ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
13.8K subscribers
3.69K photos
43 videos
45 files
539 links
Official ERA Telegram Channal
በዚህ የቴሌግራም ቻናል
የመንገድ ዜናዎችን
የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን
የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።
Download Telegram
መልካም በዓል!
👍105
የጣርማበር - መለያያ ሰፌድ ሜዳ የጠጠር መንገድ ጥገና እየተካሄደለት ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 21/2018 (ኢመአ)፦ ከጣርማበር መለያያ እስከ ሰፌድ ሜዳ ለሚዘልቀው የጠጠር መንገድ ጥገና እየተደረገለት ይገኛል። ጥገናው የሕዝቡን የትራንስፖርት ችግር ለማቃለል ታስቦ በትኩረት እየተከናወነ ያለ ሥራ ነው።

ይህ አጠቃላይ 118 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ ያለው የመንገድ ፕሮጀክት፣ ከዚህ ቀደም በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ አማካኝነት ግንባታው ሲካሄድ የነበረ ቢሆንም በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ሳይጠናቀቅ ተስተጓጉሎ ቆይቷል። በአሁኑ ወቅት ግን ለትራንስፖርት እጅግ አስቸጋሪ በሆነው 21.6 ኪሎ ሜትር የመንገዱ ክፍል ላይ ሰፊ የጥገና ሥራ እየተሠራ ይገኛል።

እስካሁንም በማሽን የቦይ ማጽዳት፣ የድንጋይ ሙሌት፣ በጭቃ የተበላሹ አካባቢዎችን የማስወገድ እንዲሁም በግሬደር የመንገዱን አካል የማስተካከልና የማጠናከር ሥራዎች ተከናውነዋል። የጥገና ሥራውን የኢመአ የዓለምገና መንገድ ጥገና ዲስትሪክት በራስ ኃይል እያከናወነው ሲሆን፣ የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ደግሞ የዓለምገና መንገድ ኔትወርክ ማኔጅመንት ቅርንጫፍ ቢሮ በበላይነት እየተከታተለው ነው።

የዚህ መንገድ መጠገን ማኅበረሰቡን ለእንግልትና ለትራንስፖርት መጉላላት ከዳረጉ ችግሮች የሚያላቅቅ ሲሆን፣ የትራፊክ አደጋን ከመቀነስና ጊዜን ከመቆጠብ ባሻገር የግብርና ምርቶችንና የተለያዩ ግብዓቶችን ወደ ገበያ ለማቅረብ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።

በቀጣይም ከዚህ ቀደም ይስተዋሉ የነበሩ ማነቆዎችን በመቅረፍ ሙሉ የግንባታ ሒደቱን በቀጣዩ በጀት ዓመት ለማቀላጠፍ በትኩረት እየተሠራ ነው።

በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
👍65
9ኛው የመንገድ ጥናትና ሥርፀት ኮንፈረንስ ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም(ኢመአ): የመንገድ ልማትና አስተዳደር ሥራዎችን በሳይንሳዊ ምርምርና በቴክኖሎጂ ለማገዝ የተዘጋጀው 9ኛው የመንገድ ጥናትና ሥርፀት ኮንፈረንስ ተካሂዷል።

በኮንፈረንሱ መክፈቻ ላይ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሀመድ አብዱራህማን፣ የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሂሩት ዮሐንስ እና የቀድሞው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዛይድ ወልደገብርኤልን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የዘርፉ ባለሙያዎችና ተመራማሪዎች ተገኝተዋል።

ባለፉት ስምንት ዓመታት የተካሄዱት ተከታታይ የምርምር ኮንፈረንሶች በሀገሪቱ የመንገድ ልማት ላይ ውጤታማ ለውጦችን ማምጣት ችለዋል። በአሁኑ 9ኛ ኮንፈረንስም በርካታ ጥናታዊ ጽሑፎች የቀረቡ ሲሆን፣ ተያያዥ አውደርዕይም ተካሂዷል። በጥናቶቹ በሌሎች አገራትና ፕሮጀክቶች ላይ ተተግብረው ውጤታማ የሆኑ የመንገድ ግንባታና አስተዳደር ልምዶች የተዳሰሱ ሲሆን፣ እነዚህ ተሞክሮዎች ለሀገሪቱ የመሠረተ ልማት ዕድገት አዳዲስ ዕድሎችን ይዘው ይመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በተለይም በአሁኑ ወቅት በዘርፉ ላይ ፈተና እየሆኑ ያሉትን እንደ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ እና የመንገድ መሸራተት (ናዳ) ያሉ ዋና ዋና ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ ተግባራዊ የመፍትሔ ሐሳቦች በኮንፈረንሱ ላይ በስፋት ተመክሮባቸዋል። ከተቀመጡት የመፍትሔ አቅጣጫዎች መካከልም ዘላቂነትን ለማረጋገጥ በሲሚንቶ ኮንክሪት በሚሠሩ መንገዶች ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሠራ በጥናት ተመልክቷል።

