ለጁምኣችን!
💚
በመካ ከተማ አንድ ሰው ግራ ቀኙን እየቃኘ በመንገድ ሲያልፍ አንዲት አሮጊት እርጅና ባጎበጠው እድሜ ባሰለላቸው እጆቻቸው እየተንቀጠቀጠቀጡ ምግብ የሚያበስሉበትን እንጨት ተሸክመው ወደቤታቸው ሊሄድ ሲያጣጥሩ ይመለከታል። በአሮጊቷ ተግባር ልቡ የተነካው ይህ ሰውም በቀስታ ወደሴትየዋ ተጠግቶ « ቤትዎን ያሳዩኝ እኔ ተሸክሜ አደርስልዎታለሁ» አላቸው።
የሴትየዋ ቤት እጅግ እሩቅ ከመሆኑ ባሻገር ጸሀዩ ሲጠብሰው የዋለው አሸዋ ልክ በጋለ ፍም ላይ የመራመድ ያክል እግርን ክፉኛ ይለበልብ ነበር! ጸሀዩዋም መካ ብቻ ጓዟን ጠቅላ የሰፈረች ይመስል እንደእሳት ትፋጃለች። በነፋሱ እየተንሳፈፈ የሚመጣው የአሸዋ ብናኝም ፊትን በሀይል ይጋረፋል! እንግዲህ ይህን ፈተና ችሎ ነው ሰውየው የአሮጊቷን የደረቁ እንጨቶች ለመሸከም የወሰነው
በሰውዬው ድርጊት እየተገረሙና እየተደነቁ ቤታቸው የደረሱት ምስኪኗ አሮጊትም መልካሙን ሰውዬ ትኩር ብለው እየተመለከቱ እንዲህ አሉት ..
«ልጄ ሆይ እንዲያው ባሮጊት አንደበቴ እመርቅሀለሁ እንጂ ላደረግህልኝ ነገር መካሻ ይሆን ዘንድ የምሰጥህ አንዳች የሌለኝ ምስኪን ደሀ ነኝ ልጄ እባክህ ከሰማኸኝ አንድ ምክር ልለግስህ። ወደህዝቦችህ ወደመካ ስትመለስ እዚያ አንድ ነብይ ነኝ የሚል ሙሀመድ የሚሉት ደጋሚ ሰው አለ። በፍጹም እሱን እንዳትከተል እንዳታምነውም!» አሉት።
ሰውዬውም ረጋ ብሎ «ለምን?» ብሎ ጠየቀ!
አሮጊቷም «ልጄ እርሱ መጥፎ ስነምባር ነው ያለው ሲሉ ሰምቻለሁ» ብለው መለሱ።ሰውዬው በሴትየዋ ንግግር ተገርሞ «እኔስ ሙሀመድ ብሆን?» አላቸው። ሴትየዋም የሰሙት ነገር በጣም አስገርማቸው ለካስ ይህ ደግ ሰው ራሳቸው ነብዩ ሙሀመድ (ሰ.አ.ወ) ነበሩ። አስተውሉ ... ነብዩ ለአሮጊቷ ቸርነትን ሲያደርጉ ሀይማኖታቸውን ፈፅሞ አልጠየቁም። ፍቅር የሀይማኖትን ድንበር፣ የዘርና የጎሳን አጥር እንደሚያልፍ ያውቁ ነበርና። ስብከት ያልሰበረውን ልብና ትምህርት ያላንበረከከውን ማንነት ፍቅር ብቻ ትህትናና በጎ ምግባር ብቻ ያንበረክከዋል!
ያማረ ጁምኣ!💚
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta
💚
በመካ ከተማ አንድ ሰው ግራ ቀኙን እየቃኘ በመንገድ ሲያልፍ አንዲት አሮጊት እርጅና ባጎበጠው እድሜ ባሰለላቸው እጆቻቸው እየተንቀጠቀጠቀጡ ምግብ የሚያበስሉበትን እንጨት ተሸክመው ወደቤታቸው ሊሄድ ሲያጣጥሩ ይመለከታል። በአሮጊቷ ተግባር ልቡ የተነካው ይህ ሰውም በቀስታ ወደሴትየዋ ተጠግቶ « ቤትዎን ያሳዩኝ እኔ ተሸክሜ አደርስልዎታለሁ» አላቸው።
የሴትየዋ ቤት እጅግ እሩቅ ከመሆኑ ባሻገር ጸሀዩ ሲጠብሰው የዋለው አሸዋ ልክ በጋለ ፍም ላይ የመራመድ ያክል እግርን ክፉኛ ይለበልብ ነበር! ጸሀዩዋም መካ ብቻ ጓዟን ጠቅላ የሰፈረች ይመስል እንደእሳት ትፋጃለች። በነፋሱ እየተንሳፈፈ የሚመጣው የአሸዋ ብናኝም ፊትን በሀይል ይጋረፋል! እንግዲህ ይህን ፈተና ችሎ ነው ሰውየው የአሮጊቷን የደረቁ እንጨቶች ለመሸከም የወሰነው
በሰውዬው ድርጊት እየተገረሙና እየተደነቁ ቤታቸው የደረሱት ምስኪኗ አሮጊትም መልካሙን ሰውዬ ትኩር ብለው እየተመለከቱ እንዲህ አሉት ..
«ልጄ ሆይ እንዲያው ባሮጊት አንደበቴ እመርቅሀለሁ እንጂ ላደረግህልኝ ነገር መካሻ ይሆን ዘንድ የምሰጥህ አንዳች የሌለኝ ምስኪን ደሀ ነኝ ልጄ እባክህ ከሰማኸኝ አንድ ምክር ልለግስህ። ወደህዝቦችህ ወደመካ ስትመለስ እዚያ አንድ ነብይ ነኝ የሚል ሙሀመድ የሚሉት ደጋሚ ሰው አለ። በፍጹም እሱን እንዳትከተል እንዳታምነውም!» አሉት።
ሰውዬውም ረጋ ብሎ «ለምን?» ብሎ ጠየቀ!
አሮጊቷም «ልጄ እርሱ መጥፎ ስነምባር ነው ያለው ሲሉ ሰምቻለሁ» ብለው መለሱ።ሰውዬው በሴትየዋ ንግግር ተገርሞ «እኔስ ሙሀመድ ብሆን?» አላቸው። ሴትየዋም የሰሙት ነገር በጣም አስገርማቸው ለካስ ይህ ደግ ሰው ራሳቸው ነብዩ ሙሀመድ (ሰ.አ.ወ) ነበሩ። አስተውሉ ... ነብዩ ለአሮጊቷ ቸርነትን ሲያደርጉ ሀይማኖታቸውን ፈፅሞ አልጠየቁም። ፍቅር የሀይማኖትን ድንበር፣ የዘርና የጎሳን አጥር እንደሚያልፍ ያውቁ ነበርና። ስብከት ያልሰበረውን ልብና ትምህርት ያላንበረከከውን ማንነት ፍቅር ብቻ ትህትናና በጎ ምግባር ብቻ ያንበረክከዋል!
ያማረ ጁምኣ!💚
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta
✨ውበትን ማድነቅ
🔆አለምን የናቀ አንድ መነኩሴ ከሌሎች መነኩሴዎችጋር አብሮ በመንገድ ሲሄድ እጅግ አብዝታ የተዋበች ቆንጆ ሴት አይኑ ውስጥ ትገባለች፡፡ መነኩሴውም በሴቷ ውበት እጅጉን በጣም ከመደነቁ የተነሳ አይኑን ከሷ ላይ መንቀል ጭራሽ አቃተው፡፡ ይህን ድርጊቱን የተመለከቱ አብረውት የነበሩት ሌሎች መነኩሴዎች በድርጊቱ በአፍረት ተሞልተው ተጠጉትና፡-
✨‹‹ወንድማችን አንተ አለምን እንደኛ የናቅህ መነኩሴ ሆነህ ሳለ በሴት ልጅ ውበት እንዲህ ተደንቀህ ፈዘህ ስናስተውልህ አዝነናል፡፡ አለማዊ ድርጊት እየፈፀምህ መሆንህን አላስተዋልክምን?››በማለት ይጠይቁታል፡፡
🔆‹‹ወዳጆቼ በዚህች ቆንጆ ሴት ውበት ውስጥ እየተመለከትኩ የማደንቀው ውበትን እንዳሻው እየለዋወጠ በስራው የሚደሰተውን ፈጣሪዋን እንጂ እሷን አልነበረም፡፡ አይኖቼ የተዋበን ስጋ ሳይሆን የተዋበ ነገር የሚፈጥረውን ፈጣሪ ለማየት እንደተሰሩ አምናለሁ፡፡ በዚያም የተዋበን ነገር መፍጠር የሚችለውን የአምላክ ችሎታ ሥጋ ለብሶ አየዋለሁ መደነቄም በዚህ የተነሳ ነው፡፡››በማለት መለሰላቸው፡፡
✨በውበት ውስጥ የምናደንቀው የተፈጠረውን ነገር ብቻ ሳይሆን ከበስተጀርባው ሆኖ ያንን የተዋበ ነገርን የፈጠረውንም ማድነቅ ከቻልን በርግጥም ታላቅ ፀጋና ጥበብ ከኛ ጋር ነው፡፡
ውብ አሁን!!!❤️
✍ነፀብራቅ ብርሀኔ
✨🔆✨🔆✨🔆✨🔆✨🔆✨🔆✨🔆
@EthioHumanity
@EthioHumanity
🔆አለምን የናቀ አንድ መነኩሴ ከሌሎች መነኩሴዎችጋር አብሮ በመንገድ ሲሄድ እጅግ አብዝታ የተዋበች ቆንጆ ሴት አይኑ ውስጥ ትገባለች፡፡ መነኩሴውም በሴቷ ውበት እጅጉን በጣም ከመደነቁ የተነሳ አይኑን ከሷ ላይ መንቀል ጭራሽ አቃተው፡፡ ይህን ድርጊቱን የተመለከቱ አብረውት የነበሩት ሌሎች መነኩሴዎች በድርጊቱ በአፍረት ተሞልተው ተጠጉትና፡-
✨‹‹ወንድማችን አንተ አለምን እንደኛ የናቅህ መነኩሴ ሆነህ ሳለ በሴት ልጅ ውበት እንዲህ ተደንቀህ ፈዘህ ስናስተውልህ አዝነናል፡፡ አለማዊ ድርጊት እየፈፀምህ መሆንህን አላስተዋልክምን?››በማለት ይጠይቁታል፡፡
🔆‹‹ወዳጆቼ በዚህች ቆንጆ ሴት ውበት ውስጥ እየተመለከትኩ የማደንቀው ውበትን እንዳሻው እየለዋወጠ በስራው የሚደሰተውን ፈጣሪዋን እንጂ እሷን አልነበረም፡፡ አይኖቼ የተዋበን ስጋ ሳይሆን የተዋበ ነገር የሚፈጥረውን ፈጣሪ ለማየት እንደተሰሩ አምናለሁ፡፡ በዚያም የተዋበን ነገር መፍጠር የሚችለውን የአምላክ ችሎታ ሥጋ ለብሶ አየዋለሁ መደነቄም በዚህ የተነሳ ነው፡፡››በማለት መለሰላቸው፡፡
✨በውበት ውስጥ የምናደንቀው የተፈጠረውን ነገር ብቻ ሳይሆን ከበስተጀርባው ሆኖ ያንን የተዋበ ነገርን የፈጠረውንም ማድነቅ ከቻልን በርግጥም ታላቅ ፀጋና ጥበብ ከኛ ጋር ነው፡፡
ውብ አሁን!!!❤️
✍ነፀብራቅ ብርሀኔ
✨🔆✨🔆✨🔆✨🔆✨🔆✨🔆✨🔆
@EthioHumanity
@EthioHumanity
#እምወድሽዋ!❤️ ቅዳሜዋ!❤️ሸጋዬ❤️
እንድርያስ ይባላል.... ከወንበሬ ፊት ለፊት ነው የሚቀመጠው ባልደረባዬ ነው ዝምተኛም ተግባቢም ነው....ያነባል ታሪክ ፣ፖለቲካ ፣ ኪነጥበብ ይተነትናል
...አብረን ነው የምንሰራው
ቃል ኪዳን ትባላለች ትህትናዋ ከፍርሃት ጋ የተዋሃደባት ልጅ ነች ፤ በምሰራበት ድርጅት በፅዳት ከተቀጠረች ቆየች.... ያልቆሸሸ ሁለት ልብስ ብቻ እንደምትለብስ አስተውያለሁ . .. .የገንዘብ ውስንነት እንዳለባት ታስታውቃለች
እንድርያስ ለቃልኪዳን ከኔ በተሻለ ያዝንላታል ለሷ እንደሱ ማዘን ስላልቻልኩ እራሴን እወቅሰዋለሁ .....እሱ ከኔ የተሻለ ነፍስ እንዳለው እረዳለሁ!!!
