7 (ሰባት) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት የተሰጠ የሰበር ውሳኔ፤ መዝገብ ቁጥር 271726
ከዚህ በፊት በሰ/መ/ቁጥር 249795 ላይ “ሠራተኛዉ በተከታታይ ከ5 ቀናት በላይ ለሆነ ጊዜ ከሥራ ቢቀር እንኳ ከሥራ ለቀረበት ለእያንዳንዱ ቀን አሠሪዉ ማስጠንቀቂያ (Warning in Writing) ሳይሰጥ የሥራ ዉልን ለማቋረጥ እንደማይችል” ተገልጾ የተሰጠው የህግ ትርጉም ተለውጦ “የአዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀጽ 27(1)(ለ) ድንጋጌ ሠራተኛዉ በዚሁ አዋጅ ከተመለከቱ እረፍቶችና ልዩ ልዩ ፈቃዶች ዉጭ ለአምስት ተከታታይ የሥራ ቀናትና ከዚያ በላይ ለሆነ ጊዜ ከሥራ ላይ ከቀረ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ (Warning in Writing) መስጠት ሳያስፈልግ የሥራ ዉልን ያለ ማስጠንቀቂያ ማቋረጥ ይቻላል” በሚል ተተርጉሟል፡፡
የውሳኔውን ሙሉ ይዘት በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ከቴሌግራም ቻናላችን ማግኘት ይችላሉ፡፡
ከዚህ በፊት በሰ/መ/ቁጥር 249795 ላይ “ሠራተኛዉ በተከታታይ ከ5 ቀናት በላይ ለሆነ ጊዜ ከሥራ ቢቀር እንኳ ከሥራ ለቀረበት ለእያንዳንዱ ቀን አሠሪዉ ማስጠንቀቂያ (Warning in Writing) ሳይሰጥ የሥራ ዉልን ለማቋረጥ እንደማይችል” ተገልጾ የተሰጠው የህግ ትርጉም ተለውጦ “የአዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀጽ 27(1)(ለ) ድንጋጌ ሠራተኛዉ በዚሁ አዋጅ ከተመለከቱ እረፍቶችና ልዩ ልዩ ፈቃዶች ዉጭ ለአምስት ተከታታይ የሥራ ቀናትና ከዚያ በላይ ለሆነ ጊዜ ከሥራ ላይ ከቀረ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ (Warning in Writing) መስጠት ሳያስፈልግ የሥራ ዉልን ያለ ማስጠንቀቂያ ማቋረጥ ይቻላል” በሚል ተተርጉሟል፡፡
የውሳኔውን ሙሉ ይዘት በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ከቴሌግራም ቻናላችን ማግኘት ይችላሉ፡፡
👍14❤4
ከመንፈስ መጫን ምክንያት ዉጪ ስጦታን ለመቀነስ ወይም ለመሰረዝ የሚቀርብ ክስ ይርጋ 10 ዓመት መሆኑ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሰመቁ 232628 የሰጠዉ የህግ ትርጉም።
የፍ/ሕግ ቁጥር 2441(1) ይዘት ስጦታ እንዲቀነስ ወይም እንዲሰረዝ የሚቀርብ ጥያቄ፣ ስጦታው ከተደረገበት ቀን ጀምሮ እስከ ሁለት ዓመት ለዳኞች ካልቀረበ በስተቀር ዋጋ የለውም ይላል።
የክርክሩ አመጣጥ
አመልካች በጀርመን ሀገር የሚኖሩ ሲሆን፣ 1ኛ ተጠሪ በጀርመንኛ የተጻፈ ውክልናን ትርጉም በማዛባት የአመልካችን የውርስ ድርሻ ለ2ኛ ተጠሪ በስጦታ አስተላልፈዋል በማለት የስጦታ ውሉ እንዲፈርስ ክስ አቅርበዋል።
ተጠሪዎች በበኩላቸው አመልካች ቀደም ብለው ድርሻቸውን መልቀቃቸውን እና ክሱ በሁለት ዓመት ይርጋ ይታገዳል በማለት ተከራክረዋል።
የሥር ፍርድ ቤቶች ውሳኔ
የስጦታ ውልን ለመቃወም ያለው የይርጋ ጊዜ 2 ዓመት ነው በሚል ክሱን በይርጋ ውድቅ አድርገውታል።
የሰበር ሰሚ ችሎቱ ውሳኔው
ምንም እንኳን ይህ የሕግ ቁጥር (2441) በስጦታ ላይ የሁለት ዓመት ገደብ ቢያስቀምጥምየሰበር ችሎቱ
በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 2441 የተመለከተው የ2 ዓመት ይርጋ የሚያገለግለው በስጦታ ሰጪው ላይ "የመንፈስ መጫን" (Undue Influence) ተፈጥሮ የተደረገን ስጦታ ለማፍረስ በሚቀርብ ክስ ላይ ብቻ ነው።
ከመንፈስ መጫን ውጭ ባሉ ሌሎች ምክንያቶች (ለምሳሌ በውክልና ሥልጣን ያለአግባብ መጠቀም) የሚቀርብ የስጦታ ውል ለማፍረስ ወይም ለመቀነስ የሚቀርብ ክስ በሕግ ቁጥር 1845 መሠረት በ10 ዓመት የይርጋ ደንብ የሚመራ መሆኑን ችሎቱ ወስኗል።
👇👇
https://t.me/ethiolawtips
የፍ/ሕግ ቁጥር 2441(1) ይዘት ስጦታ እንዲቀነስ ወይም እንዲሰረዝ የሚቀርብ ጥያቄ፣ ስጦታው ከተደረገበት ቀን ጀምሮ እስከ ሁለት ዓመት ለዳኞች ካልቀረበ በስተቀር ዋጋ የለውም ይላል።
የክርክሩ አመጣጥ
አመልካች በጀርመን ሀገር የሚኖሩ ሲሆን፣ 1ኛ ተጠሪ በጀርመንኛ የተጻፈ ውክልናን ትርጉም በማዛባት የአመልካችን የውርስ ድርሻ ለ2ኛ ተጠሪ በስጦታ አስተላልፈዋል በማለት የስጦታ ውሉ እንዲፈርስ ክስ አቅርበዋል።
ተጠሪዎች በበኩላቸው አመልካች ቀደም ብለው ድርሻቸውን መልቀቃቸውን እና ክሱ በሁለት ዓመት ይርጋ ይታገዳል በማለት ተከራክረዋል።
የሥር ፍርድ ቤቶች ውሳኔ
የስጦታ ውልን ለመቃወም ያለው የይርጋ ጊዜ 2 ዓመት ነው በሚል ክሱን በይርጋ ውድቅ አድርገውታል።
የሰበር ሰሚ ችሎቱ ውሳኔው
ምንም እንኳን ይህ የሕግ ቁጥር (2441) በስጦታ ላይ የሁለት ዓመት ገደብ ቢያስቀምጥምየሰበር ችሎቱ
በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 2441 የተመለከተው የ2 ዓመት ይርጋ የሚያገለግለው በስጦታ ሰጪው ላይ "የመንፈስ መጫን" (Undue Influence) ተፈጥሮ የተደረገን ስጦታ ለማፍረስ በሚቀርብ ክስ ላይ ብቻ ነው።
