የጣርማበር - መለያያ ሰፌድ ሜዳ የጠጠር መንገድ ጥገና እየተካሄደለት ነው
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 21/2018 (ኢመአ)፦ ከጣርማበር መለያያ እስከ ሰፌድ ሜዳ ለሚዘልቀው የጠጠር መንገድ ጥገና እየተደረገለት ይገኛል። ጥገናው የሕዝቡን የትራንስፖርት ችግር ለማቃለል ታስቦ በትኩረት እየተከናወነ ያለ ሥራ ነው።
ይህ አጠቃላይ 118 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ ያለው የመንገድ ፕሮጀክት፣ ከዚህ ቀደም በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ አማካኝነት ግንባታው ሲካሄድ የነበረ ቢሆንም በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ሳይጠናቀቅ ተስተጓጉሎ ቆይቷል። በአሁኑ ወቅት ግን ለትራንስፖርት እጅግ አስቸጋሪ በሆነው 21.6 ኪሎ ሜትር የመንገዱ ክፍል ላይ ሰፊ የጥገና ሥራ እየተሠራ ይገኛል።
እስካሁንም በማሽን የቦይ ማጽዳት፣ የድንጋይ ሙሌት፣ በጭቃ የተበላሹ አካባቢዎችን የማስወገድ እንዲሁም በግሬደር የመንገዱን አካል የማስተካከልና የማጠናከር ሥራዎች ተከናውነዋል። የጥገና ሥራውን የኢመአ የዓለምገና መንገድ ጥገና ዲስትሪክት በራስ ኃይል እያከናወነው ሲሆን፣ የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ደግሞ የዓለምገና መንገድ ኔትወርክ ማኔጅመንት ቅርንጫፍ ቢሮ በበላይነት እየተከታተለው ነው።
የዚህ መንገድ መጠገን ማኅበረሰቡን ለእንግልትና ለትራንስፖርት መጉላላት ከዳረጉ ችግሮች የሚያላቅቅ ሲሆን፣ የትራፊክ አደጋን ከመቀነስና ጊዜን ከመቆጠብ ባሻገር የግብርና ምርቶችንና የተለያዩ ግብዓቶችን ወደ ገበያ ለማቅረብ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
በቀጣይም ከዚህ ቀደም ይስተዋሉ የነበሩ ማነቆዎችን በመቅረፍ ሙሉ የግንባታ ሒደቱን በቀጣዩ በጀት ዓመት ለማቀላጠፍ በትኩረት እየተሠራ ነው።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 21/2018 (ኢመአ)፦ ከጣርማበር መለያያ እስከ ሰፌድ ሜዳ ለሚዘልቀው የጠጠር መንገድ ጥገና እየተደረገለት ይገኛል። ጥገናው የሕዝቡን የትራንስፖርት ችግር ለማቃለል ታስቦ በትኩረት እየተከናወነ ያለ ሥራ ነው።
ይህ አጠቃላይ 118 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ ያለው የመንገድ ፕሮጀክት፣ ከዚህ ቀደም በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ አማካኝነት ግንባታው ሲካሄድ የነበረ ቢሆንም በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ሳይጠናቀቅ ተስተጓጉሎ ቆይቷል። በአሁኑ ወቅት ግን ለትራንስፖርት እጅግ አስቸጋሪ በሆነው 21.6 ኪሎ ሜትር የመንገዱ ክፍል ላይ ሰፊ የጥገና ሥራ እየተሠራ ይገኛል።
እስካሁንም በማሽን የቦይ ማጽዳት፣ የድንጋይ ሙሌት፣ በጭቃ የተበላሹ አካባቢዎችን የማስወገድ እንዲሁም በግሬደር የመንገዱን አካል የማስተካከልና የማጠናከር ሥራዎች ተከናውነዋል። የጥገና ሥራውን የኢመአ የዓለምገና መንገድ ጥገና ዲስትሪክት በራስ ኃይል እያከናወነው ሲሆን፣ የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ደግሞ የዓለምገና መንገድ ኔትወርክ ማኔጅመንት ቅርንጫፍ ቢሮ በበላይነት እየተከታተለው ነው።
የዚህ መንገድ መጠገን ማኅበረሰቡን ለእንግልትና ለትራንስፖርት መጉላላት ከዳረጉ ችግሮች የሚያላቅቅ ሲሆን፣ የትራፊክ አደጋን ከመቀነስና ጊዜን ከመቆጠብ ባሻገር የግብርና ምርቶችንና የተለያዩ ግብዓቶችን ወደ ገበያ ለማቅረብ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
በቀጣይም ከዚህ ቀደም ይስተዋሉ የነበሩ ማነቆዎችን በመቅረፍ ሙሉ የግንባታ ሒደቱን በቀጣዩ በጀት ዓመት ለማቀላጠፍ በትኩረት እየተሠራ ነው።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
👍6❤5
9ኛው የመንገድ ጥናትና ሥርፀት ኮንፈረንስ ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም(ኢመአ): የመንገድ ልማትና አስተዳደር ሥራዎችን በሳይንሳዊ ምርምርና በቴክኖሎጂ ለማገዝ የተዘጋጀው 9ኛው የመንገድ ጥናትና ሥርፀት ኮንፈረንስ ተካሂዷል።