ከዕለታት በአንዱ ቀን የመቶ ብር ኖቶች ፀጉርሽን መሰርያ ብሎ ሲሸጉጥ በጨረፍታ አይቼው አውቃለሁ.... አንገቷን ስብር አድርጋ ተግደርድራ ተቀበለችው። አመሰገነችውም
በልቤ አንተ ከቅዱሳን መሃል ትገኛለህ አልኩት
ከእኔ በተሻለ ይቆረቆርላታል . እሷ ወንበሩን በመወልወል እንዳትደክም ሳትመጣ ሲወለውል አይቸው አውቃለሁ
መልካምነቱ ያደበዝዘኛል
ለእሷ ባለው ቦታ እኔ እራሴ እደስትበታለሁ። የፃዲቅ መልካምነት የሚጀምረው በዙሪያቸው ባሉ ሰዎች ነው።
ከብዙ ጊዜ በኋላ በቀደም ቅዳሜ ደወለችልኝ እንደትንሽ ልጅ ፈራ ተባ እያለች በተሰበረ በለሆሳስ ድምፅ "ላናግርህ ፈልጌ ነበር አለችኝ" .....?መሳቀቋን ላለማድመቅ በቶሎ እሺ አልኳት....ተገናኘን
የለበሰችውን አመድማ ሹራብ እጅጌ ጎትታ ጣቶቿን አልብሳዋለች ። ማድያቷ እንዳ'ፍንጫዋ ከሩቁ መታየት ጀምሯል ። ፊቷ ክስም ፤ግርጥት ብሏል። ልቅም ያለች ወብ መሆኗ ይሄ ሁላ ጉስቁልና አላወደመውም
ይቅርታ በጣም "ከአንተ በላይ የሚቀርበው ሰው ስለማላውቅ ነው"
ዝም ብዬ ተመለከትኳት
* እንድርያስን እንድታናግርልኝ ነው "🙏 ስለምንጉዳይ ???..... አቀረቀረች .... በሆዴ የያዝኩት ልጅ የእሱ ነው አይንሽን ላፈር አለኝ ሳረግዝ ጠላኝ .....
ዞረብኝ ....
አፈጠጥኩኝ......
" አገባሻለሁ ተማሪ እያለ እየመከረ ፣እየወደደ፣ እየተንከባከበ፣ በፍቅር አክንፎ .....በፍቅር አባብሎ .....ስፀንስ ተፀየፈኝ: የደረጃ ልዩነታችን ተገለፀለት ማነሴ ኮሰኮሰው
የትም ስትንዘላዘይ ያመጣሽውን አለኝ😭
አቀርቅራለች
ፀጥታ ሰፈነ .....ቀና ስትል አይኗ በእንባ ተጨማልቋል
*ቢያንስ አባትነቱን ይመንልኝ እኔ ከሱ ውጪ ወንድ እንደማላቅ እሱ እራሱ ምስክር ነው ። ከፈለገ ልጁ የሱ መሆኑን ያስመርምር*
.
.
እንድርያስ እኔንም ነው የከዳኝ ሰውነቴ ውስጥ ድብርት ሲፈስብኝ እየታወቀኝ ነው
በአይኗ ውስጥ በደሏን አይቼ ሰለራሴ... ስለእህቴ .....ስለ ነገ ልጄ.. ስለ ጓደኛዬ .....ውሃ መሳይ ፊቴ ላይ ከአይኔ እየወጣ ሲረማመድ ተሰማኝ
.......
#ማሳሰብያ
የሰይጣን አምሳያ የሆነው ሰው መምጫ መንገዱ መቼ ይታወቃል ።ከሚታዩ መጥፎ ነገሮች መልካም የሚመስሉ
መጥፎ ነገሮች ያከስማሉ
....
ደርባባ ቅዳሚት ትሁንልን!❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta
እንድርያስ ይባላል.... ከወንበሬ ፊት ለፊት ነው የሚቀመጠው ባልደረባዬ ነው ዝምተኛም ተግባቢም ነው....ያነባል ታሪክ ፣ፖለቲካ ፣ ኪነጥበብ ይተነትናል
...አብረን ነው የምንሰራው
ቃል ኪዳን ትባላለች ትህትናዋ ከፍርሃት ጋ የተዋሃደባት ልጅ ነች ፤ በምሰራበት ድርጅት በፅዳት ከተቀጠረች ቆየች.... ያልቆሸሸ ሁለት ልብስ ብቻ እንደምትለብስ አስተውያለሁ . .. .የገንዘብ ውስንነት እንዳለባት ታስታውቃለች
እንድርያስ ለቃልኪዳን ከኔ በተሻለ ያዝንላታል ለሷ እንደሱ ማዘን ስላልቻልኩ እራሴን እወቅሰዋለሁ .....እሱ ከኔ የተሻለ ነፍስ እንዳለው እረዳለሁ!!!
ከዕለታት በአንዱ ቀን የመቶ ብር ኖቶች ፀጉርሽን መሰርያ ብሎ ሲሸጉጥ በጨረፍታ አይቼው አውቃለሁ.... አንገቷን ስብር አድርጋ ተግደርድራ ተቀበለችው። አመሰገነችውም
በልቤ አንተ ከቅዱሳን መሃል ትገኛለህ አልኩት
ከእኔ በተሻለ ይቆረቆርላታል . እሷ ወንበሩን በመወልወል እንዳትደክም ሳትመጣ ሲወለውል አይቸው አውቃለሁ
መልካምነቱ ያደበዝዘኛል
ለእሷ ባለው ቦታ እኔ እራሴ እደስትበታለሁ። የፃዲቅ መልካምነት የሚጀምረው በዙሪያቸው ባሉ ሰዎች ነው።
ከብዙ ጊዜ በኋላ በቀደም ቅዳሜ ደወለችልኝ እንደትንሽ ልጅ ፈራ ተባ እያለች በተሰበረ በለሆሳስ ድምፅ "ላናግርህ ፈልጌ ነበር አለችኝ" .....?መሳቀቋን ላለማድመቅ በቶሎ እሺ አልኳት....ተገናኘን
የለበሰችውን አመድማ ሹራብ እጅጌ ጎትታ ጣቶቿን አልብሳዋለች ። ማድያቷ እንዳ'ፍንጫዋ ከሩቁ መታየት ጀምሯል ። ፊቷ ክስም ፤ግርጥት ብሏል። ልቅም ያለች ወብ መሆኗ ይሄ ሁላ ጉስቁልና አላወደመውም
ይቅርታ በጣም "ከአንተ በላይ የሚቀርበው ሰው ስለማላውቅ ነው"
ዝም ብዬ ተመለከትኳት
* እንድርያስን እንድታናግርልኝ ነው "🙏 ስለምንጉዳይ ???..... አቀረቀረች .... በሆዴ የያዝኩት ልጅ የእሱ ነው አይንሽን ላፈር አለኝ ሳረግዝ ጠላኝ .....
ዞረብኝ ....
አፈጠጥኩኝ......
" አገባሻለሁ ተማሪ እያለ እየመከረ ፣እየወደደ፣ እየተንከባከበ፣ በፍቅር አክንፎ .....በፍቅር አባብሎ .....ስፀንስ ተፀየፈኝ: የደረጃ ልዩነታችን ተገለፀለት ማነሴ ኮሰኮሰው
የትም ስትንዘላዘይ ያመጣሽውን አለኝ😭
አቀርቅራለች
ፀጥታ ሰፈነ .....ቀና ስትል አይኗ በእንባ ተጨማልቋል
*ቢያንስ አባትነቱን ይመንልኝ እኔ ከሱ ውጪ ወንድ እንደማላቅ እሱ እራሱ ምስክር ነው ። ከፈለገ ልጁ የሱ መሆኑን ያስመርምር*
.
.
እንድርያስ እኔንም ነው የከዳኝ ሰውነቴ ውስጥ ድብርት ሲፈስብኝ እየታወቀኝ ነው
በአይኗ ውስጥ በደሏን አይቼ ሰለራሴ... ስለእህቴ .....ስለ ነገ ልጄ.. ስለ ጓደኛዬ .....ውሃ መሳይ ፊቴ ላይ ከአይኔ እየወጣ ሲረማመድ ተሰማኝ
.......