ከመንፈስ መጫን ውጭ ባሉ ሌሎች ምክንያቶች (ለምሳሌ በውክልና ሥልጣን ያለአግባብ መጠቀም) የሚቀርብ የስጦታ ውል ለማፍረስ ወይም ለመቀነስ የሚቀርብ ክስ በሕግ ቁጥር 1845 መሠረት በ10 ዓመት የይርጋ ደንብ የሚመራ መሆኑን ችሎቱ ወስኗል።
👇👇
https://t.me/ethiolawtips
❤13👏2
Forwarded from Mulugeta Belay Law Office
አዲሱ የወንጀል ሥነ-ሥርዓት እና የማስረጃ ሕግ በኢትዮጵያ የፍትሕ ሥርዓት ላይ ከፍተኛ ለውጥ ይዞ የመጣ ሰነድ ነው። ይህ ሕግ ከረዥም ዓመታት በኋላ የቆየውን የ1954ቱን የሥነ-ሥርዓት ሕግ በመተካት፣ ዘመናዊና ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የሰብአዊ መብት መርሆችን ያካተተ ነው በትክክል ስራ ላይ የሚል ከሆነ በወንጀል የፍትህ ስረአቱ ላይ የሚያመጣው ለውጥ እጅግ የላቀ ነው ።
1. የሕጉ ዋና ዓላማ
* የፍትሕ ጥራትን ማሻሻል፡ የወንጀል ምርመራ እና የክስ ሂደት ግልጽ፣ ቀልጣፋ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት እንዲሆን ማድረግ።
* የተከሳሾችን መብት ማስጠበቅ፡ ሕገ-መንግሥታዊ የሆኑ የተከሳሽ መብቶች በተግባር እንዲተረጎሙ ማገዝ።
* የማስረጃ አቀራረብን ማዘመን፡ የቴክኖሎጂ ውጤቶች (Digital Evidence) በችሎት ፊት እንዴት ተቀባይነት እንደሚያገኙ ዝርዝር ሥርዓት መዘርጋት።
### 2. በሕጉ ውስጥ የተካተቱ አዳዲስ ለውጦች
* የማስረጃ ሕግ መካተት፡ ቀደም ሲል ራሱን የቻለ የማስረጃ ሕግ ባለመኖሩ ይፈጠሩ የነበሩ ክፍተቶችን በመሙላት፣ የወንጀል ሥነ-ሥርዓቱ እና የማስረጃ ሕጉ በአንድ ላይ እንዲጠቃለሉ ተደርጓል።
* የምርመራ ዘዴዎች፡ ሳይንሳዊ እና ዘመናዊ የምርመራ ዘዴዎች (ለምሳሌ የዲ.ኤን.ኤ/DNA ምርመራ እና የኤሌክትሮኒክስ መረጃዎች) አጠቃቀም
እና ሌሎችም
በቅርብ ቀን ሊያውቋቸው የሚገቡ ገሀዳዬች ላይ በቪዲዬ እንመለስበታለን።
1. የሕጉ ዋና ዓላማ
* የፍትሕ ጥራትን ማሻሻል፡ የወንጀል ምርመራ እና የክስ ሂደት ግልጽ፣ ቀልጣፋ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት እንዲሆን ማድረግ።
* የተከሳሾችን መብት ማስጠበቅ፡ ሕገ-መንግሥታዊ የሆኑ የተከሳሽ መብቶች በተግባር እንዲተረጎሙ ማገዝ።
* የማስረጃ አቀራረብን ማዘመን፡ የቴክኖሎጂ ውጤቶች (Digital Evidence) በችሎት ፊት እንዴት ተቀባይነት እንደሚያገኙ ዝርዝር ሥርዓት መዘርጋት።
### 2. በሕጉ ውስጥ የተካተቱ አዳዲስ ለውጦች
* የማስረጃ ሕግ መካተት፡ ቀደም ሲል ራሱን የቻለ የማስረጃ ሕግ ባለመኖሩ ይፈጠሩ የነበሩ ክፍተቶችን በመሙላት፣ የወንጀል ሥነ-ሥርዓቱ እና የማስረጃ ሕጉ በአንድ ላይ እንዲጠቃለሉ ተደርጓል።
* የምርመራ ዘዴዎች፡ ሳይንሳዊ እና ዘመናዊ የምርመራ ዘዴዎች (ለምሳሌ የዲ.ኤን.ኤ/DNA ምርመራ እና የኤሌክትሮኒክስ መረጃዎች) አጠቃቀም
እና ሌሎችም
በቅርብ ቀን ሊያውቋቸው የሚገቡ ገሀዳዬች ላይ በቪዲዬ እንመለስበታለን።
❤14👍2👌1
አዳዲስ የጊዜ ገደቦች
አዲሱ የወንጀል ሕግ ሥነ ሥርዓት እና ማስረጃ ዐዋጅ ቁጥር 1410/2018 ከሚደነቅባቸው አንዱ ነገር ብዙ አዳዲስ የወንጀል ፍትሕ ሂደት የጊዜ ገደቦችን መደንገጉ ነው:: ከእነዚህ መካከል ዋና ዋናዎቹን እንጠቃቅሳለን::👴🏽
(By Hailu Hasena (Lawyer)
1. የተጨማሪ የወንጀል ምርመራ ጊዜ ቀጠሮ በአንድ ጊዜ እስከ 14 ቀን ሊፈቀድ የሚቻል ሲሆን አጠቃላይ የምርመራ ጊዜ ግን #በማናቸውም ምክንያት ከ4 (አራት) ወር ሊበልጥ አይችልም: ተብሎ ትደንግጓል:: አንቀጽ 119(2)
ይሁንና ወንጀሎች ቀላል፣ መካከለኛ እና ከባድ ተብለው የተከፋፈሉ እንደመሆኑ አጠቃላይ የምርመራ ጊዜ ቀጠሮም በዚህ አግባብ ቢከፋፈል ጥሩ ነበር::👴🏽
2. የወንጀል ምርመራው ተጠናቆ በዐቃቤ ሕግ ክስ እስኪመሠርት ያለው የመሸጋገሪያ ጊዜ ቀጠሮ በመደበኛነት እስከ 20 ቀን ሆኖ በአጠቃላይ ግን ከ 34 ቀን ሊበልጥ አይችልም: ተብሎ ተደንግጓል:: አንቀጽ 119(4)፣ 197(1)፣ 198(2)
* የጊዜ ገደቡ የሚሠራው ተጠርጣሪው ተይዞ ያለ ከሆነ ብቻ ነው::
3. ፍርድ ቤት በዐቃቤ ሕግ የተመሠረተን መደበኛ ክስ አይቶ ውሳኔ የሚሰጥበት ጊዜ ተገድቧል:: አንቀጽ 232 (1), (2)::
በዚህ መሠረት:-
*ቀላል ክሶች=3 ወር (+45 ቀን) ማለትም በአጠቃላይ በ4 ወር ከ15 ቀን ውስጥ በፍ/ቤት ውሳኔ ማግኘት አለባቸው::
*መካከለኛ ክሶች =6 ወር (+3ወር) ማለትም በአጠቃላይ በ9 ወር ውስጥ በፍ/ቤት ውሳኔ ማግኘት አለባቸው::
*ከባድ ክሶች=12 ወር (+6ወር) ማለትም በአጠቃላይ በአንድ ዓመት ከ6 ወር ውስጥ በፍ/ቤት ውሳኔ ማግኘት አለባቸው::
~ያልገባኝ በእነዚህ የጊዜ ገደቦች ውስጥ ውሳኔ ካልተሰጠ ውጤቱ ምን ይሆናል የሚለው ነው—ዳኛው መዝገቡን ባለበት ይዘጋል ቢባል ጥሩ ነበር::🙄
4. በዋስትና በመስጠት፣ በመከልከል ወይም በተፈቀደ የዋስትና ዓይነት ወይም መጠን ላይ ይግባኝ ማቅረብ የሚቻለው ብይኑ በተሰጠ በ20 ቀን ውስጥ ነው::
*ይህ እንኳን ከጊዜ ገደብ አኳያ አዲስ አይደለም—ከነባሩ የወ/መ/ሥ/ሥ/ቁ. 75(1) ጋር ተመሳሳይ ነው::
ይሁንና የዋስትና ይግባኝ የቀረበለት ፍ/ቤት ይግባኙ ከቀረበበት ቀን ጀምሮ ባሉት 5 ቀናት ውስጥ በይግባኙ ላይ ውሳኔ መስጠት እንዳለበት ተደንግጓል:: አንቀጽ 152(1), 153
*ይሁንና በተለይ በቀድሞው የወ/መ/ሥ/ሥ/ቁ. 66 ሥር ማናቸውም ፍ/ቤት የዋስትና ጉዳይ ሲመጣለት በ48 ሰዓት ውስጥ መወሰን አለበት ከሚለው አኳያ ሲታይ አዲሱ ሕግ ያዘገየዋል::