በኮንፈረንሱ መክፈቻ ላይ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሀመድ አብዱራህማን፣ የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሂሩት ዮሐንስ እና የቀድሞው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዛይድ ወልደገብርኤልን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የዘርፉ ባለሙያዎችና ተመራማሪዎች ተገኝተዋል።
ባለፉት ስምንት ዓመታት የተካሄዱት ተከታታይ የምርምር ኮንፈረንሶች በሀገሪቱ የመንገድ ልማት ላይ ውጤታማ ለውጦችን ማምጣት ችለዋል። በአሁኑ 9ኛ ኮንፈረንስም በርካታ ጥናታዊ ጽሑፎች የቀረቡ ሲሆን፣ ተያያዥ አውደርዕይም ተካሂዷል። በጥናቶቹ በሌሎች አገራትና ፕሮጀክቶች ላይ ተተግብረው ውጤታማ የሆኑ የመንገድ ግንባታና አስተዳደር ልምዶች የተዳሰሱ ሲሆን፣ እነዚህ ተሞክሮዎች ለሀገሪቱ የመሠረተ ልማት ዕድገት አዳዲስ ዕድሎችን ይዘው ይመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በተለይም በአሁኑ ወቅት በዘርፉ ላይ ፈተና እየሆኑ ያሉትን እንደ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ እና የመንገድ መሸራተት (ናዳ) ያሉ ዋና ዋና ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ ተግባራዊ የመፍትሔ ሐሳቦች በኮንፈረንሱ ላይ በስፋት ተመክሮባቸዋል። ከተቀመጡት የመፍትሔ አቅጣጫዎች መካከልም ዘላቂነትን ለማረጋገጥ በሲሚንቶ ኮንክሪት በሚሠሩ መንገዶች ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሠራ በጥናት ተመልክቷል።
በመድረኩ የተሳተፉ ባለሙያዎች በኮንፈረንሱ ያገኟቸውን አዳዲስ ዕውቀቶች፣ ቴክኖሎጂዎችና ፈጠራዎች በመጠቀም በመንገድ ግንባታ፣ ዲዛይን፣ ጥገና እና አስተዳደር ሥራዎች ላይ የላቀ ሙያዊ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ ተብሎ ይታመናል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም(ኢመአ): የመንገድ ልማትና አስተዳደር ሥራዎችን በሳይንሳዊ ምርምርና በቴክኖሎጂ ለማገዝ የተዘጋጀው 9ኛው የመንገድ ጥናትና ሥርፀት ኮንፈረንስ ተካሂዷል።
በኮንፈረንሱ መክፈቻ ላይ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሀመድ አብዱራህማን፣ የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሂሩት ዮሐንስ እና የቀድሞው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዛይድ ወልደገብርኤልን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የዘርፉ ባለሙያዎችና ተመራማሪዎች ተገኝተዋል።
ባለፉት ስምንት ዓመታት የተካሄዱት ተከታታይ የምርምር ኮንፈረንሶች በሀገሪቱ የመንገድ ልማት ላይ ውጤታማ ለውጦችን ማምጣት ችለዋል። በአሁኑ 9ኛ ኮንፈረንስም በርካታ ጥናታዊ ጽሑፎች የቀረቡ ሲሆን፣ ተያያዥ አውደርዕይም ተካሂዷል። በጥናቶቹ በሌሎች አገራትና ፕሮጀክቶች ላይ ተተግብረው ውጤታማ የሆኑ የመንገድ ግንባታና አስተዳደር ልምዶች የተዳሰሱ ሲሆን፣ እነዚህ ተሞክሮዎች ለሀገሪቱ የመሠረተ ልማት ዕድገት አዳዲስ ዕድሎችን ይዘው ይመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በተለይም በአሁኑ ወቅት በዘርፉ ላይ ፈተና እየሆኑ ያሉትን እንደ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ እና የመንገድ መሸራተት (ናዳ) ያሉ ዋና ዋና ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ ተግባራዊ የመፍትሔ ሐሳቦች በኮንፈረንሱ ላይ በስፋት ተመክሮባቸዋል። ከተቀመጡት የመፍትሔ አቅጣጫዎች መካከልም ዘላቂነትን ለማረጋገጥ በሲሚንቶ ኮንክሪት በሚሠሩ መንገዶች ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሠራ በጥናት ተመልክቷል።
በመድረኩ የተሳተፉ ባለሙያዎች በኮንፈረንሱ ያገኟቸውን አዳዲስ ዕውቀቶች፣ ቴክኖሎጂዎችና ፈጠራዎች በመጠቀም በመንገድ ግንባታ፣ ዲዛይን፣ ጥገና እና አስተዳደር ሥራዎች ላይ የላቀ ሙያዊ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ ተብሎ ይታመናል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
❤7👍1