#ማሳሰብያ
የሰይጣን አምሳያ የሆነው ሰው መምጫ መንገዱ መቼ ይታወቃል ።ከሚታዩ መጥፎ ነገሮች መልካም የሚመስሉ
መጥፎ ነገሮች ያከስማሉ
....
ደርባባ ቅዳሚት ትሁንልን!❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta
👍1
#ዛሬ ሽቅርቅሯ ቅዳሚት ነች..❤ አንድ የቻናላችን ቤተሰብ የሆነች እንዲህ አለችኝ.... በእርግጠኝነት እንደኔ ይሄ ነገር የሚሰማቸው ፣ ግራ የሚያጋባቸው ፣ የተጎዱበት ......ህመሜ ህመማቸው ይኖራሉ እና ይሄን እዚህ ቻናል ላይ ለጥፍልኝ አለችኝ.....#ከዚህ በታች ያለውን ስሜቷን ህመሟን ግራ መጋባቷን እንዲህ አስቀምጣዋለች......#ምናልባት ይሄን የምታነቡ ቤተሰቦች እናተም በዚህ ነገር ውስጥ ናቹ ወይንም አልፋችሁት ይሆናል........ተጋበዙልኝ🙏🙏
👇👇👇
በቃ አንዳንዶች አሉ
.
.
ፍላጎታቸው በትክክል ምን እንደሆነ የማይገቡህ::
የትውውቃችሁ መጀመሪያ አከባቢ ጥሩ ይሆኑልህና ከትንሽ ግዜ በኋላ
የሚቀየሩብህ::አንተን የፍቅር ስሜት ውስጥ ከከተቱህ በኋላ ከነሱ ተመሳሳይ ስሜት
ስትፈልግ የማይመልሱልህ::
.
.
...በቃ አንዳንዶች አሉ!
.
.
ካንተ ጋ መሆን እየፈለጉ ነገር ግን በህይወቴ ሌላ ሰው ቢመጣስ ብለው ወይም ደግሞ
ባለፈ የፍቅር ህይወታቸው ፍራቻ ፍቅርህን የማይቀበሉ::የማይሸሹህ!..የማይቀረቡ!..ሄዱ
ስትላቸው የሚመጡ!..መጡ ስትላቸው የሚሄዱ::
.
.
በቃ አንዳንዶች አሉ!
.
.
ሌላ ሰው እስከሚተዋወቁ አንተን እንደ ባጣ ቆየኝ የመጠቀሙ!
.
.
በቃ አንዳንዶች አሉ!
.
.
ሁሌ አንተ ቀድመህ መልዕክት እንድትልክላቸው ወይም ደግሞ እንድትደውልላቸው
የሚፈልጉ!አንተም አያስችልህም መልዕክት ትልካለህ!..ትደውላለህ!...እንደ ነገሩ
ያዋሩሀል!..ግን ደግሞ ብልጦች ናቸው!...ጨርሰህ እንድትለያቸው ስለማይፈልጉ ተስፋህን
ሙሉ ለሙሉ አይነጥቁህም!..ጭላንጭል ያስቀሩልሀል!..አንተም የቀረህን ጭላንጭል
ተስፋ ይዘህ አብረሀቸው መንገድ ትቀጥላለህ!
.
.
የሆነ ሰዓት ይሰለችሀል!ልትደውልላቸው ስልክህን ታነሳና መልሰህ
ታሰቀምጠዋህ!..ከራስህ ጋ ብዙ ትታገላለህ!..በመርሳትና በፍቅር ስሜት መሀል ሆነ
ለረጅም ግዜ ዝምምም ትላቸዋለህ::
.
.
የዚህን ግዜ የነሱ ተራ ይጀምራል!..እያንዳንዷ የተሰማህ ስሜት የሰማቸዋል!..እያንዳንዷ
ያመምህ ህመም ያማቸዋል!...ይቁነጠነጣሉ!..አስር ግዜ መልዕክት
ይልኩልሀል!...ይደውሉልሀል!...ቀን ሙሉ ያስቡሀል!
.
.
በቃ አንዳንዶች አሉ!...
.
.
ፍቅር ስትሰጣቸው ጀርባ ሰጥተውህ ስትርቃቸው የሚከተሉህ!
.
.
ስታዋራቸው ዝም ብለው ዝም ስትላቸው የሚያዋሩህ!.!
.
.
ግራ የተጋቡ!የተወሳሰቡ..በትክክል ፍላጎታቸው ምን እንደሆነ የማትረዳቸው!....
.
✍ፀዲ
ሀሳብ ካላቹ ....ማካፋል ትችላላችሁ 🙏
ሽብርቅርቅ ያለች ቅዳሜ!❤
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta
👇👇👇
በቃ አንዳንዶች አሉ
.
.
ፍላጎታቸው በትክክል ምን እንደሆነ የማይገቡህ::
የትውውቃችሁ መጀመሪያ አከባቢ ጥሩ ይሆኑልህና ከትንሽ ግዜ በኋላ
የሚቀየሩብህ::አንተን የፍቅር ስሜት ውስጥ ከከተቱህ በኋላ ከነሱ ተመሳሳይ ስሜት
ስትፈልግ የማይመልሱልህ::
.
.
...በቃ አንዳንዶች አሉ!
.
.
ካንተ ጋ መሆን እየፈለጉ ነገር ግን በህይወቴ ሌላ ሰው ቢመጣስ ብለው ወይም ደግሞ
ባለፈ የፍቅር ህይወታቸው ፍራቻ ፍቅርህን የማይቀበሉ::የማይሸሹህ!..የማይቀረቡ!..ሄዱ
ስትላቸው የሚመጡ!..መጡ ስትላቸው የሚሄዱ::
.
.
በቃ አንዳንዶች አሉ!
.
.
ሌላ ሰው እስከሚተዋወቁ አንተን እንደ ባጣ ቆየኝ የመጠቀሙ!
.
.
በቃ አንዳንዶች አሉ!
.
.
ሁሌ አንተ ቀድመህ መልዕክት እንድትልክላቸው ወይም ደግሞ እንድትደውልላቸው
የሚፈልጉ!አንተም አያስችልህም መልዕክት ትልካለህ!..ትደውላለህ!...እንደ ነገሩ
ያዋሩሀል!..ግን ደግሞ ብልጦች ናቸው!...ጨርሰህ እንድትለያቸው ስለማይፈልጉ ተስፋህን
ሙሉ ለሙሉ አይነጥቁህም!..ጭላንጭል ያስቀሩልሀል!..አንተም የቀረህን ጭላንጭል
ተስፋ ይዘህ አብረሀቸው መንገድ ትቀጥላለህ!
.
.
የሆነ ሰዓት ይሰለችሀል!ልትደውልላቸው ስልክህን ታነሳና መልሰህ
ታሰቀምጠዋህ!..ከራስህ ጋ ብዙ ትታገላለህ!..በመርሳትና በፍቅር ስሜት መሀል ሆነ
ለረጅም ግዜ ዝምምም ትላቸዋለህ::
.
.
የዚህን ግዜ የነሱ ተራ ይጀምራል!..እያንዳንዷ የተሰማህ ስሜት የሰማቸዋል!..እያንዳንዷ
ያመምህ ህመም ያማቸዋል!...ይቁነጠነጣሉ!..አስር ግዜ መልዕክት
ይልኩልሀል!...ይደውሉልሀል!...ቀን ሙሉ ያስቡሀል!
.
.
በቃ አንዳንዶች አሉ!...
.
.
ፍቅር ስትሰጣቸው ጀርባ ሰጥተውህ ስትርቃቸው የሚከተሉህ!
.
.
ስታዋራቸው ዝም ብለው ዝም ስትላቸው የሚያዋሩህ!.!
.
.
ግራ የተጋቡ!የተወሳሰቡ..በትክክል ፍላጎታቸው ምን እንደሆነ የማትረዳቸው!....
.
✍ፀዲ
ሀሳብ ካላቹ ....ማካፋል ትችላላችሁ 🙏
ሽብርቅርቅ ያለች ቅዳሜ!❤
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta
<< የሚዋደድ ሰው ሁሉ አንድ አይነት ነገር መውደድ የለበትም... >>
📖መነሻ ሃሳብ :- " ማታ ማታ - ገጽ 110
🔺" ማሰብ ተፈጥሮአዊ ባህሪህ ቢሆንም በማሰብ ላይ ያለህ ብስለት ከሚገለጽባቸው መንገዶች አንዱ ደግሞ ካንተ የተለየ ሀሳብ ሲያጋጥምህ ለሃሳቡ በምትሰጠው ምላሽ(ግብራዊ) ነው ። እምትወደው ሰው የግድ ባንተ ሃሳብ የሚስማማ ወይም አንተ የምትወደውን ብቻ የሚወድ መሆን የለበትም ። እንደዛ አይነት ሰው ከፈለግክ ያንተን ሁሉ አሜን ብሎ የሚቀበል የሀሳብና የፍላጎት_ወዛደር እንጂ አሳቢን አታገኝም ።
❤️የሚዋደድ ሰው ሁሉ አንድ አይነት ነገር በመውደድ አይደለም መዋደዱ የሚገለጸው ። ካንተ ለተለየ ነገር ሁሉ ጥላቻ ከሆነ ምላሽህ በትክክል ማሰብ መቻልህ ጥያቄ ውስጥ ይገባል ። በሃሳብ መፋለስ የልዩነት እንጂ የጥላቻም ሆነ ያለመዋደድ መንስኤም ሆነ ምልክት አይደለም ። አንተ ራስህ በየቀንና በየሰአቱ የምታስባቸው ሃሳቦች ልዩነት ሊኖራቸው ይችላል ግን አቻችለሀቸው እየኖርህ ነው ። ታድያ የሰውን ልዩነት ማቻቻልስ እንዴት ያቅትሀል...…?
ለራሳችን ጥያቄ ሰተነው እንደምድም::
የሀሳብ ልዩነቶችን ለምን በስድብ እናጣጣቸዋለን?…………
ሰዎች እኛ ያልደገፍነውን ስለደገፉ ለምን እንዲያፍሩ እናደርጋቸዋለን?...……"
ፍቅር አሁን !