5. ፍ/ቤት የቅጣት ውሳኔ የሚሰጥበት ጊዜ ተገድቧል:: ይህም ፍ/ቤት በተከሳሽ ላይ የጥፋተኛነት ፍርድ ከሰጠ በኋላ ግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየታቸውን አጠቃለው ካቀረቡበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ቀናት ውስጥ ፍ/ቤቱ የቅጣት ውሳኔ ማስተላለፍ አለበት ተብሎ ተደንግጓል:: አንቀጽ 301(1)
6. በዋናው የወንጀል ጉዳይ ላይ ይግባኝ የሚቀርብበት ጊዜ ፍርዱ፣ ውሳኔው፣ ብይኑ ወይም ትእዛዙ ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ ባሉት 60 ተከታታይ ቀናት ውስጥ እንዲሆን ተደንግጎአል:: አንቀጽ 332(4)
*ይህም በቀድሞው የወ/መ/ሥ/ሥ/ቁ. 187 (1)፣ (2) መሠረት ይግባኝ ለማለት የሚፈልግ አካል ለይግባኝ የመዝገብ ግልባጭ እንዲሰጠው ውሳኔው በተሰጠ 15 ቀን ውስጥ ለወሰነው ፍ/ቤት ማመልከቻ የማቅረብ እና እና የውሳኔ ግልባጩ በደረሰው 30 ቀን ውስጥ ይግባኝ የማከፈት በድምሩ የ45 ቀን አሳሳች አሠራርን ቀሪ የሚያደርግ ነው::
ስለሆነም የወንጀልና የፍ/ብሔር ይግባኝ አቀራረብ የጊዜ ገደብ ተመሳሳይ ሆነ ማለት ነው::
7. የሰበር አቤቱታ የሚቀርብበት ጊዜ የመጨረሻ ውሳኔ በተሰጠ 90 ተከታታይ ቀናት ውስጥ መሆን እንዳለበት ተደንግጎአል:: አንቀጽ 344(3)
*ያው በቀድሞው የወ/መ/ሕ/ሥ/ሥ ኮድ ውስጥ ባለመጠቀሱ ምክንያት ለፎርማሊቲ ያህል አዲስ ነው ብለን ጠቀስነው እንጂ በተግባር አዲስ አይደለም::
8. የፍ/ቤት መጥሪያ ከቀነ ቀጠሮ 10 ቀን በፊት እንዲደርስ ተደንግጓል:: ማለትም የዐ/ሕግ ክስ ማመልከቻ ፍ/ቤቱ ቀጠሮ ክስ ለማንበብ ከያዘው ቀን አሥር (10) ቀን ቀደም ብሎ ለተከሳሽ ሊደርሰው ይገባል:: አንቀጽ 214(3)
እንዲሁም የተከሳሽ የመከላከያ ማስረጃ ዝርዝር መግለጫ ፍ/ቤቱ የመከላከያ ማስረጃ ለመስማት ከቀጠረበት ቀን አስቀድሞ ከ10 ቀናት በፊት ለዐ/ሕግ ሊደርሰው ይገባል:: አንቀጽ 288(2)
9. የግል አቤቱታ (private prosecution) እንዲያቀርብ በዐ/ሕግ የተፈቀደለት ሰው ፈቃዱን ባገኘ 15 የሥራ ቀን ውስጥ ክሱን አዘጋጅቶ ሥልጣን ላለው ፍ/ቤት ማቅረብ አለበት።
በመሆኑም ይህ ጊዜ ካለፈ በኋላ ክስ ማቅረብ አይችልም:: አንቀጽ 200(3)
10. የግል የወንጀል ምርመራ አቤቱታ (complaint) የሚያቀርብ ሰው አቤቱታውን ባቀረበ 10 የሥራ ቀናት ውስጥ ቀርቦ ለመርማሪ ፖሊስ ካላስረዳ የግል አቤቱታው ይሠረዛል::
አቤቱታው ከተሠረዘ በኋላ በጉዳዩ ላይ ድጋሚ አቤቱታ ማቅረብ አይችልም: ተብሎ ተደንግጓል:: አንቀጽ 64(4)
11. በልዩ የወንጀል ምርመራ ዘዴ ማስረጃ እንዲሰበሰብ በፍ/ቤት የሚሰጥ ጊዜ በመደበኛነት ከሦስት ወር አይበልጥም:: ይሁንና በዚህ ዘዴ ማስረጃ እንዲሰበሰብ በፍ/ቤት የሚሰጥ ጊዜ በማንኛውም ምክንያት ከ12 ወራት ሊበልጥ አይችልም::
አንቀጽ 105 (1)፣ (2)፣ (3)
12. የጥፋተኛነት ድርፍር (Plea bargaing) ማድረጊያ ጊዜም ተገድቧል:: ማለትም ዐቅም በላይ የሆነ ምክንያት ካላጋጣመ በስተቀር ዐ/ሕግና ተከሳሹ (ጠበቃው) የጥፋተኛነት ድርድር ለማካሄድ ከተስማሙበት ቀን ጀምሮ 45 (አርባ አምስት) ቀናት ውስጥ ድርድሩ መጠናቀቅ አለበት፡፡
አንቀጽ 175(4)
*"ከዐቅም በላይ የሆነ ምክንያት ድርድሩ እስከመቼ እንደሚራዘም ቁርጥ ገደብ ቢቀመጥ ሸጋ ነበረ::
13. ተከሳሽ በሌለበት የተሰጠ ፍርድ ድጋሚ እንዲታይ የሚቀርብ አቤቱታ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ መቅረብ አለበት:: አንቀጽ 221
*ይህ ጊዜ ከቀድሞው የወ/መ/ሥ/ሥ/ቁ. 198 ጋር ተመሳሳይ ነው::
ይሁንና በቀድሞው ኮድ የአንድ ወሩ ጊዜ መቆጠር የሚጀምረው ተከሳሹ በሌለበት ጉዳዩ ታይቶ ፍርድ እንደተሰጠበት ካወቀበት ቀን አንሥቶ ሲሆን በአዲሱ ኮድ ግን በሌለበት ጉዳዩ ታይቶ ፍርድ እንዲሰጥበት ያደረገው ምክንያት ከቀረበት ወይም ከተወገደበት ቀን ጀምሮ ነው::
*በነገራችን ላይ ጉዳዩ ተከሳሽ በሌለበት በመታየት ሂደት ላይ ያለ (ፍርድ ያላገኘ) ከሆነ ተከሳሹ በማንኛውም ጊዜ ክርክሩን መቀላቀል ይችላል:: ማለትም ፍ/ቤቱ በሌለህበት ጉዳዩን ለማየት ብይን (Ex parte ruling) ስለሰጠሁ ወደ ክርክሩ መግባት አትችልም ሊለው አይችልም:: አንቀጽ 218(4)
* አደራ! ተከሳሽ በሌለበት (trial in absentia) የተሰጠ ፍርድን ድጋሚ ማየት [አንቀጽ 218-222] እና ተከሳሽ ባለበት (trial in praesentia) ታይቶ የተሰጠ ፍርድን ድጋሚ ማየት [አንቀጽ 353-357] የተለያዩ ፅንሰ ሀሳቦች ናቸውና አይቀላቀል::
በዚህ መሠረት ተከሳሽ ባለበት ታይቶ የተሰጠ ፍርድ ድጋሚ እንዲታይ (review of judgement) ለመጠየቅ የሚቀርብ አቤቱታ የመጨረሻው ፍርድ ከተሰጠ በኋላ በማንኛውም ጊዜ ፍርዱን ለሰጠው ፍ/ቤት ሊቀርብ ይችላል:: አንቀጽ 355(1)
ነገሮች እየተወሳሰቡ፣ ጽሑፉም እየረዘመ ስለሆነ እዚህ እንቋጨው::😌
አዲሱ የወንጀል ሕግ ሥነ ሥርዓት እና ማስረጃ ዐዋጅ ቁጥር 1410/2018 ከሚደነቅባቸው አንዱ ነገር ብዙ አዳዲስ የወንጀል ፍትሕ ሂደት የጊዜ ገደቦችን መደንገጉ ነው:: ከእነዚህ መካከል ዋና ዋናዎቹን እንጠቃቅሳለን::👴🏽
