቸው ጋር ማላቦ የገቡት።
በቆይታቸውም በሰብዓዊ እርዳታ ፣ ፀረ ሽብር ጉዳዮች እና ኢ-ሕገመንግሥታዊ በሆነ መንገድ ሥልጣን ለመያዝ የሚደረጉ ጥረቶችን መከላከል ላይ በሚያተኩረው በሕብረቱ ጉባኤ ላይ ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ማላቦ ሲደርሱ በአገሪቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ምንጭ፦ ኢቢሲ
የኢትዩትዩብ ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ። ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
YouTube: https://youtube.com/ethiotube
Instagram: https://instagram.com/ethiotube
Twitter: https://twitter.com/EthioTube
Facebook: https://facebook.com/EthioTube
Telegram: https://t.me/ethiotubemedia
በማደጎ የወሰደችውን ህፃን የገደለችው ግለሰብ በ 18 አመት ፅኑ እስራት ተቀጣች
(እለታዊ የኢትዩትዩብ መረጃዎች)
አሳዳጊዋ ህፃኑን መግደሉን ብታምንም ይህ የሆነው ግን ሆን ብላ እንዳልገደለችው ተናግራለች።
ግለሰቧ እንደተናገረችው በአጋጣሚ በሚያለቅስበት ወቅት ዝም ለማሰኘት በምትነቀንቀው ወቅት በድንገት ጭንቅላቱን ከሶፋው መደገፊያ ጋር ተጋጭቷል ስትል ተናግራለች።
ነገር ግን ጎረቤቶቿ በበኩላቸው በሰጡት ምስክርነት የልጁን ለቅሶ ምንም እንዳልሰሙና የሷን ግን በከፍተኛ ንዴት የተሞላበት ጩኸት ይሰማ ነበር ብለዋል።
የጨቅላውን አስከሬን የመረመሩ የጤና ባለሙያዎች በበኩላቸው ህፃኑ ጭንቅላት ላይ የደረሰው ጉዳት በከባድ ምት የተከሰተ እንደሆነና ጭንቅላቱም ከግድግዳ ጋር ወይም ከወለል ጋር ተጋጭቷል ብለው እንደሚያምኑም አስረድተዋል።
ከሶፋው ጋር መጋጨት ህፃኑ ለታየበት ከፍተኛ የውስጥ ደም መፍሰስ ምክንያት እንደማይሆንና የደረሰበትንም ጉዳት በከፍተኛ ፍጥነት ከሚደርስ የመኪና አደጋ ጋር አመሳስለውታል።
ገና በ 8 ወሩ ለማደጎ ወላጆቹ የተሰጠ ሲሆን ግለሰቧ ባሏ ስራ በሄደበት ወቅት ህጻኑን በአጸያፊ ስድብ ከመጥራት ጀምሮ ምን ያህል ትጠላው እንደነበር መልዕክት ልካለታለች ተብሏል።
ታህሳስ ወር መጨረሻም ላይ ግለሰቧ ህፃኑ ከሶፋ ከወደቀ በኋላ ራሱን መሳቱንና በአስቸጋሪ ሁኔታ እየተነፈሰ መሆኑን ለፖሊስ ደውላ ተናገረች።
በማግስቱም በሊቨርፑል ውስጥ በሚገኘው የአልደር ሄይ የህጻናት ሆስፒታል መሞቱም ተነግሯል።
ዳኛው ጄረሚ ቤከር ጨቅላው የማደጎ እናቱን በፍጹም ሊለምድ እንዳልቻለ ተናግረው ይህ ሲከሰት ልጁን ከመመለስ ይልቅ "ራስ ወዳድ በመሆኗ ይህ አሳዛኝ ክስተት መፈጠሩንም" ጠቁመዋል።
ስለሆነም የ38 አመቷ ግለሰብ በነፍስ ግድያና በልጆች ጭካኔ ወንጀል ጥፋተኛ ሆና እንዳገኛትም ገልጾ የ18 አመት እስር ፈርዶባታል።
ምንጭ፦ ቢቢሲ
የኢትዩትዩብ ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ። ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
YouTube: https://youtube.com/ethiotube
Instagram: https://instagram.com/ethiotube
Twitter: https://twitter.com/EthioTube
Facebook: https://facebook.com/EthioTube
Telegram: https://t.me/ethiotubemedia
(እለታዊ የኢትዩትዩብ መረጃዎች)
አሳዳጊዋ ህፃኑን መግደሉን ብታምንም ይህ የሆነው ግን ሆን ብላ እንዳልገደለችው ተናግራለች።
ግለሰቧ እንደተናገረችው በአጋጣሚ በሚያለቅስበት ወቅት ዝም ለማሰኘት በምትነቀንቀው ወቅት በድንገት ጭንቅላቱን ከሶፋው መደገፊያ ጋር ተጋጭቷል ስትል ተናግራለች።
ነገር ግን ጎረቤቶቿ በበኩላቸው በሰጡት ምስክርነት የልጁን ለቅሶ ምንም እንዳልሰሙና የሷን ግን በከፍተኛ ንዴት የተሞላበት ጩኸት ይሰማ ነበር ብለዋል።
የጨቅላውን አስከሬን የመረመሩ የጤና ባለሙያዎች በበኩላቸው ህፃኑ ጭንቅላት ላይ የደረሰው ጉዳት በከባድ ምት የተከሰተ እንደሆነና ጭንቅላቱም ከግድግዳ ጋር ወይም ከወለል ጋር ተጋጭቷል ብለው እንደሚያምኑም አስረድተዋል።
ከሶፋው ጋር መጋጨት ህፃኑ ለታየበት ከፍተኛ የውስጥ ደም መፍሰስ ምክንያት እንደማይሆንና የደረሰበትንም ጉዳት በከፍተኛ ፍጥነት ከሚደርስ የመኪና አደጋ ጋር አመሳስለውታል።
ገና በ 8 ወሩ ለማደጎ ወላጆቹ የተሰጠ ሲሆን ግለሰቧ ባሏ ስራ በሄደበት ወቅት ህጻኑን በአጸያፊ ስድብ ከመጥራት ጀምሮ ምን ያህል ትጠላው እንደነበር መልዕክት ልካለታለች ተብሏል።
ታህሳስ ወር መጨረሻም ላይ ግለሰቧ ህፃኑ ከሶፋ ከወደቀ በኋላ ራሱን መሳቱንና በአስቸጋሪ ሁኔታ እየተነፈሰ መሆኑን ለፖሊስ ደውላ ተናገረች።
በማግስቱም በሊቨርፑል ውስጥ በሚገኘው የአልደር ሄይ የህጻናት ሆስፒታል መሞቱም ተነግሯል።
ዳኛው ጄረሚ ቤከር ጨቅላው የማደጎ እናቱን በፍጹም ሊለምድ እንዳልቻለ ተናግረው ይህ ሲከሰት ልጁን ከመመለስ ይልቅ "ራስ ወዳድ በመሆኗ ይህ አሳዛኝ ክስተት መፈጠሩንም" ጠቁመዋል።
ስለሆነም የ38 አመቷ ግለሰብ በነፍስ ግድያና በልጆች ጭካኔ ወንጀል ጥፋተኛ ሆና እንዳገኛትም ገልጾ የ18 አመት እስር ፈርዶባታል።
ምንጭ፦ ቢቢሲ
የኢትዩትዩብ ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ። ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
YouTube: https://youtube.com/ethiotube
Instagram: https://instagram.com/ethiotube
Twitter: https://twitter.com/EthioTube
Facebook: https://facebook.com/EthioTube
Telegram: https://t.me/ethiotubemedia