@keney_serezoch
@EthioHumanity
📖መነሻ ሃሳብ :- " ማታ ማታ - ገጽ 110
🔺" ማሰብ ተፈጥሮአዊ ባህሪህ ቢሆንም በማሰብ ላይ ያለህ ብስለት ከሚገለጽባቸው መንገዶች አንዱ ደግሞ ካንተ የተለየ ሀሳብ ሲያጋጥምህ ለሃሳቡ በምትሰጠው ምላሽ(ግብራዊ) ነው ። እምትወደው ሰው የግድ ባንተ ሃሳብ የሚስማማ ወይም አንተ የምትወደውን ብቻ የሚወድ መሆን የለበትም ። እንደዛ አይነት ሰው ከፈለግክ ያንተን ሁሉ አሜን ብሎ የሚቀበል የሀሳብና የፍላጎት_ወዛደር እንጂ አሳቢን አታገኝም ።
❤️የሚዋደድ ሰው ሁሉ አንድ አይነት ነገር በመውደድ አይደለም መዋደዱ የሚገለጸው ። ካንተ ለተለየ ነገር ሁሉ ጥላቻ ከሆነ ምላሽህ በትክክል ማሰብ መቻልህ ጥያቄ ውስጥ ይገባል ። በሃሳብ መፋለስ የልዩነት እንጂ የጥላቻም ሆነ ያለመዋደድ መንስኤም ሆነ ምልክት አይደለም ። አንተ ራስህ በየቀንና በየሰአቱ የምታስባቸው ሃሳቦች ልዩነት ሊኖራቸው ይችላል ግን አቻችለሀቸው እየኖርህ ነው ። ታድያ የሰውን ልዩነት ማቻቻልስ እንዴት ያቅትሀል...…?
ለራሳችን ጥያቄ ሰተነው እንደምድም::
የሀሳብ ልዩነቶችን ለምን በስድብ እናጣጣቸዋለን?…………
ሰዎች እኛ ያልደገፍነውን ስለደገፉ ለምን እንዲያፍሩ እናደርጋቸዋለን?...……"
ፍቅር አሁን !
@keney_serezoch
@EthioHumanity
🔱በሌሎች ስኬት አትቅና!
💫“ቅንአት (jealousy) ሲብራራ፣ አንተ ያለህን ነገር ወስጄ የእኔ ማድረግ እፈልጋለሁ የማለት ስሜት ሲሆን፣ ይህ ቅንአት መራራነት (resentment) ሲጨመርበት፣ አንተ ያለህን ነገር የእኔ ማድረግ እፈልጋለሁ፣ አንተ ደግሞ ምንም ነገር እንዲኖርህ አልፈልግም ወደሚለው ከረር ያለ ስሜት ይሻገራል . . . ወደመራራነት የተሸጋገረ ቅንአት ፍትህ እንደጎደለ ከማሰብ ሊመጣ እንደሚችልና ከዚያም ባሻገር በውስጣችን ከተደበቀ በራስ ያለመተማመንና የዝቅተኝት ስሜት ሊነሳ ይችላል፡፡
🔱በሕይወትህ ከሌሎች የምትሻልበት ነገር እንዳለህ ሁሉ ሌሎች ሰዎች ከአንተ የሚሻሉበት ነገር እንዳለም አምነህ ተቀበል፡፡ ይህንን አመለካከት ከመብለጥና ከመበለጥ ስሜት አንጻር ሳይሆን አንተ እንዲሳካልህ የመፈለግህን ያህል ሌሎችም እንዲሳካላቸው ከመፈለግ አንጻር ልትይዘው ይገባሃል፡፡ በሌሎች ሰዎች ስኬት የሚቀኑ ሰዎች ልቀው በተገኙበት መስክ ሳይቀር የተበለጡ ሰዎች ናቸው፡፡ ምክንያቱም ትኩረታቸውን ከግባቸው ላይ አንስተው ሌላውን ሰው ለመጣልና በልጦ ለመገኘት ስለሚጣጣሩ ነው፡፡
💫አንዳንድ ሰዎች በአንድ አቅጣጫ ልቀው የሚገኙት ምናልባት ለዚያ ነገር ከአንተ የተለየ ትኩረት ስለሰጡት ሊሆን ይችላል፡፡ ምክንያቱ ያም ሆነ ይህ አንተም ደግሞ ከእነዚ ሰዎች የተሻልክባቸው ሁኔታዎች እንዳሉ በማሰብ ወደፊት ካልቀጠልቅ ከቅንአት ህመም አታመልጥም፡፡
🔱ሰውን ለማሸነፍ ከመሯሯጥ ወጥተህ ራስህን በማሸነፍ ወደ ትክክለኛ ስኬት ለመድረስ ከፈለግህ በመጀመሪያ ከዓላማህና ከራእይህ ጋር የሚመጥን ግብ ማውጣት አለብህ፡፡ የዚህ ግብህ ከፍታ በፍጹም ከሌላው ሰው ሁኔታ ጋር መነካካት የለበትም፡፡ የሌላው ሰው ስኬት የራስህን ግብ ለመከታተል ሊያነሳሳህ ይገባል እንጂ ወደ ፉክክር ሊጨምርህ አይገባም፡፡
(“ራስን ማሸነፍ” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ መጽሐፍ የተወሰደ)
መልካም ምሽት
🔱💫🔱💫🔱💫🔱💫🔱💫
@EthioHumanity
@EthioHumanity
💫“ቅንአት (jealousy) ሲብራራ፣ አንተ ያለህን ነገር ወስጄ የእኔ ማድረግ እፈልጋለሁ የማለት ስሜት ሲሆን፣ ይህ ቅንአት መራራነት (resentment) ሲጨመርበት፣ አንተ ያለህን ነገር የእኔ ማድረግ እፈልጋለሁ፣ አንተ ደግሞ ምንም ነገር እንዲኖርህ አልፈልግም ወደሚለው ከረር ያለ ስሜት ይሻገራል . . . ወደመራራነት የተሸጋገረ ቅንአት ፍትህ እንደጎደለ ከማሰብ ሊመጣ እንደሚችልና ከዚያም ባሻገር በውስጣችን ከተደበቀ በራስ ያለመተማመንና የዝቅተኝት ስሜት ሊነሳ ይችላል፡፡
🔱በሕይወትህ ከሌሎች የምትሻልበት ነገር እንዳለህ ሁሉ ሌሎች ሰዎች ከአንተ የሚሻሉበት ነገር እንዳለም አምነህ ተቀበል፡፡ ይህንን አመለካከት ከመብለጥና ከመበለጥ ስሜት አንጻር ሳይሆን አንተ እንዲሳካልህ የመፈለግህን ያህል ሌሎችም እንዲሳካላቸው ከመፈለግ አንጻር ልትይዘው ይገባሃል፡፡ በሌሎች ሰዎች ስኬት የሚቀኑ ሰዎች ልቀው በተገኙበት መስክ ሳይቀር የተበለጡ ሰዎች ናቸው፡፡ ምክንያቱም ትኩረታቸውን ከግባቸው ላይ አንስተው ሌላውን ሰው ለመጣልና በልጦ ለመገኘት ስለሚጣጣሩ ነው፡፡
💫አንዳንድ ሰዎች በአንድ አቅጣጫ ልቀው የሚገኙት ምናልባት ለዚያ ነገር ከአንተ የተለየ ትኩረት ስለሰጡት ሊሆን ይችላል፡፡ ምክንያቱ ያም ሆነ ይህ አንተም ደግሞ ከእነዚ ሰዎች የተሻልክባቸው ሁኔታዎች እንዳሉ በማሰብ ወደፊት ካልቀጠልቅ ከቅንአት ህመም አታመልጥም፡፡
🔱ሰውን ለማሸነፍ ከመሯሯጥ ወጥተህ ራስህን በማሸነፍ ወደ ትክክለኛ ስኬት ለመድረስ ከፈለግህ በመጀመሪያ ከዓላማህና ከራእይህ ጋር የሚመጥን ግብ ማውጣት አለብህ፡፡ የዚህ ግብህ ከፍታ በፍጹም ከሌላው ሰው ሁኔታ ጋር መነካካት የለበትም፡፡ የሌላው ሰው ስኬት የራስህን ግብ ለመከታተል ሊያነሳሳህ ይገባል እንጂ ወደ ፉክክር ሊጨምርህ አይገባም፡፡
(“ራስን ማሸነፍ” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ መጽሐፍ የተወሰደ)
መልካም ምሽት
🔱💫🔱💫🔱💫🔱💫🔱💫
@EthioHumanity
@EthioHumanity
ለውብ ቀን!
💚
ነፍስን ፍለጋ!
ይሉኝታ በሚሉት የውሸት አጋም አጥር ተሸብበን ውስጠታችን ከሚሻው እውነተኛ ማንነት ግልባጭ ፅንፍ የቆምን ስንቶቻችን እንሆን? በተበላሸው አቅራቦታችን ምክንያት ልንናገራቸው ፈልገን ያልተናገርናቸው ፣ ልንወቅስ ፈልገን ያልወቀስናቸው ፣ ልናደንቅ ከጅለን ያላደነቅናቸው በታወሱን ጊዜ ነፍሶቻችንን በቁጭት ወረንጦ የሚሸነቁጡ ስንት ኩነቶች አልፈዋል?
በየእለቱ ከምናገኛቸው በአካል ቅርብ ከሆኑ ባልንጀሮቻችን በሆያሆዬ ደምቀን እና ተሰብስበን ሳለን ከልባችን ያን እውነተኛ ሀሴት መጎናፀፍ ተስኖን በነፍስ በስንት ሺህ ማይል ተራርቀን ይሆን?
በህይወት ዑደት ውስጥ ወደኛ ህይወት የገቡ እልፍ ሰዎችን በመጀመሪያ መስተጋብራችን እራሳችንን በተንሸዋረረ መልኩ አሳይተን ከአካላችን ባሻገር እውነታችንን እና ነፍሳችንን የገለጥልናቸው ምን ያክሉን ነው?
በጓደኝነት አለም አልያም በማህበራዊ ህይወት ከልብ የሆነ መቆራኘትን ሳንቆራኝ ፣ ውስጣዊ እኛነታችን ለየቅል ሆኖ ሁላችንም ታመን ሳለ ከመንጋው ላለመፈንገል የወየበ ጥቀርሻ ልብ ይዘን ሀጫ በረዶ ጥርስ እየመፀወትን ስንቶቻችን ይሆን የምንጋፋው?
ንግግራችን ፣ ሰላምታችን ፣ ሳቃችን ፍቅራችን ምን ያክል ነፍሳዊ ነው? ምን ያክል ጥልቅ ነው? እንጃ!!
✍አብድል ማሊክ
@EthioHumanity
@EthioHumanity
💚
ነፍስን ፍለጋ!