(By Hailu Hasena (Lawyer)
1. የተጨማሪ የወንጀል ምርመራ ጊዜ ቀጠሮ በአንድ ጊዜ እስከ 14 ቀን ሊፈቀድ የሚቻል ሲሆን አጠቃላይ የምርመራ ጊዜ ግን #በማናቸውም ምክንያት ከ4 (አራት) ወር ሊበልጥ አይችልም: ተብሎ ትደንግጓል:: አንቀጽ 119(2)
ይሁንና ወንጀሎች ቀላል፣ መካከለኛ እና ከባድ ተብለው የተከፋፈሉ እንደመሆኑ አጠቃላይ የምርመራ ጊዜ ቀጠሮም በዚህ አግባብ ቢከፋፈል ጥሩ ነበር::👴🏽
2. የወንጀል ምርመራው ተጠናቆ በዐቃቤ ሕግ ክስ እስኪመሠርት ያለው የመሸጋገሪያ ጊዜ ቀጠሮ በመደበኛነት እስከ 20 ቀን ሆኖ በአጠቃላይ ግን ከ 34 ቀን ሊበልጥ አይችልም: ተብሎ ተደንግጓል:: አንቀጽ 119(4)፣ 197(1)፣ 198(2)
* የጊዜ ገደቡ የሚሠራው ተጠርጣሪው ተይዞ ያለ ከሆነ ብቻ ነው::
3. ፍርድ ቤት በዐቃቤ ሕግ የተመሠረተን መደበኛ ክስ አይቶ ውሳኔ የሚሰጥበት ጊዜ ተገድቧል:: አንቀጽ 232 (1), (2)::
በዚህ መሠረት:-
*ቀላል ክሶች=3 ወር (+45 ቀን) ማለትም በአጠቃላይ በ4 ወር ከ15 ቀን ውስጥ በፍ/ቤት ውሳኔ ማግኘት አለባቸው::
*መካከለኛ ክሶች =6 ወር (+3ወር) ማለትም በአጠቃላይ በ9 ወር ውስጥ በፍ/ቤት ውሳኔ ማግኘት አለባቸው::
*ከባድ ክሶች=12 ወር (+6ወር) ማለትም በአጠቃላይ በአንድ ዓመት ከ6 ወር ውስጥ በፍ/ቤት ውሳኔ ማግኘት አለባቸው::
~ያልገባኝ በእነዚህ የጊዜ ገደቦች ውስጥ ውሳኔ ካልተሰጠ ውጤቱ ምን ይሆናል የሚለው ነው—ዳኛው መዝገቡን ባለበት ይዘጋል ቢባል ጥሩ ነበር::🙄
4. በዋስትና በመስጠት፣ በመከልከል ወይም በተፈቀደ የዋስትና ዓይነት ወይም መጠን ላይ ይግባኝ ማቅረብ የሚቻለው ብይኑ በተሰጠ በ20 ቀን ውስጥ ነው::
*ይህ እንኳን ከጊዜ ገደብ አኳያ አዲስ አይደለም—ከነባሩ የወ/መ/ሥ/ሥ/ቁ. 75(1) ጋር ተመሳሳይ ነው::
ይሁንና የዋስትና ይግባኝ የቀረበለት ፍ/ቤት ይግባኙ ከቀረበበት ቀን ጀምሮ ባሉት 5 ቀናት ውስጥ በይግባኙ ላይ ውሳኔ መስጠት እንዳለበት ተደንግጓል:: አንቀጽ 152(1), 153
*ይሁንና በተለይ በቀድሞው የወ/መ/ሥ/ሥ/ቁ. 66 ሥር ማናቸውም ፍ/ቤት የዋስትና ጉዳይ ሲመጣለት በ48 ሰዓት ውስጥ መወሰን አለበት ከሚለው አኳያ ሲታይ አዲሱ ሕግ ያዘገየዋል::
5. ፍ/ቤት የቅጣት ውሳኔ የሚሰጥበት ጊዜ ተገድቧል:: ይህም ፍ/ቤት በተከሳሽ ላይ የጥፋተኛነት ፍርድ ከሰጠ በኋላ ግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየታቸውን አጠቃለው ካቀረቡበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ቀናት ውስጥ ፍ/ቤቱ የቅጣት ውሳኔ ማስተላለፍ አለበት ተብሎ ተደንግጓል:: አንቀጽ 301(1)
6. በዋናው የወንጀል ጉዳይ ላይ ይግባኝ የሚቀርብበት ጊዜ ፍርዱ፣ ውሳኔው፣ ብይኑ ወይም ትእዛዙ ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ ባሉት 60 ተከታታይ ቀናት ውስጥ እንዲሆን ተደንግጎአል:: አንቀጽ 332(4)
*ይህም በቀድሞው የወ/መ/ሥ/ሥ/ቁ. 187 (1)፣ (2) መሠረት ይግባኝ ለማለት የሚፈልግ አካል ለይግባኝ የመዝገብ ግልባጭ እንዲሰጠው ውሳኔው በተሰጠ 15 ቀን ውስጥ ለወሰነው ፍ/ቤት ማመልከቻ የማቅረብ እና እና የውሳኔ ግልባጩ በደረሰው 30 ቀን ውስጥ ይግባኝ የማከፈት በድምሩ የ45 ቀን አሳሳች አሠራርን ቀሪ የሚያደርግ ነው::
ስለሆነም የወንጀልና የፍ/ብሔር ይግባኝ አቀራረብ የጊዜ ገደብ ተመሳሳይ ሆነ ማለት ነው::
7. የሰበር አቤቱታ የሚቀርብበት ጊዜ የመጨረሻ ውሳኔ በተሰጠ 90 ተከታታይ ቀናት ውስጥ መሆን እንዳለበት ተደንግጎአል:: አንቀጽ 344(3)
*ያው በቀድሞው የወ/መ/ሕ/ሥ/ሥ ኮድ ውስጥ ባለመጠቀሱ ምክንያት ለፎርማሊቲ ያህል አዲስ ነው ብለን ጠቀስነው እንጂ በተግባር አዲስ አይደለም::
8. የፍ/ቤት መጥሪያ ከቀነ ቀጠሮ 10 ቀን በፊት እንዲደርስ ተደንግጓል:: ማለትም የዐ/ሕግ ክስ ማመልከቻ ፍ/ቤቱ ቀጠሮ ክስ ለማንበብ ከያዘው ቀን አሥር (10) ቀን ቀደም ብሎ ለተከሳሽ ሊደርሰው ይገባል:: አንቀጽ 214(3)
እንዲሁም የተከሳሽ የመከላከያ ማስረጃ ዝርዝር መግለጫ ፍ/ቤቱ የመከላከያ ማስረጃ ለመስማት ከቀጠረበት ቀን አስቀድሞ ከ10 ቀናት በፊት ለዐ/ሕግ ሊደርሰው ይገባል:: አንቀጽ 288(2)
9. የግል አቤቱታ (private prosecution) እንዲያቀርብ በዐ/ሕግ የተፈቀደለት ሰው ፈቃዱን ባገኘ 15 የሥራ ቀን ውስጥ ክሱን አዘጋጅቶ ሥልጣን ላለው ፍ/ቤት ማቅረብ አለበት።
በመሆኑም ይህ ጊዜ ካለፈ በኋላ ክስ ማቅረብ አይችልም:: አንቀጽ 200(3)
10. የግል የወንጀል ምርመራ አቤቱታ (complaint) የሚያቀርብ ሰው አቤቱታውን ባቀረበ 10 የሥራ ቀናት ውስጥ ቀርቦ ለመርማሪ ፖሊስ ካላስረዳ የግል አቤቱታው ይሠረዛል::
አቤቱታው ከተሠረዘ በኋላ በጉዳዩ ላይ ድጋሚ አቤቱታ ማቅረብ አይችልም: ተብሎ ተደንግጓል:: አንቀጽ 64(4)
11. በልዩ የወንጀል ምርመራ ዘዴ ማስረጃ እንዲሰበሰብ በፍ/ቤት የሚሰጥ ጊዜ በመደበኛነት ከሦስት ወር አይበልጥም:: ይሁንና በዚህ ዘዴ ማስረጃ እንዲሰበሰብ በፍ/ቤት የሚሰጥ ጊዜ በማንኛውም ምክንያት ከ12 ወራት ሊበልጥ አይችልም::
አንቀጽ 105 (1)፣ (2)፣ (3)