በመድረኩ የተሳተፉ ባለሙያዎች በኮንፈረንሱ ያገኟቸውን አዳዲስ ዕውቀቶች፣ ቴክኖሎጂዎችና ፈጠራዎች በመጠቀም በመንገድ ግንባታ፣ ዲዛይን፣ ጥገና እና አስተዳደር ሥራዎች ላይ የላቀ ሙያዊ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ ተብሎ ይታመናል።

በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
7👍1
የጎንጂ-ቆለላ አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት 98.82 በመቶ አፈጻጸም ላይ ደረሰ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢመአ)፤ በጎንጂ ቆለላ ወረዳ የሚገነባው የቆሬ - አዲስ ዓለም የአስፋልት መንገድ ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት የ10.59 ኪሎ ሜትር ግንባታን በማጠናቀቅ 98.82 በመቶ አጠቃላይ አፈጻጸም ላይ ደርሷል። ከባህር ዳር ወደ ሞጣ በሚወስደው መንገድ ላይ ከምትገኘው ቆሬ ቀበሌ ተነስቶ ምስራቅ አቅጣጫ በመጓዝ ሂዳሴ መንደርን አቋርጦ አዲስ ዓለም ከተማ የሚገባው ይህ ፕሮጀክት፣ በአጠቃላይ 10.74 ኪሎ ሜትር ርዝመት አለው። ቀድሞ የነበረውን የጠጠር መንገድ ወደ አስፋልት ደረጃ የሚያሳድገው ይህ ግንባታ፣ የመንገዱ ስፋት በገጠር 10 ሜትር፣ በቀበሌ 12 ሜትር እንዲሁም በወረዳ 21.5 ሜትር ሆኖ እየተገነባ ይገኛል።
 
ግንባታው ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሲሆን በአካባቢው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ አዲስ ተስፋ ይዞ ይመጣል። በተለይም አርሶ አደሩ በአካባቢው በስፋት የሚያመርታቸውን እንደ ጤፍ፣ ሰሊጥ፣ በርበሬና ማሽላ ያሉ የግብርና ምርቶችን ያለምንም እንግልት በወቅቱ ወደ ገበያ ለማቅረብና የቱሪዝም መዳረሻዎችን በቀላሉ ለማገናኘት ጉልህ ሚና ይኖረዋል። ከዚህም በላይ ነዋሪዎች ቀድሞ ለመጓጓዝ ይወስድባቸው የነበረውን የጉዞ ጊዜ በአንድ ሰዓት ያህል በማሳጠር የዕለት ተዕለት ህይወታቸውን ያቀልላቸዋል።
 
ይህ ታላቅ ተስፋ የተሰነቀበት ፕሮጀክት ግንባታው እስከአሁን ድረስ ያጋጠሙና በሥራው ፍጥነት ላይ ጫና ያሳደሩ እንደ የጸጥታ፣ እና የወሰን ማስከበር ችግሮች እንዲሁም የነዳጅ እጥረት ተግዳሮቶችን ቀርፎ አሁን ያለበት ደረጃ ደርሷል። ሥራው እንዳይቋረጥ ከተለያዩ የመንግስት አካላት ጋር በቅንጅት በመሥራት፣ ለግንባታው የሚሆን ነዳጅ በቅድሚያ እንዲያገኝ በማድረግና ከፍተኛ ክትትል በማድረግ የተከለሰው የፕሮጀክቱ ማጠናቀቂያ ቀን በጥቅምት ወር 2019 ዓ.ም እንዲሆን ተደርጓል።
 
የበጀት ፍሰቱን በተመለከተ ቫትን ጨምሮ ከ333 ሚሊዮን ብር በላይ የተመደበለት ሲሆን፣ የስራ ተቋራጭነቱን ኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ሲያከናውነው የሃይዌይ ኢንጂነርስ ኤንድ ኮንሰልታንትስ ኃ/ተ/ግ/ማ ደግሞ የአማካሪነት ሚናውን እየተወጣ ይገኛል። ተቋራጩ አፈጻጸሙን እንዲያሻሽልና ቀሪ ሥራዎችን በተያዘው የበጀት ዓመት እንዲያጠናቅቅም በየደረጃው ከፍተኛ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገለት ነው።
 
በአሁኑ ወቅት የጠረጋ፣ የአፈር ቆረጣና ሙላት፣ የሰብ ቤዝ፣ የቤዝ ኮርስ ንጣፍ እንዲሁም ሙሉ የ10.74 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ንጣፍ ሥራዎች 100 በመቶ ሙሉ በሙሉ ተጠናቀዋል። በተጨማሪም የፍሳሽ ማስወገጃ (ድሬኔጅ) ሥራው 98.58 በመቶ ላይ የደረሰ ሲሆን፤ እንደ እግረኛ መንገድና የመንገድ ምልክቶች ያሉ ቀሪ ሥራዎችንም 50 በመቶ በማድረስ ፕሮጀክቱን ሙሉ በሙሉ ወደ ማጠናቀቂያው ምዕራፍ ለማሸጋገር የመጨረሻ ደረጃ ሥራዎች በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወኑ ይገኛሉ።

በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
3👍2