ይሉኝታ በሚሉት የውሸት አጋም አጥር ተሸብበን ውስጠታችን ከሚሻው እውነተኛ ማንነት ግልባጭ ፅንፍ የቆምን ስንቶቻችን እንሆን? በተበላሸው አቅራቦታችን ምክንያት ልንናገራቸው ፈልገን ያልተናገርናቸው ፣ ልንወቅስ ፈልገን ያልወቀስናቸው ፣ ልናደንቅ ከጅለን ያላደነቅናቸው በታወሱን ጊዜ ነፍሶቻችንን በቁጭት ወረንጦ የሚሸነቁጡ ስንት ኩነቶች አልፈዋል?
በየእለቱ ከምናገኛቸው በአካል ቅርብ ከሆኑ ባልንጀሮቻችን በሆያሆዬ ደምቀን እና ተሰብስበን ሳለን ከልባችን ያን እውነተኛ ሀሴት መጎናፀፍ ተስኖን በነፍስ በስንት ሺህ ማይል ተራርቀን ይሆን?
በህይወት ዑደት ውስጥ ወደኛ ህይወት የገቡ እልፍ ሰዎችን በመጀመሪያ መስተጋብራችን እራሳችንን በተንሸዋረረ መልኩ አሳይተን ከአካላችን ባሻገር እውነታችንን እና ነፍሳችንን የገለጥልናቸው ምን ያክሉን ነው?
በጓደኝነት አለም አልያም በማህበራዊ ህይወት ከልብ የሆነ መቆራኘትን ሳንቆራኝ ፣ ውስጣዊ እኛነታችን ለየቅል ሆኖ ሁላችንም ታመን ሳለ ከመንጋው ላለመፈንገል የወየበ ጥቀርሻ ልብ ይዘን ሀጫ በረዶ ጥርስ እየመፀወትን ስንቶቻችን ይሆን የምንጋፋው?
ንግግራችን ፣ ሰላምታችን ፣ ሳቃችን ፍቅራችን ምን ያክል ነፍሳዊ ነው? ምን ያክል ጥልቅ ነው? እንጃ!!
✍አብድል ማሊክ
@EthioHumanity
@EthioHumanity
🌗የሌሊት ወፍ
🌙“የሌሊት ወፍ በቀን የመኖር ስልጣን የላትም” ይላል ምንጩ ያልታወቀ የጥንት አፈ-ታሪክ፡፡ “ለዚህ ነው ሌሊቱን እየጠበቀች ከመሸ ተደብቃ ወጥታ ሳይነጋ ተደብቃ የምትገባው”፡፡
🌗በጥንት ጊዜ በሰማይ አእዋፍና በምድር አራዊት መካከል ውጊያ ነበር ይባላል፡፡ የአሁኗ የሌሊት ወፍ ያን ጊዜ እንደማንኛውም የወፍ ዝርያ ነበረች፡፡ ይህቺ ወፍ (የአሁኗ የሌሊት ወፍ) በውጊያው ጊዜ የምድር አራዊት ሲያሸነፍ ለእነሱ ታግዝ ነበር፤ የሰማዩ ሲያሸነፍ ደግሞ ተገልብጣ ለእነሱ ታግዝ ነበር፡፡
🌗አንድ ጊዜ ግን እነዚህ ሁለት ጸበኞች ታረቁና የጦርነቱ ሁኔታና ትውስታ ሲነሳ ምን ስታደርግ እንደነበረ ታወቀባት፡፡ ከዚያ ቀን ጀምሮ በሁሉም የተጠላችና የተገፋች ወደመሆን ስለመጣች በቀን የመኖር ስልጣኗን አጣችና ሌሊት መኖር ጀመረች ይባላል፡፡
🌙አስመሳይነት፣ ሁለት መልክ ያለው ሕይወት፣ አቋም የለሽነት፣ ውሸተኛነት፣ አታላይነት፣ መስሎ አዳሪነት፣ ባለ ሁለት ምላስነት፣ ሸንጋይነት፣ ለሆድ አዳሪነት . . . የዘመኑ ችግር!
🌑የብዙዎችን በነጻነትና ቀና ብሎ በድፍረት የመኖር አቅም ያሳጣ የዘመኑ ወረርሽኝ!
አስመሳይ ሆነህ ወዳጅህ ከሚበዛ፣ እውነተኛ ሆነህ ጠላትህ ቢበዛ ይሻላል፡፡ ሁለት መልክ ይዘህ ትርፋማ ከምትሆን፣ አንድ መልክ ይዘህ ባለህ ነገር መኖር ይሻልሃል፡፡
✍ከዶ/ር እዮብ ማሞ
በሰላም እደሩ❤️
🌙🌗🌙🌗🌙🌗🌙🌗🌙🌗
@EthioHumanity
@EthioHumanity
🌙“የሌሊት ወፍ በቀን የመኖር ስልጣን የላትም” ይላል ምንጩ ያልታወቀ የጥንት አፈ-ታሪክ፡፡ “ለዚህ ነው ሌሊቱን እየጠበቀች ከመሸ ተደብቃ ወጥታ ሳይነጋ ተደብቃ የምትገባው”፡፡
🌗በጥንት ጊዜ በሰማይ አእዋፍና በምድር አራዊት መካከል ውጊያ ነበር ይባላል፡፡ የአሁኗ የሌሊት ወፍ ያን ጊዜ እንደማንኛውም የወፍ ዝርያ ነበረች፡፡ ይህቺ ወፍ (የአሁኗ የሌሊት ወፍ) በውጊያው ጊዜ የምድር አራዊት ሲያሸነፍ ለእነሱ ታግዝ ነበር፤ የሰማዩ ሲያሸነፍ ደግሞ ተገልብጣ ለእነሱ ታግዝ ነበር፡፡
🌗አንድ ጊዜ ግን እነዚህ ሁለት ጸበኞች ታረቁና የጦርነቱ ሁኔታና ትውስታ ሲነሳ ምን ስታደርግ እንደነበረ ታወቀባት፡፡ ከዚያ ቀን ጀምሮ በሁሉም የተጠላችና የተገፋች ወደመሆን ስለመጣች በቀን የመኖር ስልጣኗን አጣችና ሌሊት መኖር ጀመረች ይባላል፡፡
🌙አስመሳይነት፣ ሁለት መልክ ያለው ሕይወት፣ አቋም የለሽነት፣ ውሸተኛነት፣ አታላይነት፣ መስሎ አዳሪነት፣ ባለ ሁለት ምላስነት፣ ሸንጋይነት፣ ለሆድ አዳሪነት . . . የዘመኑ ችግር!
🌑የብዙዎችን በነጻነትና ቀና ብሎ በድፍረት የመኖር አቅም ያሳጣ የዘመኑ ወረርሽኝ!
አስመሳይ ሆነህ ወዳጅህ ከሚበዛ፣ እውነተኛ ሆነህ ጠላትህ ቢበዛ ይሻላል፡፡ ሁለት መልክ ይዘህ ትርፋማ ከምትሆን፣ አንድ መልክ ይዘህ ባለህ ነገር መኖር ይሻልሃል፡፡
✍ከዶ/ር እዮብ ማሞ
በሰላም እደሩ❤️
🌙🌗🌙🌗🌙🌗🌙🌗🌙🌗
@EthioHumanity
@EthioHumanity
❤️የሰው አእምሮ በውሸትና በተጣመመ! መረጃ ላይ እንደሚበላሽ በምንም አይበላሽም። በተለይም ውሸትን ሥራዬ ብለው በራስ ወዳድነት ስሜት የሚረጩ ሰዎች በሌሎች ልብና አእምሮ ውስጥ እሾህና አሜኬላን ይዘራሉ።
💡 ስንት ጥሩ ሰዎች በክፉና በስግብስግብ ውሸተኞች ኑሯቸው ፈርሷል። ትዳራቸው ተበትኗል!
❤️ስንት ሥልጣኔዎችንና አገሮችን ከጥቅም ውጭ አድርገዋል። አያለ ጨቅላዎች በውሸት በተመረዘ ንግግር እንጭጭ አእምሯአቸው ከንቱ ሆኖ ቀርቷል።
💡ዓለምን በአንደኝነት ያጠፋው ክፉ ሰዎች የዘሩት ውሸት ነው። የሰው ውድቀት የጀመረውም በውሸት ነው። እውነትን በትዕግሥትና በሰከነ ልቦና እንደ መልካም ዘር ካልፈለግናትና ካልተንከባከብናት ውሸት እንደ አረም ከክፉ ሰዎች የልብ ዕርሻ ላይ እየተዛመተ መልካም ልቦችን ማጥፋትና መውረስ አይቀርም።
❤️እውነትን ታውቃላችሁ እውነትም ነጻ ያወጣችኃል'የሚለው የትልቁ መጽሐፍ ቃል እንደት ያለ እውነት ነው?
💡በዓለም ላይ ከሁሉ አስከፊው እስር ቤት የሰው አእምሮ ባመነጨው ውሸት ሲጠፈርና በዚያ ቀንበር ውስጥ ሲኖር ነው። እውነተኛ ነጻነት የኀሊና ነጻነት ነው። የኀሊና ነጻነት ደግሞ እውነትን በማወቅና በመኖር ነጻ ከወጣ አእምሮ ብቻ የሚገኝ ጸጋ ነው።
❤️የብዙ አእምሮዎች መቆለፍና መዛግ መንሥኤው ባንድም በሌላም መንገድ ወደ ውስጣቸው የገባው ውሸትና ነጻ የሚያወጣቸውን እውነት አለማወቃቸው የፈጠረው ገደል ነው።
💡ከእውነት በፊትም ሆነ በላይ ለአእምሮ ጠንነትና ነጻነት ምን ምን መድኀንት ይገኛል?እውነት ማወቅ ነጻ ቢያወጣም፣ እውነት ዋጋዋ እጅግ ውድ መድኀኒት ናት።
የተቆለፈበት ቁልፍ[ገፅ፡278]
✍ምህረት ደበበ
❤️💡❤️💡❤️💡❤️💡❤️💡
@EthioHumanity
@EthioHumanity
💡 ስንት ጥሩ ሰዎች በክፉና በስግብስግብ ውሸተኞች ኑሯቸው ፈርሷል። ትዳራቸው ተበትኗል!