12. የጥፋተኛነት ድርፍር (Plea bargaing) ማድረጊያ ጊዜም ተገድቧል:: ማለትም ዐቅም በላይ የሆነ ምክንያት ካላጋጣመ በስተቀር ዐ/ሕግና ተከሳሹ (ጠበቃው) የጥፋተኛነት ድርድር ለማካሄድ ከተስማሙበት ቀን ጀምሮ 45 (አርባ አምስት) ቀናት ውስጥ ድርድሩ መጠናቀቅ አለበት፡፡
አንቀጽ 175(4)
*"ከዐቅም በላይ የሆነ ምክንያት ድርድሩ እስከመቼ እንደሚራዘም ቁርጥ ገደብ ቢቀመጥ ሸጋ ነበረ::
13. ተከሳሽ በሌለበት የተሰጠ ፍርድ ድጋሚ እንዲታይ የሚቀርብ አቤቱታ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ መቅረብ አለበት:: አንቀጽ 221
*ይህ ጊዜ ከቀድሞው የወ/መ/ሥ/ሥ/ቁ. 198 ጋር ተመሳሳይ ነው::
ይሁንና በቀድሞው ኮድ የአንድ ወሩ ጊዜ መቆጠር የሚጀምረው ተከሳሹ በሌለበት ጉዳዩ ታይቶ ፍርድ እንደተሰጠበት ካወቀበት ቀን አንሥቶ ሲሆን በአዲሱ ኮድ ግን በሌለበት ጉዳዩ ታይቶ ፍርድ እንዲሰጥበት ያደረገው ምክንያት ከቀረበት ወይም ከተወገደበት ቀን ጀምሮ ነው::
*በነገራችን ላይ ጉዳዩ ተከሳሽ በሌለበት በመታየት ሂደት ላይ ያለ (ፍርድ ያላገኘ) ከሆነ ተከሳሹ በማንኛውም ጊዜ ክርክሩን መቀላቀል ይችላል:: ማለትም ፍ/ቤቱ በሌለህበት ጉዳዩን ለማየት ብይን (Ex parte ruling) ስለሰጠሁ ወደ ክርክሩ መግባት አትችልም ሊለው አይችልም:: አንቀጽ 218(4)
* አደራ! ተከሳሽ በሌለበት (trial in absentia) የተሰጠ ፍርድን ድጋሚ ማየት [አንቀጽ 218-222] እና ተከሳሽ ባለበት (trial in praesentia) ታይቶ የተሰጠ ፍርድን ድጋሚ ማየት [አንቀጽ 353-357] የተለያዩ ፅንሰ ሀሳቦች ናቸውና አይቀላቀል::
በዚህ መሠረት ተከሳሽ ባለበት ታይቶ የተሰጠ ፍርድ ድጋሚ እንዲታይ (review of judgement) ለመጠየቅ የሚቀርብ አቤቱታ የመጨረሻው ፍርድ ከተሰጠ በኋላ በማንኛውም ጊዜ ፍርዱን ለሰጠው ፍ/ቤት ሊቀርብ ይችላል:: አንቀጽ 355(1)
ነገሮች እየተወሳሰቡ፣ ጽሑፉም እየረዘመ ስለሆነ እዚህ እንቋጨው::😌
❤14👌2
ተሽከርካሪዎ እንዳይወረስ ከሰበር ሰሚ ችሎት የተሰጠ አዲስ የሕግ ትርጉም
*******
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 204922 በሰጠው አስገዳጅ ውሳኔ፤ አንድ ተሽከርካሪ የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን ለመደበቅ እንዲያስችል ተደርጎ አካሉ ተለውጦ (ሻግ ተበጅቶለት) ከተገኘ፣ ባለንብረቱ ድርጊቱን "አላውቅም" ቢል እንኳ ተሽከርካሪው ተወርሶ ለመንግስት ገቢ እንደሚሆን አጽንቷል።
ውሳኔው በጉምሩክ አዋጅ ቁጥር 859/2006 አንቀጽ 147 (3) ላይ የተመሰረተ ሲሆን፣ ሕጉ ኮንትሮባንድ የጫነ ተሽከርካሪ እንዲወረስ የሚያዝዘው በተሽከርካሪው አካል ላይ የዕቃ መደበቂያ ተሰርቶበት መገኘቱ ሲረጋገጥ ብቻ መሆኑን ይገልጻል።
በዚህ ረገድ ባለንብረቱ ስለ ድርጊቱ አስቀድሞ ማወቁ ወይም አለማወቁ በሕጉ ፊት ዋጋ የማይሰጠው በመሆኑ፣ ተሽከርካሪው የመንግስት ንብረት ሆኖ እንዲመዘገብ የተሰጠውን ውሳኔ ሰበር ሰሚ ችሎቱ አጽንቶታል።
ይህ ውሳኔ የመኪና ባለንብረቶች ለተሽከርካሪዎቻቸው ጥንቃቄና ክትትል እንዲያደርጉ የሚያሳስብ ጠንካራ የሕግ መልዕክት ያስተላልፋል።
*******
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 204922 በሰጠው አስገዳጅ ውሳኔ፤ አንድ ተሽከርካሪ የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን ለመደበቅ እንዲያስችል ተደርጎ አካሉ ተለውጦ (ሻግ ተበጅቶለት) ከተገኘ፣ ባለንብረቱ ድርጊቱን "አላውቅም" ቢል እንኳ ተሽከርካሪው ተወርሶ ለመንግስት ገቢ እንደሚሆን አጽንቷል።
ውሳኔው በጉምሩክ አዋጅ ቁጥር 859/2006 አንቀጽ 147 (3) ላይ የተመሰረተ ሲሆን፣ ሕጉ ኮንትሮባንድ የጫነ ተሽከርካሪ እንዲወረስ የሚያዝዘው በተሽከርካሪው አካል ላይ የዕቃ መደበቂያ ተሰርቶበት መገኘቱ ሲረጋገጥ ብቻ መሆኑን ይገልጻል።
በዚህ ረገድ ባለንብረቱ ስለ ድርጊቱ አስቀድሞ ማወቁ ወይም አለማወቁ በሕጉ ፊት ዋጋ የማይሰጠው በመሆኑ፣ ተሽከርካሪው የመንግስት ንብረት ሆኖ እንዲመዘገብ የተሰጠውን ውሳኔ ሰበር ሰሚ ችሎቱ አጽንቶታል።
ይህ ውሳኔ የመኪና ባለንብረቶች ለተሽከርካሪዎቻቸው ጥንቃቄና ክትትል እንዲያደርጉ የሚያሳስብ ጠንካራ የሕግ መልዕክት ያስተላልፋል።
❤14👍7
Forwarded from ስለ-ሕግ ⚖️ ABOUT-LAW
1776842465240.pdf
1.6 MB
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ
መንግሥት የገጠር መሬት
አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ
መንግሥት የገጠር መሬት
አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ
❤6
#የተዘጋ_መዝገብ_ለማንቀሳቀስ_አመልካች_በራሱ_ጉድለት_ወይም_ቸልተኝነት_ቀጠሮውን_ሳይከታተል_ቀርቶ_ካልሆነ_በቀር_ፍትህ_የማግኘትና_የመከራከር_መብት_ከግምት በማስገባት አመልካች የገጠመዉ እክል እንደ በቂ ምክንያት በመዉሰድ ለተጠሪ በቂ ወጪና ኪሳራ አስከፍሎ መዝገቡን ማንቀሳቀስ የሚገባ ስለመሆኑ።