❤️ስንት ሥልጣኔዎችንና አገሮችን ከጥቅም ውጭ አድርገዋል። አያለ ጨቅላዎች በውሸት በተመረዘ ንግግር እንጭጭ አእምሯአቸው ከንቱ ሆኖ ቀርቷል።
💡ዓለምን በአንደኝነት ያጠፋው ክፉ ሰዎች የዘሩት ውሸት ነው። የሰው ውድቀት የጀመረውም በውሸት ነው። እውነትን በትዕግሥትና በሰከነ ልቦና እንደ መልካም ዘር ካልፈለግናትና ካልተንከባከብናት ውሸት እንደ አረም ከክፉ ሰዎች የልብ ዕርሻ ላይ እየተዛመተ መልካም ልቦችን ማጥፋትና መውረስ አይቀርም።
❤️እውነትን ታውቃላችሁ እውነትም ነጻ ያወጣችኃል'የሚለው የትልቁ መጽሐፍ ቃል እንደት ያለ እውነት ነው?
💡በዓለም ላይ ከሁሉ አስከፊው እስር ቤት የሰው አእምሮ ባመነጨው ውሸት ሲጠፈርና በዚያ ቀንበር ውስጥ ሲኖር ነው። እውነተኛ ነጻነት የኀሊና ነጻነት ነው። የኀሊና ነጻነት ደግሞ እውነትን በማወቅና በመኖር ነጻ ከወጣ አእምሮ ብቻ የሚገኝ ጸጋ ነው።
❤️የብዙ አእምሮዎች መቆለፍና መዛግ መንሥኤው ባንድም በሌላም መንገድ ወደ ውስጣቸው የገባው ውሸትና ነጻ የሚያወጣቸውን እውነት አለማወቃቸው የፈጠረው ገደል ነው።
💡ከእውነት በፊትም ሆነ በላይ ለአእምሮ ጠንነትና ነጻነት ምን ምን መድኀንት ይገኛል?እውነት ማወቅ ነጻ ቢያወጣም፣ እውነት ዋጋዋ እጅግ ውድ መድኀኒት ናት።
የተቆለፈበት ቁልፍ[ገፅ፡278]
✍ምህረት ደበበ
❤️💡❤️💡❤️💡❤️💡❤️💡
@EthioHumanity
@EthioHumanity
Falling In Love - Alan Watts
<unknown>
❤️" ፍቅር የሚጀመረውም ሆነ የሚፈፀመው በራሱ ነው። እናንተ ልትጨነቁበት አይገባም። ከእናንተ በላይ ነው። ከእናንተ እጅግ የገዘፈ ነው።
እናንተ ግን ፍቅርን ልትቆጣጠሩት ወደ ምትችሉት ግንኙነት ቀየራችሁት። ለዚህም ነው እናንተ ወደ ፍቅር ሀይል ያልገባችሁትና ስለሱም ምንም የማታቁት። የእናንተ ራስወዳድነት ሊቆጣጠረው አይችልም። ራሳችሁን በቁጥጥር ስር አውላችሁአል።
💙ማንም ፍቅርን ሊጀምር አይችልም። ልክ እንደ ማብርያና ማጥፍያ የምታበሩትና የምታጠፉት አይደለም። ራሳችሁን ብቻ በአሁኑ ጊዜ ብቻ አስቀምጡት። ሲሆን ይሆናል። ከምንም ተነስቶ ነው የሚፈጠረው። ልክ እንደ መሬት መንቀጥቀጥ ይወዘውዛችሁአል ከስራችሁ ይነቅላቹሃል ከእግራችሁ በታች ያለው መሬት ይጠፋል። ለዚህ ነው ፍቅር "በፍቅር መውደቅ" ተብሎ ሚጠራው። ራሳችሁን መሆን ታቆማላችሁ። መቆጣጠሩ ስነምግባሩ በፍቅር ውስጥ ቦታ የለውም። መጀመር ሳትችሉ እንዴት ልታቆሙት ትችላላቹ?
የፍቅር መንገዶች ከናንተ በላይ ናቸው። ትክክለኛውን ጊዜ ለማወቅ አይቻላችሁም።
❤️በፈለጋችሁ ጊዜ ጀምራችሁ ምትጨርሱት ፍቅር እርሱ ፍቅር አይሆንም ። ሰው ሰራሽ ነው የሚሆነው።በሚስቱ ቁጥጥር ስር ያለ ባል አስቀያሚ ፍቅር የማያውቅ ፍቅር የማይገባው ይመስላል። ስለዚህ ሚስቱ እራሷ ከልብ ልታፈቅረው አትችልም። ለናንተ ባርያ የሆነች ሴት እንዴት ልታፈቅሩ ትችላላችሁ?
💙ፍቅር በጓደኞች መካከል እንጂ በባርያና በጌታ መካከል አይሆንም። ባርያን ልታዙ እንጂ ልታፈቅሩ አትችሉም። ፍቅር ሊያፈቅር የሚችለው እኩዮችን ነው።"
✍ኦሾ
@EthioHumanity
@EthioHumanity
እናንተ ግን ፍቅርን ልትቆጣጠሩት ወደ ምትችሉት ግንኙነት ቀየራችሁት። ለዚህም ነው እናንተ ወደ ፍቅር ሀይል ያልገባችሁትና ስለሱም ምንም የማታቁት። የእናንተ ራስወዳድነት ሊቆጣጠረው አይችልም። ራሳችሁን በቁጥጥር ስር አውላችሁአል።
💙ማንም ፍቅርን ሊጀምር አይችልም። ልክ እንደ ማብርያና ማጥፍያ የምታበሩትና የምታጠፉት አይደለም። ራሳችሁን ብቻ በአሁኑ ጊዜ ብቻ አስቀምጡት። ሲሆን ይሆናል። ከምንም ተነስቶ ነው የሚፈጠረው። ልክ እንደ መሬት መንቀጥቀጥ ይወዘውዛችሁአል ከስራችሁ ይነቅላቹሃል ከእግራችሁ በታች ያለው መሬት ይጠፋል። ለዚህ ነው ፍቅር "በፍቅር መውደቅ" ተብሎ ሚጠራው። ራሳችሁን መሆን ታቆማላችሁ። መቆጣጠሩ ስነምግባሩ በፍቅር ውስጥ ቦታ የለውም። መጀመር ሳትችሉ እንዴት ልታቆሙት ትችላላቹ?
የፍቅር መንገዶች ከናንተ በላይ ናቸው። ትክክለኛውን ጊዜ ለማወቅ አይቻላችሁም።
❤️በፈለጋችሁ ጊዜ ጀምራችሁ ምትጨርሱት ፍቅር እርሱ ፍቅር አይሆንም ። ሰው ሰራሽ ነው የሚሆነው።በሚስቱ ቁጥጥር ስር ያለ ባል አስቀያሚ ፍቅር የማያውቅ ፍቅር የማይገባው ይመስላል። ስለዚህ ሚስቱ እራሷ ከልብ ልታፈቅረው አትችልም። ለናንተ ባርያ የሆነች ሴት እንዴት ልታፈቅሩ ትችላላችሁ?
💙ፍቅር በጓደኞች መካከል እንጂ በባርያና በጌታ መካከል አይሆንም። ባርያን ልታዙ እንጂ ልታፈቅሩ አትችሉም። ፍቅር ሊያፈቅር የሚችለው እኩዮችን ነው።"
✍ኦሾ
@EthioHumanity
@EthioHumanity
እምወድሽዋ!❤️ቅዳሜዋ!❤️ሸጋዬዋ!❤️
ማለዳ ከአልጋዬ ስነሳ አይኔን በአይበሉባዬ እያሸሁና የቆሙ ጸጉሮቼን ወደታች ለመመለስ እየታገልኩ ወደመጸዳጃ ቤት በእንግድግድ እርምጃዎች እገባና በሩን በሚዘጋበት ሀይል መጥኜ አሽቀንጥሬ እስኪዘጋ ሳልጠብቅ በፍጥነት ለተወጠረው ፊኛዬ ምላሽ ልሰጥ እቀመጣለሁ,,,,።
<<ኡፍፍ,,,,, መተንፈስን የፈጠርክ ፈጣሪ አለመተንፈስንም ፈጥረሀልና ትመሰገናለህ,,,,,!!>>
ጥርሴን ልቦርሽ መስታወቱ ፊለፊት ስቆም በህሊናዬ ተከስሼ ፍርዴን እየተጠባበቅኩ እንደቆምኩ አስቤው ቀፈፈኝ ።
የጥርስ ሳሙናውን ሆድ በጣቶቼ ተጭኜ ብሩሼ ላይ ካደረግኩ በኋላ በደመነፍስ አሁንም መስታወቱ ላይ አፈጣለሁ።
ጨብራራ ጸጉሬ ፣ ኩሉ የገፈፈ ቅንድቤን ፣ ወደአንድ በኩል ያጋደለው ሰፊው ቲሸርቴ ፣ የተጨናበሱ አይኖቼን አንገቴን አስግጌ ይበልጥ ቀርቤ በጣቶቼ ጥግ ማዕድን እንደሚፈልግ ሰው በረበርኳቸውና አጸዳኋቸሁ።
<< ለምንድነው ዳኛ መስለህ እፊቴ የተገተርከው,,,,? ለምንስ ከውበቴ እንከኔን ታሳየኛለህ,,,? ብሽቅቅ,,,,! >> ብሩሹ ላይ ያለውን ሳሙና ውሀ አስነካሁና መስታወቱ ላይ ረጫጨሁት ። አሁንም ይዳኘኛል,,,?
የአፌን አረፋ ተፋሁበት ።
<<ቱ! ግድ አይደለም ባንተ ውስጥ እራሴን ማየቴ እሺ ,,,,? በውጫዊው አካሌማ አትዳኘኝም! ከቻልክ ውስጤን እያሳየህ ጉድለቴን ነቅሰህ አውጣ ደካማ,,,,,!!>>
ጥርሴን ተጉመጥምጬና ታጥቤ ስጨርስ "እኝኝ "እንዳልኩ እንደልማዴ ወደመስታወቱ ፊቴን ሰገግ ሳደርግ በሳሙና ጭጋግ ተሸፍኗል። በስራዬ ተገርሜ እንከተከት ጀመር። እራሴው እንከኔን እንዳይነግረኝ ሸፍኜው የጸዳሁ ሲመስለኝ ፈለግኩት "ቂቂቂቂ...." አለ መኪ።
<< ለምንድን ጉድለታችንን ከሚነግሩን ይልቅ የሚክቡን ጋር መሆን ምቾት የሚሰጠን ? ደካሞች ነን,,,።
ብዙ ጠንካራ ጎን እያለን ለመጽናናት ፈንታ በድክመታችን ተሸማቀን ስለምንኖር ብርታታችንን መስካሪ እንጂ ጉድለታችንን ነቃሽ የማይመቸን,,,,,!! >>
(የሚቀጥል ግን የማይቀጥል,,)
✍መርየም
@EthioHumanity
@EthioHumanity
ማለዳ ከአልጋዬ ስነሳ አይኔን በአይበሉባዬ እያሸሁና የቆሙ ጸጉሮቼን ወደታች ለመመለስ እየታገልኩ ወደመጸዳጃ ቤት በእንግድግድ እርምጃዎች እገባና በሩን በሚዘጋበት ሀይል መጥኜ አሽቀንጥሬ እስኪዘጋ ሳልጠብቅ በፍጥነት ለተወጠረው ፊኛዬ ምላሽ ልሰጥ እቀመጣለሁ,,,,።
<<ኡፍፍ,,,,, መተንፈስን የፈጠርክ ፈጣሪ አለመተንፈስንም ፈጥረሀልና ትመሰገናለህ,,,,,!!>>
ጥርሴን ልቦርሽ መስታወቱ ፊለፊት ስቆም በህሊናዬ ተከስሼ ፍርዴን እየተጠባበቅኩ እንደቆምኩ አስቤው ቀፈፈኝ ።
የጥርስ ሳሙናውን ሆድ በጣቶቼ ተጭኜ ብሩሼ ላይ ካደረግኩ በኋላ በደመነፍስ አሁንም መስታወቱ ላይ አፈጣለሁ።
ጨብራራ ጸጉሬ ፣ ኩሉ የገፈፈ ቅንድቤን ፣ ወደአንድ በኩል ያጋደለው ሰፊው ቲሸርቴ ፣ የተጨናበሱ አይኖቼን አንገቴን አስግጌ ይበልጥ ቀርቤ በጣቶቼ ጥግ ማዕድን እንደሚፈልግ ሰው በረበርኳቸውና አጸዳኋቸሁ።
<< ለምንድነው ዳኛ መስለህ እፊቴ የተገተርከው,,,,? ለምንስ ከውበቴ እንከኔን ታሳየኛለህ,,,? ብሽቅቅ,,,,! >> ብሩሹ ላይ ያለውን ሳሙና ውሀ አስነካሁና መስታወቱ ላይ ረጫጨሁት ። አሁንም ይዳኘኛል,,,?
የአፌን አረፋ ተፋሁበት ።
<<ቱ! ግድ አይደለም ባንተ ውስጥ እራሴን ማየቴ እሺ ,,,,? በውጫዊው አካሌማ አትዳኘኝም! ከቻልክ ውስጤን እያሳየህ ጉድለቴን ነቅሰህ አውጣ ደካማ,,,,,!!>>
ጥርሴን ተጉመጥምጬና ታጥቤ ስጨርስ "እኝኝ "እንዳልኩ እንደልማዴ ወደመስታወቱ ፊቴን ሰገግ ሳደርግ በሳሙና ጭጋግ ተሸፍኗል። በስራዬ ተገርሜ እንከተከት ጀመር። እራሴው እንከኔን እንዳይነግረኝ ሸፍኜው የጸዳሁ ሲመስለኝ ፈለግኩት "ቂቂቂቂ...." አለ መኪ።
<< ለምንድን ጉድለታችንን ከሚነግሩን ይልቅ የሚክቡን ጋር መሆን ምቾት የሚሰጠን ? ደካሞች ነን,,,።
ብዙ ጠንካራ ጎን እያለን ለመጽናናት ፈንታ በድክመታችን ተሸማቀን ስለምንኖር ብርታታችንን መስካሪ እንጂ ጉድለታችንን ነቃሽ የማይመቸን,,,,,!! >>
(የሚቀጥል ግን የማይቀጥል,,)
✍መርየም
@EthioHumanity
@EthioHumanity
💎ፊት ለፊት ትይዩ የተገነቡ ሁለት ቤቶች አሉ ። በሁለቱ ቤቶች ጣሪያዎች ላይ ደግሞ የእግር መርገጫ ስፋት ብቻ ያለው የጣውላ መረማመጃ ድልድይ ቢጋደምና በላዩ ላይ ተራምዳችሁ ከአንዱ ጣርያ ወደሌላው እንድትሻገሩ ብትጠየቁ ፈቃደኛ ላትሆኑ ትችላላችሁ ። ይኸው ጣውላ መሬት ላይ ተጋድሞላችሁ እንድትራመዱበት ብትጠየቁ ግን ህፃን ፣ ወጣት ፣ አዛውንት ሳይባል ፣ ሁላችሁም ሳትወድቁ ትራመዱበታላችሁ ።
📜 የጣውላ መረማመጃው ያው ነው ፤ እናንተም ያው እናንተው ናችሁ ፤ ታድያ ጣውላው በቤቶቹ ጣሪያዎች ላይ በተጋደመ ጊዜ እንድትራመዱበት ስትጠየቁ ለምን እምቢ አላችሁ? መሬት ላይ በተደጋጋሚ ጊዜ ብዙ ሰዎች ሳይወድቁ ተረማምደውበታል ። ታድያ ችግሩ ምንድን ነው? ችግሩ ያለው ሌላ ቦታ ነው ።
🔑 መሬት ላይ ተጋድሞ ሳለ ጣውላው ላይ ለመረማመድ ንቁ መሆን አያስፈልግም ።ንቃት አልባ ሆናችሁ ልትራመዱ ትችላላችሁ ። በጣውላው ላይ ተረማምዳችሁ ከጣሪያ ጣርያ ለመሻገር ግን ንቁ መሆን ይኖርባችኋል ። ንቃት እንደሌለን እናውቃለን ፤ በዚህም ምክንያት ወድቀን እንዳንሞት እንፈራለን ። መሬት ላይ ስንራመድ ግን ብንወድቅ እንኳን እንደማንሞት እናውቃለን ።
💎 አልፎ አልፎ አደጋ በሚያጋጥመን ቅፅበት ንቃት ይኖራል ። ሌላ ግዜ ግን እንቅልፍ ላይ ነን ። ሞት ሲቀርበን ንቃት ይኖራል ፤ አለዚያ ግን ንቁ አይደለንም ። ልማዶቻችንን መቀየር የማንፈልገው ለዚህ ነው ፤ ምክንያቱም ልማዶች ሲለወጡ ንቁ መሆን ያስፈልጋል ። አሮጌ ልማዶች የእናንተን ንቃት አይፈልጉም ።
📖 የንቃት ፀሃይ /ኦሾ/
ገጽ 99-100
ትርጉም ✍ መርሻ በነበሩ
💎🔑💎🔑💎🔑💎🔑💎🔑💎🔑
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanitybot
📜 የጣውላ መረማመጃው ያው ነው ፤ እናንተም ያው እናንተው ናችሁ ፤ ታድያ ጣውላው በቤቶቹ ጣሪያዎች ላይ በተጋደመ ጊዜ እንድትራመዱበት ስትጠየቁ ለምን እምቢ አላችሁ? መሬት ላይ በተደጋጋሚ ጊዜ ብዙ ሰዎች ሳይወድቁ ተረማምደውበታል ። ታድያ ችግሩ ምንድን ነው? ችግሩ ያለው ሌላ ቦታ ነው ።
🔑 መሬት ላይ ተጋድሞ ሳለ ጣውላው ላይ ለመረማመድ ንቁ መሆን አያስፈልግም ።ንቃት አልባ ሆናችሁ ልትራመዱ ትችላላችሁ ። በጣውላው ላይ ተረማምዳችሁ ከጣሪያ ጣርያ ለመሻገር ግን ንቁ መሆን ይኖርባችኋል ። ንቃት እንደሌለን እናውቃለን ፤ በዚህም ምክንያት ወድቀን እንዳንሞት እንፈራለን ። መሬት ላይ ስንራመድ ግን ብንወድቅ እንኳን እንደማንሞት እናውቃለን ።
💎 አልፎ አልፎ አደጋ በሚያጋጥመን ቅፅበት ንቃት ይኖራል ። ሌላ ግዜ ግን እንቅልፍ ላይ ነን ። ሞት ሲቀርበን ንቃት ይኖራል ፤ አለዚያ ግን ንቁ አይደለንም ። ልማዶቻችንን መቀየር የማንፈልገው ለዚህ ነው ፤ ምክንያቱም ልማዶች ሲለወጡ ንቁ መሆን ያስፈልጋል ። አሮጌ ልማዶች የእናንተን ንቃት አይፈልጉም ።
📖 የንቃት ፀሃይ /ኦሾ/
ገጽ 99-100
ትርጉም ✍ መርሻ በነበሩ
💎🔑💎🔑💎🔑💎🔑💎🔑💎🔑
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanitybot
☯There's a reason you can learn from everything: you have basic wisdom, basic intelligence, and basic goodness.“Would you like to save your country from destruction ? Then step away from Mass movements and quietly go to work on your own self-awareness.
☯If you want to Awaken all of humanity, then Awaken all of yourself. If you want to eliminate the suffering in your country, then eliminate all that is dark and negative in yourself. Truly, the greatest gift you have to give is your own self-transformation.”
🔆we can simply explore Humanity and all of creation in the form of ourselves. Everything that human beings feel, we also feel. We can become extremely wise and sensitive to all of Humanity and the whole universe simply by knowing ourselves,Just as we are.