በፌ/ብ/ሥ/ሥ/ሔ/ቁ.74 (2) ድንጋጌ መሰረት ‛በቂ ሆኖ የሚገመት እክል“ ምን እንደሆነ የተመከከተ ባይሆንም በቀጠሮ ለመቅረት ምን ምክንያት እንደሆነ አጠቃላይ ሁኔታዉን መመርመር የሚያስፈልግ ሆኖ፣ አመልካች በራሱ ጉድለት ወይም ቸልተኛነት ቀጠሮዉን ሳይከታተል ቀርቶ ካልሆነ በቀር፣ ፍትህ የማግኘትና የመከራከር መብት ከግምት በማስገባት አመልካች የገጠመዉ እክል እንደ በቂ ምክንያት በመዉሰድ ለተጠሪ ተገቢ ኪሳራና ወጪ በማስከፈል፣ የተዘጋዉ መዝገብ ተከፍቶ ክርክሩ እንዲሰማ መደረጉ አግባብ ስለመሆኑ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ 182136 በቅፅ 24 ላይ የተሰጠ አስገዳጅ ውሳኔ።
የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ.32 (2) እና 74 (1)
በፌ/ብ/ሥ/ሥ/ሔ/ቁ.74 (2) ድንጋጌ መሰረት ‛በቂ ሆኖ የሚገመት እክል“ ምን እንደሆነ የተመከከተ ባይሆንም በቀጠሮ ለመቅረት ምን ምክንያት እንደሆነ አጠቃላይ ሁኔታዉን መመርመር የሚያስፈልግ ሆኖ፣ አመልካች በራሱ ጉድለት ወይም ቸልተኛነት ቀጠሮዉን ሳይከታተል ቀርቶ ካልሆነ በቀር፣ ፍትህ የማግኘትና የመከራከር መብት ከግምት በማስገባት አመልካች የገጠመዉ እክል እንደ በቂ ምክንያት በመዉሰድ ለተጠሪ ተገቢ ኪሳራና ወጪ በማስከፈል፣ የተዘጋዉ መዝገብ ተከፍቶ ክርክሩ እንዲሰማ መደረጉ አግባብ ስለመሆኑ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ 182136 በቅፅ 24 ላይ የተሰጠ አስገዳጅ ውሳኔ።
የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ.32 (2) እና 74 (1)
❤9
አንድ የመንግስት ሰራተኛ በተከሰሰበት የዲስፕሊን ጥፋት ምክንያት ከስራ እንዲሰናበት ካልተወሰነበት በስተቀር ከስራ በታገደበት ወቅት ሳይከፈለው የቀረው ደመወዝ የሚከፈለው ስለመሆኑ ። ቅፅ 24 መዝገብ ቁጥር 161880
በአዲሱ የፌዴራል መንግስት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 1353/2024 (2025) መሰረት፡
የመንግስት ሰራተኛ በዲስፕሊን ጥፋት ምክንያት ከስራ ሲታገድ፣ በእግዱ ጊዜ ደመወዙ ሊቆም ይችላል።
በመጨረሻ ከስራ እንዲሰናበት ውሳኔ ካልተወሰነበት (ወይም ውሳኔው ካልተረጋገጠ)፣ በእግዱ ወቅት ያልተከፈለው ሙሉ ደመወዝ ያለ ወለድ መከፈል አለበት።
በአዲሱ የፌዴራል መንግስት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 1353/2024 (2025) መሰረት፡
የመንግስት ሰራተኛ በዲስፕሊን ጥፋት ምክንያት ከስራ ሲታገድ፣ በእግዱ ጊዜ ደመወዙ ሊቆም ይችላል።
በመጨረሻ ከስራ እንዲሰናበት ውሳኔ ካልተወሰነበት (ወይም ውሳኔው ካልተረጋገጠ)፣ በእግዱ ወቅት ያልተከፈለው ሙሉ ደመወዝ ያለ ወለድ መከፈል አለበት።
👍13❤2
በዋስትና ከመፈታት አኳያ አዲሱ የወንጀል ሥነ ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ ያመጣቸው አዳዲስ ነገሮች መካከል:-
By Hailu Hasena (Legal Advocate)
1. "ያለ ዋስትና መለቀቅ (Release without bail/unconditional release)" የተሰኘ አዲስ ድንጋጌ አምጥቷል::
በዚህ ድንጋጌ መሠረት ተጠርጣሪው የተጠረጠበትን ወንጀል ስለመፈጸሙ ወይም የተባለው ወንጀል ስለመፈጸሙ አጠራጣሪ (doubtful) በሆነ ጊዜ የወንጀል ምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ፍ/ቤትም ሆነ ቀዳሚ ምርመራ አድራጊ ፍ/ቤት ተጠርጣሪውን ያለ ዋስትና እንዲሁ እንዲለቁት ይገደዳሉ:: አንቀጽ 118(4)፣ 137(2)
*በቀድሞው የወ/መሕ/ሥ/ሥ/ቁ. 59(1) እና 93 መሠረት የጊዜ ቀጠሮ እና የቀዳሚ ምርመራ ፍ/ቤቶች ተጠርጣሪው ወንጀል ስለመፈጸሙም ሆነ ወንጀሉ ራሱ ስለመፈጸሙ ቢጠራጠሩም ስንኳ ተጠርጣሪውን የግድ ዋስትና እንዲያስይዝ ወይም በማረፊያ ቤት እንዲቆይ እንዲያዙ ይገደዱ ነበር:: በአዲሱ መድብለ ሕግ ያ አሠራር ተሽሯል::
*ይህ ድንጋጌ በተለይ ለሚታፈሱ ወይም በመመሳጠር በፍ/ብሔር ወይም ወንጀል ባልሆነ ጉዳይ ለሚታሰሩ ሰዎች ይህ ትልቅ የሕግ ጥበቃ የሚያደርግ ነው::
*ስለዚህ የተያዙ ሰዎች የሚለቀቁባቸው መንገዶች እነዚህ ናቸው—ያለ ዋስትና መለቀቅ፣ ያለ ገደብ መለቀቅ፣ በራስ ዋስትና መለቀቅ፣ በንብረት ዋስትና መለቀቅ፣ በሰው ዋስትና፣ በገንዘብ ዋስትና መለቀቅ፣ በተጨማሪ ዋስትና መለቀቅ::
*ስለሆነም ከእንግዲህ የጠበቆች ሥራ የታሰረን ሰው በዋስትና ማስፈታት ብቻ ሳይሆን ያለ ዋስትና ማስፈታትንም ይጨምራል::
*Note: በፍ/ቤት መደበኛ ክስ (charge) የተከፈተ ከሆነ ያለ ዋስትና የመለቀቅ ጉዳይ አይነሣም::
2. በሕግ ዋስትና የሚያስከለክሉ ወንጀሎች (non-bailable crimes)
* በሞት የሚያስቀጡ ወንጀሎች፣ ወይም
* በ ≥15 ዓመት ጽኑ እሥራት የሚያስቀጡ ሰው የሞተባቸው ወንጀሎች ብቻ እንዲሆኑ የተደነገገ ስለሆነ በእንደዚህ ዓይነት ወንጀሎች ውጭ ያሉ ወንጀሎች በሙሉ በሕግ ዋስትና የማያስከለክሉ ወንጀሎች (bailable crimes) ሆነዋል:: አንቀጽ 138(2,3)
ስለሆነም:-
➡️ስለሆነም በሕግ ዋስትናን በማይከለከልባቸው ወንጀሎች በመሉ ተጠርጣሪዎች/ተከሳሾች በዋስትና የመለቀቅ መብት አለው::
➡️በዕድሜ ልክ ወይም የጽኑ እሥራት ጣሪያ በሆነው በ25 ጽኑ እሥራት የሚያስቀጣ ወንጀል ብቻውን ዋስትናን አያስከለክልም::
➡️በማንኛውም የሙስና ወንጀል የተጠረጠረ/የተከሰሰ ሰው በሕግ ዋስትናን አይከለከልም—all corruption crimes have become bailable.
ከዚህ ቀደም በዐዋጅ ቁ. 434/1997 (በዐዋጅ ቁ. 882/2007 እንደተሻሻለ) አንቀጽ 4(1) መሠረት "ከ10 ዓመት በላይ በሚያስቀጣ የሙስና ወንጀል የተጠረጠረ ወይም የተከሰሰ ሰው በዋስትና አይለቀቅም በማለት ከ10 ዓመት በላይ የሚያስቀጡትን ለይቶ non-bailable corruption crimes ተደርጎ የነበረው ድንጋጌ ቀሪ (abolished) ተደርጎአል::
➡️በአደገኛ ቦዘኔነት ዐዋጅ ቁጥር 384/96 አንቀጽ 6(3) "በአደገኛ ቦዘኔነት ተጠርጥሮ የተያዘ ሰው በዋስትና አይለቀቅም:" ተብሎ በወንጀል ዓይነት ዋስትና ይከለከል የነበረው (categorical bail denial) ዘፈቀዳዊ ነው ተብሎ በዚህ ዐዋጅ ተሽሮአል::
➡️በሕግ ዋስትና የማያስከለክሉ ወንጀሎችን (bailable crimes) አስመልክቶ ዋስትና መብት (right) ሲሆን ዋስትና ሊከለከልም ሊፈቀድም የሚችለው በዳኞች ፍቅድ ሥልጣን (judicial discretion) ነው::
ፍቅድ ሥልጣኑ የሚመራባቸው መርኆዎችም ደግሞ "ዳኛው ተጠርጣሪውን/ተከሳሹን በዋስትና ይለቃል የሚል ግምት (presumption of release on bail) ይወሰዳል:"፤ "ዋስትናን በሁኔታ የሚያስከለክሉ ሁኔታዎችም አይኖሩም: ተብሎ ይገመታል::"
"ዋስትናን ለመከልከል የሚያበቁ ልዩ ሁኔታዎች በጠባቡ እና ለተከሳሽ/ተጠርጣሪ በሚጠቅም መልኩ ይተረጎማሉ:" የሚሉ ናቸው—ከተመድ የሰብኣዊ መብቶች የዋስትና መብት ትርጉም አኳያ::
ለምሳሌ:- ተጠርጣሪው በዋስ ቢወጣ ሌላ ወንጀል ይፈጽማል ወይም ማስረጃ ያጠፋል ወይም በተፈለገ ጊዜ አይቀርብም ወይም ቋም አድራሻ የለውም ወይም መውጣቱ ለኅ/ሰቡ ደኅንነት ያሰጋል ወይም የዋስትና ግዴታውን አይወጣም ወዘተ. የሚል ግምት አይያዝም::
ስለሆነም መርማሪ ፖሊስ ወይም ዐቃቤ ሕግ እነዚህን መርኀዊ ግምቶች ለማስተባበልና ለመሠረታዊ መብቶች (የነጻነት መብት፣ ንጹሕ ሆኖ የመገመት መብት) የሥነ ሥርዓታዊ ጥበቃ የሆነውን የዋስትና መብት ለመቃወም ሕጋዊ፣ በቂ እና አሳማኝ ምክንያት ያለ መሆኑን በቂ ማስረጃ በማቅረብ ማስረዳት ይኖርበታል::
3. የድኅረ ጥፋተኝነት ፍርድ ዋስትና (Post-conviction bail) የተሰኘ አዲስ ድንጋጌ አምጥቷል::
አንቀጽ 301(2)
ይህ ድንጋጌ ተከሳሹ በተከሰሰበት ወንጀል ጥፋተኛ ነህ ተብሎ ከተፈረደበት በኋላ የቅጣት ውሳኔ እስኪተላለፍበት ድረስ ባለው ጊዜ በዋስትና እንዲቆይ የሚያደርግ ነው::
ይሁንና ይህ ዋስትና የሚሠራው ወንጀሉ በመቀጮ ብቻ የሚያስቀጣ ሲሆን ነው::
እንደሚታወቀው በነባሩ የወ/ሕ/ሥ/ሥ መሠረት ዳኞች የፈረዱበትን ማንኛውንም ሰው ቅጣቱ እስኪወሰን ድረስ 'ታስሮ' እንዲቆይ ያዙ ነበር—በጣም ጥቂት ሰብኣዊነት ላይ የተመሠረተ ልዩነት ቢኖርም::
ለዚህ እንደ ምክንያት ይጠቀስ የነበረው የዋስትና መብት ንጹሕ ሆኖ ከመገመት መርኅ ጋር ብቻ የተቆራኘ ስለሆነ ተከሳሹ ጥፋተኛ ሲባል መብቱም ዐብሮ ቀሪ ይሆናል፣ ጥፋተኛ ከተባለ በኋላ በዋስትና ቢወጣ ሊጣልበት የሚችለውን ቅጣት ፈርቶ ላይቀርብ ስለሚችል የሚጣለው ቅጣት አፈጻጸም ችግር እንዳይገጥመው የሚል ግምት በመያዝ ነበር::
ይሁንና ሁለቱም ምክንያቶች የተሳሳቱ እና የሕግ ፍልስና መሠረት የሌላቸው ስለሆኑ በሥሡ ለማረም ተሞክሯል::
*ለምሳሌ በፌስታል ዐዋጅ ቁ. 1383/2017 አንቀጽ 25(1/ሀ) ሥር ፌስታል በመጠቀም ወይም ለመጠቀም ይዞ በመገኘት ወንጀል ተከሶ የጥፋተኛነት ፍርድ የተሰጠበት ተከሳሽ የቅጣት ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ በማረፊያ/በማቆያ ቤት እንዲቆይ አዲሱ ሕግ አይፈቅድም
By Hailu Hasena (Legal Advocate)
1. "ያለ ዋስትና መለቀቅ (Release without bail/unconditional release)" የተሰኘ አዲስ ድንጋጌ አምጥቷል::
በዚህ ድንጋጌ መሠረት ተጠርጣሪው የተጠረጠበትን ወንጀል ስለመፈጸሙ ወይም የተባለው ወንጀል ስለመፈጸሙ አጠራጣሪ (doubtful) በሆነ ጊዜ የወንጀል ምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ፍ/ቤትም ሆነ ቀዳሚ ምርመራ አድራጊ ፍ/ቤት ተጠርጣሪውን ያለ ዋስትና እንዲሁ እንዲለቁት ይገደዳሉ:: አንቀጽ 118(4)፣ 137(2)
*በቀድሞው የወ/መሕ/ሥ/ሥ/ቁ. 59(1) እና 93 መሠረት የጊዜ ቀጠሮ እና የቀዳሚ ምርመራ ፍ/ቤቶች ተጠርጣሪው ወንጀል ስለመፈጸሙም ሆነ ወንጀሉ ራሱ ስለመፈጸሙ ቢጠራጠሩም ስንኳ ተጠርጣሪውን የግድ ዋስትና እንዲያስይዝ ወይም በማረፊያ ቤት እንዲቆይ እንዲያዙ ይገደዱ ነበር:: በአዲሱ መድብለ ሕግ ያ አሠራር ተሽሯል::
*ይህ ድንጋጌ በተለይ ለሚታፈሱ ወይም በመመሳጠር በፍ/ብሔር ወይም ወንጀል ባልሆነ ጉዳይ ለሚታሰሩ ሰዎች ይህ ትልቅ የሕግ ጥበቃ የሚያደርግ ነው::
*ስለዚህ የተያዙ ሰዎች የሚለቀቁባቸው መንገዶች እነዚህ ናቸው—ያለ ዋስትና መለቀቅ፣ ያለ ገደብ መለቀቅ፣ በራስ ዋስትና መለቀቅ፣ በንብረት ዋስትና መለቀቅ፣ በሰው ዋስትና፣ በገንዘብ ዋስትና መለቀቅ፣ በተጨማሪ ዋስትና መለቀቅ::
*ስለሆነም ከእንግዲህ የጠበቆች ሥራ የታሰረን ሰው በዋስትና ማስፈታት ብቻ ሳይሆን ያለ ዋስትና ማስፈታትንም ይጨምራል::
*Note: በፍ/ቤት መደበኛ ክስ (charge) የተከፈተ ከሆነ ያለ ዋስትና የመለቀቅ ጉዳይ አይነሣም::
2. በሕግ ዋስትና የሚያስከለክሉ ወንጀሎች (non-bailable crimes)
* በሞት የሚያስቀጡ ወንጀሎች፣ ወይም
* በ ≥15 ዓመት ጽኑ እሥራት የሚያስቀጡ ሰው የሞተባቸው ወንጀሎች ብቻ እንዲሆኑ የተደነገገ ስለሆነ በእንደዚህ ዓይነት ወንጀሎች ውጭ ያሉ ወንጀሎች በሙሉ በሕግ ዋስትና የማያስከለክሉ ወንጀሎች (bailable crimes) ሆነዋል:: አንቀጽ 138(2,3)
ስለሆነም:-
➡️ስለሆነም በሕግ ዋስትናን በማይከለከልባቸው ወንጀሎች በመሉ ተጠርጣሪዎች/ተከሳሾች በዋስትና የመለቀቅ መብት አለው::
➡️በዕድሜ ልክ ወይም የጽኑ እሥራት ጣሪያ በሆነው በ25 ጽኑ እሥራት የሚያስቀጣ ወንጀል ብቻውን ዋስትናን አያስከለክልም::
➡️በማንኛውም የሙስና ወንጀል የተጠረጠረ/የተከሰሰ ሰው በሕግ ዋስትናን አይከለከልም—all corruption crimes have become bailable.
ከዚህ ቀደም በዐዋጅ ቁ. 434/1997 (በዐዋጅ ቁ. 882/2007 እንደተሻሻለ) አንቀጽ 4(1) መሠረት "ከ10 ዓመት በላይ በሚያስቀጣ የሙስና ወንጀል የተጠረጠረ ወይም የተከሰሰ ሰው በዋስትና አይለቀቅም በማለት ከ10 ዓመት በላይ የሚያስቀጡትን ለይቶ non-bailable corruption crimes ተደርጎ የነበረው ድንጋጌ ቀሪ (abolished) ተደርጎአል::
➡️በአደገኛ ቦዘኔነት ዐዋጅ ቁጥር 384/96 አንቀጽ 6(3) "በአደገኛ ቦዘኔነት ተጠርጥሮ የተያዘ ሰው በዋስትና አይለቀቅም:" ተብሎ በወንጀል ዓይነት ዋስትና ይከለከል የነበረው (categorical bail denial) ዘፈቀዳዊ ነው ተብሎ በዚህ ዐዋጅ ተሽሮአል::
➡️በሕግ ዋስትና የማያስከለክሉ ወንጀሎችን (bailable crimes) አስመልክቶ ዋስትና መብት (right) ሲሆን ዋስትና ሊከለከልም ሊፈቀድም የሚችለው በዳኞች ፍቅድ ሥልጣን (judicial discretion) ነው::
ፍቅድ ሥልጣኑ የሚመራባቸው መርኆዎችም ደግሞ "ዳኛው ተጠርጣሪውን/ተከሳሹን በዋስትና ይለቃል የሚል ግምት (presumption of release on bail) ይወሰዳል:"፤ "ዋስትናን በሁኔታ የሚያስከለክሉ ሁኔታዎችም አይኖሩም: ተብሎ ይገመታል::"
"ዋስትናን ለመከልከል የሚያበቁ ልዩ ሁኔታዎች በጠባቡ እና ለተከሳሽ/ተጠርጣሪ በሚጠቅም መልኩ ይተረጎማሉ:" የሚሉ ናቸው—ከተመድ የሰብኣዊ መብቶች የዋስትና መብት ትርጉም አኳያ::
ለምሳሌ:- ተጠርጣሪው በዋስ ቢወጣ ሌላ ወንጀል ይፈጽማል ወይም ማስረጃ ያጠፋል ወይም በተፈለገ ጊዜ አይቀርብም ወይም ቋም አድራሻ የለውም ወይም መውጣቱ ለኅ/ሰቡ ደኅንነት ያሰጋል ወይም የዋስትና ግዴታውን አይወጣም ወዘተ. የሚል ግምት አይያዝም::
ስለሆነም መርማሪ ፖሊስ ወይም ዐቃቤ ሕግ እነዚህን መርኀዊ ግምቶች ለማስተባበልና ለመሠረታዊ መብቶች (የነጻነት መብት፣ ንጹሕ ሆኖ የመገመት መብት) የሥነ ሥርዓታዊ ጥበቃ የሆነውን የዋስትና መብት ለመቃወም ሕጋዊ፣ በቂ እና አሳማኝ ምክንያት ያለ መሆኑን በቂ ማስረጃ በማቅረብ ማስረዳት ይኖርበታል::
3. የድኅረ ጥፋተኝነት ፍርድ ዋስትና (Post-conviction bail) የተሰኘ አዲስ ድንጋጌ አምጥቷል::
አንቀጽ 301(2)
ይህ ድንጋጌ ተከሳሹ በተከሰሰበት ወንጀል ጥፋተኛ ነህ ተብሎ ከተፈረደበት በኋላ የቅጣት ውሳኔ እስኪተላለፍበት ድረስ ባለው ጊዜ በዋስትና እንዲቆይ የሚያደርግ ነው::
ይሁንና ይህ ዋስትና የሚሠራው ወንጀሉ በመቀጮ ብቻ የሚያስቀጣ ሲሆን ነው::
እንደሚታወቀው በነባሩ የወ/ሕ/ሥ/ሥ መሠረት ዳኞች የፈረዱበትን ማንኛውንም ሰው ቅጣቱ እስኪወሰን ድረስ 'ታስሮ' እንዲቆይ ያዙ ነበር—በጣም ጥቂት ሰብኣዊነት ላይ የተመሠረተ ልዩነት ቢኖርም::
ለዚህ እንደ ምክንያት ይጠቀስ የነበረው የዋስትና መብት ንጹሕ ሆኖ ከመገመት መርኅ ጋር ብቻ የተቆራኘ ስለሆነ ተከሳሹ ጥፋተኛ ሲባል መብቱም ዐብሮ ቀሪ ይሆናል፣ ጥፋተኛ ከተባለ በኋላ በዋስትና ቢወጣ ሊጣልበት የሚችለውን ቅጣት ፈርቶ ላይቀርብ ስለሚችል የሚጣለው ቅጣት አፈጻጸም ችግር እንዳይገጥመው የሚል ግምት በመያዝ ነበር::
ይሁንና ሁለቱም ምክንያቶች የተሳሳቱ እና የሕግ ፍልስና መሠረት የሌላቸው ስለሆኑ በሥሡ ለማረም ተሞክሯል::
*ለምሳሌ በፌስታል ዐዋጅ ቁ. 1383/2017 አንቀጽ 25(1/ሀ) ሥር ፌስታል በመጠቀም ወይም ለመጠቀም ይዞ በመገኘት ወንጀል ተከሶ የጥፋተኛነት ፍርድ የተሰጠበት ተከሳሽ የቅጣት ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ በማረፊያ/በማቆያ ቤት እንዲቆይ አዲሱ ሕግ አይፈቅድም
❤17👏3