የሰው ልጅ እኩልነትን እንደማስረጃ ከሚያሳዩት አንዱ"ሰው"መሆን ነው።
🔆ሰው መሆን ማለት ደግሞ፤ ራቁታችንን ከተወለድን በኋላ፤ ከልብስ ጀምሮ አካላችንን ከሚሸፍኑት የማንነት ሽፋኖች መላቀቅ ነው። ሰው ራቁቱን በመወለድ ይዞት የመጣውን መሰረታዊ ማንነት፦ ማለትም መወለድ፣ መኖርና መሞትን ይዘነጋል።
☯ገላው በእናቱ ሆድ የለመደው ሙቀት ሲቀርበት እንዳይበርደውና እንዳይቆረፍድ ልብስ መደረብን፣ ቆይቶ መለያ ስምን፣ ሃይማኖት፣ ዘር፣ ብሄር፣ በተሰብ፣ ሙያ፣ ትምህርትና ስፍርን የመሰሉ ግዑዝና ምናባዊ አልባሳትን በመደረብ" ሰው- ነቱን" ያጣል።
🔆በቀረ ዘመኑ ሁሉ ይዞት የተወለደውን ማንነት ፍለጋ አውቆም ሆነ ሳያውቅ ሲዳክር ይኖራል። ሰው መሆን ከዚህ ሁሉ ድርብርብ ሽፋን የበለጠ መሆኑን ሳያውቅ ወይንም ሳይረዳ ህይወቱን ይገፋል። ሰው መሆንን ለማወቅ የሚሄድበት ትግል፣ ሁሉም ከብርድ ለመሽሽ ከሌላና ጥላ፣ እንዲሁም ሽፋን እንደመፈለግ ነው።
☯ለዚህ ማሳያው የአብዛኛው ሰው ቋሚ ፍላጎት ህይወትን"መለወጥ" ነው። ሁሉም ሰው "ራሴን ለውጬ" ፣ "በተሰቤን ለውጬ" ፣ "መለወጥ አለብኝ ...።" ፤ " ቤተሰቤን ልለውጥ" ፣ "ሀገሬን ልለውጥ" ፣ " ሀይማኖቴን ልለውጥ "እያለ ይኖራል።
✨ከዚህ ሁሉ ለውጥ ውስጥ እያንዳንዱ አድስ ለውጥ አሮጌ ህይወት እየሆነ እንደ ልብስ ከመደረብ ውጭ እውነተኛ ለውጥ ሳይሆን ይቀራል ። እውነተኛ ለውጥ የማይኖረው ሰው ስላልጣራና ስላልሞከረ ሳይሆን ለውጥ ሂደት እንጂ መድረሻ ባለመሆኑ ነው ።
🔆በአንድ ለውጥ መርጋት በሰው ተፈጥሮ ውስጥ ከማይቻሉት ሀቆች አንዱ ነው። በመሆኑም ሰው ቢለውጥ፣ ቢለውጥ ከደረባቸው የማንነት አልባሳት አንዱን ወይንም ሌላውን እንጂ ሰው -- ነቱን" ሊሆን አይችልም።
☯ከዚህ የማንነት ግራ መጋባት ነፃ የሚወጣው በሞቱ ነው።
ሞት ትልቁ ነፃ አውጪ ነው። እንዳልነበረ ይረሳል። ስሙና ማንነቱን ሌላ ይወርሰዋል ።
✍አለመኖር ገፅ፡ 111- 112
በዳዊት ወንድምአገኝ /ዶክተር /
☮🔆☯🔆☮🔆☯🔆☮🔆☯🔆
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanityBot
☯If you want to Awaken all of humanity, then Awaken all of yourself. If you want to eliminate the suffering in your country, then eliminate all that is dark and negative in yourself. Truly, the greatest gift you have to give is your own self-transformation.”
🔆we can simply explore Humanity and all of creation in the form of ourselves. Everything that human beings feel, we also feel. We can become extremely wise and sensitive to all of Humanity and the whole universe simply by knowing ourselves,Just as we are.
የሰው ልጅ እኩልነትን እንደማስረጃ ከሚያሳዩት አንዱ"ሰው"መሆን ነው።
🔆ሰው መሆን ማለት ደግሞ፤ ራቁታችንን ከተወለድን በኋላ፤ ከልብስ ጀምሮ አካላችንን ከሚሸፍኑት የማንነት ሽፋኖች መላቀቅ ነው። ሰው ራቁቱን በመወለድ ይዞት የመጣውን መሰረታዊ ማንነት፦ ማለትም መወለድ፣ መኖርና መሞትን ይዘነጋል።
☯ገላው በእናቱ ሆድ የለመደው ሙቀት ሲቀርበት እንዳይበርደውና እንዳይቆረፍድ ልብስ መደረብን፣ ቆይቶ መለያ ስምን፣ ሃይማኖት፣ ዘር፣ ብሄር፣ በተሰብ፣ ሙያ፣ ትምህርትና ስፍርን የመሰሉ ግዑዝና ምናባዊ አልባሳትን በመደረብ" ሰው- ነቱን" ያጣል።
🔆በቀረ ዘመኑ ሁሉ ይዞት የተወለደውን ማንነት ፍለጋ አውቆም ሆነ ሳያውቅ ሲዳክር ይኖራል። ሰው መሆን ከዚህ ሁሉ ድርብርብ ሽፋን የበለጠ መሆኑን ሳያውቅ ወይንም ሳይረዳ ህይወቱን ይገፋል። ሰው መሆንን ለማወቅ የሚሄድበት ትግል፣ ሁሉም ከብርድ ለመሽሽ ከሌላና ጥላ፣ እንዲሁም ሽፋን እንደመፈለግ ነው።
☯ለዚህ ማሳያው የአብዛኛው ሰው ቋሚ ፍላጎት ህይወትን"መለወጥ" ነው። ሁሉም ሰው "ራሴን ለውጬ" ፣ "በተሰቤን ለውጬ" ፣ "መለወጥ አለብኝ ...።" ፤ " ቤተሰቤን ልለውጥ" ፣ "ሀገሬን ልለውጥ" ፣ " ሀይማኖቴን ልለውጥ "እያለ ይኖራል።
✨ከዚህ ሁሉ ለውጥ ውስጥ እያንዳንዱ አድስ ለውጥ አሮጌ ህይወት እየሆነ እንደ ልብስ ከመደረብ ውጭ እውነተኛ ለውጥ ሳይሆን ይቀራል ። እውነተኛ ለውጥ የማይኖረው ሰው ስላልጣራና ስላልሞከረ ሳይሆን ለውጥ ሂደት እንጂ መድረሻ ባለመሆኑ ነው ።
🔆በአንድ ለውጥ መርጋት በሰው ተፈጥሮ ውስጥ ከማይቻሉት ሀቆች አንዱ ነው። በመሆኑም ሰው ቢለውጥ፣ ቢለውጥ ከደረባቸው የማንነት አልባሳት አንዱን ወይንም ሌላውን እንጂ ሰው -- ነቱን" ሊሆን አይችልም።
☯ከዚህ የማንነት ግራ መጋባት ነፃ የሚወጣው በሞቱ ነው።
ሞት ትልቁ ነፃ አውጪ ነው። እንዳልነበረ ይረሳል። ስሙና ማንነቱን ሌላ ይወርሰዋል ።
✍አለመኖር ገፅ፡ 111- 112
በዳዊት ወንድምአገኝ /ዶክተር /
☮🔆☯🔆☮🔆☯🔆☮🔆☯🔆
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanityBot
ለውብ ቀን!
💚
፩ (አንድ)
ግለ-ሰብ የትግል አርማ ሊሆን አይገባም። የትግል አርማ መሆን ያለበት የትግሉ ውጤት ነው። ግለሰብ ግለሰብ ነው። ይውሸለሸላል፤ይማልላል፤ይሻፍዳል፤
ይታበያል፤ይሰርቃል ፤ይደክማል ፤ይሳሳታል፤ ይደለላል። ግለሰብ ላይ የተንጠለጠለ ድል ግለ-ሰብ ላይ ያልተንጠለጠለ ስርአት ካልተዘረጋ ድሉ ድል አይደለም ።
፪ (ሁለት)
በየትኛውም የግፍ ዘመን ውስጥ ዳር ሆኖ ያየ ትልቅ ነኝ ባይ፤ የተሳተፈ ፤ዝምታን የመረጠ አባት፤ ያልመከረ ምሁር ፤ በደልን ያስተባበለ አንዱም ሳይቀር በየደረጃው ሃጥያተኛ ነው።
፫ (ሷስት )
.....
ብልህ በተበጀለት ሽል ውስጥ ሆኖ አይወራጭም። የራሱን መወራጫ ነገን ያማከለ ርእይ በውብ ሃሳብ በልኩ ያጎለብታል እንጂ ።
፬ (አራት)
ከተወለድንበት ሰፈር፤ ከምንከተለው ሃይማኖት ፤ አሽቆልጠን ከምናገኘው ፍርፋሪ፤ ግዜ ከሚያፈዘው ስልጣንም ሆነ ሳንቲም ሁሉ ሰውነት ይገዝፋል።
፭ (አምስት)
ሁሌም ጥግ ለጥግ ሆነው ከሚካረሩት አክራሪዎች ይልቅ መሃል ላይ ያሉ እንዳይበጠስ የሚዳክሩት ቅዱስም ምስጉንም ናቸው🙏🙏
ውብ ቀን!💚
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@balmbaras
💚
፩ (አንድ)
ግለ-ሰብ የትግል አርማ ሊሆን አይገባም። የትግል አርማ መሆን ያለበት የትግሉ ውጤት ነው። ግለሰብ ግለሰብ ነው። ይውሸለሸላል፤ይማልላል፤ይሻፍዳል፤
ይታበያል፤ይሰርቃል ፤ይደክማል ፤ይሳሳታል፤ ይደለላል። ግለሰብ ላይ የተንጠለጠለ ድል ግለ-ሰብ ላይ ያልተንጠለጠለ ስርአት ካልተዘረጋ ድሉ ድል አይደለም ።
፪ (ሁለት)
በየትኛውም የግፍ ዘመን ውስጥ ዳር ሆኖ ያየ ትልቅ ነኝ ባይ፤ የተሳተፈ ፤ዝምታን የመረጠ አባት፤ ያልመከረ ምሁር ፤ በደልን ያስተባበለ አንዱም ሳይቀር በየደረጃው ሃጥያተኛ ነው።
፫ (ሷስት )
.....
ብልህ በተበጀለት ሽል ውስጥ ሆኖ አይወራጭም። የራሱን መወራጫ ነገን ያማከለ ርእይ በውብ ሃሳብ በልኩ ያጎለብታል እንጂ ።
፬ (አራት)
ከተወለድንበት ሰፈር፤ ከምንከተለው ሃይማኖት ፤ አሽቆልጠን ከምናገኘው ፍርፋሪ፤ ግዜ ከሚያፈዘው ስልጣንም ሆነ ሳንቲም ሁሉ ሰውነት ይገዝፋል።
፭ (አምስት)
ሁሌም ጥግ ለጥግ ሆነው ከሚካረሩት አክራሪዎች ይልቅ መሃል ላይ ያሉ እንዳይበጠስ የሚዳክሩት ቅዱስም ምስጉንም ናቸው🙏🙏
ውብ ቀን!💚
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@balmbaras
❤️ደግነት በቃላት ሲገለጽ ልበ ሙሉነትን ያመጣል፡፡
ደግነት በኃሳብ ሲሆን የስብዕና ጥልቀት ይፈጥራል፡፡
ደግነት በመስጠት ሲሆን ፍቅር ከውስጡ ያብባል፡፡
ውብ ምሽት❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
ደግነት በኃሳብ ሲሆን የስብዕና ጥልቀት ይፈጥራል፡፡
ደግነት በመስጠት ሲሆን ፍቅር ከውስጡ ያብባል፡፡
ውብ ምሽት❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity